Why & how"

Why & how" Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Why & how", Media/News Company, Addis Ababa.

04/02/2020

ገና የኮሮና ቫይረስ ጉዳይ ሳይሰማ በሚሰራበት ሆስፒታል ይህን አስደንገጭ ወረረረሽኝ በመገንዘብ ለማሥጠንቀቅ የሞከረው ዶክተር በፖሊስ አማካኝነት አፉን እንዲዘጋና ምንም እንዳይል ቢታዘዝም ዛሬ ላይ ከሆስፒታል አልጋ ላይ እንደተጋደመ ታሪኩን ሲያጋራ ቻይናዉን "ጀግናችን" እያሉት ነው፡፡
*****
ዶክተር ሊ ይባላል ገና በወርሃ ታህሳስ በሚሰራበት ሆሰፒታል ዉስጥ 7 የቫይረሱ ምልከት ሚታይባቸው ሰዎች ሲያጋጥሙት በ2003 ተከስቶ ከነበረው ሳርስ እየተባለ የሚጠራው ቫይረስ እንደሚሆን በመገመት ለዶክተር ወዳጆቹ ጥኝቃቄ ያደርጉ ዘንድ መለእክት ላከላቸው ፡፡ ያጋጠመው ቫይረስ ግን አደገኛው ኮሮና ቫይረስ ነበር
*****
ይሁን እንጂ ከቀናት በኋላ ፖሊሶች መጥተው የሀሰት መረጃ ከማሰራጨት እንዲታቀብ አስጠንቅቀው ወረቀት አስፈረሙት፡፡
ከሳምንተ በኋላ በኮሮና ቫይረስ መያዟን ያለወቀው ሌላስትን የግላኮማ ህክምና እየሰጣት ቆየ፤፡
*****
ዌቦ በተባለ ማህበራዊ ድረገጽ ላይ ሂደቱን አብራርቶ ሲቀርብ የዉሃን ከተማ ባለስልጣኖች ይቅርታ አድርግልን ቢሉትም ነገሩ ግን የረፈደ ነበር
****
ከጥር 10 ጀሞሮ ሃይለኛ ሳል በማግስቱ ትኩሳት እያለ በመጨረሻም ሆስፒታል ገባ፡፡ ቤተሰቦቹ በተመሳሳይ ምልክት ወደ ሆስፒታል ተከተሉት፡፡ ከዚህ በኋላ ቻይና በጥር 20 ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ይፋ አደረገች፡፡
*****
‘የጤና ተቋም ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሆንም እንደ ዶክተር ሊ ያሉ ሚሊዮኖችን እንፈልጋለን’ የሚሉ ቻይናውያንም ዶክተሩን ጅግናችን እያሉት ይገኛሉ፡፡

31/01/2020
Doc abiy is making a difference that we can see and I hope he ll do more but I still ...
12/04/2018

Doc abiy is making a difference that we can see and I hope he ll do more but I still ...

27/02/2018

its actually a problem it is not normal and i dont know why we do it as in its normal

የዛሬው መስከረም 2 ባልኖርበትም ከእንቁጣጣሽ ይልቅ ደምቆ የሚከበር የነፃነት ቀን ነበር እንዲህ እንደዛሬ ተራውን ለግንቦት 20 አሳልፎ ሳይሰጥ
12/09/2017

የዛሬው መስከረም 2 ባልኖርበትም ከእንቁጣጣሽ ይልቅ ደምቆ የሚከበር የነፃነት ቀን ነበር እንዲህ እንደዛሬ ተራውን ለግንቦት 20 አሳልፎ ሳይሰጥ

01/05/2016

happy ester for all of u gyz

ድሮ ድሮ ዝናብ ሲመጣ ጥላ ያልያዙ ሰዎች ነበሩ እየሮጡ መጠለያ የሚፈልጉት መኪና ያላቸውና ጭራሽ አይታሰብም ነበር። ጊዜ እያደገ የአገራችን ኢኮኖሚም እየተመነደገ ሲመጣ ከክረምቱ ዝናብ አደለም...
03/08/2015

ድሮ ድሮ ዝናብ ሲመጣ ጥላ ያልያዙ ሰዎች ነበሩ እየሮጡ መጠለያ የሚፈልጉት መኪና ያላቸውና ጭራሽ አይታሰብም ነበር። ጊዜ እያደገ የአገራችን ኢኮኖሚም እየተመነደገ ሲመጣ ከክረምቱ ዝናብ አደለም ሰው ይቅርና መኪናዎችም መጠለል ጀምረዋል። በአብዛኛዋ የመዲናችነ አከባቢዎች ዝናብ መዝነብ ከጀመረ መኪናዎች በየብስ የሚጋዙ ሳይሆኑ በብህር የሚጋዙ መስለው እስከ ወገባቸው ድረስ በውሃ ይሸፈናሉ። ከሁሉም በጣም የሚገርመኝ ይህ ችግር አዳዲስ በተሰሩ መንገዶቻችን ላየ እጅጉን የሚስተዋል መሆኑ ነው። ባሳለፍነው ሳምንት ዶክተር ቴድሮስ በጣመ ዘናያልክበት ግጥም ብለው ወይ አዲስ አበባ ወይ ራዳ ሆይ ባቡሩን ስንጠብቅ መርከብ አማረሽ ወይ ብለወ በገፃቸው ላ ለጥፈውት ነበር እሱን ተከትሎ ከተሰጦ ኮሜንቶች እኔም ዛነ ያልኩበት "ዶክተር ቴዎድሮሰ ቆየት ብላችሁ ኢኮኖሚያችን በ11 በመቶ እያደገ ስለሆነ ዝናቡ ሥእብዝቶ መዝነብ ስለጀመረ ነው ብላችሁ ዜና ታሰራላችሁ" የሚለውን ነበር

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ፕሮጀክት እነሆ ተመርቆ ስራ ይጀምራል ከተባለ አደለም ስራ ለመጀመር ይቅርና የማጠቃለያ ስራዎች ሙሉ በሙሉ መጠናቀቅ ሳይችሉ ወራት በወራት ላይ እየተደራረቡ ነው። ከ...
31/07/2015

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ፕሮጀክት እነሆ ተመርቆ ስራ ይጀምራል ከተባለ አደለም ስራ ለመጀመር ይቅርና የማጠቃለያ ስራዎች ሙሉ በሙሉ መጠናቀቅ ሳይችሉ ወራት በወራት ላይ እየተደራረቡ ነው። ከሁሉም በጣም የተመቸኝ ባቡሩ ገና ሳይጠናቀቅ በአንድ መስመር ላይ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት አሟልተው ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት መመረቁ ነው። "ተመርቆ ስራ የማይጀምር የዚህ ዘመን የዩንቨርስቲ ተማሪ ነበር ፕሮጀክቱiም እንደዘንድሮ የዩንቨርስቲ ተማሪ ሆኗል" እየተባለ ይቀለድ ተይዟል።አሁንም ቢሆን መቼ ይጀምራል ሲባል ከሚሰጠው በመላ ምት ላይ የተመረኮዘ መልስ እንደቀጠለ ነው። ለምን ዘገየ ክፍተቱ የት ነው ያለው እየለ የሚጠይቅ ጋዜጠኛ ቢኖርም የመንግስት ከሆኑ ወደ ስምምነት በመሄድ *(social responsiblity) በማውጋት ጉዳዩ እንዲዳፈን ሲጠየቁ የግል ሲኮን ደግሞ ድርስ አናስብልም እያሉ ተመርቆ ስራ ሳይጀምር ከ5 ወር በላይ ሆኖታል።

ማንኛውም ፕሮጀክቶች መሰረት ላይና አጨራረስ ላይ እጅጉን ጊዜ ይፈጃሉ። ፕሮጀክቱም እንዲሁ አጨራረሱን ለማሳመር እየሰሩ ናቸው። (ያው በየመንገዱ እንደምናየው) ታዲያ ምናለበት ይህንኑ እውነት ተናግረው ቢገላገሉ። ከ1 ወር በፊት ሲጠየቁ ከ95 በመቶ በላይ ተጠኗቋል ዛሬም እንዲሁ ታዲያ መቼ ነው ሙሉ በሙሉ የሚጠናቀቀው። አስታውሳለሁ ከ2 ወር ገደማ በፊት የድርጅቱ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ከ95 በመቶ በላይ እንደተጠናቀቀ ነግረውኝ ነበር።

ምናልባት ቁጥሩ ሊጨምር ይችላል ግን ቁጥር ለሂሳብ ባለሞያ ነው እንጂ ለማንም ሲጠቅም አላየንም። እኔ 95 ገባ 98 ውይንም 99 እንዲያው 100 ፐርሰንት ቢባልም እንኳን ስራ ጀምሮ ያስመረረኝን የቤት ኪራይ ለመቀነስ ከከተማው ራቅ ብዬ ወጥቼ ተከራይቼ ከስራዬ እንዳልቀር በጠዋቱ ተሳፍሬበት ቢሮዬ መድረስ ካልቻለኩኝ ቁጥር ቢደረደር ፋይዳው ሚዛን አይደፋም።

የባቡር ኮርፖሬሺኑ የሃይል እጥረት አጋጠመኝ ሲለን አሌክትሪክ ሃይል ደግሞ የለም የሃይል አቅርቦቱ አለ እያሉን እርስ በርስ ይሸዋወዳሉ።

አንዳንዴ ሳስበው ከሆነ ከተለየ አጋጣሚ ጋር አገናኝተው ሊያስጀምሩ ይመስለኝ ነበር። ለምሳሌ ባራክ ኦባማ የመጣ ጊዜ እሱን ሊያሳፍሩና በዛው ስራ ጀመረ ሊሉን። እሱም አልሆነም።
"ሚስጥርና ቅዠት የሆነው የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ፕሮጀክት"

ይህ ባቡር ለሙከራ የወጣ ባቡር ነው እኔ ግን ባቡሩ ለሙከራ ከመውጣቱ በላይ አደጋ  እና ሌላም ነገሮችን ለመከለል የተዘረጋውን ፕላስቲክ (ይቅርታ ብረት አለመሆኑን አረጋግጫለሁ) የሚዘለው ሰው...
26/01/2015

ይህ ባቡር ለሙከራ የወጣ ባቡር ነው እኔ ግን ባቡሩ ለሙከራ ከመውጣቱ በላይ አደጋ እና ሌላም ነገሮችን ለመከለል የተዘረጋውን ፕላስቲክ (ይቅርታ ብረት አለመሆኑን አረጋግጫለሁ) የሚዘለው ሰው በጣም አስገረመኝ።

ለነገሩ ምን ያድርግ በተዘጋጀው ማቃረጫ ለመሻገር ቢያንስ ከ100 ሜትር በላይ በእግሩ ማዝገም አለበት። ታዲያ አማራጩ መዝለሉ ሆነ ማለት አደለም ።

ምን ማለት እንደሆነ እኔ አልገባኝም። መሸጋገሪያዎቹን እንዲህ ማራዘም ያስፈለገበት ምክንያት ምን እንደሆነ ማወቅ አልቻልኩም። ለመኪናም ይሁን ለእግረኛ እረዘም ያለ ርቀት መራመድ እና መንዳት ያሻል።

እግረኛውስ እንደሚታየው ዘሎ አለፍ። ችግሩ ነጂዎች እረዝሞባቸው እነሱም ዘለው የገቡ ቀን ነው።

እነሆ አገራችንን በባቡር ከሚደርሱ አደጋዎች ይጠብቃት

ትናንት  በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ ቻርሊ በተሰኘ መፅሄት ላይ በደረሰ የሽብር ጥቃት የመፅሄቱን ኤዲተር  ስቲፋኒ ቻርቦነር ጨምሮ 12 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 11 የሚሆኑ ደግሞ ቆስለዋል።ለምን ቻር...
08/01/2015

ትናንት በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ ቻርሊ በተሰኘ መፅሄት ላይ በደረሰ የሽብር ጥቃት የመፅሄቱን ኤዲተር ስቲፋኒ ቻርቦነር ጨምሮ 12 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 11 የሚሆኑ ደግሞ ቆስለዋል።

ለምን ቻርሊ መፅሄት የጥቃቱ አላማ ሆነ
ነገሩ የሚጀምረው ከፈረንጆቹ 2011 ጀምሮ ነው። በዋናነትም በወቅቱ በመፅሄቱ የፊት ገፅ ላይ የነብዩ መሃመድን ምስል የያዘ ሆኖ ለገበያ መቅረቡ በአክራሪ ዎቹ ዘንድ ክፉኛ ቅሬታን ያጫረ ሲሆን እሱን ተከትሎ በአልቃይዳ በከፍተኛ ደረጃ ከሚፈለጉ ግለሰቦች ተርታም የመፅሄቱ አዘጋጅ ተቀምጦ ነበር። አልቃይዳም ቢዘገይም ጥቃቱንከማድረስ ወደኋላ እንደማይልም አስፈራርቶ ነበር።

አዘጋጁም በወቅቱ ከተናገራቸው መካከል" ለመኖር ብዬ ከምንበረከክ ቆሜ ብሞት ይሻለኛል " የሚለው ንግግሩ በማህበራዊ ድረ ገፁ ላይ በስፋት ታይቶ ነበር።

ትናንት ማምሻውን ታዲያ ተወንጫፊ ሮኬቶች ጭምር የታጠቁ ሁለት ግለሰቦች በቀጥታ መፅሄቱ ወደ ሚታተምበት ቦታ በማምራት ሳምንታዊ የኤዲቶሪያል ስብሰባ እየተደረገ በሚገኝበት ሰዓት ጥቃት የከፈቱ ሲሆን በጥቃቱም ሁለት ፖሊሶችን ጨምሮ 12 ሰዎች ተገለዋል 11 ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ጉዳዩ ከሚዲያው ነፃነት ጋር አያይዘው የጀርመን እና የእንግሊዝ መሪዎች የሃዘን መልክታቸውን አስተላልፈዋል።

የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት በበኩላቸው ሃሙስ ያሀዘን ቀን አንዲሆን ያወጁ ሲሆን ሽብርተኝነቱን ለመዋጋት ህብረት ወሳኝ መሆንን በማንሳት እጅ ለእጅ መያያዝ አለብን ሲሉ ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት የፈረንሳይ ፖሊስ ሺሪፍ እና ሰይድ የተባሉ ወንድማማቾች ከጥቃቱ ጀርባ እንዳሉ በማመን ምስላቸውን የለቀቀ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥም አሸባሪዎቹን ለማደን እየሰራ መሆኑን አስታውቃል።

በማህበራዊ ድረገፁ ላይም "Je Suis Charlie" ማለተም እኔ ቻርሊ ነኝ የሚል መፈክር በስፋት የታየ ሲሆን የCNN ዘገባ እንደሚያሳየው በደቂቃ ከ2 ሺህ ጊዜ በላይ ትዊት ይደረግ ነበር።
ከዚህ ባለፈም የፓሪስ ነዋሪዎች ይሀንኑ መፈክር በማንገብ በአደባባይ ላይ በስፋት የተሰበሰቡ ሲሆን አንፈራም የሚል መፈክርም በመካከል ጎላ ብሎ ይታይ ነበር።

RIP

01/01/2015

አፍሪካ በ2014 (Afrika in 2014) በአዲሱ ረታ

ፖለቲካዊ ክስተቶች

በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ የመሪነት ዘመን የተዘጋጀው የአፍሪካ - አሜሪካ የመሪዎች ጉባዔ የተካሄደበት ዓመት ሆኖ አልፏል።በዚህ በመጀመሪያው የአፍሪካ - አሜሪካ የመሪዎች ጉባዔ ላይ የ 50 የአፍሪካ አገራት መሪዎች ተሳተፊ ሆነዋል።

በጉባዔው ቆይታ ወቅት የአሜሪካው ምክትል ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አንዳሉት ''አሁን እንደ ቀድሞው ለአፍሪካ ምን እናድርግ የምንልበት ጊዜ ሳይሆን ከአፍሪካ ጋር ምን እንስራ የምንልበት ወቅት ነው'' ብለው ነበር።

በተጠናቀቀው ዓመት በአፍሪካ በተለያዩ አገራት ይነስም ይብዛም መንግታትን ከማስደንገጥና ከስልጣን እስክ ማውረድ የደረሱ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራዎች በሌሴቶ፣ በብሩኪናፋሶና በጋምቢያ ተከስተዋል።

የአፍሪካ ትንሿ አገር ሌሴቶ በአገሪቷ ልዩ ኃይል በተሞከረ የመፈንቅለ መንግስት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተወሰኑ ቀናትን በደቡብ አፍሪካ እንዳሳለፉ መገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ስጥተውታል።

በዓመቱ መገባደጃ ላይ የጋምቢያው ፕሬዚዳንት ያያህ ጃሜህ ጎርቤት አገር ቻድ በጉብኝት ላይ በነበሩበት ወቅት በአገሪቷ ወታደሮች የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መደረጉን የተለያዩ የዜና ምንጮች ዘግበውታል።

27 ዓመታትን በስልጣን ላይ የቆዩት የብሩኪና ፋሶው ፕሬዚዳንት ብሌይስ ኮምፓዎሬ በአገሪቷ በተቀሰቀሳው ህዝባዊ ተቃዉሞ ምክንያት ከስልጣን ተውግዷል።ወታደራዊ መንግስት ስልጣን ያያዘ ቢሆንም አገሪቷ በጊዜያዊ የሽግግር መንግስት እንድትተዳደር ተደርጓል።

ምጣኔ ኃብታዊ ክስተቶች

የናይጄሪያ ዋና ስታቲስቲካል ቢሮ ባወጣው መረጃ መሰረት የአገሪቷ ኢኮኖሚ በአህጉሪቱ ቀድሞ በደቡብ አፍሪካ ተይዞ የነበረውን የምጣኔ ኃብታዊ የበላይነት ቦታ መረከቡንና ናይጄሪያም በዓለም 26ኛ ግዙፉ የኢኮኖሚ ባለቤት መሆኗን አብራርቷል።

የናይጄሪያውያን ዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢም ከ 1 ሺህ 437 የአሜሪካን ዶላር ወደ 2ሺህ 258 ዶላር ከፍ ማለቱ በዘገባው ተብራርቶ ነበር።

የአፍሪካውያን ቢሊየነሮች ቁጥርም በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረበት ዓመት መሆኑም ይታወሳል።

በፎርብስ መጽሔት ላይ በ 2014 ከተመዘገቡት አጠቃላይ 1 ሺህ 645 ቢሊየነሮች መካከል 29ኙ አፍሪካውያን ባለጸጎች ናቸው።ናይጄሪያዊው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ ደግሞ በ 21 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶለር አህጉሪቷን ኃብታሞች ሰንጠረዥ በእንደኝነት ይመራል።

የኬኒያ መንግስት እስካሁን በአገሪቷ የተመዘገበው ምጣኔ ኃብታዊ እድገት አገሪቷ መካክለኛ ገቢ ካለቸው አገራት ተርታ መመደብ ያስችላታል ማለቱም በስፋት የተዘገበበት ዓመት ነበር።
ሙዲስ፣ ስታንዳርድ ኤንደ ፑርና ፊች የተባሉ ታዋቂ ዓለም ዓቀፍ የምጣኔ ኃብት እድገት መዛኞችና ደረጃ አውጪዎች የኢትዮጵያን ደረጃ B መሆኑን ይፋ አድርጓል በዚህም መሰረት አገሪቷ የዩውሮ ቦንድ ገዝታለች።

የተለያዩ አደጋዎች

የዓለምን ህዝብ ክፉኛ ካሳዘኑ አደጋዎች መካከል ቁጥራቸው 273 የሚደርሱ የናይጄሪያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሴት ተማሪዎች በአገሪቷ የሽብር ተግባራትን እየፈጸመ በሚገኘው ቦኮሃረም በተባል ሽብርተኛ ቡደን የተወሰዱበት ዓመት ነበር።

የናይጄሪያ መንግስት ተማሪዎቹን ለማስለቀቅ ያደረገው የተላያዩ ሙከራዎች ያልተሳኩ መሆናቸውንና የኢስላማዊ ቡድኑ የሽብር ተግባር ተጠናክሮ የቀጠለበት ዓመት መሆኑም የተስተዋልበት ዓመት ነበር።

ሌለኛው አሳቃቂው አደጋ በ 2014 መጀመሪያ አካባቢ በምዕራብ አፍሪካ አገራት የተቀሰቀሰውና እስካሁን በቁጥጥር ስር ያልዋለው የኢቦላ ቫይረስ ወረርሺኝ ነው።

በሽታው ከባለፈው ነኃሴ ወር ጀምሮ ዓለም አቀፍ አደጋነት ተውጆ የመከላከል ስራው ተጠናክሮ የቀጠለ ቢሆንም በቅርቡ የወጡ የአለም ጤና ድርጅት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ቫይረሱ ከ 7 ሺህ በላይ ዜጎችን ለሞት የዳረገ ሲሆን በአጠቃላይ ወደ 19 ሺህ የሚጠጉ ዜጎች ደግሞ በቫይረሱ ወረርሺኝ ተጠቅተዋል።

የእርስ በርስ ጦርነትና ሹክቻዎች

ባሳለፍነው ዓመት ደቡብ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፓብሊክ ክፉኛ በእርስ በርስ ግጭት ሲታመሱ ነበር። ደቡብ ሱዳናውያን ገና ራሳቸውን ማስተዳደር ከጀመሩ ሁለት ዓመት ሳይሞላቸው በ 2013 ማብቂያ ላይ በገጠማቸው የውስጥ ግጭት ብዙ ሰቆቃዎችን ተጋፍጠዋል።

ግጭቱ እስካሁንም እልባት ያለገኘ ቢሆንም በምራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስጣን (ኢጋድ) አባል አገራት በኩል ተደጋጋሚ የሽምግልና ሙከራዎች ሲደረጉም ቆይተዋል።

የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፓብሊክ ህዝቦች እስልምናንና ክርስትና ኃይማኖትን ለግጭት መንስኤነት በመጠቀም ለከፋ ጉዳት ተዳርሰው ነበር።በዚህም ቁጥራቸው ከ 2600 በላይ ዜጎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ወደ 1 ሚሊየን የሚጠጉ የአገሪቱ ዜጎች ደግሞ መፈናቀል እጣፈንታቸው ሆኖ ነበር።

ከነዚህ አገራት ባሻገር በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፓብሊክ፣ በኢጅፕት፣ በሶማሊያ፣ በማሊ፣ በናይጄሪያና በሱዳን ከተለያዩ አማጺ ቡድኖችና ሽብርተኞች እንዲሁም ህዝባዊ ተቃውሞዎች ተስተውለዋል።

የመዝናኛው ዓለም ምልከታ

2014 ኬኒያዊቷ ተዋናይት ሉፒታ ንዮንጎ ሆሊድ ውስጥ በሳየችው አስገራሚ የተውና በቃት የኦስካር ተሸላሚ የሆነችበት ዓመት ነበር።

ከዚህም ባለፈ people የተባለ መጽሔትና ሌሎች ታዋቂ መጸሔቶች ሉፒታን የ 2014 ውብ ሴት አድርገው ሰይሟት ነበር።

የተጠናቀቀው ዓመት ታዋቂው የቀድሞ ላይቤሪያዊ እግር ኳስ ተጫዋች ጆርጅ ዊሃ በላይቤሪያ ሴኔት ውስጥ ተወዳድሮ አሸናፊ የሆነበት ዓመት ነው።

ሞሮኮ የኢቦላ ወረርሺኙ ወደ አገሬ ሊገባ ይችላል በሚል ስጋት የአዘጋጅት ድርሻውን እንደማትፈልግ በመግለጿ የአፍሪካ እግር ኳስ ማህበር (ካፍ) አገሪቷን ከእግር ኳስ ማገዱን አሳውቋል።

በዚህም ምክንያት ቀጣዩ የ 2015ቱ የአፍሪካ ዋንጫ በኢኩዋቶሪያል ጊኒ ዝግጅቱ በመካሄድ ላይ እንሚገኝም በስፋት ተዘግቧል።

ህግና ፍትህ

የዓለም ዓቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) በተለያዩ ወቅቶች በአፍሪካውያን ላይ ያለው አቋም ግልጽ አለመሆኑ ይገለጻል።ኢትዮጵያ በተያዩ መድረኮች ፍርድ ቤቱን በመሪነት በመቃወም ላይ ትገኛለች።

የኬኒያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬኒያታ በዚሁ በተጠናቀቀው የአውሮጳውያን ዓመት ሄግ በሚገኘው የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ቀርቦ የተመሰረተበትን ክስ ተከራክሮ ሲመለስ የአገሪቷ ዜጎች ደማቅ አቀባበል አድርገውለት ነበር።

የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ሃሰን አልበሺር በ 2009 በዳርፉር በተከሰተው የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመሰረተበት ክስ ምክንያት ፍርደ ቤት ቀርቦ ነበር።

---END---

በአዲሱ ረታ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Why & how" posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Why & how":

Share