Ethio-Online

Ethio-Online Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethio-Online, Media/News Company, Olompiya, Addis Ababa.

እነኾ ስሙአተ - ነገር 3!ዛሬ (መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓም) ምሽት፣ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ፤ ጉምቱ የጥበብ ሰው (ተዋናይ፣ አዘጋጅ፣ ጸሐፈ ተውኔት፣ ገጣሚ እና የማስታወቂያ ባለሙያ) የሆ...
16/03/2026

እነኾ ስሙአተ - ነገር 3!
ዛሬ (መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓም) ምሽት፣ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ፤ ጉምቱ የጥበብ ሰው (ተዋናይ፣ አዘጋጅ፣ ጸሐፈ ተውኔት፣ ገጣሚ እና የማስታወቂያ ባለሙያ) የሆነውን የዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ-ን ሥራዎች አድንቀን፤ አክብረናል፤ መጽሐፉንም መርቀናል። ክብር ለታላላቆቻችን!!!

ወዳጆች- አንድ ሰው ግን ስንት ነው!?እኔ፣ በግሌ እኔን ሳየው እና ሳውቀው- ሌላ ነው፤ ጋዜጠኛው ምንይሉ ሲያየኝ እና ያየውን ሲያመላክተኝ ደግሞ ፈጽሞ ሌላ ሰውዬ አልሆንላችሁ!!! አሁን ሌላ...
03/02/2026

ወዳጆች- አንድ ሰው ግን ስንት ነው!?
እኔ፣ በግሌ እኔን ሳየው እና ሳውቀው- ሌላ ነው፤ ጋዜጠኛው ምንይሉ ሲያየኝ እና ያየውን ሲያመላክተኝ ደግሞ ፈጽሞ ሌላ ሰውዬ አልሆንላችሁ!!!
አሁን ሌላ- "ደግሞ" ልጨምርና ነገ ረቡዕ 27/05/2018 ዓ.ም ከአመሻሹ 12:00 ሠዓት ላይ በ:- Minyilu podcasy "ምንይሉ ፖድካስት" ስትመለከቱኝ ደግሞ (እዚህም ጋር ሾልካ ገባች) ሌላ ሰውዬ እንደምሆንባችሁ አልጠራጠርም! ሳይንሳዊ ሃቅ ነው።
እነዚህ የማያባሩ እኔዎች ግን አይገርሙም? እኔስ ገርሞኝም አላባራ!!!
https://www.facebook.com/share/v/1ChCgQrRe1/

ማነው ጠያቂ? ማነው ተጠያቂ?! (ሚስጥር ነው!)ቀደም ሲል በዋና' (ሜኒስትሪም) ሚዲያ ዘርፍ ከሚታወቀው፤ አሁን ደግሞ በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ከተሰማራው ጋዜጠኛ ምንይሉ ጋር ዛሬ (ማክሰኞ ጥር...
27/01/2026

ማነው ጠያቂ? ማነው ተጠያቂ?!
(ሚስጥር ነው!)
ቀደም ሲል በዋና' (ሜኒስትሪም) ሚዲያ ዘርፍ ከሚታወቀው፤ አሁን ደግሞ በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ከተሰማራው ጋዜጠኛ ምንይሉ ጋር ዛሬ (ማክሰኞ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም) ጥሩ የቃለ-መጠይቅ መርሃ-ግብር አከናውነናል። ምንይሉ ፖድካስት-ን (Menyelu Podcast) እንዲከታተሉ እነኾ በአክብሮት ተጋብዘዋል። ነገር ግን፣ ማነው ጠያቂ? ማነው ተጠያቂ?! (ሚስጥር ነው!)
ይህን ሚስጥር ለፈታ፣
የ 100 ብር ካርድ በአንድ አፍታ!!!

አልቅሼ ዝም ከምል-ብዬ!ጌታቸው ወርቁእናንተዬ! እንዳለ ጌንቦ- ሞተ፤ ምነው ያ እንዳለ- የኮልፌው፤ የመርካቶው፤ የአዲስ ከተማው፤ የአሜሪካ ጊቢው፤ የለገሃሩ፤ የፒያሳው፤ የጊዮርጊሱ፤ የፈረንሳ...
02/01/2026

አልቅሼ ዝም ከምል-ብዬ!
ጌታቸው ወርቁ

እናንተዬ! እንዳለ ጌንቦ- ሞተ፤ ምነው ያ እንዳለ- የኮልፌው፤ የመርካቶው፤ የአዲስ ከተማው፤ የአሜሪካ ጊቢው፤ የለገሃሩ፤ የፒያሳው፤ የጊዮርጊሱ፤ የፈረንሳዩ፤ የቤላው፤ የአዲስ አበባው። የዐርባ ምንጩ- የጨንቻው። የኢትዮጵያው የሥነ-ጽሑፍ ልጅ።

ህይወትን እንዳቀለላት፣ እንዳሾፈባት፣ እንደሸሻት፣ እንደፈራት፣ እያነበበባት- እየፃፈባት (እርሷም በበኩሏ እላዩ ሰውነቱ ላይ ጽፋበት!) ሞተ።

ህይወቱ: እንደ ድርሰት ትልም- ተሞንጭራ፣ ባልተቋጨ ድርሰት- ዘይቤ፤ ባላለቀ ግጥም- ዜማ፣ ቤት ሳይደፋ፤ አንድ ነገር ሊፈጥር እንደዋተተ፣ ሳያልቅ- ተቋጨ እንደተባለ ወለፈንዴ ቴአትር- ሞተ ተባልን፤ እኛም አልን፤ ለፈፍን።

እኔ እንዳለን በምዕራፍ ዐንድ ሳውቀው እንዲህ ነበር:-

ለመጀመሪያ ጊዜ ያየሁት፣ ታዳጊ-ወጣት የ"ሃይ ስኩል" ተማሪ ሆኜ፣ በጎን ደግሞ ተሰጥዖዬን ለማወቅ በምጥርበት የ"አማተርነት" ጊዜዬ ነበር።

በአዲስ ከተማ አካባቢ የሚገኝ አንድ የኪነ-ጥበብ ክበብ፣ ለአዲስ ዓመት ዋዜማ መርሃ-ግብር ለማቅረብ:- ሙዚቃ፣ ግጥም፣ ወግ፣ አጭር ልቦለድ፣ እና የትወና ጥበብን አወዳድሮ ለመምረጥ ባወጣው ማስታወቂያ ተስበን ቀርበን ነበር- የተተዋወቅነው።

እኔ፣ በአዲስ ዓመት ተስፋ ላይ ተመስርቼ የፃፍኩትን ግጥም መድረክ ላይ አቅርቤ ስወርድ፣ በልበሙሉነት ጠጋ አለኝና ወረቀቱን እየተቀበለኝ "ግጥሙ አሪፍ ነበር፤ በመድረክ ፍርሃት ጨቆንከው፤ እንዲሁም፣ ከሚገባው በላይ አስረዘምከው፤ ቀደም ብሎ አይቼው ቢሆን ኖሮ፣ ከዚህ በላይ እናሳምረው ነበር" አለኝ።

ከፈታኞቹ አንዱ መስሎኝ ነበር።

በትወና ጥበብ ላይ የሚወዳደሩ ልጆች ሥማቸው ሲጠራ መድረክ ላይ ወጣ፤ የአንድ ሰካራም ገጸ-ባህሪን ወክሎ ተወነ፤ መድረኩ ላይ ሁለት ወደፊት፣ አንድ ወደኋላ እየተራመደ፣ በየመሐሉ የሰካራም ስቅታ እያሰማ፣ አሁን የማላስታውሰውን "ሞኖሎግ" አቅርቦ- ሁላችንንም አሳቀን።

አጨበጨብንለት።

ይሄ ክበብ፣ በሥነጽሑፍና ትወና ጥበብ ሁለታችንንም በአባልነት መረጠን። በሳምንት ሁለት ቀን የድምጽና እና የትወና ልምምድ በምናደርግበት ወቅት- ጓደኝነታችን ተፈጠረ።

ውሎው፣ መርካቶ አሮጌ መጽሐፍት ተራ፣ አዲስ ከተማ ወደ ሰባተኛ መውረጃ ነጋሽ መጽሐፍት ቤት (እውቁ ወግ ጸሐፊ መስፍን ሀብተማርያም) ቤት አካባቢ፣ ወደ በኋላ ደግሞ ድል በትግል አዳራሽ እና ምን አለሽ ተራ አካባቢ እንደነበረ- አስታውሳለሁ። ቆየት ብሎም፣ ለገሃር፣ ፒያሳ ጊዮርጊስ መጽሐፍት ተራ ማዕከሉ ሆነ።

ብዙ ጊዜ መርካቶ "የተቀመመች" የሚባል ቤት ለየት ያለ ምግብ:- ቅንጬ፣ ቡላ፣ እንቁላል፣ አይብ፣ ሽሮ ... ቅልቅል በእንጀራ እና በዳቦ ይጋብዘኝ ነበር።

በዚህ ጊዜ፣ እንዳለጌታ ከበደ (ደራሲ)፣ ወልቂጤ ከተማ ለከፈተው ቤተ-መጽሐፍት (በሃያ አምስት ሳንቲም የመጽሐፍት ኪራይ) ወደ አዲስ አበባ እየተመላለሰ፣ መጽሐፍት ይገዛል፤ እንዳለ ጌንቦ-ም ይተባበረው ስለነበር ወዳጅነታችን ጀመረ።

የእንዳለጌታ ከበደ-ን ገና ያልታተሙ ሥራዎች ያን ጊዜ ማንበብ ቻልን። እርሱ ቀደም ብሎ እፍታ ቅፆች ላይ ሥራዎቹ ታትመውለት ስለነበ፤ የእርሱን ዳና ተከትለን ተስፋዬ ገብረአብን እና መኩሪያ መካሻ (ተባባሪ ፕሮፌሰር)ን ለማግኘትና ለማነጋገር ታትረናል።

ከዕለታት በአንዱ ቀን- እንዳለ ጌንቦ፣ "ጌች፣ ሐመረ ኪን የጥበብ ክበብ- ፒያሳ ብንገባ እነ በእውቀቱ ስዩም፣ በኃይሉ ገ/እግዚአብሔር፣ አበበ ቶላ (አቤ ቶክቻው)ን እናገኛቸዋለን።

ፍካት ክበብ- አራት ኪሎ ብንገባ ደግሞ እነ ጀማል አህመድ፣ አንቀጸ ደስታ (በቀለ ሙለታ)፣ ዓለማየሁ ገላጋይ (አለገላ) እና ደራሲ ደምሴ ጽጌ እና ጋዜጠኛ ጌታቸው ሰናይ-ን እናገኛለን።

አሊያም "ውበት አማተር " እንግባ፣ ብዙ ባለተሰጥዖ ልጆቾ አሉ፤ እዛ ይሻለናል- አለኝ።

ሳላውቀው ፍካት ምርጫዬ ሆነ። በየጊዜው አራት ኪሎ እየሄድን እንማማር ጀመር። ያኔ ደምሴ ጽጌ፣ ጋሽ አስፋው ዳምጤ በእንግድነት ይመጡ ነበር።

ይሄ የጥበብ ህይወት መንገድ ጉዞ ቀጥሎ፣ በድምጻዊ ሽመልስ አራርሶ ይመራ የነበረው "ሚዩዚክ ሜይ ዴይ" የመጸሐፍ ንባብና ሂስ ክበብ አባል ሆንን፤ በየሁለት ሳምንቱ ገርጂ መንገድ ኢምፔሪያል ሆቴል ታዳሚ- ነበርን።

በአናቱም፣ በሩሲያ የሳይንስና የባሕል ማዕከል (ፑሽኪን) አባል ሆነን፣ በየወሩ የሚቀርበው መድረክ ላይ የጥበብ ሥራዎቻችን ይቀርቡ ጀመር።

በዚህ ወቅት፣ በሩሲያ ሥነ-ጽሑፍ ፍቅር ተነደፍን። እንዳለ፣ በድፍረት ራሱን የሩስኪ ቋንቋ አስተማረና፣ ሩሲያኖች በሚንቀሳቀሱበት ሥፍራ እየዋለ የአስተርጓሚነት ሥራ ጀመረ።

እነሱም አንድ የራሺያ ሥም አወጡለት፤ ይመስለኛል "ፒትረፋ" (ይሄን የሩስኪ ቃል ጠይቄ አጣራለሁ)። የአማርኛ ትርጉሙ ግን "ትንሹ የጎዳና ልጅ" የሚል እንደነበር በደንብ አስታውሳለሁ።

በዚህ ወቅት በጥበብ ሥራ ተነቃቅተን ነበር።

የእርሱን ድርሰት መጀመሪያ- እኔ፣ የእኔን ድርሰት ደግሞ- እርሱ አይቶ ሂስ ካደረግን በኋላ ነበር፣ ለሌላ ሰው የምናስነብበውና ለመድረክ እንዲውል የምንልከው።

በነዚህ የጊዜ ዑደቶች፣ አንዳለ ብዙ ውጣ ውረድ አልፏል፤ ጥሩ ሁኔታ ውስጥ ባልሆነበት ጊዜ ሁሉ፤ እንዳለ ከቤተሰብ፣ ከጓደኞቹ (ከእኛ) እና ከወዳጆቹ ሁሉ ይርቃል። ይጠፋል። ጥሩ ሁኔታ ላይ አለመሆኑ ይሰማል፤ ግን አይገኝም። ያዩት ልጆች ሲጠሩት፣ ባልሰማ ያልፋቸዋል። እነርሱም እንደልማዱ ዐመሉ ተነሳበት ብለው ይተዉታል።

በአንፃሩ፣ ጥሩ ሁኔታ ላይ ሲሆን ደግሞ፣ እንደርሱ ጓደኞቹንና ወዳጆቹን የሚፈልግና ሊወዱት ይችላሉ ወይም ዝንባሌያቸው ነው ያለውን መጽሐፍት አፈላልጎ በስጦታ መልክ የሚያበረክት አላየሁም።

የዩኒቨርሲቲ ትምህርቴን አጠናቅቄ፣ ወደ ሚዲያ ሥራ ከተሰማራሁ በኋላ፣ በየሰራሁባቸው ጋዜጦቾና መጽሔቶች በጽሑፍ አቅራቢነትና በዓምደኝነት ይሳተፍ ነበር። ኢትዮ-ምሕዳር ጋዜጣን ስመሰርት አብሮኝ ነበር- በዓምደኝነት። በራሱ ፍላጎት "ጠጅ ቤት" የሚል ዓምድ ከፍቶ በማኅበራዊ- ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ በነፃነት ይጽፍ ነበር። ይሳለቀው ነበር- አይገልጸውም።

ገጣሚ፣ ደራሲ፣ ተርጓሚ፣ አስተርጓሚ፣ የልጆች መጽሐፍት ጸሐፊ እና ኢትዮ-ምሕዳር ጋዜጣን ጨምሮ በልዩ ልዩ መጽሔቶችና ጋዜጦች ላይ በዓምደኝነት ያገለገለው እንዳለ ጌንቦ ጌዛ- ዛሬ ማለዳ ዐርፎ፣ ተሲያት በኋላ ተቀበረ። አለቀ በቃ- ኦሮማይ!!!

ውድ የሥነ-ጽሑፍ ቤተሰቦች!ወንድማችን፣ ጓደኛችንና ወዳጃችን ደራሲ እንዳለ ጌንቦ  ጌዛ፤ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፉን እህቱ ወ/ሮ ዘውድነሽ (0968502012) ዛሬ ማለዳ አረዳችኝ። የቀብር ሥ...
02/01/2026

ውድ የሥነ-ጽሑፍ ቤተሰቦች!
ወንድማችን፣ ጓደኛችንና ወዳጃችን ደራሲ እንዳለ ጌንቦ ጌዛ፤ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፉን እህቱ ወ/ሮ ዘውድነሽ (0968502012) ዛሬ ማለዳ አረዳችኝ።

የቀብር ሥነ-ስርዓቱም ዛሬ ዓርብ 24/04/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሠዓት ዊንጌት በሚገኘው ቅዱስ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን መካነ መቃብር ሥፍራ ይፈጸማል።

ወዳጆች ሆይ! በሕይወት ልንደርስለት የሞከርነው ባይሳካም ቅሉ፤ ኑ ወዳጃችንን በአግባቡ እና በወጉ እንሸኘው። እግዚአብሔር ነፉሱን በሠላም ያሳርፋት፤ አሜን!!!

ውድ ጓድ! ከዩኒቨርሲቲዎች ገና እንደወጣን በጠንካራ የጋዜጠኝነት ሙያ የሀገራችንን ፍትሕ፣ እኩልነት፣ ዴሞክራሲ እና የኢኮኖሚ እድገት ለማቅናት ላደረግነው ሙያዊ ትግል እና ለከፈልነው ሁሉ መስ...
30/12/2025

ውድ ጓድ!
ከዩኒቨርሲቲዎች ገና እንደወጣን በጠንካራ የጋዜጠኝነት ሙያ የሀገራችንን ፍትሕ፣ እኩልነት፣ ዴሞክራሲ እና የኢኮኖሚ እድገት ለማቅናት ላደረግነው ሙያዊ ትግል እና ለከፈልነው ሁሉ መስዋዕትነት- ቺርስ!

በላቀ ደስታና በከፋ መከራ ተፈትኖ ላለፈው ጓደኝነታችን (ወንድማማችነታችን)- እነኾ መንቶ ቺርስ!

ጓድ- ላሳየኸኝ/ላሳየሁህ ጥቅም ላልለወጠው እውነተኝነትና ታማኝነት- ባለህበት ባሕር ማዶ እነኾኝ ሰለስቱ-ቺርስ!!!

(ለጋዜጠኛ ኤፍሬም በየነ ዮሴፍ)

የራሺያ ሥነ-ጽሑፍ እና እኛ!ከዕለታት በአንዱ ቀን፣ "ጋሽ ስብሃት" አልኩት፤"ለበይክ" አለኝ-በዐረብኛ ቋንቋ፤ እንደ ህንድ የቡዲስት ካህን ሁለት እግሮቹን ወለሉ ላይ አጣጥፎ በተመስጦ ተቀሞጦ...
29/12/2025

የራሺያ ሥነ-ጽሑፍ እና እኛ!

ከዕለታት በአንዱ ቀን፣ "ጋሽ ስብሃት" አልኩት፤
"ለበይክ" አለኝ-በዐረብኛ ቋንቋ፤ እንደ ህንድ የቡዲስት ካህን ሁለት እግሮቹን ወለሉ ላይ አጣጥፎ በተመስጦ ተቀሞጦ- ቡና ሲጠጣ።

"የራሺያን ሥነጽሑፍ ሳነብ፣ የሀገሬን ስነጽሑፍ ያነበብኩ ያህል ነው የሚሰማኝ፤ ታሪኩ፣ መቼቱ፣ ገጸባህሪዎቹ፣ ሥነ-ልቦናቸው ወዘተ"።

ከጥቂት ተመስጦ በኋላ ...

"ጌቾ! ወደፊት ደራሲ መሆንህ ስለማይቀር፣ እሳት የላሰው ትውልድ ዐባል ስለሆንክም ጭምር- ልብ ብለህ ስማ፤" አለኝ- ደራሲ ስብሓት ገብረእግዚአብሔር።

"አየህ! ድርሰት ዓለማቀፍ ባህርይ አለው፤ ያው የትም ያለው አንድ የሰው ዘር ነው- አይደል! ይህን አትርሳ። ማፍቀር- መጥላት፣ ክፋት-ደግነት፣ መረዳዳት-ምቀኝነት ወዘተርፈ የሰው ሁሉ ባህርያት ናቸው።"

ጥቂት ዝምታ በመካከላችን ሰፈነ። ...

"ራሺያ እና እኛ ያለን ተመሳስሎሽ ግን ለየት ይላል" አለኝ ኮስተር ብሎ። "አባት አገር ራሺያ ቀደምት ባለታሪክ አገር ነው፤ እናት ሀገር ኢትዮጵያም እንዲሁ ቀደምት ናት፤ ሁለታችንም ለየህልውናችን በርካታ ተጋድሎ አድርገን- በድል ተወጥተናል።

ንጉሣዊያን ሥርዓቶች እዚያም እዚህም አይነኬ ሆነው ሰፍነው ነበረ፤ በሂደትም ኮስምነው ከስመዋል፤ እረ እንደውም በዐብዮቶች- ተገርስሰዋል!

የዐብዮት ምስቅልቅሎሽ እዚያም እዚህም ብዙ ጠባሳ አሳርፈዋል፤ የኑሮ ትግል ከበረዶ እና ከውቅያኖስ ጋር-እዚያ፣ ከጥቁር ዐፈር ጋር የኑሮ ትግል- እዚህ።

ከዚያ ደግሞ ሁለታችንንም እንደ መቀነት የሚያስተሳስሩን የኦርቶዶክስ ክርስትና እና እስልምና ደግሞ አሉልህ።

ይሄ ሁሉ በሰዎች ሥነልቦና ላይ የሚያሰርፀው ባህርይ (በእኛም ላይ ይሰፍናል!)- ገጸ-ባህርይ ሆኖ ተከሽኖ በድርሰት መልክ ሲቀርብልህ- አይ የሰው መመሳሰል እንደምትለው ሁሉ፣ ለአገራትም እንዲሁ ይሰራል።

ደግሞ ደራሲዎቻቸው ኃያልና ብርቱ ብዕርን ያነገቡ ናቸው። ሊዮ ቶልስቶይ፣ ፊዮዶር ዶስቶዮቭስኪ፣ አንቶን ቼክሆቭ፣ አሌክሳንደር ፑሽኪን፣ ኒኮላይ ጎጎል፣ ኢቫን ቱርጌኔቭ፣ ማክሲም ጎርኪ፣ አይቶማቶቭ ... እያልክ የንባብህን ያህል መሄድ ነው እንግዲህ! ...

ነገር ግን- እሳት የላሰው ትውልድ፣ አንድ ቁም ነገር አትዘንጋ፤ ራሺያን ሳይንስ እና ቴክኖሎጂን ጠንቅቀው- ያውቃሉ፤ ያለመታደል ሆኖ እኛ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ገና ጨዋ ነን- ዐራት ነጥብ

ወንድማችን:- ገጣሚ፣ ደራሲ፣ ተርጓሚ፣ የልጆች መጽሐፍት ጸሐፊ እና ኢትዮ-ምሕዳር ጋዜጣን ጨምሮ በልዩ ልዩ መጽሔቶችና ጋዜጦች ላይ በዓምደኝነት የሚታወቀው እንዳለ ጌንቦ ጌዛ፤  ከረቡዕ 15/...
28/12/2025

ወንድማችን:- ገጣሚ፣ ደራሲ፣ ተርጓሚ፣ የልጆች መጽሐፍት ጸሐፊ እና ኢትዮ-ምሕዳር ጋዜጣን ጨምሮ በልዩ ልዩ መጽሔቶችና ጋዜጦች ላይ በዓምደኝነት የሚታወቀው እንዳለ ጌንቦ ጌዛ፤ ከረቡዕ 15/04/18 ዓ.ም ጀምሮ በጠና ታሞ፣ 6 ኪሎ ያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው ሚሲዮን ክሊኒክ (ማዘር ቴሬዛ) ተኝቶ እንደሚገኝ የቀድሞ የሥራ ባልደረባችን አህመድ ባለኬር (0913700922) ዛሬ ከሰዓት በኋላ አሳወቀኝ።
በአዲስ አበባ ኮልፌ የሚኖሩት ቤተሰቦቹ (እህቶቹ) ያለበትን ሁኔታ ስለማያውቁ፣ የስልክ አድራሻቸው ያላችሁ አሳውቁን።
ደራሲ ዓለማየሁ ገላጋይ፣ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ (ዶ/ር) እና ገጣሚ ምስራቅ ተረፈ በውስጥ መስመር አግኙን። ከቻልን በሕይወት እንድረስለት፤ ካልቻልን ደግሞ በአግባቡ (በወጉ)እንሸኘው።

12/11/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር 70ኛ ዓመቱን ክብረ- በአል፣ ዛሬ ሕዳር 3 ቀን 2018 ዓም ከቀኑ 7:30 ሰዓት ጀምሮ ማክበር ይጀምራል!

በዛሬው መርሃ ግብር:-
- የማርሽ ባንድ ትርኢት፣
- የባሕል ሙዚቃ፣
- የመክፈቻ ስነ ስርዓት፣
- የቴአትር ቤቱ የ70 ዓመታት ጉዞ ቅኝት፣
- የቫራይቲ ኦርኬስትራ ትርኢት፣
- ከቀድሞ ቴአትሮች ቅንጭብጭብ፣ እና
-"ዴጊያ" የተሰኘ አዲስ ቴአትር ይቀርባል።

Address

Olompiya
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio-Online posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio-Online:

Share