EBC-መዝናኛ

EBC-መዝናኛ Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.
(1)

አርቲስት ዘለቀ ገሰሰ በእሑድ ቤት ዚያራ 🔥*************እሑድ ቤት የሬጌ አርቲስት ዘለቀ ገሰሰን  ዘይሯል።በሬጌ ሙዚቃ በአፍሪካ ብቸኛው የግራሚ አዋርድ ተሸላሚ ነው። የቦብ ማርሌይ ል...
17/08/2025

አርቲስት ዘለቀ ገሰሰ በእሑድ ቤት ዚያራ 🔥
*************

እሑድ ቤት የሬጌ አርቲስት ዘለቀ ገሰሰን ዘይሯል።

በሬጌ ሙዚቃ በአፍሪካ ብቸኛው የግራሚ አዋርድ ተሸላሚ ነው። የቦብ ማርሌይ ልደት ላይም የሙዚቃ ሥራውን አቅርቧል።

አሜሪካ በከፈተው ክለብ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማን ጨምሮ ታዋቂ ሰዎች ሥራዎቹን ይታደሙ ነበር።

ዘለቀ ገሰሰ የአርት ማሰልጠኛ ማዕከልም በመጀመር ተተኪ ለማፍራት እየጣረ ነው።

ከጎሬ እስከ አሜሪካ የሕይወት ጉዞውን በእሑድ ቤት ዚያራ አጫውቶናል ይመልከቱት!
https://www.youtube.com/watch?v=kG8HpbSSF0w

#ዚያራ

አዳዲስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የኢቢሲን መተግበሪያ ከአፕ ስቶር እና ፕለይ ስቶር አውርደው ዲጂታል ኢቢሲን ይቀላቀሉ።

አንድሮይድ (Android) ስልክ የምትጠቀሙ በዚህ ሊንክ ➡️ https://shorturl.at/6KegY

አይኦኤስ (iOS) ስልክ የምትጠቀሙ ደግሞ በዚህ ሊንክ ➡️ https://shorturl.at/hFuA1

እሑድ ቤት የሬጌ አርቲስት ዘለቀ ገሰሰን ዘይሯል። በሬጌ ሙዚቃ በአፍሪካ ብቸኛው የግራሚ አዋርድ ተሸላሚ ነው። የቦብ ማርሌይ ልደት ላይ የሙዚቃ ሥራውን አቅርቧል። አሜሪካ በከፈተው ክለ...

ባለትዳሮቹ  ድምፃዊት ብፅአት ስዩም እና አርቲስት ተስፋዬ ገ/ሃና በእሑድ ቤት🔥**********************ባለትዳሮቹ  ድምፃዊት ብፅአት ስዩም እና አርቲስት ተስፋዬ ገ/ሃና በእሑድ ቤ...
17/08/2025

ባለትዳሮቹ ድምፃዊት ብፅአት ስዩም እና አርቲስት ተስፋዬ ገ/ሃና በእሑድ ቤት🔥
**********************

ባለትዳሮቹ ድምፃዊት ብፅአት ስዩም እና አርቲስት ተስፋዬ ገ/ሃና በእሑድ ቤት እንግዶቻችን ሆነው ተገኝተዋል።

በቆይታቸውም ብፅአት ስዩም ወደ ሙዚቃ የገባችበትንና ሙዚቃ ያቆሞችበትን አጋጣሚ አጫውታናለች።

አርቲስት ተስፋዬ ገ/ሃና የሙያ ፍቅር ከኢትዮጵያ እስከ አውስትራልያ ገጠመኙን አጋርቷል።
ድምፃዊት ብፅአት ስዩም እና አርቲስት ተስፋዬ ገ/ሃና በልጅ ልጆቻቸው ታጅበው እሑድ ቤትን አድምቀውታል።

የነበራቸውን አስደሳች ቆይታ ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ! https://www.youtube.com/watch?v=qT_13DJ_L6Q

አዳዲስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የኢቢሲን መተግበሪያ ከአፕ ስቶር እና ፕለይ ስቶር አውርደው ዲጂታል ኢቢሲን ይቀላቀሉ።

አንድሮይድ (Android) ስልክ የምትጠቀሙ በዚህ ሊንክ ➡️ https://shorturl.at/6KegY

አይኦኤስ (iOS) ስልክ የምትጠቀሙ ደግሞ በዚህ ሊንክ ➡️ https://shorturl.at/hFuA1

ብፅአት ስዩም ወደ ሙዚቃ የገባችበትንና ሙዚቃ ያቆሞችበትን አጋጣሚ አጫውታናለች።አርቲስት ተስፋዬ ገ/ሃና የሙያ ፍቅር ከኢትዮጵያ እስከ አውስትራልያ ገጠመኙን አጋርቷል።ድምፃዊት ብ.....

17/08/2025

የኢትዮጵያ አይዶል ወላይታ ሶዶ በቀጥታ - የካዎ ጦና ከተማ ድምፆች

ከውብ ሕዝቦች መገኛዋ ጋምቤላ - የኑዌሮች ባህል****የጋምቤላ ክልል ውብ መልከዓ ምድራዊ አቀማመጥ ያለው ሲሆን፤ በወርቅ፣ በእንስሳት ሃብት፣ በዓሳ ምርት፣ በማር እና በተለያዩ የተፈጥሮ መስ...
17/08/2025

ከውብ ሕዝቦች መገኛዋ ጋምቤላ - የኑዌሮች ባህል
****

የጋምቤላ ክልል ውብ መልከዓ ምድራዊ አቀማመጥ ያለው ሲሆን፤ በወርቅ፣ በእንስሳት ሃብት፣ በዓሳ ምርት፣ በማር እና በተለያዩ የተፈጥሮ መስህቦች የበለጸገ ነው።

እርሻ ውጤቶች ጋር ተያያዥነት ያለው ሰፊ ሃብት አለው፡፡

በጋምቤላ ክልል ከሚገኙ ብሔረሰብ ውስጥ የኑዌርብሔረሰብ አንዱ ነው፡፡

ኡራንግ እየተባለ የሚጠራ ስፍራ አለ፡፡ ማኀበረሰቡ በርካታ እሴት እና ባህሎችም አሉት፡፡

በኡራንግ አካባቢ የሚገኙ ኑዌሮች በከብት ሀብታቸው በሰፊው ይታወቃሉ።

የኑዌሮች ባህል እና እሴት ከከብቶቻቸው ሕይወት ጋር የተቆራኘም ነው፡፡

የአብዛኛው ማኀበረሰብ ኑሮ እና መተዳደሪያው አርብቶ አደርነት ሲሆን፤ የእርሻን ሥራን ጎን ለጎንም ያካሂዳሉ፡፡

የቤት ውስጥ ሥራዎች በአብዛኛው በሴቶች የሚከወን ሲሆን፤ ወንዶች የተቀረውን የመስክ ሥራ ያግዛሉ፡፡

ልጆች ሲርባቸውም ሆነ ሲጠማቸው በአጠገባቸው ያሉ ላሞችን አልበው ወተት ይጠጣሉ እንጂ ወላጆቻቸውን ምግብ ብለው እንደማያስቸግሩም ነው የአካባቢው ማህበረሰቦች የሚያስረዱት፡፡

መኖሪያ ቤቶቻቸው ጎጆ ቤቶች ሲሆኑ ማህበረሰቡ እርስ በእርስ በመደጋገፍ እና በመተባበርም ነው የሚኖሩት፡፡

ምግቦቻቸውን ከበቆሎ፣ ከማሽላ እና ከስንዴ የሚዘጋጁ ሲሆን፤ በብዛት ግን በማህበረሰቡ ዘንብድ የበቆሎ ገንፎ ይዘወተራል፡፡

ኑዌሮች እርስ በእርስ በመደጋገፍ እና በተለያዩ እሴቶቹ በስፋት ይታወቃል፡፡

በሜሮን ንብረት

አዳዲስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የኢቢሲን መተግበሪያ ከአፕ ስቶር እና ፕለይ ስቶር አውርደው ዲጂታል ኢቢሲን ይቀላቀሉ።

አንድሮይድ (Android) ስልክ የምትጠቀሙ በዚህ ሊንክ ➡️ https://shorturl.at/6KegY

አይኦኤስ (iOS) ስልክ የምትጠቀሙ ደግሞ በዚህ ሊንክ ➡️ https://shorturl.at/hFuA1

አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ********በኪነ-ጥበቡ ዓለም ታላቅ ዐሻራቸውን ያሳረፉት ክቡር ዶክተር አርቲስት ደበበ እሸቱ ማረፋቸውን ከቤተሰባቸው የተገኘው መረጃ ያመለክታል...
17/08/2025

አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ
********

በኪነ-ጥበቡ ዓለም ታላቅ ዐሻራቸውን ያሳረፉት ክቡር ዶክተር አርቲስት ደበበ እሸቱ ማረፋቸውን ከቤተሰባቸው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ክቡር ዶክተር አርቲስት ደበበ እሸቱ ለሀገራቸው ያላቸውን የማይናወጥ ፍቅር እስከ እስትንፋሳቸው መጨረሻ ያሳዩ ፅኑ ሀገር ወዳድ ነበሩ።

የታሪክ ድርሳናቸው እንደሚያስረዳው አርቲስት ደበበ እሸቱ በ1934 ዓ.ም ነው የተወለዱት። የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አዲስ አበባ በሚገኘው ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተከታትለዋል።

በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪ እያሉ ቲያትር የመስራት ዕድሉ ገጥሟቸው ነበር።

ከዛ በመቀጠል የአብራሪነት ስልጠና ለመውሰድ እጩ መኮንን ሆነው የኢትዮጲያ አየር ሀይልን ተቀላቀሉ። በአየር ኃይል የመዝናኛ ክፍሉ ላይ በመሳተፍ ቲያትር ሰርተዋል።

አርቲስት ደበበ እሸቱ፤ በሀገር ፍቅርና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ (የአሁኑ ብሔራዊ ቴአትር) መድረክ ላይ ለረዥም ዓመታት በተዋናይነትና በአዘጋጅነት አገልግለዋል።

በተለያዩ ፊልሞች ላይ በመሪ ተዋናይነትም ተሳትፈዋል። በሆሊውድ በተሠራው 'ሻፍት ኢን አፍሪካ' በተሰኘው ፊልም ላይ በመሳተፍም ስማቸውን በደማቁ ፅፈዋል።

በእንግሊዘኛ ከሠሩባቸው ፊልሞች መካከል 'ዘ ሴይለር ፍሮም ጂብራልታር'፣ 'ጉማ'፣ 'ዘ አፍሪካን ስፓይ'፣ 'ዜልዳ'፣ 'ዘ ግሬቭ ዲገር' እና 'ዘ ግሬት ሪቤሊየን ' ይጠቀሳሉ።

'ዘ ጌም ኦፍ ቼዝ' ላይ በትወና ፣ 'ኦቴሎ' ላይ በመተወን እና በማዘጋጀትም የጥበብ አሻራቸውን አኑረዋል።

ደበበ እሸቱ ከአርቲስቱ በተጨማሪ በራድዮና በቴሌቪዥን ሥራዎችም ላይ ተሳትፈዋል። 'ያላቻ ጋብቻ'፣ 'ሮሚዎና ዡልየት' እና 'ዳንዴው ጨቡዴ' ከተወኑባቸው ሥራዎች ጥቂቶቹ ናቸው።

አርቲስት ደበበ እሸቱ እ.አ.አ. በ1985 ዚምባቡዌ በተካሄደው ቴአትር ለልማትና ዕድገት ወርክሾፕ ላይ በብቃት በመሳተፍ የአፍሪካ የመድረክ ባለሙያዎች ማሕበርን አስተባብረው በማቋቋም የማሕበሩም መስራች ፕሬዚዳንት ሆነው ለ12 ዓመታት አገልግለዋል።

ለአፍሪካ ቲያትር ባደረጉት አስተዋጽኦ የዚምባብዌን ማላካይት አዋርድ ወስደዋል። ጣይቱ ኢንተርቴንመንት በዋሽንግተን ዲሲ በቲያትር ዘርፍ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ አድርጓቸዋል።

በአትላንታ ጂኦርጂያ የከተማው ምክር ቤት ለዓለም ቲያትር ባደረጉት አስተዋጽኦ ኖቬምበር 24ን የደበበ እሸቱ ቀን በሚል ሰይሞላቸዋል።

የኢትዮጲያ ባህል ሚኒስትርም ለኢትዮጲያ ፊልም እድገት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ሸልሟቸዋል።

በጉማ አዋርድም የሕይወት ዘመን ተሸላሚ ሆነዋል።

እ.አ.አ በ2015 በቫንኮቨር ዓለማቀፍ ፊልም ፌስቲቫልም በምርጥ መሪ ተዋናይ ዘርፍ ተሸላሚ ሆነዋል። በ2015 ዓ.ም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለሃገራቸው ባበረከቱት አስተዋጽኦ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሸልሟቸዋል።

አርቲስት ደበበ እሸቱ በ1995 ዓ.ም በሃገራዊ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ውስጥ በመሳተፍ የምክር ቤት አባል እና የፓርቲያቸው የሕዝብ ግንኙነት በመሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉ ሰው ናቸው። በዚህም ከሌሎች አመራሮች ጋር በተለያዩ ጊዜያት ለእስር ተዳርገው ነበር።

ኢቢሲ ለቤተሰባቸው፣ ለወዳጅ ዘመድ እና ለመላው አድናቂዎቻቸው መጽናናትን ይመኛል።

የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የኪነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ሚና ከተጫወቱ አንዱና ግንባር ቀደሙ አንጋፋው የመድረክ ፈርጥ፣ ደራሲ፣ ተርጓሚ፣ ተዋናይ፣ ከያኒ፣ ጋዜጠኛ፣ የመብት ተሟጋች እና ሀገር ወዳዱ የክብር ዶክተር አርቲስት ደበበ ህልፈተ ሕይወት የተሰማውን ሐዘን ገልጿል።

ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው በ83 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን በመስማታችን ታላቅ ሀዘን ተሰምቶናል ሲልም ሚኒስቴሩ መግለጫ አውጥቷል።

የከብቶች ሃብት ማብሰሪያ ስነ-ስርዓት በወላይታ*******በወላይታ ብሔር ባህል መሰረት አንድ ግለሰብ ያፈራቸው የከብቶች ብዛት 100፣ 1000 እና 10 ሺ ሲሞላ የሀብት ማብሰሪያ ስነ-ስርዓት...
17/08/2025

የከብቶች ሃብት ማብሰሪያ ስነ-ስርዓት በወላይታ
*******

በወላይታ ብሔር ባህል መሰረት አንድ ግለሰብ ያፈራቸው የከብቶች ብዛት 100፣ 1000 እና 10 ሺ ሲሞላ የሀብት ማብሰሪያ ስነ-ስርዓት ይደረጋል።

ይህ ስነስርዓት የማህበረሰቡን የቁጠባ ባህል በእጅጉ የሚያሳድግ ሲሆን የከብቶች ቁጥር 100 ሲሆን ዳላ፣ 1000 ሲሆን ሊቃ፣ 10 ሺ ሲሞላ ደግሞ ኡማ በመባል ይታወቃል።

በእነዚህ የሀብት ማብሰሪያ ቀናት የከብቶቹ ባለቤት ድግስ አዘጋጅቶ ወዳጅ ዘመዶቹን ይጋብዛል።

በእለቱ ከብቶቹ በሙሉ ወደ አንድ የታጠረ ስፍራ የሚሰበሰቡ ሲሆን፣ ደጋሹ የቤተሰቡን እና የእራሱን የቁጠባ ባህል በሽለላ እና በቀረርቶ ያሰማል።

ለሌሎችም የቁጠባ ባህሉን ተሞክሮ የሚያካፍልበት ሂደትም የድግሱ አካል ይሆናል።

ሀብቱን የሚያበስረው ግለሰብ እና ባለቤቱ በባህላዊ አልባሳት እና ጌጣጌጦች ደምቀው የሚታዩበት ዕለትም ነው።

በዕለቱ ለስነ-ስርአቱ ማድመቂያ የፈረስ ጉግስ ይካሄዳል።

በተመስገን ተስፋዬ

አዳዲስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የኢቢሲን መተግበሪያ ከአፕ ስቶር እና ፕለይ ስቶር አውርደው ዲጂታል ኢቢሲን ይቀላቀሉ።

አንድሮይድ (Android) ስልክ የምትጠቀሙ በዚህ ሊንክ ➡️ https://shorturl.at/6KegY

አይኦኤስ (iOS) ስልክ የምትጠቀሙ ደግሞ በዚህ ሊንክ ➡️ https://shorturl.at/hFuA1

ደቡብ ኮሪያ ያሰማራቻቸው የሆሎግራፊክ ቴክኖሎጂ ፖሊሶች *******ደቡብ ኮሪያ ሰዎች በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች ላይ ወንጀሎችን ለመከላከል እና ደህንነትን ለማጠናከር የሚረዱ የስሪ ዲ (3D) ...
17/08/2025

ደቡብ ኮሪያ ያሰማራቻቸው የሆሎግራፊክ ቴክኖሎጂ ፖሊሶች

*******

ደቡብ ኮሪያ ሰዎች በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች ላይ ወንጀሎችን ለመከላከል እና ደህንነትን ለማጠናከር የሚረዱ የስሪ ዲ (3D) ቴክኖሎጂ ምስለ ፖሊሶችን አገልግሎት ላይ አውላለች።

በቴክኖሎጂ ስማቸው "ሆሎግራፊክ" በመባል የሚጠሩት እነዚህ ስሪ ዲ ምስሎች በብርሃን የተሞሉ እና እውነተኛ የሚመስል ገፅታ ያላቸው ናቸው።

ፖሊሶቹ 170 ሴ.ሜ ቁመት ሲኖራቸው ከምሽት 1 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት ድረስ በማዕከላዊ ሴኡል ውስጥ በሚገኘው የጁዶንግ ፓርክ መታየት ጀምረዋል።

"ሆሎግራሚካ" በተባለ ኩባንያ የተሰሩት እነዚል ምስለ ፖሊሶች ድንገተኛ አደጋ ከተፈጠረ የሚያደርጉት ነገር አይኖርም። ይልቁንም ፖሊስ በፍጥነት እስኪመጣም አካባቢውን የሚቃኙ የደህንነት ካሜራዎች መኖራቸውን ለሰዎች ይነግራሉ።

የስሪ ዲ ፖሊሶቹ አገልግሎት ላይ ከዋሉበት ጊዜ አንስቶ በፓርኩ ውስጥ የሚፈጸሙ ወንጀሎች በ22 በመቶ ቀንሰዋል ሲል የሴኡል ሜትሮፖሊታን ፖሊስ ኤጀንሲ አስታውቋል።

የጁንግቡ ፖሊስ አዛዥ አን ዶንግ-ሃዩን እንዳሉት ሆሎግራም የስነ-ልቦና መረጋጋትን የሚሰጥ እና ስርዓት አልበኝነትን የሚከላከል የደህንነት መሳሪያ መሆኑን ገልፀዋል።

ምንም እንኳን ይህ ቴክኖሎጂ ወንጀለኞችን በቀጥታ መያዝ ባይችልም፣ ወንጀልን በመከላከል እና የደህንነት ስሜትን በመፍጠር ረገድ ትልቅ ውጤት እንዳለው የዘገበው ኦዲት ሴንትራል ነው።

አዳዲስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የኢቢሲን መተግበሪያ ከአፕ ስቶር እና ፕለይ ስቶር አውርደው ዲጂታል ኢቢሲን ይቀላቀሉ።

አንድሮይድ (Android) ስልክ የምትጠቀሙ በዚህ ሊንክ ➡️ https://shorturl.at/6KegY

አይኦኤስ (iOS) ስልክ የምትጠቀሙ ደግሞ በዚህ ሊንክ ➡️ https://shorturl.at/hFuA1

“ልዑል ሲሳይ ጋር ባለመስራቴ እቆጫለሁ” የሙዚቃ ባለሙያው ሚካኤል ሀይሉ (ሚኪ  ጃኖ)👉“ታናናሾቼ የማያፍሩበትን ሥራ መስራት እፈልጋለሁ”
16/08/2025

“ልዑል ሲሳይ ጋር ባለመስራቴ እቆጫለሁ” የሙዚቃ ባለሙያው ሚካኤል ሀይሉ (ሚኪ ጃኖ)

👉“ታናናሾቼ የማያፍሩበትን ሥራ መስራት እፈልጋለሁ”

“ልዑል ሲሳይ ጋር ባለመስራቴ እቆጫለሁ” የሙዚቃ ባለሙያው ሚካኤል ሀይሉ (ሚኪ ጃኖ)

👉“ታናናሾቼ የማያፍሩበትን ሥራ መስራት እፈልጋለሁ”

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ለሙዚቃ ወዳጆች ከሚደርሱ አልበሞች ጀርባ በቅንብር ደረጃ ከፍተኛ ተሳትፎ በማድረግ ላይ የሚገኘው የሙዚቃ ባለሙያው ሚካኤል ሀይሉ (ሚኪ ጃኖ) በስራዎቹ ዙሪያ ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 መሰንበቻ የሬድዮ ፕሮግራም ጋር ቆይታ አይድርጓል፡፡

በእዚህ መንገድ ለሙዚቃ አፍቃሪያን ከደረሱት አልበሞች መካከል ‹‹አንድ ቃል›› የተሰኘው የሚካኤል በላይነህ አልበም ሲጠቅስ በእዚህ አልበም ውስጥ ከተካተቱ ስራዎች ውስጥ ‹‹ጠይም›› ሙዚቃ የተለየ ስሜት እንደሚፈጥርበት ተናግሯል፡፡

በሙዚቃ ጉዞ ውስጥ ‹‹ኢንዱስትሪው ላይ አንድ ነገር ጠብ ያደረኩኝ ይመስለኛል።›› ሲል የገለፀው ሚኪ ጃኖ በሚሰሩ የሙዚቃ ስራዎች ዙሪያ ህዝብ የሚሰጠውን ግብረ መልስ ለማየት እንደሚጓጓ በቆይታው አንስቷል፡፡

በእዚህ መነሻነት ‹የሙዚቃ ስራ ስሜት ማጋባት ነው። እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ ወደፊት ሙዚቃችንን እየቀየርነው፡፡›› ያለ ሲሆን በእዚህ ሂደት ውስጥ የሙዚቃ አፍቃሪው ስሜት መልካም እና ጥሩ ስሜት ፈጣሪ እንደሆነ ገልጿል፡፡

ከዚህ ባሻገር በእርሱ የሙዚቃ ቅንብር ዙሪያ ባነሳው ሃሳብ ‹‹አንድ አርቲስት ወደ እኔ ሲመጣ መገለጫውን አልነፍገውም›› ያለ ሲሆን የእዚያን ባለሙያ መገለጫ ቀለም ተከትሎ ሥራዎችን ለመስራት እንደሚሞክር አንስቷል፡፡

‹‹የመጣሁት ሙዚቃ ልሰራ ነው፡፡›› ያለው ሚኪ ጃኖ ‹‹የመጣሁበትን እያደረኩ የምወደውን ሙዚቃ እየሰራሁ ነው፡፡›› ሲል የገለፀው ሙዚቃኛው እርሱ ወደ ሙዚቃ እንዲገባ ምክንያት የሆኑት እና እንደ አርኣያ የሚያያቸው ባለሙያዎች እንዳሉም አስታውቋል፡፡

አክሎም በእርሱ እርሱን አርአያ አድርገው ሙዚቃን መስራት የሚሹ ወጣቶች ‹‹የማያፍሩበትን ሥራ ለመስራት እጥራሉ፤ ለእነርሱ የሚረዳ ነገር ባስቀምጥላቸው ደስ ይለኛል፡፡›› ሲል በቆይታው የጠቆመው ሚኪ ጃኖ ‹‹ዕድሜ እና ጊዜ ሰጥቶች ባስተምር ደስ ይለኛል›› ሲል ሚኪ ጃኖ አሁንም በአዳዲስ ስራዎች ወደ ሙዚቃ ወዳጆች የመምጣት ጉዞው እንደማይገታ ተናግሯል፡፡

ከእዚህ ቀደም በነበረው ልምዱ ከፍተኛ የስራ ጫና ውስጥ ይገባ እንደነበር በማንሳት በቂ እንቅልፍ የሚያገኝበት አጋጣሚ እንዳልነበር ያስታወሰ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን ቢያንስ ሰባት ሰዓታት እንደሚተኛ ገልጿል፡፡

ከበርካታ ድምፃዊያን ጋር የመስራት እድል ያገኝው ሚኪ ጃኖ ቅርብ ከመጡ ድምፃውያን ከልዑል ሲሳይ ጋር መስራት ባለመቻሉ ግን እንደሚቆጭ ለኤፍ ኤም አዲስ 97.1 መሰንበቻ ፕሮግራም ገልፆል::

የሙዚቃ ባለሙያወ ከመሰንበቻ ጋር ያደረገውን ሙሉ ቆይታ ተከታዩን ሊንክ በመጫን ቀሪውን ያድምጡት

https://youtu.be/NQXnmEgpQs8?si=FUOtk_34vb723Kug

ናትናኤል ሀብታሙ

ክረምት እና የጥርስ ህመም ***********የክረምት ወቅት በተለያዩ የሰውነት ክፍሎቻችን ላይ ቅዝቀዘዜ በደንብ የሚሰማበት ወቅት ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ የክረምት ወቅት የጥርስ ህመም ስሜቱ ...
16/08/2025

ክረምት እና የጥርስ ህመም
***********

የክረምት ወቅት በተለያዩ የሰውነት ክፍሎቻችን ላይ ቅዝቀዘዜ በደንብ የሚሰማበት ወቅት ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ የክረምት ወቅት የጥርስ ህመም ስሜቱ ጎልቶ የሚሰማበት ወቅትም ጭምር መሆኑ በተደጋጋሚ ይነሳል፡፡

ኢቢሲ በአዲሰ ቀን ክረምት እና የጥርስ ህመም ምን ያገናኛቸዋል ሲል ከባለሙያ ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡ የጥርስ እና የአፍ ውስጥ ሐኪም ዶክተር ተድላ ተሰማ በህክምናው ዘርፍ 14 ዓመታት እንዳገለገሉ ገልፀዋል፡፡ ክረምት እና የጥርስ ህመም ሰፊ ግንኙነት እንዳላቸውም ባለሙያው አንስተዋል፡፡

በጥርስ ዙሪያ በበጋ ወቅት ችግር የነበረባቸው እንደ ጥርስ መቦርቦር፤ የድድ መሸሽ፤ የጥርስ መበላት እና የመሳሰሉት ችግሮች በበጋ ወቅት ሙቀት በመሆኑ ህመሙ ሳይሰማ ቆይቶ በክረምት ወቅት ህመሙ እንደሚጎላ ባለሙያው አብራርተዋል፡፡

ችግሩ ከ20 እስከ 50 የእድሜ ክልል ውስጥ በሚገኙ ሰዎች የጎላ ቢሆንም ጣፋጭ ነገሮችን በሚጠቀሙ ልጆች ላይም እየተስተዋለ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ የልጆች ጥርስ እንደ አዋቂዎች ጠንካራ ባለመሆኑ ለመጎዳት ቅርብ መሆኑን አያይዘው ተናግረዋል፡፡

ለጥርስ ህመም መከሰት ትልቁን ድርሻ የሚወስደው የጥርስ ፅዳትን አለመጠበቅ ሲሆን ከጥርስ መታጠብ ጋር በተያያዘ የጥርስ መስታወት ይጎዳል የሚለው አመለካከት የተሳሳተ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

የማህበረሰቡ የአፍ እና የጥርሱን ጤና የመጠበቅ ባህሉ ዝቅተኛ መሆኑን የሚናገሩት ባለሙያው፤ ጥርስ በሚታጠብበት ወቅት በርካታ ቆሻሻዎች ድድን አሽሽተው ተቀምጠው ይገኛሉ ብለዋል፡፡

ከጥርሱ ላይ ሲወገዱ ጥርሱ በቆሻሻ ተሸፍኖ የቆየ ስለሆነ የቅዝቃዜ ስሜት ህመም ይፈጥራልም ነው ያሉት፡፡

የጥርስ ህመም ከሌሎች የህመም አይነቶች ከፍ ያለ ሲሆን፤ ይህም የሆነበት ምክንያት በአንዲት ዘለላ ጥርስ ውስጥ የደም ስሮች እና የነርቭ ክፍሎች በመገኘታቸው ነው ብለዋል፡፡

ጥርስ ችግር በሚኖርበት ወቅት የደም ስር ስለሚሰፋ የነርቭን ክፍል አጣብቆ ስለሚይዘው ከፍተኛ ህመም እንዲፈጠር ምክንት ይሆናል ነው ያሉት ባለሙያው፡፡

በንፍታሌም እንግዳወርቅ

16/08/2025

ኪን ኢትዮጵያ - የማንሰራራት ብስራት
*******************
በቻይና ሁቤይ ግዛት የመድረክ ዝግጅት
ዛሬ ምሽት 1 ሰዓት በኢቲቪ መዝናኛ ቻናል ይጠብቁን

የመጀመሪያ የዓለም ሮቦቶች ጨዋታ በቤጂንግ *******በቻይና ቤጂንግ የመጀመሪያው የዓለም ሮቦቶች ጨዋታ በመካሄድ ላይ ይገኛል።በውድድሩ ላይ አሜሪካን፣ ጀርመንን እና ጃፓንን ጨምሮ ከ16 ሀገ...
15/08/2025

የመጀመሪያ የዓለም ሮቦቶች ጨዋታ በቤጂንግ
*******

በቻይና ቤጂንግ የመጀመሪያው የዓለም ሮቦቶች ጨዋታ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በውድድሩ ላይ አሜሪካን፣ ጀርመንን እና ጃፓንን ጨምሮ ከ16 ሀገራት የተውጣጡ ቡድኖች እንየተሳተፉ መሆኑ ተገልጿል።

ሮቦቶቹ አትሌቲክስን ፣ እግር ኳስን ፣ ዳንስን እና ማርሻል አርትን ጨምሮ በተለያዩ የውድድር ዘርፎች ላይም እየተወዳደሩ ይገኛል።

በቤጂንግ በመካሄድ ላይ ያለው የሮቦቶች ውድድር ታዲያ ማዝናናትን ብቻ አይደለም አላማ ያደረገው።

አዘጋጆቹ እንዳሉት ውድድሮቹ የሮቦቶችን አስተሳሰብ፣ እንቅስቃሴ እና የመቆጣጠር ችሎታን ለመፈተሽ ያግዛሉ።

ከዚህ በኋላም በተጠናከረ ሁኔታ ሮቦቶች በፋብሪካዎች እና ቤቶች ውስጥ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ ጥቅም ላይ ሊውሉ ይችላሉ ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።

በሴራን ታደሰ

15/08/2025

ኪን ኢትዮጵያ - የማንሰራራት ብስራት
*******************
በቻይና ሁቤይ ግዛት የመድረክ ዝግጅት
ነገ ምሽት 1 ሰዓት በኢቲቪ መዝናኛ ቻናል ይጠብቁን

Address

Churchil Road
Addis Ababa
+251115516977

Telephone

+251115172539

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EBC-መዝናኛ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EBC-መዝናኛ:

Share

Our Story

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website.