Henok Abera Mamo

Henok Abera Mamo There can be no higher law in journalism than to tell the truth and to shame the devil. Walter Lippma

በጣም ልብ ይሰብራል በአደጋዉ ለሞቱት ሰላማዊ እረፍትን ላዘኑ ልቦች ደግሞ መጽናናትን እመኛለሁ!
30/12/2024

በጣም ልብ ይሰብራል በአደጋዉ ለሞቱት ሰላማዊ እረፍትን ላዘኑ ልቦች ደግሞ መጽናናትን እመኛለሁ!

የታሪክ የቅርስ የስልጣኔ እና የፖለቲካ ማዕከል የሆነዉ የኢትዮጵያ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እድሳት ተጠናቅቆ ለጉብኝት ክፍት ሆኗል
30/12/2024

የታሪክ የቅርስ የስልጣኔ እና የፖለቲካ ማዕከል የሆነዉ የኢትዮጵያ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እድሳት ተጠናቅቆ ለጉብኝት ክፍት ሆኗል

አዲስ ተቋም ሌላ ስራአዲስ ኃላፊነት ብዙ የሰራሁበት ፣ በብዙም የተሰራሁበት ፣ አያሌ ያተረፍኩበት ፣ በተቻለኝ መጠን በታማኝነትም ያገለገልኩበት የደቡብ ሬዲዮና ቴለቪዥን ድርጅት አመራሮች እና...
17/12/2024

አዲስ ተቋም
ሌላ ስራ
አዲስ ኃላፊነት

ብዙ የሰራሁበት ፣ በብዙም የተሰራሁበት ፣ አያሌ ያተረፍኩበት ፣ በተቻለኝ መጠን በታማኝነትም ያገለገልኩበት የደቡብ ሬዲዮና ቴለቪዥን ድርጅት አመራሮች እና ባልደርቦቼ አብረን ያሳለፍነው መልካም ጊዜና በትጋት ያከናወንናቸዉ ስራዎቻችን ፣ ያጎበዙን ፈተናዎች ትናንትን ማያ ትዝታዬና ኩራቴም ናቸው።
ብርታቴ የነበራችሁ ሁሉ አመሰግናለሁ!
በእርሱ ጊዜ ስለሆነዉ አዲስ ነገር እግዚአብሔር ይመስገን!

ታህሳስ 08-04-2017
አዲስ አበባ: ኢትዮጵያ

በብዙ ጉዳይ ላይ ከብዙ ግለሰቦች ጋር ቃለምልልስ አድርጌያለሁ።አብዛኞቹን አልረሳቸውም።ከብዙ አመታት በኋላ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ አገናኘን።▯▹አስታወስከኝ ዶክተር...
19/11/2024

በብዙ ጉዳይ ላይ ከብዙ ግለሰቦች ጋር ቃለምልልስ አድርጌያለሁ።
አብዛኞቹን አልረሳቸውም።

ከብዙ አመታት በኋላ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ አገናኘን።

▯▹አስታወስከኝ ዶክተር?
ዉይ ልጄ የት ነበር የምንተዋወቀው? ማን ነበር ስምህ?
▯▹ሄኖክ እባላለሁ። በርግጥ ረጅም ጊዜ ሆኖታል ቢሾፍቱ (ደብረዘይት) አንተ አሰልጣኝ ሆነህ እኔ ደግሞ ሰልጣኝ ሆኜ ተገናኝተን የሬዲዮ እንግዳ አድርጌህ ስለ ጋዜጠኝነት(በተለይ ስለ Investigative journalism) ብዙ አዉግተን ነበር።

የደቡብ ሬዲዮው ልጅ? በጣም ትልቅ ሰዉ ሆነሃልኮ! በጣም ነው የማስታዉሰዉ ግን ረጅም ጊዜ ሆኖታል እንዴት ነህ?
ደግመን ተጨባበጥን ተቃቀፍን
ብዙ ነገር ተጠያየቅን
ግለ ታሪክ ላይ ያተኮረ መጽሐፍ እያዘጋጀ እንደሆነም አጫወተኝ።
ላነበዉ እንደምጓጓ ነግሬው ተለያየን

በኢትዮጵያ ዉስጥ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጀማሪ ነው ዶክተር ንጉሴ ተፈራ።
ባሰራዉ የምርመራ ዘገባ ምክንያት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃ/ማሪያም ቤተመንግሥት አስጠርቶ ፊት ለፊት አናግሮታል።
◌አንተ ነህ ንጉሴ ማለት?
አዎን ክቡርነትዎ
◌የምታቀርባቸዉ ፕሮግራሞች አያመልጡኝም። የትናንቱን ዘገባ የሰራዉን የጋዜጠኞች ቡድን አንተ እንዳሰማራሄዉ ስምቻለሁ።
ዘገባው ትክክል ከሆነ ጥሩ
ዘገባው የተሳሳተ ከሆነ ግን ቤተሰብ ካለህ ተሰናበት ይሄው ስልክ ከፈለግክ አሉት
ዶክተር ንጉሴን ኃይለኛ ድንጋጤ ወረራቸዉ
አይኔ ከኮሎኔል መንግሥቱ ጠረጴዛ ላይ ባለው ሽጉጥ አረፈ ፍርሃቴ ሰማይ ነካ
ደግሞ በዚያው ጭንቀት መሃል ቀና ስል ከግድግዳው ላይ የቅድስት ማሪያም ምስል ተሰቅሎ አየሁ። ልቤም ትንሽ ተረጋጋ። በቃ ኃይማኖተኛ ከሆኑ አይገድሉኝም ብዬ ተጽናናሁ።
በወቅቱ የደርግ መንግስት ባለስልጣናት በአፋር ዉስጥ የሰፈራ ፕሮግራም በተሳካ ሁኔታ ተፈፅሟል ብለዉ የሰጡት መግለጫን የኢትዮጵያ ሬዲዮ የምርመራ ዘገባ ቡድን ለሰፈራ በተዘጋጀው ስፍራ እንደተባለዉ ሰዉ አለመስፈሩንና መግለጫዉ የተሳሳተ መሆኑን ማጋለጡን ተከትሎ ነው ኮሎኔሉ ያስጠሩት
ኮሎኔል መንግስቱ አንድ ሀሳብ አመጡ። ◌መግለጫውንና ዘገባውን የሚያጣራ ገለልተኛ ቡድን ወደ ስፍራው እንልካለን
እንዳሉትም በአስቸኳይ ከመንግሥትም ከጋዜጠኞችም የተውጣጣ ቡድን ወደ አፋር ተላከ
መሬት ላይ የነበረው እዉነትም የመግለጫውን ሳይሆን የዘገባውን ትክክለኛነት አረጋገጠ
ጋዜጠኝነትም አሸነፈ
የምርመራ ዘገባውን ተከትሎም ኮሎኔሉ የተሳሳተ መግለጫ ያቀረቡ ባለስልጣናትን አባረረ

ዶክተር ንጉሴ በጋዜጠኝነት ሙያ ለሀገር ያበረከተው አስተዋጽኦ ብዙ ነው።
አምባገነን በሆነ ስርዓት ዉስጥ መንግስትን ሞግቷል። የማህበረሰብን ህይወት አደጋ ላይ በሚጥሉ ድብቅ ስራዎች ላይ ተሰማርተው የነበሩ የዉጭ ካምፓኒዎች ፍቃዳቸው እንዲሰረዝ ምክንያት የሆኑ ዘገባዎችን ሰርቷል።
ያኔ በቃለመጠይቁ ጊዜ ዶክተር ንጉሴ ይህን እውነት በተረከልኝ ወቅት ተገርሜያለሁ።

ከአንድ አመት በፊት እያዘጋጀሁት ነዉ ያለኝ አያሌ የጋዜጠኝነት አለም ልምዶችን የያዘዉ "ዞር ብዬ ሳየዉ" የዶክተር ንጉሴ ተፈራ በቅርቡ ለንባብ እንደሚቀርብ ስሰማ እጅግ ደስ ብሎኛል።
በሚዲያ እና በኮሚኒኬሽን ዘርፍ ዉጤታማ መሆን ለሚሻ ሰው ልዩ ተሞክሮ የሚገኝበት እንዲሆነ አምናለሁ።

ዶክተር #ንጉሴተፈራ እንኳን ደስ አለህ!

ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የምታበድረውን ገንዘብ፤ በድፍድፍ ነዳጅ ለማስከፈል የሚያስችል አማራጭ የያዘ ስምምነት በፓርላማ ጸደቀ ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ለምትበደረው 738.26 ሚሊዮን ዶላር፤ ወ...
05/11/2024

ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የምታበድረውን ገንዘብ፤ በድፍድፍ ነዳጅ ለማስከፈል የሚያስችል አማራጭ የያዘ ስምምነት በፓርላማ ጸደቀ

ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ለምትበደረው 738.26 ሚሊዮን ዶላር፤ ወደፊት የምትፈጽመውን ክፍያ በድፍድፍ ነዳጅ እንድትመልስ አማራጭ የሚሰጥ የብድር ስምምነት በፓርላማ ጸደቀ። በብድር ስምምነቱ የሚገኘው ገንዘብ፤ በደቡብ ሱዳን እና ኢትዮጵያ ድንበር ከምትገኘው ፓጋክ ከተማ በመነሳት እስከ ፓሎች ከተማ ድረስ ያለውን 220 ኪሎ ሜትር መንገድ ለመገንባት የሚያስችል ነው።

በሁለቱ ጎረቤት ሀገራት መካከል የተደረገው የብድር ስምምነት ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 26፤ 2017 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በቀረበበት ወቅት፤ ማብራሪያውን በንባብ ያሰሙት በፓርላማ የመንግስት ዋና ተጠሪው ዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌ ናቸው። ዶ/ር ተስፋዬ የብድር ስምምነቱ የሁለቱ ሀገራትን ፍላጎት መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለተግባራዊነቱም የተለያዩ የዝግጅት እና የትብብር ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ለምክር ቤቱ አባላት ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ብድር የምትሰጥበት የስምምነት ሰነድ በዛሬው ዕለት ለፓርላማ ይቀርብ እንጂ፤ ሁለቱ ሀገራት ስምምነቱን የተፈራረሙት በግንቦት 2015 ዓ.ም ነበር። የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዳት በተገኙበት በጁባ ከተማ በተካሄደው የፊርማ ስነ ስርዓት ላይ፤ ኢትዮጵያን በመወከል ፊርማቸውን ያኖሩት የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታው ዶ/ር እዮብ ነበሩ።

ደቡብ ሱዳን በብድር የምታገኘው ገንዘብ፤ በጋምቤላ በኩል ካለው የኢትዮጵያ ድንበር በመነሳት በነዳጅ ሀብት ወደ በለጸገው ፓሎች አካባቢ የሚዘረጋውን መንገድ ወደ አስፋልት ለማሳደግ የሚውል ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ የሲቪል እና የአማካሪ ስራዎች የሚከናወኑት በኢትዮጵያውያን ኮንትራክተሮች እንደሆነ በስምምነቱ ላይ ተጠቅሷል።

በኢትዮጵያ በኩል የመንገድ ፕሮጀክቱ የሚመራው በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ነው። የደቡብ ሱዳን መንገዶች ባለስልጣን በደቡብ ሱዳን በኩል ተመሳሳይ ኃላፊነት እንደሚወስድ በስምምነቱ ላይ ሰፍሯል። ለፕሮጀከቱ ማስፈጸሚያ ይውል ዘንድ ከኢትዮጵያ መንግስት የሚሰጠው የ738.26 ሚሊዮን ዶላር ብድር፤ በውጪ ምንዛሬ ከሚፈለጉት የውጪ ስራዎች በስተቀር በብር የሚከፈል እንደሆነ ዶ/ር ተስፋዬ በዛሬው የፓርላማ ስብሰባ ላይ አስረድተዋል።

via

ዜና ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የምታበድረውን ገንዘብ፤ በድፍድፍ ነዳጅ ለማስከፈል የሚያስችል አማራጭ የያዘ ስምምነት በፓርላማ ጸደቀ November 5, 2024 FacebookTwitterTelegramWhatsAppEmailCopy URL በቤርሳቤህ ገ...

በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ ቀበሌያት በሚገኙ የሶዶ ጉራጌ ተወላጆች ላይ ባነጣጠረ የ''ሸኔ'' ጥቃት እስከ 40 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ።ጥቃቱ የደረሰው በክልሉ የምስራቅ ሸዋ ዞን ከማዕከላዊ ኢትዮ...
01/11/2024

በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ ቀበሌያት በሚገኙ የሶዶ ጉራጌ ተወላጆች ላይ ባነጣጠረ የ''ሸኔ'' ጥቃት እስከ 40 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ።

ጥቃቱ የደረሰው በክልሉ የምስራቅ ሸዋ ዞን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ጋር በሚዋሰንባቸው የዱግዳ ቦራ ወረዳ ቀበሌያት ነው።

በዚህም በዱግዳ ቦራ ወረዳ ቢርቢርሳና ጋሌ ተብለው በሚጠሩ ቀበሌያት ልዩ ስማቸው ደረባ፣ ኩሬ እንዲሁም ቢጢሲ ተብለው በሚታወቁ ስፍራዎች አሰቃቂ ጥቃት መድረሱ ተነግሯል።

በተለምዶ ''ሸኔ'' ተብሎ በሚጠራው ቡድን ታጣቂዎች አማካይነት እንደደረሰ በተገለፀው ጥቃት እስከ 40 ሰዎች መገደላቸውንና ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መኖራቸውን ከስፍራው የደረሱን ተደጋጋሚ መረጃዎች አመላክተዋል።

ጥቃቱ ትላንት ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ገደማ ጀምሮ እስከ እኩለ ለሊት መራዘሙን የጠቆሙት የአካባቢው ነዋሪዎችና የሟቾች ቤተሰቦች በጥቃቱ ሕጻናትን ጨምሮ እናቶችና አረጋውያን መገደላቸውንም ተናግረዋል።

የተከፈተባቸውን ጥቃት መመከት ያልቻሉ አርሶ-አደሮች ቤታቸው ውስጥ እያሉ በእሳት እንዲቃጠሉ በማድረግ ከነከብቶቻቸው እንዲሞቱ መደረጉንም ነዋሪዎች ገልፀዋል።

በአካባቢው የመንግሥት መዋቅሮች በኩል እስካሁን ስለጉዳዩ ግልፅ መረጃም ሆነ ድርጊቱን የሚያወግዝ መግለጫ አልተሰጠም። እንዲህ በሕዝብ ለዛውም በንፁሐን ላይ የሚደርስን ተደጋጋሚ በደልና የሞት ዜናን በዝምታ ማለፍ ፍፁም ተቀባይነት የለውም፤ ዋጋ ያስከፍላል!

ስለምንም ነገር ሕዝብ በጊዜው መረጃ ሊሰጠው ይገባል። መደበቅም ስለማይቻል። የየመዋቅሮቹ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤቶች አንዱ የሥራ ጠባይ መገለጫ ይህ ነበር። ''መንግሥት ማለት ሕዝብ ነው'' ስለሚል ሳይንሱ! ነገር ግን ከነርሱ ይህንን መጠበቅ ከባድ ሆኗል። ቢያንስ ግን የፀጥታ አስተዳደር አካል በዚህ ልክ ከፍ ያለ አደጋና ቀውስ ሲከሰት ስለጉዳዩ ጥቂት ነገር ሊል ይገባል።

**o lema

ስፔን ሀዘን ላይ ነችበስፔን ቫለንሺያ በተከሰተ ከባድ ጎርፍ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 150 መድረሱን sky news ዘግቧል
01/11/2024

ስፔን ሀዘን ላይ ነች

በስፔን ቫለንሺያ በተከሰተ ከባድ ጎርፍ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 150 መድረሱን sky news ዘግቧል

በባሕር በር ጉዳይ ወደ ኋላ የማይል ይፋዊ አቋም አለን‼️ኢትዮጵያ ሰላማዊ በሆነ መንገድ በቀይ ባህር ላይ የባህር በር ያስፈልጋታል፡፡ በዚህ ጉዳይ ወደ ኋላ የማይል ይፋዊ አቋም አለን፡፡ ነገ...
31/10/2024

በባሕር በር ጉዳይ ወደ ኋላ የማይል ይፋዊ አቋም አለን‼️
ኢትዮጵያ ሰላማዊ በሆነ መንገድ በቀይ ባህር ላይ የባህር በር ያስፈልጋታል፡፡ በዚህ ጉዳይ ወደ ኋላ የማይል ይፋዊ አቋም አለን፡፡ ነገር ግን ይህን ለማሳካት ጦርነትም ሆነ የኃይል አማራጭ አንፈልግም፡፡ ፍላጎታችንን ማሳካት የምንሻው በሰላማዊ አማራጭ ነው፡፡ ይህ ምክንያታዊና ፍትሃዊ ጥያቄ ነው፤ እኛ ባናሳካው ልጆቻችን ያሳኩታል፡፡ ኢትዮጵያ የትኛውንም ሀገር ላይ ወረራም ሆነ ጥቃት አትፈጽምም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያን ለመንካት የሚሞክሩ ካሉ አሳፍረን እንመልሳለን፡፡ ይህን ማድረግ የሚያስችል በቂ አቅም አለን፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አሕመድ (Dr.) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ከሰጡት ማብራሪያ

Happy follow-versary to my awesome followers. Thanks for all your support! Des Thomas
23/10/2024

Happy follow-versary to my awesome followers. Thanks for all your support! Des Thomas

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Chere G Yohannes, Endush Girma Gurara, Endale Debela Hago...
23/10/2024

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Chere G Yohannes, Endush Girma Gurara, Endale Debela Hagos, Dil Sari, Melaku Adal, Melaku Admasu, Getaneh Dametew, Tekabe Genene, Argaw Ayele

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Henok Abera Mamo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Henok Abera Mamo:

Share