የአሳንሰር ጨዋታ - Discover Ethiopia

የአሳንሰር ጨዋታ - Discover Ethiopia የታሪክ እና የባህል እንዲሁም ልዩ ልዩ አዝናኝ እና ትኩስ መረጃዎች የምንጋራበት ገፅ ነው፡፡

አሳንሰር የአማርኛ ቃል ሲሆን በእንግሊዘኛው ሊፍት /ኢሊቤተር/ ማለት ነው፡፡ ኢትዮጵያ በየዘርፉ እምቅ ሀብት አላት፡፡ ስለዚህ በዚህ ገፅም በተለይ ስለ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን መረጃዎችን እንለዋወጣለን…. (Talk about Ethiopia & Ethiopians) Ethiopia is A Land of Great Civilization, A Land of Hospitality............

በአረርቲ ከተማ ለሕንፃ ግንባታ የተረበረበ እንጨት በመደርመሱ የ22 ሰዎች ሕይወት አለፈ ******* *******በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ከተማ አስተዳ...
01/10/2025

በአረርቲ ከተማ ለሕንፃ ግንባታ የተረበረበ እንጨት በመደርመሱ የ22 ሰዎች ሕይወት አለፈ

******* *******
በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ከተማ አስተዳደር አረርቲ ማርያም ቤተክርስቲያን ዓመታዊ ክብረ በዓል እየተከበረ ነበር።

በዓሉን አስመልክቶም ከጠዋቱ 1:45 ላይ እየተሰራ ያለው ቤተክርስቲያን እየተጎበኘ ባለበት ‎ሰዓት ለፊኒሺንግ ሥራ የተረበረበው እንጨት ተደርምሶ በርካታ ምዕመናን ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት ደርሷል።

የአረርቲ ከተማ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ አጥናፉ አባተ ለኢቢሲ እንደገለፁት፤ በአካባቢው በየዓመቱ በድምቀት የሚከበረው የድንግል ማሪያም በዓልን አስመልክቶ በርካታ ምዕመናን በአካባቢው ይመጣሉ።

ዛሬ ከማለዳው 2:00 ላይ በቤተክርስቲያኑ ግንባታ የሕንፃ መወጣጫ የእንጨት ርብራብ መናድ አደጋ በርካቶች መጎዳታቸውን አንስትዋል።

የጉዳቱ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ እና ከእንጨት ርብራቡ ሥር ያልወጡ ሠዎች በመኖራቸው የጉዳት መጠኑን መገመት አስቸጋሪ ነው ያሉት ኃላፊው፤ እስከአሁን የ22 ሠዎች ሕይወታቸው ማለፉ በሆስፒታል ተረጋግጧል ሲሉ አስታውቀዋል።

በተጨማሪ 55 ሰዎች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱንም ገልጸዋል። ለተጎጂዎች የመጀመሪያ ሕክምና በአንድ ሆስፒታል እና በ4 ጤና ጣቢያዎች እየተሠጠ ነው ብለዋል።

ተጎጂዎችን ለማትረፍ ኅብረተሠቡ ጥረት ማድረጉን ያነሱት ኃላፊው፤ ከርብራቡ ሥር ያልወጡትን ዜጎችም ሕይወት ለማትረፍ እና ሕክምና እንዲያገኙ ለማድረግ እየሠራን ነው ብለዋል።

የአረርቲ ሆስፒታል ኃላፊ ተወካይ አቶ ስዩም አልታዬ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ወደ አረርቲ ሆስፒታል የመጡ ተጎጂዎችን ሕክምና እየሠጠን ነው ሲሉ ለኢቢሲ የተናገሩት፤ ጉዳቱ ከፍተኛ በመሆኑ ተጨማሪ ድጋፍ ከወረዳ ባለሙያዎች እና አምቡላንሶችን በማነቀናጀት እየሠራን ነው ብለዋል።

ከፍተኛ ጉዳት የደረሠባቸው 5 ተጎጂዎች ለተጨማሪ ሕክምና ወደ አዲስ አበባ መላካቸውን አስታውቀዋል።

ምንጭ :- ኢቢሲ

ከታደለችው ሀብት ፍሬ መቋደስ የጀመረችው ኢትዮጵያ ********************* ኢትዮጵያ በጣም ዝቅተኛ ከሆነው ዳናኪል ሸለቆ አስከ ባሌ እና ሰሜን ተራሮች ያሉ ከፍታዎች፣ ከላሊበላ እስ...
27/09/2025

ከታደለችው ሀብት ፍሬ መቋደስ የጀመረችው ኢትዮጵያ
*********************

ኢትዮጵያ በጣም ዝቅተኛ ከሆነው ዳናኪል ሸለቆ አስከ ባሌ እና ሰሜን ተራሮች ያሉ ከፍታዎች፣ ከላሊበላ እስከ አክሱም ያሉ የቀደምት ኢትዮጵያውያን ጥበብ መገለጫዎች፣ ምሥጢራዊዎቹ የጢያ ትክል ድንጋዮች ያሉ ልዩ የተፈጥሮ፣ የባህል እና ታሪካዊ ቦታዎችን የታደለች የውበት ባለፀጋ ናት።

ኢትዮጵያ 12 የሚዳሰሱ እና 7 የማይዳሰሱ ቅርሶችን በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት ያስመዘገበች ሲሆን፣ ይህ ቁጥር ቅርሶችን በዓለም ቅርስነት በማስመዝገብ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሀገራት አንዷ ያደርጋታል።

ይህን ሁሉ ሀብት የያዘችው ኢትዮጵያ ግን ሀብቷን ለብልጽግናዋ ሳትጠቀም ቆይታለች። ካለፉት ሰባት ዓመታት ወዲህ ግን ይህ አካሄድ ተለውጦ የቱሪዝም ዘርፉ ከኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ምሰሶዎች አንዱ ሆኖ እየተሠራበት ነው።

መረጃዎች እንደሚያመላክቱት በፈንጆቹ 2023/24 ኢትዮጵያ 1.48 ሚሊዮን ቱሪስቶችን አስተናግዳ 4.3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ያገኘች ሲሆን፣ ይህ ገቢ ከዚያ በፊት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛው ሆኖ ተመዝግቧል።

ይህ ዕድገት የመጣው መንግሥት ቱሪዝምን አንዱ የኢኮኖሚ ምሰሶ አድርጎ ከመውሰዱም በላይ በሠራቸው ተጨባጭ ሥራዎች ነው።

በገበታ ለሸገር የተሠሩ እንደ አንድነት ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ ያሉ እንዲሁም በገበታ ለሀገር የተሠሩ እንደ ወንጪ ኢኮ ቱሪዝም ሎጅ፣ ጎርጎራ እና ጨበራ ጩርጩራ የኢኮ ቱሪዝም ሎጆች የተሠሩ ሥራዎች ለመንግሥት ቁርጠኝነት ማሳያዎች ናቸው።

የአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድ በሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ የተሠሩ ማስፋፊዎችም የዘርፉን ከፍታ ለመጨመር ወሳኝ ሲሆን፣ አየር መንገዱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ዓለም አቀፍ ተጓዦችን ቆይታ በማራዘም የኢኮኖሚውም የገጽታ ግንባታውም ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል።

የተለወጠችው እና ለበርካታ ዓለም አቀፍ እና የአፍሪካ ስብሰባዎች ተመራጭ እየሆነች የመጣችው አዲስ አበባ ባለፈው ዓመት ብቻ ያስተናገደቻቸው ታላላቅ ኮንፈረንሶችም ለዘርፉ እያበበ መሔድ ትልቁን አስተዋፅኦ አድርጓል።

ባለፈው ዓመት ብቻ ከረሃብ ነፃ ዓለም ኮንፈረንስ፣ ለልማት የገንዘብ ድጋፍ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ፣ የአፍሪካ የሰላም ኮንፈረንስ፣ ስድስተኛው የአፍሪካ ብልጽግና ኮንፈረንስ፣ 46ኛው የካፍ መደበኛ ጉባኤ፣ የአፍሪካ መከላከያ ሚኒስትሮች ኮንፈረንስ፣ ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ጉበኤን ጨምሮ ከ150 በላይ ኮንፈረንሶች በአዲስ አበባ ተካሄደዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለፓርላማ ባቀረቡት ዓመታዊ ሪፖርት ላይ እንደጠቀሱት በእነዚህ ከ150 ሺህ በላይ ኮንፈረንሶች ለመሳተፍ ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል።

በዓመቱ ከውጭ ቱሪስቶች በተጨማሪም 1.5 ሚሊዮን የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች እንደ አንድነት ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ የወዳጅነት ፓርክ እና ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ያሉ የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎችን በመጎብኘታቸው ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ እንደተገኘ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) አክለዋል።

እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ከ13 ሚሊዮን በላይ ሰዎች እነዚህ እነዚህን አካባቢዎች የጎበኙ ሲሆን፣ ይህም ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥም ሆነ ዓለም አቀፍ ቱሪዝም ስበት ማዕከል መሆኑን ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ዲያቆን፣ ዶክተር እና  ፓይለት ...."ከትንሽነቴ ጀምሮ ሶስቱንም መሆን እመኝ ነበር፤ ዲያቆን፣ ዶክተር እና ፓይለት። ከትምህር ጊዜዬ ውጪ ውሎዬ እዛው ስለሆነ፣ የፈረንሳይ ለጋሲዮን ገነተ ኢ...
04/09/2025

ዲያቆን፣ ዶክተር እና ፓይለት ....

"ከትንሽነቴ ጀምሮ ሶስቱንም መሆን እመኝ ነበር፤ ዲያቆን፣ ዶክተር እና ፓይለት። ከትምህር ጊዜዬ ውጪ ውሎዬ እዛው ስለሆነ፣ የፈረንሳይ ለጋሲዮን ገነተ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ዲያቆን ሆንኩ። እናቴ ጤና ጣቢያ ነው የምትሰራው፤ እዚያ ሥራ ቦታዋ ይዛኝ ትሄድ ነበር። ሐኪሞቹን እያየሁ እነሱን መሆን ተመኘሁ። አባቴ ደግሞ ሁሌም የአየር መንገድን ሠላምታ መፅሔት ይዞ ይመጣል። እሱን እያየሁ፤ እያነበብኩ፣ ፓይለት መሆን ተመኘሁ። ፓይለት ሆንኩ፦ አሁን ረዳት አብራሪ ነኝ።...."
---------------------------------------//---------
ይህ ወጣት ናትናኤል ስንታየሁ ይባላል። ዲያቆን፣ ዶክተር፣ ፓይለት ናትናኤል።

ተወልዶ ያደገው ፈረንሳይ ለጋሲዮን ነው። ዲያቆን ነው። ዶክተር ነው፤ የዓይን ሐኪም። ጎንደር ዩኒቨርስቲ እያከመ ያስተምር ነበር፦ ለሁለት ዓመት። ...ከዚያ ወደ አዲስ አበባ መጣ፤ በአውሮፕላን አብራሪነት ተመረቀ። አሁን ረዳት ፓይለት ነው።

via ወሰን ሰገድ ገ/ኪዳን

አንጋፋዋ ጋዜጠኛና ደራሲ የምወድሽ በቀለ ከእዚህ ዓለም በሞት ተለየችየብዙ አቅመ ደካሞች ጧሪ እና ደጋፊ የነበረችው ደራሲና ጋዜጠኛ የምወድሽ በቀለ ለአጭር ጊዜ ባጋጠማት ሕመም በሕክምና ስትረ...
30/08/2025

አንጋፋዋ ጋዜጠኛና ደራሲ የምወድሽ በቀለ ከእዚህ ዓለም በሞት ተለየች

የብዙ አቅመ ደካሞች ጧሪ እና ደጋፊ የነበረችው ደራሲና ጋዜጠኛ የምወድሽ በቀለ ለአጭር ጊዜ ባጋጠማት ሕመም በሕክምና ስትረዳ ቆይታ ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ሌሊት አርፋለች።

የምወድሽ በቀለ የፖሊስና እርምጃው ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆና ረጅም ዓመታት አገልግላለች።

በድርሰትና በስነ ግጥም ስራዎቿም በርካታ አበርክቶዎች የነበሯት ነበረች። በ1979 ዓ.ም አብዮታዊ ግጥሞች ከሚለው ስራዋ ጀምሮ ወደ 16 መፃሕፍትን አሳትማለች።

የኢትዮጵያ ሴት ደራሲያት ማሕበርን በፕሬዘደንትነት ዘለግ ላሉ አመታት የመራች ሲሆን የኢትዮጵያ ሴቶች ማሕበራት የቦርድ ሰብሳሰቢ ሆና አገልግላለች።

ሴቶች ይችላሉ Women can do it የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ነበረች።

እጅግ በርካታ የበጎ ስራ ማሕበራት ውስጥ መስራችና አመራር ሆና ስታገለግል ኖራለች።

በሴቶች፣ በሕፃናት እና ማሕበረሰብ አቀፍ የበጎ ስራዎች ላይ ከፊት ተሰልፋ ሙሉ ጊዜዋን ስትሰራ ቆይታለች።

በአሐዱ ሬዲዮ ላይ ከምወድሽ ገፆች የተሰኘ በሴቶች ላይ ያተኮረ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ ነበረች።

በአሻም ቴሌቪዥን የሚተላለፍም የምወድሽ ገፃች አዘጋጅ የነበረችው የምወድሽ በሕይወት ዘመኗ በርካታ ሽልማቶችንም ባበረከተቻቸው አስተዋፅኦዎች አግኝታለች። የ2016 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማትን ጨምሮ ሌሎችንም አግኝታለች።

ነሐሴ 19 ቀን 1951 ዓ.ም አዲስ አበባ የተወለደችው የምወድሽ በቀለ የአራት ልጆች እናትና የ5 የልጅ ልጆች አያት ነበረች።

የተወዳጁ ተዋናይ መኮንን ላእከ ወላጅ እናት....
30/08/2025

የተወዳጁ ተዋናይ መኮንን ላእከ ወላጅ እናት....

14 ነርሶች በአንድ ጊዜ ነፍሰ ጡር ሆኑ‼️በአሜሪካ ሚዙሪ ግዛት በሚገኘው የቅዱስ ሉቃስ ምስራቅ ሆስፒታል ውስጥ 14 ነርሶች በተመሳሳይ ጊዜ ነፍሰ ጡር መሆናቸው ታውቋል።እነዚህ ነርሶች የህፃ...
29/08/2025

14 ነርሶች በአንድ ጊዜ ነፍሰ ጡር ሆኑ‼️

በአሜሪካ ሚዙሪ ግዛት በሚገኘው የቅዱስ ሉቃስ ምስራቅ ሆስፒታል ውስጥ 14 ነርሶች በተመሳሳይ ጊዜ ነፍሰ ጡር መሆናቸው ታውቋል።እነዚህ ነርሶች የህፃናት ማዋለጃ እና አራስ ህፃናት ክፍል ሰራተኞች ናቸው ተብሏል።

ሆስፒታሉ የነርሶቹን የቡድን ፎቶ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲያጋራ፣ ዜናው በፍጥነት በመሰራጨት ትልቅ ሽፋን አግኝቷል።

ይህ ክስተት ነርሶቹ በራሳቸው የህይወት ጉዞ ላይ እያሉ ለሌሎች እናቶች አገልግሎት የሚሰጡ መሆናቸውን ያሳያል።

የሥራ ባልደረቦቻቸው በወሊድ ጊዜ ሊያዟቸው መቻላቸው ለእነሱም ታላቅ ደስታና መተማመኛ ሆኗል ነው የተባለው።

https://t.me/c/2080617038/1064

የቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገት መታሰቢያ በዓል  በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በአንጎለላ ጽርሐ አርያም ሰሚነሽ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን  በርካታ ምእመናን በተገኙበት በድምቀት ተ...
22/08/2025

የቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገት መታሰቢያ በዓል በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በአንጎለላ ጽርሐ አርያም ሰሚነሽ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በርካታ ምእመናን በተገኙበት በድምቀት ተከበረ።

በስኬቶች የደመቀችው ተመራቂ 🎓ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎቹን አስመርቋል።   ከሕክምና ትምህርት ቤት የማዕረህ ተመራቂዎች አንዷ ስትሆን በርካታ አስገራሚ ስኬቶች...
26/07/2025

በስኬቶች የደመቀችው ተመራቂ 🎓

ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎቹን አስመርቋል።

ከሕክምና ትምህርት ቤት የማዕረህ ተመራቂዎች አንዷ ስትሆን በርካታ አስገራሚ ስኬቶችን ተጎናፅፋለች።

🏅የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ - CGPA 3.95

🏆 የፕ/ር ዕደማሪያም ፀጋ አካዳሚክ ልህቀት በሕክምና ተሸላሚ

👩‍🎓 ከ2017 ሴት ተመራቂዎች ሰቃይ

🥇 ምርጥ ኢንተር – ከቀዶ ህክምና ትምህርት ክፍል

🥇 ምርጥ ኢንተር – ከህጻናት ህክምና ትምህርት ክፍል

Via

24/07/2025

በአ.አ የጣለው ከባድ ዝናብ እና....

በአፋር ክልል አፍዴራ ወረዳ ትናንት በነበረ ዝናብ አዘል ከባድ ነፋስ የሰው ህይወት ጠፍቷል ፤ በንብረት ላይም ከባድ ጉዳት መድረሱን የአፋር ክልል አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ገልጿል።በአደጋ...
16/07/2025

በአፋር ክልል አፍዴራ ወረዳ ትናንት በነበረ ዝናብ አዘል ከባድ ነፋስ የሰው ህይወት ጠፍቷል ፤ በንብረት ላይም ከባድ ጉዳት መድረሱን የአፋር ክልል አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

በአደጋው የ1 ሰው ሕይወት አልፏል።በተጨማሪም በ32 ሰዎች ላይ ከባድ ፤ በ22 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መደረሱ ተመላክቷል።

አደጋው በ3 ባንኮች፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮ ቴሌኮም መሠረተ ልማቶች እንዲሁም በ5 የጨው ፋብካዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

ትምህት ቤቶች እና ጤና ጣቢያዎችን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማት በአደጋው ተጎድተዋል።

በዚህ ዝናብ በቀላቀለ ከባድ ነፋስ በከተማው ጉዳት ያልደረሰበት አንድም ቤት የለም ተብሏል።

ባለትዳሮችን እስከ ማፋታት የደረሰው የማንኮራፍት መዘዝ ….።ማንኮራፋት/Snoring/ በእንቅልፍ ወቅት በአፍ እና በአፍንጫ ውስጥ ያለው የአየር ፍሰት በከፊል ሲዘጋ ይከሰታል፡፡ ይህም በጉሮሮ...
11/07/2025

ባለትዳሮችን እስከ ማፋታት የደረሰው የማንኮራፍት መዘዝ ….።

ማንኮራፋት/Snoring/ በእንቅልፍ ወቅት በአፍ እና በአፍንጫ ውስጥ ያለው የአየር ፍሰት በከፊል ሲዘጋ ይከሰታል፡፡ ይህም በጉሮሮ ውስጥ ያሉት ሕብረ ሕዋሳት እንዲርገበገቡ እና ከፍተኛ ድምፅ እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡

ከፍተኛ ድምጽ ያለው ማንኮራፋት ኦብስትራክቲቭ ስሊፕ አፕኒያ ከሚባል የጤና ችግር ጋር ይያያዛል። ይህ የጤና ችግር የጉሮሮ ክፍል ግድግዳዎች እንዲፍታታ እና እንዲጠብ በማድረግ የተለመደ የመተንፈስ ሥርዓትን በማስተጓጎል የኦክስጅን እጥረት እንዲከሰት ያደርጋል።

ኦብስትራክቲቭ ስሊፕ አፕኒያ የልብ የሥራ ማቆም ዕድልን በ140 ፐርሰንት ፣ በስትሮክ የመመታት ዕድልን 60 በመቶ እንዲሁም ለልብ ህመም የመጋለጥ ዕድልን 30 በመቶ እንደሚጨምር ጥናቶች ያመለክታሉ። በትዳር ውስጥ ያሉ ጥንዶችም በማንኮራፋት ምክንያት ክፍል ለይተው እስከመተኛት/መፋታት ሊደርሱ ይችላሉ።

የባለሙያ የድምፅ ማብራሪያ እና ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ ከስር ያለውን ሊንከ ይጫኑ …
👇
https://t.me/yotor2127/986

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና እየወሰዱ የሚገኙት የ65 ዓመቷ እናትአዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአርሲ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል እየተሰጠ የሚገኘውን የ12ኛ ክፍል ማጠ...
11/07/2025

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና እየወሰዱ የሚገኙት የ65 ዓመቷ እናት

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአርሲ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል እየተሰጠ የሚገኘውን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና እየወሰዱ ከሚገኙ ተማሪዎች መካከል የ65 ዓመት ዕድሜ ባለጸጋዋ ወ/ሮ ታሪኳ አያሌው ይገኙበታል።

በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ የተወለዱት ወ/ሮ ታሪኳ ዕድሜ ሳይገድባቸው ተምረው ዛሬ ለ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ተቀምጠዋል።

ጠንክሮ መስራት ከተቻለ ከፈለጉት ግብ መድረስ ይቻላል የሚሉት ወ/ሮ ታሪኳ፤ በአግባቡ ተምረው እና ዝግጅት አድርገው ፈተና እየወሰዱ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ትምህርትም በዕድሜ ሊገደብ እንደማይገባ በመናገርም፤ ሁሉም ሰው ባገኘው አጋጣሚ ትምህርት ላይ ትኩረት ማድረግ አለበት ብለዋል፡፡

በትምህርት ቆይታቸው የአካባቢው ማህበረሰብ ጥረታቸውን በማድነቅ ሞራል ይሰጣቸው እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡
ምንጭ ፡- FBC

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአሳንሰር ጨዋታ - Discover Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የአሳንሰር ጨዋታ - Discover Ethiopia:

Share