Ye-Fiker Abogida

Ye-Fiker Abogida በዚህ ፔጅ ፍቅር ይሰበካል, ፍቅር ይዜማል, ፍቅር ይዘመራል ♡♡

ንጉሱ በካናዳ ሊሸለሙ ነው 🔥 ክብርት ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ቴዲ አፍሮ በሙዚቃ ዘርፍ ላበረከተው ታላቅ አስተዋፅኦ የእውቅና ሽልማት ሊበረከት ነው። መቀመጫውን በካናዳ ኦንታሪዮ ግዛ...
31/08/2024

ንጉሱ በካናዳ ሊሸለሙ ነው 🔥 ክብርት ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ቴዲ አፍሮ በሙዚቃ ዘርፍ ላበረከተው ታላቅ አስተዋፅኦ የእውቅና ሽልማት ሊበረከት ነው። መቀመጫውን በካናዳ ኦንታሪዮ ግዛት በቶሮንቶ ከተማ ያደረገው የቢቂላ ሽልማት በተለያዩ የስራ እና የሙያ ዘርፎች ውጤታማ እና ለህዝባችን ጠቃሚ ስራዎችን ላከናወኑ ኢትዮጵያውያን ሽልማት ዘንድሮ ለ10ኛ ጊዜ ልዩ ሽልማት እንደሚሰጥ አስታውቋል። ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያን። የቢቂላ ሽልማት የፊታችን መስከረም 21 ቀን 2024 አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በሙዚቃ ዘርፍ ላበረከተው አስተዋፅኦ በቶሮንቶ በሚካሄደው አመታዊ የሽልማት ስነስርዓት ላይ የእውቅና ሽልማት ሊሰጥ መሆኑ ተገለፀ። በቶሮንቶ የቢቂላ አዋርድ ፕሬዝዳንት አቶ ተሰማ ሙልጌታ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ጠንክሮ በመስራት ለኢትዮጵያውያን ወጣቶች አርአያነት ያለው ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል። አርቲስቱ አክለው የመድረክ ስራዎቹ እና የበጎ አድራጎት ዝግጅቶች ለትውልዱ አርአያ እንዳደረጉት ተናግሯል። በዘንድሮው የቢቂላ ሽልማት ቴዎድሮስ ካሳሁንን ጨምሮ 15 ሰዎች የተሸለሙ ሲሆን ከነዚህም መካከል በዋሽንግተን ዲሲ ግዙፍ የፓርኪንግ ስራ ላይ የተሰማሩት፣ የኡ ስትሪት ፓርኪንግ ባለቤት አቶ ሄኖክ ተስፋዬ፣ ኢትዮጵያዊቷ ካናዳዊ የሴቶች መብት ተሟጋች መሰረት ሀይለየሱስ፣ ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም እና ሌሎች በትምህርት፣ በጤና፣ በሳይንስ፣ በኪነጥበብ እና በሌሎችም ። በሙያ ዘርፍ ለአገራቸውና ለህዝባቸው ያበረከቱ ግለሰቦች ይሸለማሉ። ምንጭ፡- ዳንኤል ገብረማርያም

የፍቅር አቦጊዳ ይልሃል!!
06/06/2023

የፍቅር አቦጊዳ ይልሃል!!

"የፍቅር አደራ ጠባቂው"
~ቴዲ አፍሮ
(ያሬድ ሹመቴ)

ገና ከመከሰቱ ግዙፍ የሕዝብ ፍቅር በአደራ ተሰጠው!

ላለፉት 22 ዓመታት የተረከበውን ውድ አደራ ከነ ሙሉ ክብሩ ጠብቆ በመቆየት ዛሬም ድረስ በታማኝነት ያላቻ የሚኖር ብርቅ ሰው ነው።

"አቡጊዳ" ሲል የጀመረው የመታመን ጉዞ "ያስተሰርያል" በሚል የትውልድ መድብል ታሽጎ በ"ጥቁር ሰው" ጀርባ "ኢትዮጵያ!" ሲል ከያዘው መንገድ ሳይዛነፍ ለዓመታት በክብር ጸንቶ መቆሙን ያየ ሁሉ፤ በዚህ ልክ ግዙፍ አደራ መሸከም የሚችል አንድም ሰው ስለመኖሩ መጠራጠሩ አይቀርም።

ባማረ ቀለም የተዋቡ ውብ እርግቦችን ላባ ደሽድሸው ክንፋቸው ላይ የሰኩ ቁራዎች ለጥቂት ጊዜያትም ቢሆን ተውበው በመታየት ቀልባችንን ሰርቀው የአእዋፋትን ንግስና ብንሰጣቸው ገና ለመብረር ሲያስቡ የተውሶ ውበት [ላባቸው] ሲረግፍ አይተን አዝነናል።

በእነዚህ የዘመን ኪሳራ፣ የትውልድ ሀዘን ወቅቶች ውስጥ የምንጽናናበትን እሱን እና ጥቂት እሱን የሚመስሉ አርአያዎችንን እያሰብን "አልሆንልህ አለኝ እኔ.." በማለት ስናዜም፤ የዘመናችንን ባለ ብዙ መከራዋ ኢትዮጵያ "ትመጣለች!" በሚል ተስፋ ከመጽናናት በቀር ከብርቱው የመናጠል አዘቅት አውጥቶ መልካሙን ርዕይ የሚያሳየን ተስፋ አላገኘንም።

የኔ ትውልድ፦ ከጉርምስናው እስከ ጉልምስናው መንገዱን በተስፋ የዋጀለትን እሱን እና ሌሎች እጅግ ጥቂት አርአያዎች የሰጠውን ቸር አምላክ ሲያመሰግን ይኖራል።

በመጨረሻም፦
ህያው አምላክ እናታችንን ከተሰወረችበት ይልክልን ዘንድ በሱ ዜማ "ባክሽ ኢትዮጵያ ነይ ቶሎ" እያልን ዛሬም እንጮሀለን!

፨፨፨

ወር የቀረው ልደቱን ከወዲሁ በማሰብ ለወዳጄ፣ ለታላቅ ወንድሜ፣ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ፣ ድምጻዊ፣ የዜማና ግጥም ደራሲ፦ ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) መልካም ልደት! ስል ከወዲሁ ከልቤ እመኛለሁ።

በአንድ ወቅት ያልኩትን ዛሬም እደግመዋለሁ፦
"ቴዲን የምንወደው ኢትዮጵያን ስለምንወዳት ነው!"

Teddy Afro "የሕዝብ አደራ የመጠበቅ ተምሳሌት"
መልካም ልደት!!!

05/03/2023
Coming Soon Afro
24/11/2022

Coming Soon Afro

16/07/2022
እያመመው መጣ እያመመው
22/06/2022

እያመመው መጣ
እያመመው

ናዕት
(እያመመው ቁጥር ፪)
➖➖➖➖➖➖

ግርም ያለ ጊዜ ሆነ ሰዓቱ
በዳንኪራው ደምቆ በምቱ
ለደቂቃም አይቆይ በስልቱ
ቦግ እልም እያለ መብራቱ

ኡኡ…ሬጌ ናዕት
ሬጌ ናዕት

ብልጭልጭ ቢሆን ዳሱ

ኡኡ…ሬጌ ናዕት
ሬጌ ናዕት

ማን ሊታደም ከድግሱ

ኡኡ…..ሬጌ ናዕት
ሬጌ ናዕት

ብልጭልጭ ቢሆን ድንኳን

ኡኡ…. ሬጌ ናዕት
ሬጌ ናዕት

አይለውጥ ጎግ የእውነት መልኳን

ቢጋርድ ሐሳብ አርጎ ሜዳን ገደል
እም አእላፍ ስቃይ ጭንቀት ቢደረደር
የነፍስ ሕላዌ መሻት ዋዌው ሳይገባቸው
ስንቶች በዘር ተዘፍቀው ታዘብናቸው

ዘውግ ያወረው ድንብር ማ‘ላውን የረሳ
ሣር ያለመልማል ዛሬም በእልፍ አእላፍ ሬሳ
እያረረ ሆዴ ብስቅ በማሽላ ዘዴ
ና ታደም ይለኛል ደግሞ በነ ኡኡ ሬጌ

ኡኡ… ሬጌ ናዕት
ሬጌ ናዕት

ብልጭልጭ ቢሆን ዳሱ

ኡኡ…. ሬጌ ናዕት
ሬጌ ናዕት

ተላላ ዝንጉ ሰብ የሙታን ሸማ ደዋሪ
ምን አለ አይል ከፊት ሆኖ ቅርብ አዳሪ
ተናገር አፌ ደፍረህ ሳትናወጥ ከቶ
ዝም አይሆንም ሜዳ ተራራ ሞት መጥቶ

ከበሮ ግም ሲል በእምቢ ነጎድጓድ ምቱ
ይናዳል የዘር ድንዛዜ ያ ድዉይ ቤቱ
ገለል በል ዔሳው ነፍሴን አንቀህ አታሳሳት
ብታገስ ባሰ ባንተ የልቤ እሳት

እያመመው መጣ
እያመመው መጣ

ያዳፈነው እሳት ከሆዱ ሳይወጣ
ልቤ እንደካቻምናው እያመመው መጣ
የሚያዜም ይመስላል ሲያጣጥር ተጨንቆ
ውስጡን ሲሰብቅለት ኡ….እያለ መሰንቆ
ኡ….ኡ…..

እያመመው መጣ

የተረገጠ እውነት በጊዜ ውስጥ እግር
ታፍኖ የቆየ በኾታ ግርግር
ትንሽ ጋብ እንዳለ የጭብጨባው ጩኸት
እረጭ ሲል ውሸት ይናገራል እውነት

እያመመው መጣ

ቂምን ሻረውና ወይ ፍቅርን አንግሠው
ኹለት ሆኖ አያውቅም አንድ ነው አንድ ሰው
ከሀገርም ይሰፋል ያ! የፍቅር ገዳም
መጠሪያው ሰው እንጂ ዘር አይደለም አዳም

ዶፍ ዶፍ ቢዘንብ እሳት
ሀገሬን ላልረሳት
ቃል አለኝ ኖሬ ሞቼም ልክሳት

ዳር አለው እንዴ ድንበር
ዳር አለው እንዴ
ዳር አለው እንዴ ፍቅር
የዘር ሐይማኖት ድንበር
ዳር አለው እንዴ ፍቅር
በዚህ ለፀና እውነት
የፍቅር ሐገር ከጥንት
ዘብ ያድራል ሁሉም እስከ ሞት
ዶፍ ቢዘንብ እቶን እሳት
ዶፍ ዶፍ ቢዘንብ እሳት
አገሬን ላልረሳት
ቃል አለኝ ኖሬ ሞቼም ልክሳት

-----------------------------//----------------------

የቃላት ፍቺ
=====

ናዕት…. ቂጣ ብርኵታ ሮሚጦ ጥረሾ ሊጡ ሳይቦካና እርሾ ሳይገባበት ወዲያው ተለውሶ የሚጋገር
ዋዌ…. የልብ ሐሳብ ድምጸት
ድዉይ…. ደዌ (በሽታ)
ዘውግ….. ዘር (ጎሣ)
ጎግ ....... ጉግማንጉግ

🟩 🟨 🟥

★ ግጥም: ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ)
★ ዜማ : ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ)
እና
ቆየት ያለ የሀገረሰብ ባህላዊ ዜማ
★ ሙዚቃ ቅንብር፣ ኪቦርድና ሚክሲንግ : በረከት ተስፋዝጊ (ቤኪ)
★ ጊታር: በረከት ተስፋዝጊ (ቤኪ)
★ መሰንቆ: ሐዲስ ዓለማዬሁ (ሐዲንቆ)
★ ድምፅ ቀረፃና ማስተሪንግ: ማሩ ዓለማዬሁ

★ ምስጋና: ይህ ሥራ የተሳካ እንዲሆን በተለያየ መንገድ አስተዋፅዖ ላደረጋችሁ ወገኖች በሙሉ
★ መታሰቢያነቱ: ባለፉት ዐራት ዓመታት በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች አላግባብ በግፍ ለተገደሉ፣ አካላቸው ለጎደለ፣ ከመኖሪያ ቀያቸው ለተፈናቀሉ ንጹሓን ዜጎች በሙሉ

Address

Addis Abeba

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00

Telephone

947615630

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ye-Fiker Abogida posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ye-Fiker Abogida:

Share