Gordena Online

Gordena Online # a media that provides news and information about the culture and history of societies .

ይድረስ ለአክቲቪስት ስዩም ተሾመ እና ለወዳጄ ሳዲቅ አህመድ ❗----ፖለቲካ ካለ እውቀት እና በቂ መረጃ በየመንገድ አይወራም  ሰሞኑ ተወልጄ ባደግኩባት የፍቅር ከተማ በሆነችው ቡታጅራ ተፈጥሮ...
02/10/2025

ይድረስ ለአክቲቪስት ስዩም ተሾመ እና ለወዳጄ ሳዲቅ አህመድ ❗
----
ፖለቲካ ካለ እውቀት እና በቂ መረጃ በየመንገድ አይወራም
ሰሞኑ ተወልጄ ባደግኩባት የፍቅር ከተማ በሆነችው ቡታጅራ ተፈጥሮ በነበረው የተወሰነ ግርግር ከላይ የጠቀስኳቸው ሁለት አካላት ከግርግሩ ጋር ፍጹም የማይሄድ ያልተገባ ስም እና ፍረጃ ሲሰጡት አይቻለሁ
ስዩም ተሾመ " ቡታጅራ ማለት ሌባ ማለት ነው ብለዋል አባ ጅፋር ሲል ሰማሁት ወዳጄ ሳዲቅ አህመድ ደግሞ ጭራሽ ግጭቱ ኃይማኖታዊ ይዘት ያለው ነው ብሎት እርፍ አለ
ሁለቱም ፍጹም የተሳሳተ ፍረጃ ነው የሰጡት
ሲጀመር ቡታጅራ የሚለውን ስያሜ የሰጡት የጅማው አባ ጅፋር አይደሉም ::
----
ከወላይታ ወደ አዲስ አበባ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ወደ ወላይታ እና ደቡብ የኢትዮጵያ ክፍል ይጓዙ የነበሩ ነጋዴዎች በመንገዳቸው መረጃ ለመለዋወጥ ሽፍታ አለ ወይ ? በአፋን ኦሮሞ ( ቡታ ጅራ ? ) ብለው ሲጠያየቁ የተፈጠረ ስያሜ ነው
ስዩም ተሾመ እንደሚለው ሌባ ማለት አይደለም ቡታጅራም ሌባ አይደለችም የአካባቢውን ተወላጆችን ብቻ ሳይሆን የኔን አባት ጨምሮ ከሌላ አካባቢ መጥተው ይኖሩ የነበሩ የሌላ ብሔረሰብ ተወላጆችን እንዴት አክብሮ ሹሞ ሸልሞ ለትልቅ ኃላፊነት አብቅቶ በአካባቢው አስተዳደርም ሆነ የሽምግልና ስርዓት ትልቅ ቦታ ሰጥቶ እስከዛሬ አክብሮ የኖረ የሰለጠነ ፍቅር የሚታፈስበት ሃገር ነው ቡታጅራ
----
ለዚህም እንደ ማሳያ የምጠቅሳቸው ከጎንደር ህብረተሰብ ተወልዶ ከአዲስ አበባ የመጣው ጋሽ በቀለ አየለ እስከዛሬ ከማክበር አልፎ ከመሸለም አልፎ በስሙ ትምህርት ቤት የተሰየመለት ጀግና ነው እስከዛሬ አስተምሯቸውም ሆነ በዳሬክተርነት ዘመኑ በሱ ስር ያለፉ ተማሪዎችም ሆነ የአካባቢው ማህበረሰብ እንደሱ የሚፈሩት እና የሚያምኑት ሰው የለም ለዚህም ማሳያው ሆስፒታሉን ጨምሮ የተለያዩ ተቋሞችን እንዲያሰራ ሃላፊነት ጥለውበት እሱም ያለ ምንም ሌብነት በጨዋነት አጠናቆ አስረክቦአል ጀግናን ማክበር የሚያውቀው የቡታጅራ እና አካባቢው ማህበረሰብ ይኸው እንዳከበረው ዘልቆአል
---
ሁለተኛው ከሃድያ ብሔረሰብ የመጡት አቶ ማቲዎስ ባካ ( ነብሳቸውን ይማር ) ይሰጡ ከነበረው የህክምና ሙያ ጎን ለጎን የቡታጅራ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የወላጅ ኮሚቴ ሊቀ መንበር በመሆን ሁሉንም ህዝብ በእኩልነት አገልግለው ለአካባቢው ልማት ደፋ ቀና እንዳሉ እንደተከበሩ አልፈውል
ለዚህ ክብራቸው ሆቴላቸውን የገዛው ጸጋዬ የተባለ ግለሰብ ምንም እንኳ ሆቴሉን የገዛው በገዛ ገንዘቡ ቢሆንም ለክብራቸው ሲል የሆቴሉን ስያሜ አልቀይርም ብሎ ይኸው እስከዛሬ የሆቴሉ ስም " ማቲዮስ ሆቴል " ነው የሚባለው
ከኦሮሞ ብሔረሰብ የተወለደው አባቴ አደም ሐሰን ከአካባቢው ሽማግሌዎች እኩል የተጣላ አስታርቆ ለሚያገባ ሽምግልና ተልኮ እኛን ወልዶ አሳድጎ ለቁም ነገር አብቅቶ እሱ የዋለበት ሽምግልና ውሸት አይነገርም ፍርድ አይጓደልም እንደተባለ እንደተከበረ አልፎአል ( አላህ ይርሃመው )
የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ስዩም ተሾመ በቡታጅራ ላይ ለፈጸመው የስም ማጥፋት ይቅርታ ሊያስጠይቀው ወይም በህግ ሊጠይቀው ይገባል
---
ወደ ወዳጄ ሳዲቅ አህመድ ስመለስ ግጭቱ ኃይማኖታዊ ይዘት እንዳለው ጽፎአል ይሄ ፍጹም ቡታጅራን የማይወክል ፍረጃ ነው
ቡታጅራ መስጂድ ሲሰራ ክርስቲያኑ የመስጂድ አሰሪ ኮሚቴ የሚሆንባት እና ገንዘብ የሚያዋጣበት ቤተ ክርስቲያን ሲሰራ ሙስሊሙ ገንዘብ የሚያዋጣባት በዓሎቻቸውን በፍቅር ተጠራርተው በጋራ የሚያከብሩባት ጎረቤታሞች የሆኑት የትልቁ መስጂድ እና የቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያ ቅዳሴ እና አዛኑ የሚንፎለፎልባት ከፍ ሲልም ሙስሊም እና ክርስትያኑ ተጋብቶ የሚኖርባት የመቻቻል ውብ ከተማ ነች ቡትዬ
----
የክርስትና እምነት ተከታይ የሆኑ በውጭ ሃገር እና በሃገር ውስጥ የሚኖሩ የቡታጅራ እና አካባቢዋ ተወላጆች በአካባቢው ለሚገኙ የእስልምና ተከታይ አቅመ ደካሞች በዓመቱ ሳይቋረጥ ለአረፋ በዓል እስከ አስር የሚጠጉ ሰንጋዎችን ገዝተው ለአረፋ በዓል አርደው የሚያበሉ እንዲሁም የእስልምና እምነት ተከታይ የሆኑ በውጭ ሃገርም ሆነ በሃገር ውስጥ ያሉ የቡታጅራ እና አካባቢዋ ልጆች ሁሌም በዓመት መስቀል አቅመ ደካማ ለሆኑ የክርስትያን ወገኖቻቸው እስከ አስር በሬዎችን ገዝተው ደሃዎች በዓመት በዓል ጾም እንዳይውሉ የሚያበሉ በማረሚያ ቤት ለሚገኙ የክርስትናም ሆነ የእስልምና እምነት ተከታይ ታራሚዎች ያለ ልዩነት በየዓመቱ ለሁለቱም በዓላት ለአረፋ እና ለመስቀል አርደው የሚያበሉ እንቁ ልጆችን ያፈራች ነች ቡትዬ
---
የአንድ ሰው መብት በሚከበርባት የዓለም ህዝብ ተሰብስቦ በአንድ ህግ እየተመራ በሰላም በሚኖርባት አሜሪካ ተቀምጠን ለዘመናት አብረው በኖሩ ሲጋቡ ሲዋለዱ በኖሩ በሁለት ወንድማማች መካከል የሚፈጠሩ ጥቃቅን ችግሮችን በውይይት እና በመቻቻል እንዲፈታ የበኩላችንን ጥረት ማድረግ ሲገባን ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ መሄድ አይገባንም ወይም ከጉዳዩ እና ከአጀንዳው በላይ መጮህ እና ማስጮህ ጩኸቱ ከፍየሏ በላይ እንዳይሆን ያሰጋል
ለማንኛውም ተወልጄ ያደግኩበት የዋህ ህዝቤን አውቀዋለሁ
አባት አለው ሽማግሌዎች አሉት ሁሉም ነገር በሰላም እና በውይይት እንደሚያልቅ ምንም ጥርጥር የለኝም እገዛችንን ስትፈልጉ ጥሩን
---
ተወልጄ ያደግኩብሽ ጣፋጩን የልጅነት እና የወጣትነት ጊዜዬን ያሳለፍኩብሽ ትዳሬን የያዝኩብሽ ቡትዬ ሁሌም ሰላምሽን እና ፍቅርሽን እመኝልሻለሁ
====
# Milli Shamoro!

02/10/2025

አሁን ባለው የብልፅግና መርህ :-........ 💡💡💡..........
🔻የትኛውም የግል ወይም የቡድን ፍላጎት በሃይል ለማስፈፀም ወይም በሌሎች ላይ በሃይል ለመጫን የሚንቀሳቀሰ ቡድን ካለ እርሱ መጨረሻው አከርካሪው ተሰብሮ መቀመጥ ነው ❗
🔻 የትኛውም ግላዊም ይሁን የቡድን ፍላጎት የሚዳኘው በሕግና ሰርዓት ብቻ ብቻ መሆኑን ያረጋገጠ ነወ ::

ወኸምያታላቅ የጉራጌ ክትፎ ምሸት ከአርቲስት ደሳለኝ መርሻ እና ከአርቲስት ፈለቀ ማሩ ጋር በለንደንበየአመቱ እየተካሄደ ያለዉ የመስቀል ክትፎ ምሽት የዘንድሮው ዝግጅት October 4, 2025...
02/10/2025

ወኸምያ
ታላቅ የጉራጌ ክትፎ ምሸት ከአርቲስት ደሳለኝ መርሻ እና
ከአርቲስት ፈለቀ ማሩ ጋር በለንደን

በየአመቱ እየተካሄደ ያለዉ የመስቀል ክትፎ ምሽት የዘንድሮው ዝግጅት October 4, 2025 በለንደን ይደረጋል፡፡ ይህ ዝግጅት ኢትዮጲያውያንን በማሰባሰብ የጉራጌን ባህል፣ ቋንቋ እና ባህላዊ ስርዓትን፣ ከሀገር ውጭ ያሉት ኢትዮጵያዊያንን ብሎም ለሌሎች ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። በ2023 አርቲስት መላኩ ቢረዳ ከካናዳ እንዲሁም በ2024 አርቲስት ሃይሉ ፈረጃ ከኢትዮጵያ ድረስ በመምጣት ማህበረሰቡን በከፍተኛ ሁኔታ መነቃቃትን ፈጥሯል።

የ2025 ዝግጅት ደግሞ አርቲስት ደሳለኝ መርሻ እና ፈለቀ ማሩ ለንደን ላይ ዝግጅታቸውን ያቀርባሉ። እንደወትሮው ዘንድሮም የሚገኘው ጠቅላላ ገቢ ለባጥና የከራስ ት/ቤት ማስገንቢያ ይውላል።

የመግቢያ ዋጋ £70 ከክትፎ እና ለአንድ መጠጥ ጋር
ትኬቶችን ለመግዛት https://www.eventbrite.co.uk/e/kitfo-night--tickets-1759441209019?aff=oddtdtcreator
ለበለጠ መረጃ
07411817066, 07414898995, 07840344545, 07939877576 ይደውሉ

Address:
Woodberry Down
N4 2TW

Nearest station: Manor House station
ኑ እየተዝናኑ ትምህርትን ለማዘመን በሚደረገው ጥረትላይ የራስዋን አሻራ ያኑሩ።

አዘጋጅ ፡ የጉራጌ ማህበረሰብ በዩኬ

መረጃውን ያደረሠን አብነት ተዋበ ነው

What a wonderful night would be

“ኢቢሲ የቴሌቪዥን  ፓርላማ   ቻናል  በይፋ  መጀመሩ   እጅግ በጣም ያስደስታል “በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳች ምር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እፀገነት መንግስቱ   አቢሲ ...
02/10/2025

“ኢቢሲ የቴሌቪዥን ፓርላማ ቻናል በይፋ መጀመሩ እጅግ በጣም ያስደስታል “

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳች ምር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እፀገነት መንግስቱ

አቢሲ የፓርላማ ቴሌቪዥን ቻናል በይፋ መጀመሩ ለሀገራችን ሁል አቀፍ ዕድገት ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳች ምር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ ተናገሩ፡፡

የፓርላማ ስራዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረ መምጣቱና በህገ- መንግሰቱ የተሰጡትን ተልዕኮዎች ይበልጥ በብቃት ለመወጣት የፓርላማ ቴሌቪዥን መመጀመሩ አዲስ አቅም መሆኑን ነው የተከበሩ እፀገነት በተለይ ለኤፍ ኤም አዲስ 97.1 የተነገሩት፡፡

ፓርለማው ተልዕኮውን በልዩ ልዩ ስልቶች አማካኝነት ሲወጣ እንደነበር ያስታወሱት የተከበሩ እጸገነት መንግስቱ ፤ይህንኑ ታላቅ ሃላፊነቱን ይበልጥ አጠናክሮ ለመወጣት የቴሌቪዥን ቻናሉ መከፈት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ነው ያሉት፡፡

ራሱን በይዘትና አቀራረብ እያዘመነ የመጣው አንጋፋው ሚዲያ ተቋም የፊታችን መስከረም 26 ቀን ቀን 2018 ነው የፓርላማ ቴሌቪዠን ቻናሉን በይፋ የሚጀምረው፡፡

ኤፍ ኤም አዲስ 97.1

♦ህብረቱ እያሰራ ያለው የሶዶ አሰተዳደር ሕንፃ አጥር የጉራጌ ባህል በሚገልፀው እንሰት ተክል ስዕል ተሸቀርቅሮ!! === # creadit- የሕብረት fb ገፅ
02/10/2025

♦ህብረቱ እያሰራ ያለው የሶዶ አሰተዳደር ሕንፃ አጥር የጉራጌ ባህል በሚገልፀው እንሰት ተክል ስዕል ተሸቀርቅሮ!!
===
# creadit- የሕብረት fb ገፅ

 # በአዲሱ የኬላ-ቱሉቦሎ የአስፓልት መንገድ ለውበት የሚሆን የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ተደረገ!  🔀🔀🔀  # Creadit - south s**o gov com.
02/10/2025

# በአዲሱ የኬላ-ቱሉቦሎ የአስፓልት መንገድ ለውበት የሚሆን የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ተደረገ!
🔀🔀🔀
# Creadit - south s**o gov com.

02/10/2025

ኬር ዬሁን ጉራጌ !
. ♦♦♦
# ሰለጉራጌ አትነት የተገጠመ ግጥም 🔖

01/10/2025

# ወሰደቱም ልብዲየ ገረዲየ!
. ምኮም ያውር አፍዲየ አፍዲየ!
..........♦♦♦-----.. Tutuka - በቲክታክ ጉራጊኛ በማሰተዋወቅ
የተዋጣላት ናት!

ለየም ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ ' ሄቦ' በዓል እንኳን አደረሳችሁ! አደረሰን ለመላዉ የየም ብሔረሰብ ተወላጆች እና ለበዓሉ ታዳሚዎች ፣ እንኳን ለ 'ሄቦ ' ለየም ብሔረሰብ  ዘመን መለወጫ በዓ...
01/10/2025

ለየም ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ ' ሄቦ' በዓል እንኳን አደረሳችሁ! አደረሰን
ለመላዉ የየም ብሔረሰብ ተወላጆች እና ለበዓሉ ታዳሚዎች ፣ እንኳን ለ 'ሄቦ ' ለየም ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ በዓል አደረሳችሁ! አደረሰን! እያልኩ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ ።

የኢትዮጵያ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የማንነቶቻቸዉ መገለጫ የሆኑ የዘርፈ ብዙ ብዝኃነት ባለቤቶች መሆናቸዉ፣ ኢትዮጵያ በብዝኃነት ያጌጠች፣ በህብረ _ቀለማት የደመቀች ሀገር እንድትሆን አስችሏታል ።

'ሄቦ' የየም ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ በዓል በትዉልዶች ቅብብሎሽ የቀጠለዉ የብሔረሰቡ የጊዜ አቆጣጣር ስርዓት ኡደት የሚዘከርበት ብቻ አይደለም ፤ 'ሄቦ' ቁርሾን ወደ ይቅርታና እርቅ ማሸጋገርያ ፣ ፍትህና ርትዕ ማስፈኛና ማፅኛ፣ በፍቅር የመሻገር ፣ በይቅርታ የመደመር እሳቤንና ትዉፊትንም ማጠናከሪያ ነዉ።

በ'ሄቦ' በዓል ዋዜማ አካባቢን ፅዱና ለኑሮ ምቹ የማድረጉ ተግባር ይጠናከራል፤የአብሮነት ትሰስሩ ይታደሳል፣ የመጠያየቅና የፍቅር መንፈስ ይበረታል ፤ የደስታ፣ የተስፋና የብርታት ድባብ ከፍ ይላል።

'ሄቦ' እና ሌሎችም መሰል ባህላዊና ማህበራዊ እሴቶች የጀመርነዉን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ የሚያሳልጡ ይሆኑ ዘንድ በአግባቡ እንድንጠቅምባቸዉ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አቀርባለሁ ፤

መልካም የ 'ሄቦ' በዓል !

አመሠግናለሁ !
====
# Dr Endeshaw Tasew

01/10/2025

Big shout out to my newest top fans! Netsanet Chala, Netsi Ayelech, Yeshi Abebe, የፃድቁ አቡየ ልጅ, Gech Feyissa, Abonsha Abera, Markettwenty Fourseven, Meteku Hiyl, Yechimbe Baharu, Amare Feleke, Habtamu Fita, Mara Amado, Pawelos Tsegaye, Firezer Dejene, Muluneh Dati, Abresh Dejene, Àsçhé Ýè Śèw Çòpý, Ayelek Kerga Dilaga, Fetle Mammo, Aschalew Man, Waseyehun Kassa, Mechano Thermo, ሶዶ ኮልፌ, Abem Abem, Hana Daniel, Temesgen Abdi Gebremariam, Tariku Habtie, Tg Tg, Mekdes Aman, Kifle Mengistu, Solomon Uloro, Mohammed Nursalih, Tizazu Aedbeb Nida, Mesay Belay, Shiferaw Jenber, Assefa Temesgen, Abdul Feta Akmel, Emebet Admassu, Zedo Gu, Welda Teshome, Esmail Abdela Gurage, Ermias Kifle, Kebede Kenso, Darsema Gulima, Kifle Haile, Selamawit Taye, Befekadih Anuregn, Zeleke Girma, Manala Degaga, Faris Temam

Address

Addis Abeba

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gordena Online posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gordena Online:

Share