30/06/2025
✍️ቡኢ ከተማና የስሟ ትርጓሜ ..‼
-------------------------------------------
👉ቡኢ የሚለው ስያሜ እንዴት ሊሰጣት ቻለ.?
👉የስሟ ትክክለኛውስ ትርጓሜ ምንድነው ..?
🎯ነገሩ እንዲህ ነው በ1940 ዎቹ ላይ የሶዶ ክስታኔ ክፍለ ህዝብ መንግስታዊ አስተዳደር መቀመጫ ገሬኖ /አማውቴ ላይ ነበር ።
፦በወቅቱ አሁን ቡኢ ብለን የምንጠራት ከተማ የነጋዴዎች መተላለፊያ ነበረች ነጋዴዎቹም በስተ ደቡብ ኬላ - ዳሎቻ- በወቅቱ አጠራር ሲዳሞ ክፍለ ሃገር _ወላይታ ሶዶ -ሃገረ ማርያም ና ያቤሎ ድረስ በስተሰሜን አዲስ አበባ ድረስ በስተምዕራብ ጨቦና ጉራጌ አውራጃ ድረስ በስተምስራቅ መቂ (ዱቢሳ )ድረስ የንግድ መስመር ዘርግተው የሚተላለፉባት ሲሻቸው በእግር ሲያሻቸው በፈረስ ና በቅሎ እየተዘዋወሩባት ንግዱን የሚያሳልጡባት መንገዳቸው ነበረች
👉በሗላ ላይ ግን አሁን ቡኢ ብለን በምንጠራት ከተማ ላይ በወቅቱ አጠራር "አርጉ መቀል " የተባለ መንደር ውስጥ ሽፍቶች ተደራጅተው ነጋዴውን መዝረፍ ና መግደል ማሰቃየት ይጀምራሉ ይሄም የንግዱን ስረዓት ክፉኛ ጎዳው !!
👉በሗላ ላይ ይሄ የንግድ መስመር መሰበር በኢኮኖሚ ላይ ሊያመጣ የሚችለውን ጫና በመረዳት ፊታውራሪ ሩጋ አሻሚ (የመርከቶው ነፃ አውጪ ) ለአውራጃ አስተዳዳሪዎች ምክረ ሃሳብ ያቀርባሉ ምክረ ሃሳቡም እንዲህ የሚል ነበረ "መንግስታዊ ተቋማትን ከአማውቴ /ገሬኖ አውርደን ሽፍቶች አሉበት በተባለው አካባቢ ብናቋቁም ና በቂ ነፍጠኛ ፖሊስ ( የታጠቀ የፀጥታ ሃይል ) ብናሰማራ የሽፍቶቹን እንቅስቃሴ በመግታት ወደ ደማቁ የንግድ ስረዓት እንመለሳለን " የሚል ምክረ ሃሳብ ቀርቦ በወቅቱ በነበሩ ሹማምንት ፀደቀ ከዛም በኢትዮጲያዊያን አቆጣጠር በ1944 ዓ/ም ከተራራማው ገሬኖ /አማውቴ ወደ ታችኛው በዝቅተኛ ስፍራ ወደ ተመሰረተችው ቡኢ የሶዶ ክስታኔ ክፍለ ህዝብ መንግስታዊ ስረአቱ ወረደ
👉አቶ ደምሴ አወቀም የመጀመሪያው ሊቀመንበር (አስተዳዳሪ ) ሆነው ህዝቡን እንዲመሩ ተሾሙ ።
👉በወቅቱ ከተለያየ የኦሮሚያ አካባቢ ጉዳይ ለማስፈፀም ወይም ለተለያየ አገልግሎት ወደገሬኖ /አማውቴ መጥተው መንግስት ተቋማትን ፈልገው ሲያጡ "እገሌ የሚባለው ተቋምስ ብለው በኦሮሚፋ ሲጠይቁ በአካባቢው መንግስት ተቋማት ከዳገት ወደዝቅተኛው ስፍራ መቀየሩን ለማመልከት ቡኢ (ውረድ ) እዛ ታገኛቸዋለህ እያለ ይጠቁም ነበር ።
👉ይሃን መነሻ በማድረግ :- ቡኢ የሚል ስያሜ ተሰጣት ከዚያን ጊዜም ጀምሮ ቡኢ ተብላ ተጠራች ‼
🥇🥇እና የሁላችን ከተማ የሆነችው ቡኢ የትናንት ምስረታዋ ና ስያሜዋ ይሄን ይመስላል 🎯🎯🎯
🙏🙏ምስጋና 🙏🙏🙏
👉ይሄን የታሪክ ሰነድ ስሰንድ ለተባበሩኝ
(*ቀኝ አዝማች ጫካ አሰፋ አለቃ ብርሃኑ ዋካ ጋሽ እንዳልካቸው እሸቴ ና ሌሎችም አባቶቻችንን ከልብ አመሰግናለሁ እድሜና ጤና ይስጥልኝ ,,🙏🙏 )
-----
በፊታውራሪ እንዳሻው አለማየሁ !!