Gordena Online

Gordena Online # a media that provides news and information about the culture and history of societies .

ክስታኔ ባንድ !💖💖💖ታዋቂ አርቲስቶች እንደነ ቴዲ አፍሮ : አብነት አጎናፈር: ጎሳዬ ተስፋዬ : ፀጋዬ ሲሜ እንዲሁም ሌሎችም የነበሩበት የጥንቱ የባህል ኪነት ባንድ !====ከድጻዊ ቴዲ አፍሮ...
14/07/2025

ክስታኔ ባንድ !
💖💖💖
ታዋቂ አርቲስቶች እንደነ ቴዲ አፍሮ : አብነት አጎናፈር: ጎሳዬ ተስፋዬ : ፀጋዬ ሲሜ እንዲሁም ሌሎችም የነበሩበት የጥንቱ የባህል ኪነት ባንድ !
====
ከድጻዊ ቴዲ አፍሮ አንድ ጉራጊኛ ነጠላ ዜማ እንፈልጋለን !
💓💓💓
በዚህ አጋጣሚ መልካም ልደት ለንጉሱ 49th yr

~ ከክስታኔ ባንድ አባላት ማንን ታስታውሳላችሁ ?
💗💗💗

 # የሚደነቅ የመሪነት ሚና !          ⏳⏳⏳
14/07/2025

# የሚደነቅ የመሪነት ሚና !
⏳⏳⏳

06/07/2025

ዬቦላላ !
🥰🥰🥰
የክስቶ እሚት !

✍️ቡኢ ከተማና የስሟ ትርጓሜ ..‼    -------------------------------------------👉ቡኢ የሚለው ስያሜ እንዴት ሊሰጣት ቻለ.?👉የስሟ ትክክለኛውስ ትርጓሜ ምንድነው ...
30/06/2025

✍️ቡኢ ከተማና የስሟ ትርጓሜ ..‼
-------------------------------------------
👉ቡኢ የሚለው ስያሜ እንዴት ሊሰጣት ቻለ.?
👉የስሟ ትክክለኛውስ ትርጓሜ ምንድነው ..?
🎯ነገሩ እንዲህ ነው በ1940 ዎቹ ላይ የሶዶ ክስታኔ ክፍለ ህዝብ መንግስታዊ አስተዳደር መቀመጫ ገሬኖ /አማውቴ ላይ ነበር ።
፦በወቅቱ አሁን ቡኢ ብለን የምንጠራት ከተማ የነጋዴዎች መተላለፊያ ነበረች ነጋዴዎቹም በስተ ደቡብ ኬላ - ዳሎቻ- በወቅቱ አጠራር ሲዳሞ ክፍለ ሃገር _ወላይታ ሶዶ -ሃገረ ማርያም ና ያቤሎ ድረስ በስተሰሜን አዲስ አበባ ድረስ በስተምዕራብ ጨቦና ጉራጌ አውራጃ ድረስ በስተምስራቅ መቂ (ዱቢሳ )ድረስ የንግድ መስመር ዘርግተው የሚተላለፉባት ሲሻቸው በእግር ሲያሻቸው በፈረስ ና በቅሎ እየተዘዋወሩባት ንግዱን የሚያሳልጡባት መንገዳቸው ነበረች
👉በሗላ ላይ ግን አሁን ቡኢ ብለን በምንጠራት ከተማ ላይ በወቅቱ አጠራር "አርጉ መቀል " የተባለ መንደር ውስጥ ሽፍቶች ተደራጅተው ነጋዴውን መዝረፍ ና መግደል ማሰቃየት ይጀምራሉ ይሄም የንግዱን ስረዓት ክፉኛ ጎዳው !!
👉በሗላ ላይ ይሄ የንግድ መስመር መሰበር በኢኮኖሚ ላይ ሊያመጣ የሚችለውን ጫና በመረዳት ፊታውራሪ ሩጋ አሻሚ (የመርከቶው ነፃ አውጪ ) ለአውራጃ አስተዳዳሪዎች ምክረ ሃሳብ ያቀርባሉ ምክረ ሃሳቡም እንዲህ የሚል ነበረ "መንግስታዊ ተቋማትን ከአማውቴ /ገሬኖ አውርደን ሽፍቶች አሉበት በተባለው አካባቢ ብናቋቁም ና በቂ ነፍጠኛ ፖሊስ ( የታጠቀ የፀጥታ ሃይል ) ብናሰማራ የሽፍቶቹን እንቅስቃሴ በመግታት ወደ ደማቁ የንግድ ስረዓት እንመለሳለን " የሚል ምክረ ሃሳብ ቀርቦ በወቅቱ በነበሩ ሹማምንት ፀደቀ ከዛም በኢትዮጲያዊያን አቆጣጠር በ1944 ዓ/ም ከተራራማው ገሬኖ /አማውቴ ወደ ታችኛው በዝቅተኛ ስፍራ ወደ ተመሰረተችው ቡኢ የሶዶ ክስታኔ ክፍለ ህዝብ መንግስታዊ ስረአቱ ወረደ
👉አቶ ደምሴ አወቀም የመጀመሪያው ሊቀመንበር (አስተዳዳሪ ) ሆነው ህዝቡን እንዲመሩ ተሾሙ ።
👉በወቅቱ ከተለያየ የኦሮሚያ አካባቢ ጉዳይ ለማስፈፀም ወይም ለተለያየ አገልግሎት ወደገሬኖ /አማውቴ መጥተው መንግስት ተቋማትን ፈልገው ሲያጡ "እገሌ የሚባለው ተቋምስ ብለው በኦሮሚፋ ሲጠይቁ በአካባቢው መንግስት ተቋማት ከዳገት ወደዝቅተኛው ስፍራ መቀየሩን ለማመልከት ቡኢ (ውረድ ) እዛ ታገኛቸዋለህ እያለ ይጠቁም ነበር ።
👉ይሃን መነሻ በማድረግ :- ቡኢ የሚል ስያሜ ተሰጣት ከዚያን ጊዜም ጀምሮ ቡኢ ተብላ ተጠራች ‼
🥇🥇እና የሁላችን ከተማ የሆነችው ቡኢ የትናንት ምስረታዋ ና ስያሜዋ ይሄን ይመስላል 🎯🎯🎯
🙏🙏ምስጋና 🙏🙏🙏
👉ይሄን የታሪክ ሰነድ ስሰንድ ለተባበሩኝ
(*ቀኝ አዝማች ጫካ አሰፋ አለቃ ብርሃኑ ዋካ ጋሽ እንዳልካቸው እሸቴ ና ሌሎችም አባቶቻችንን ከልብ አመሰግናለሁ እድሜና ጤና ይስጥልኝ ,,🙏🙏 )
-----
በፊታውራሪ እንዳሻው አለማየሁ !!

|| የቡኢ ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ቤት ይለያል ||         ***   ***በቡኢ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ የበይነ መረብ (Online)  ፈተ...
30/06/2025

|| የቡኢ ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ቤት ይለያል ||
*** ***
በቡኢ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ የበይነ መረብ (Online) ፈተና መስጠት ተጀመረ።
ቡኢ ፤ ሰኔ 23/2017 (መንግስት ኮሚዩኒኬሽን)፦ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡኢ ከተማ አስተዳደር በሶዶ ቡኢ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የመጀመሪያው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ የበይነመረብ( online) ፈተና መስተጠት ተጀምሯል።
የመጀመሪያው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና እስከ ሰኔ 30/ 2017 ዓ/ም በበይነ መረብ (Onlne) እንደሚሰጥ የታወቀ ሲሆን በዚህም ወንድ 92 ሴት 79 በድምሩ 171 ተፈታኝ ተማሪዎች ተቀምጠዋል።
የዘንድሮው የ2017 ትምህርት ዘመን የ12 ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በሁለት ዙር የሚሰጥ ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ ከሰኔ 23 እስከ ሰኔ 30/2017 ዓ/ም እና እንዲሁም በሁለተኛው ዙር በማህበራዊ ሳይንስ ከሐምሌ 01 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ/ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።
ፈተናው ተጀምሮ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር ከፍተኛ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱንም ተገልጿል።
---
#ዘገባው የቡኢ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።
ለተጨማሪ መረጃዎች ገፆቻችን ይከታተሉይ

 # ቃል በተግባር !    ***   ***የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አንደሻው ጣሰው
25/06/2025

# ቃል በተግባር !
*** ***
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አንደሻው ጣሰው

 # ቃል በተግባር !   === ===> በዛሬው ዕለት የትምህርት ሚኒስቴር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የቡኢ ቦርዲንግ ስኩል መጎብኘታቸው ተነገረ ።> የቡኢ አዳሪ ት/ቤት የመጀመሪያ ምዕራፍ የግንባታ ...
12/06/2025

# ቃል በተግባር !
=== ===
> በዛሬው ዕለት የትምህርት ሚኒስቴር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የቡኢ ቦርዲንግ ስኩል መጎብኘታቸው ተነገረ ።
> የቡኢ አዳሪ ት/ቤት የመጀመሪያ ምዕራፍ የግንባታ ሂደት መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን በ2018 ዓ.ም ተማሪዎች መቀበል ይጀምራል ተብሎዋል ።
===
# creadit -Buei town gov comm.

 # የቡኢ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም !       🔹🔹🔹 # የተጀመረው የስታዲየም ግንባታ ለስፓርት ወዳዱ ለቡኢ ወጣት ትልቅ የምስራች ነው :: ለግንባታው መጠናቀቅ ሁላችንም መረባረብ ይኖርብናል...
30/05/2025

# የቡኢ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም !
🔹🔹🔹
# የተጀመረው የስታዲየም ግንባታ ለስፓርት ወዳዱ ለቡኢ ወጣት ትልቅ የምስራች ነው :: ለግንባታው መጠናቀቅ ሁላችንም መረባረብ ይኖርብናል ::
===
# photo creadit - ፊታውራሪ እንደሻው

 # በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው ከአፍሪካ በሎም በአለም ደረጃ እጅግ ግዙፍ የሆነው የጮቢ በአታ ለማርያም አንድነት ገዳም ሕንጻ ቤተ-ክርስቲያን !+++++
29/05/2025

# በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው ከአፍሪካ በሎም በአለም ደረጃ እጅግ ግዙፍ የሆነው የጮቢ በአታ ለማርያም አንድነት ገዳም ሕንጻ ቤተ-ክርስቲያን !
+++++

 # ሰለሰሞኑ አጀንዳ አንድ ምክረ ሀሳብ !!   🔹🔹🔹 # ትልቁ ትግላችን መሆን ያለበት የመላው ማህበረሰባችን ሰላም : አንድነት : ሕብረትና ብልፅግና ለማፅናት መሆን ይኖርበታል ::  # የ...
04/05/2025

# ሰለሰሞኑ አጀንዳ አንድ ምክረ ሀሳብ !!
🔹🔹🔹
# ትልቁ ትግላችን መሆን ያለበት የመላው ማህበረሰባችን ሰላም : አንድነት : ሕብረትና ብልፅግና ለማፅናት መሆን ይኖርበታል ::
# የማህበረሰብ አንድነት የሚሸረሽር : ማህበረሰቡን እርሰ በእርሰ እንዲጠራጠሩ የሚያደርግ የትኛውም የተዛባ አመለካከት : ትርክትና ፅንፈኝነት በጋራ ልንዋጋውና ሰላማችንን በጋራ ልናፀና ይገባል ::
# አሁን ያለው ማህበረሰባችን የተገነባው የተለያዩ ደማዊ ማንነት ባላቸው ጎሳዎች ሕብረት ብሎም የማይነጣጠል ደማዊ ውህደት በመፍጠር የጋራ የሆነ ማህበረሰባዊ ቋንቋ : ባህልና ስነልባና የጋራ ማህረሰባዊ አሰተዳደር ስርዓት በመፍጠር የተገነባ ነው ::
# እንደ ማህበረሰብ አንድ የሚያደርጉን የጋራ ባህል : ቋንቋና ስነልቦና እንጂ ከአንድ ወንዝ የተቀዳ አንድ አይነት ደማዊ ማንነት ወይም አጥንት እንዳልሆነ መረዳ ያስፈልጋል ::
===
# ታዲያ ዛሬ ላይ ፀጉር ስንጠቃ ውሰጥ የገቡና ማህበረሰቡን እርሰበእርሰ በማጋጨት ሰራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችን የመንግስት የፀጥታ መዋቅር ለሕግ የማቅረቡ ሰራ እጅግ የሚበረታታና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር ሲሆን ነገር ግን ለማህበረሰቡ ተቆርቃሪ የሆኑና እጃቸው እዚህ ውሰጥ የሌለ ግለሰቦችን በጅምላ የማሰርና ማንገላታት ተገቢነት የለውም :: መንግስት የተጣሪ መረጃ በመያዝ የማህበረሰቡን ሰላም የሚውኩ ግለሰቦችን ለሕግ ማቅረብ ይኖርበታል ::
===
# Gordena Online

 # ሕዝብ ልብ ዉስጥ መግባት የቻሉ ሕዝባዊ መሪ !  ------ በሕብረ-ብሔራዊ አንድነት የሚያምኑና ጽንፍኝነትን ብሎም ነጠላ ትርክትን የሚጽየፉና ቁርጠኛ መሪ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የማዕከ...
27/04/2025

# ሕዝብ ልብ ዉስጥ መግባት የቻሉ ሕዝባዊ መሪ !
------
በሕብረ-ብሔራዊ አንድነት የሚያምኑና ጽንፍኝነትን ብሎም ነጠላ ትርክትን የሚጽየፉና ቁርጠኛ መሪ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕስ መስተዳደር ክቡር እንድሻው ጣስው (ዶ/ር)

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gordena Online posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gordena Online:

Share