Gordena Online

Gordena Online news and information on the Ethiopian culture and traditions.

 ...  ?  !የሶዶ ክስታኔ ማህበረሰብ በልማት እና በመሠረተ ልማት ዙሪያ የቆዩ ጥያቄዎች ያሉበት አካባቢ ነው። በተለይም የጢያ የዓለም ቅርስ ስፍራ ያለውን የቱሪዝም እምቅ አቅም በማልማት ...
22/07/2026

... ?

!

የሶዶ ክስታኔ ማህበረሰብ በልማት እና በመሠረተ ልማት ዙሪያ የቆዩ ጥያቄዎች ያሉበት አካባቢ ነው። በተለይም የጢያ የዓለም ቅርስ ስፍራ ያለውን የቱሪዝም እምቅ አቅም በማልማት የአካባቢውን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት የተጀመረው የጢያ ማስፋፊያ ፕሮጀክት በወቅቱ በህዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ተስፋ ፈጥሮ ነበር።
የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ እስከ ባለፈው ሰኔ ወር መጨረሻ ድረስ እንዲጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ እንደነበር ይታወሳል። ይሁን እንጂ፣ ዛሬ ላይ ፕሮጀክቱ የት እንደደረሰ፣ የመጀመሪያው ምዕራፍ መጠናቀቁን ወይም አለመጠናቀቁን እና ቀጣይ የሥራ ሂደቱ ምን እንደሚመስል የሚያሳይ ግልጽ ይፋዊ መረጃ ለህዝብ አልቀረበም።
በማንኛውም የህዝብ ፕሮጀክት ውስጥ የግንባታ እድገትን በወቅቱ ማሳወቅ የተጠያቂነት መርህ አካል ነው። ይህም የህዝብን እምነት ያጠናክራል፣ የሚነሱ ጥያቄዎችንም ይቀንሳል።
ስለሆነም ከሚመለከታቸው ተቋማት የፕሮጀክቱ የአሁኑ የአፈጻጸም ደረጃ፣ የተከናወኑ ሥራዎች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች (ካሉ) እና የቀጣይ የሥራ ዕቅድ በተመለከተ ግልጽና ወቅታዊ ማብራሪያ እንዲሰጥ የህብረተሰቡ ጥያቄ እያቀረበ ይገኛል።
የጢያ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የት ደረሰ? የሚለው ጥያቄ ከመቼውም በላይ ግልጽና ወቅታዊ መልስ የሚፈልግ ሆኗል።
===
Gordena Online

ራጋ ማጋ የማረቆ ብሔረሰብ ባህላዊ መተዳደሪያ ደንብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸጎርደና ሚዲያ | ማረቆየማረቆ ብሔረሰብ ለብዙ ትውልዶች ያስተላለፈው ባህላዊ የመተዳደ...
21/07/2026

ራጋ ማጋ የማረቆ ብሔረሰብ ባህላዊ መተዳደሪያ ደንብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

ጎርደና ሚዲያ | ማረቆ

የማረቆ ብሔረሰብ ለብዙ ትውልዶች ያስተላለፈው ባህላዊ የመተዳደሪያ ሥርዓት የሆነው "ራጋ ማጋ" የማረቆ ልዩ ወረዳ ሁለንተናዊ ልማትን፣ ማህበራዊ አንድነትን እና ዘላቂ ሰላምን በማጠናከር ረገድ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ ገለጹ።

አቶ ጀማል አማሮ እንደገለጹት፣ ራጋ ማጋ የማረቆ ብሔረሰብ ለዘመናት ያዳበረው ባህላዊ የመተዳደሪያ ደንብ ሲሆን፣ በማህበረሰቡ መካከል ፍትሕን፣ መከባበርን፣ አብሮነትን፣ እርቅን እና ትብብርን በማጠናከር ለሰላማዊ ኑሮ ጠንካራ መሠረት ሆኖ ቆይቷል። በመሆኑም ይህንን ባህላዊ ሥርዓት ጠብቆ ማስቀጠልና ለአዲሱ ትውልድ ማስተዋወቅ የሁሉም ዜጋ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል።

እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለጻ፣ የማረቆ ልዩ ወረዳ በልማት፣ በመልካም አስተዳደር እና በዘላቂ ሰላም የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግብ ከመንግሥታዊ መዋቅሮች ጎን ለጎን ባህላዊ ተቋማትና እሴቶች የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ እጅግ ወሳኝ ነው። በተለይም ራጋ ማጋ በማህበረሰቡ ውስጥ የሚከሰቱ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ በመፍታት፣ የማህበራዊ ትስስርን በማጠናከር እና የህግ የበላይነትን በባህላዊ መሠረት በማጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው።

አቶ ጀማል አማሮ በመጨረሻ እንዳሳሰቡት፣ ራጋ ማጋ የማረቆ ብሔረሰብ የባህል ቅርስ ብቻ ሳይሆን ለልዩ ወረዳው ሁለንተናዊ ብልጽግና፣ ዘላቂ ሰላም እና የማህበረሰብ አንድነት መሠረት የሆነ እሴት ነው። በመሆኑም ሁሉም የማረቆ ብሔረሰብ አባላት፣ ወጣቶች፣ ምሁራን እና የማህበረሰብ መሪዎች ይህንን ባህላዊ ሥርዓት በአግባቡ በመገንዘብ፣ በመጠበቅና ለቀጣይ ትውልድ በማስተላለፍ ለአካባቢው ዘላቂ ልማትና ሰላም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል።

Gordena Online

    !  !! የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ የዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክ እውቅና ለማግኘት የሚደረገው የመስክ ግምገማ በምስራቅ ጉራጌ ዞን ተጀምሯል።ግምገማው ከሀምሌ 14 እስከ 16 ቀን 2...
21/07/2026

!

!!

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ የዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክ እውቅና ለማግኘት የሚደረገው የመስክ ግምገማ በምስራቅ ጉራጌ ዞን ተጀምሯል።

ግምገማው ከሀምሌ 14 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ የመጀመሪያዋን የዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክ እውቅና ለማግኘት እያደረገችው ያለው ጥረት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተገልጿል።

በግምገማው የጂኦ ቅርሶች ዓለም አቀፍ እሴት፣ የአስተዳደር ሥርዓት፣ የቅርስ ጥበቃ፣ ዘላቂ ቱሪዝም እና የማህበረሰብ ተሳትፎ በዩኔስኮ መመዘኛዎች መሰረት ይገመገማሉ።

በሶዶ ወረዳ ባህል አዳራሽ ለዩኔስኮ የግምገማ ቡድን ደማቅ አቀባበል የተደረገ ሲሆን፣ ይህ ሂደት የአካባቢውን የተፈጥሮ እና የባህል ቅርሶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅና ዘላቂ ቱሪዝምን ለማጠናከር ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተጠቁሟል።

====
የምስራቅ ጉራጌ ዞን የመንግስት ኮምኒኬሽን !

Gordena Online

የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ማረጋገጥ ስራ በቅንጅት እንዲፋጠን ተጠቆመ !  ! የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 አካል የሆነው የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ማረጋገጥና ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራ በቅንጅት...
20/07/2026

የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ማረጋገጥ ስራ በቅንጅት እንዲፋጠን ተጠቆመ !

!

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 አካል የሆነው የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ማረጋገጥና ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራ በቅንጅት እንዲፋጠን ተጠቆመ።
በሆሳዕና በተካሄደው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመረጃ ማረጋገጥ ስራ ግምገማ መድረክ፣ ተግባሩ ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ ለመገንባትና የመረጃ ግልጽነትን ለማስፈን ያለው ሚና ተጠቅሷል።
የርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪና የግብረ ሃይሉ ሰብሳቢ ንጉሴ አስረስ (ዶ/ር) ተግባሩን ለማሳካት ባለድርሻ አካላት በተቀናጀ መንገድ መስራትና የግንዛቤ ክፍተቶችን መፍታት እንደሚገባ ገልጸዋል።
የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮም የመረጃ አያያዝ ችግሮችን በመቅረፍና የዲጂታል ስርዓቱን በማጠናከር ላይ ትኩረት እንደሚሰጥ አስታውቋል።
በመድረኩም የመረጃ ምዝገባ ክፍተቶችን መቅረፍና ስራውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ አቅጣጫ ተቀምጧል።
====
#ምንጭ:- የክልሉ መንግስት ኮምኒኬሽን !!

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና 97.4 በመቶ የማለፍ ውጤት አስመዘገበ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በፌስቡክ ገፃቸው  እንዳስ...
20/07/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና 97.4 በመቶ የማለፍ ውጤት አስመዘገበ



የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በፌስቡክ ገፃቸው እንዳስታወቁት፣ በ2018 የትምህርት ዘመን በክልሉ የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 97.4 በመቶ የሚሆኑት ፈተናውን በተሳካ ሁኔታ ማለፍ ችለዋል።

እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፣ ይህ ከፍተኛ ውጤት በክልሉ የመማርና የማስተማር ሂደትን በማጠናከር፣ የማስተማር ስነ-ዘዴን በማሻሻል፣ የፈተና አስተዳደር ሥርዓትን በማጠናከር እንዲሁም የተማሪዎችን በራስ የመተማመን ስነ-ልቦና ለማጎልበት በተከናወኑ ተከታታይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ሥራዎች የተገኘ ውጤት መሆኑን አመልክተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ በየደረጃው ያሉ የትምህርት ሴክተር አመራሮችና ባለሙያዎች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራን፣ ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ የትምህርት አመራር ኮሚቴ አባላት እና ለውጤቱ መመዝገብ አስተዋጽኦ ያደረጉ ሁሉንም አካላት በራሳቸውና በክልሉ መንግስት ስም አመስግነዋል። በተጨማሪም "እንኳን ደስ አላችሁ" በማለት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም፣ በክልሉ የትምህርት ጥራትን እና የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ለማሻሻል የተጀመረው ጥረት የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
===
Gordena Online

📰   !      :የቡኢ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ትልቅ ተስፋና ጉጉት የፈጠረ ፕሮጀክት ሆኖ ቆይቷል። ትምህርት ቤቱ የትምህርት ጥራት...
20/07/2026

📰 !

:

የቡኢ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ትልቅ ተስፋና ጉጉት የፈጠረ ፕሮጀክት ሆኖ ቆይቷል። ትምህርት ቤቱ የትምህርት ጥራትን ከማሳደግ ባለፈ፣ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለቡኢ ከተማ ነዋሪዎች ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል በሚል ተስፋ ሲጠበቅ ቆይቷል።
ሆኖም በቅርቡ ተቋሙ የሥራ መደቦቹን ለመሙላት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አማካኝነት በውስጥ ዝውውር ብቻ የቅጥር ማስታወቂያ ማውጣቱ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ቅሬታ ማስነሳቱ ተገልጿል። እንደ አስተያየት ሰጪዎች፣ ይህ አሰራር በተለይ ለአካባቢው የተማሩና ሥራ ፈላጊ ወጣቶች የነበረውን ተስፋ ያጠበበ ነው።
ማህበረሰቡ እንደሚገልጸው፣ አዲስ የመንግስት ተቋማት ሲቋቋሙ የቅጥር ሂደታቸው ግልፅ፣ ፍትሃዊ እና ለሁሉም ብቁ ዜጎች እኩል ተደራሽ መሆን ይገባዋል። በአንድ ተቋም ብቻ የተወሰነ የውስጥ ዝውውር መፈጸሙ የቅጥር አሰራሩን ፍትሃዊነት ላይ ጥያቄ አስነስቷል ብለዋል።
እንዲሁም ትልቅ የመንግስት ተቋማት በአንድ አካባቢ ሲገነቡ የአካባቢው ማህበረሰብ በሥራ ዕድልና በሌሎች የልማት ተጠቃሚነቶች ተሳታፊ መሆን እንዳለበት ጠቅሰው፣ በቀጣይ በአካዳሚክ፣ በሬጅስትራርና በሌሎች የሥራ መደቦች ላይ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለቡኢ ከተማ ነዋሪዎች እኩል ዕድል የሚሰጥ፣ ግልፅና ፍትሃዊ የቅጥር ሂደት እንዲተገበር ጥሪ አቅርበዋል።

© | #ፈጣን፣ #ተዓማኒ እና #ሚዛናዊ #መረጃ

🚨   |  በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሐሰተኛ (ፌክ) አካውንቶችንና የተሳሳተ መረጃ ስርጭትን ለመቆጣጠር ድንገተኛ የስልክ ፍተሻ ሊካሄድ መሆኑ ተሰማ።ጎርደና ሚዲያ ከደረሰው መረጃ መሠረት፣ በምስራቅ...
18/07/2026

🚨 |

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሐሰተኛ (ፌክ) አካውንቶችንና የተሳሳተ መረጃ ስርጭትን ለመቆጣጠር ድንገተኛ የስልክ ፍተሻ ሊካሄድ መሆኑ ተሰማ።

ጎርደና ሚዲያ ከደረሰው መረጃ መሠረት፣ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በማህበራዊ ሚዲያ እየተስፋፋ ያለውን ሐሰተኛ (ፌክ) አካውንቶች አጠቃቀም እና የተሳሳተ መረጃ ስርጭት ለመግታት ያለመ ድንገተኛ የስልክ ፍተሻ ሊካሄድ መሆኑ ታውቋል።

እንደ ደረሰን መረጃ፣ ፍተሻው ከዞን መዋቅር እስከ ወረዳ ባሉ የተለያዩ ሴክተር አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ እንደሚካሄድ ተገልጿል። ዋና ዓላማውም በተለያዩ ስሞች የተከፈቱ ሐሰተኛ አካውንቶች፣ ማህበረሰቡን ለማደናገር የሚሰራጩ የውሸት መረጃዎች እና ሕግን የሚቃረኑ የዲጂታል እንቅስቃሴዎችን ለመለየት መሆኑ ተጠቁሟል።

ምንጮች እንደሚያመለክቱት፣ በቅርብ ጊዜ በማህበራዊ ሚዲያ የተስፋፉ ሐሰተኛ መረጃዎች የሕዝብ አንድነትን፣ የተቋማት ተዓማኒነትን እና የሰላም ሁኔታን ሊጎዱ ስለሚችሉ ይህ እርምጃ ትኩረት እንዲሰጠው ተደርጓል።

ጎርደና ሚዲያ በጉዳዩ ላይ የሚኖሩ ተጨማሪ እድገቶችን በቅርብ በመከታተል ለአንባቢዎቹ ወቅታዊ መረጃዎችን ያደርሳል ።

18/07/2026
18/07/2026

" #አለምብሬ"
💞💞💞
!
የሳሌሚያ የጉራጊኛ ዜማ ለAFRIMA Music Awards እጩ ሆነ !

|

ለጉራጌ ባህል፣ ቋንቋና የሙዚቃ ቅርስ ታላቅ የምስራች ዜና ተሰምቷል። አርቲስት ሳሌሚያ በድጋሚ ባቀረበችው የጉራጊኛ ዜማ "አለምብሬ" በአፍሪካ ከፍተኛው የሙዚቃ ሽልማት AFRIMA (All Africa Music Awards) ላይ ለሽልማት እጩ ሆና ቀርባለች።
"አለምብሬ" በጉራጌ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ ያለውና በታላቁ ድምፃዊ ጋሽ አርጋው በዳሶ የተቀነቀነ የማይረሳ ዜማ ነው። አርቲስት ሳሌሚያ ይህን የባህል ቅርስ በዘመናዊ የሙዚቃ ስልት በማቀናበር ለአዲሱ ትውልድ እና ለዓለም አቀፍ አድማጮች አድርሳዋለች።
ይህ እጩነት የአንድ አርቲስት ስኬት ብቻ ሳይሆን፣ የጉራጌ ቋንቋ፣ ባህልና የሙዚቃ ሀብት በአፍሪካ ደረጃ እውቅና እያገኘ መሆኑን የሚያሳይ ታሪካዊ እርምጃ ነው። ከዚህም በላይ የጋሽ አርጋው በዳሶ የኪነ-ጥበብ አሻራ በአዲስ ትውልድ እና በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ብሎ እንዲወሳ ትልቅ መንገድ ይከፍታል።
የጉራጌ ባህላዊ ዜማዎች በጥራት ተቀናብረው ወደ ዓለም መድረክ መውጣታቸው ቋንቋውን ለማስተዋወቅ፣ ባህሉን ለማስጠበቅ እና ለወጣቱ ትውልድ የቅርስ እሴቶችን ለማስተላለፍ የሚያበረታታ ትልቅ እድል ነው።
ጎርደና ሚዲያ ለአርቲስት ሳሌሚያ በAFRIMA ሽልማት ውድድር የተሻለ ውጤት እንድታስመዘግብ መልካም ምኞቱን ይገልጻል። ይህ ስኬት የጉራጌ ሙዚቃ በአፍሪካና በዓለም መድረክ የሚኖረውን ቦታ የበለጠ እንዲያጠናክር እንመኛለን።

— ጎርደና ሚዲያ | የጉራጌ ባህል፣ ቋንቋና ታሪክ ድምፅ

 #ከስኬት ጀርባ ፣ ሁሌም ቢሆን  #ታታሪነትና  #ሰራ  #ወዳድነት አለ ::  #ታታሪነትና    ደግሞ  #የጉራጌዎች ልዩ መገለጫ ነው ::   ❗።። 💞💞💞።።።።Gordena Online
18/07/2026

#ከስኬት ጀርባ ፣ ሁሌም ቢሆን #ታታሪነትና #ሰራ #ወዳድነት አለ :: #ታታሪነትና ደግሞ #የጉራጌዎች ልዩ መገለጫ ነው ::


።። 💞💞💞።።።።

Gordena Online

Address

Dubai
Addis Abeba

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gordena Online posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gordena Online:

Shortcuts

Share