Yilmana Ethics Liason Office

Yilmana Ethics Liason Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Yilmana Ethics Liason Office, Social Media Agency, adet, Adet.

06/01/2023

ቀን.28/04/2015

የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍሉ ወቅታዊ ጥሪ እና ሳምንታዊ መልእክት
በወረዳችን ብልሹ አሰራር እና ሌብነትን መታገል ከጀመርን የቆየን ቢሆንም ባለዉ ዉስብስብ እና አስቸጋሪ ሁኔታ ያልተጋለጡ አለያም ተጣርተዉ ለሚመለከተዉ አካል ቀርበዉ ግን ዉሳኔ ያልተሰጣቸዉ እንዳሉ እርግጠኞቸ ነን፤
በመሆኑም በዙሪያችን ለተሰለፋችሁ የፀረ ሙስና ንቅናቄ ሀይሎች የምናቀርበዉ ጥሪና መልእክት ከኑሮ ዉድነት እና ከስራ አጥነት ቀጥሎ ግብር ከፋይ ደንበኛውንና ጠቅላላ ህዝቡን እያማረረ ያለዉን ሌብነትና ማጭበርበር በተዘረጋው ሚስጢራዊ የአሰራር ስርአት ጥቆማና መርጃ አድርሱን ፤ሽፋን ሰጭዎች፣ደላሎች፣ተላላኪዎች፣አቀባባዮች፣ተካፋዮች፣ሰዋሪዎች ደግሞ ድርጊታችሁን አቁሙ ለህዝብና ለሃገር ቁሙ ፤ፈጣሪያችሁን ቀና ብላችሁ እዩ፣ለነፍሳችሁ አስቡ፣ከዚህ እኩይ ተግባር እራሳችሁን አርቁ ይህንን ማድረግ ካልቻላችሁ ህዝቡ የሚታገስበት ጊዜና ነባራዊ ሁኔታ ያበቃ መሆኑን እራሳችሁን ቆም ብላችሁ እዩ ፡፡ ጊዜው ፖለቲካን ስልጣንን ሀይልን ጉልበትንና ጨለማን የማይፈራ ነው፡፡ ሲል የይልማና ዴንሳ ወረዳ አስተዳደር የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍል መልእክቱን ያስተላልፋል፡፡

13/12/2022
17/11/2022

ቀን 02/03/2015
የትውልድ የስነ-ምግባር ግንባታ ስራ ወቅቱ የሚጠይቀው ሀገራዊ ህልውና
የትውልድ የስነ-ምግባር ግንባታ በአግባቡ ባለመስራቱ የስ-ነምግባርን ከልጅነት ጀምሮ የመቅረፅየወላጅ ሚና ደካማ በመሆኑ እንዲሁም በዚህ ዙሪያ ድርሻቸውን መወጣት ያለባቸው መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ አካለት ኃላፊነታቸውን በተገቢው ሁኔታ ባለመወጣታቸው አሁን እንደ ክልልንና እንደሀገር ላጋጠመን የብልሹ አሰራርና ሙስና ፈተናና ተግዳሮት አስተዋፅኦው ከፍተኛ ሆኗል፡፡ ችግሩ አሳሳቢ ደረጃ የደረሰና ጊዜ የማይሰጠው በመሆኑ እንደ ይ/ዴንሳ ወረዳ ወላጆች በልጆቻች፣በህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቆም ብለን እንስብ ፣ልጆቻችን የተስተካከለ ስብዕና እንዲኖራቸው የሚያስችል ስራ እንስራ ፣ትምህርት ተቋማት ለኀገር ለሀገር እድገት ፣ልማትና ዴሞክራሲ ግንባታ ጠቃሚ የሆነ ትውልድ ማፈራት መንግስታዊ ተልዕኮ በእናንተ ላይ የወደቀ በመሆኑ በተጠያቂነት አስተሳሰብና ቁርጠኛ በሆነ የትም/ አመራር ትውልድ የማነጽ ስራችንን እናስቀጥል የሚለው ሳምንታዊ መልዕክታችን ሲሆን የስነ-ምግባር እና የፀረ-ሙሽና ኮሚሽን በአዲስ ያወጣውን የተማሪዎች የስነ-ምግባር ክበባት አደረጃጀትና አሰራር መመሪያ ቁጥር 17/2013 ለመተግበር ትምህርት ተቋማትና የወረዳው የስነምግባር መከታተያ ክፍል ባደረጉት የምክክርና የውይይት መድረክ ላይ መግባባት ክበባት በ79 የመንግስትና በ3 የግል በድምሩ በ82 የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተደራጁ ሲሆን ሴት 17668 ወንድ 16710 በድምሩ 34378 ተማሪዎች በአባልነት ተመዝግበው ወደተግባራዊ እንቅስቃሴ የተገባ በመሆኑ የሚመለከታችሁ ዘካላት ሁለንተናዊ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ የድርሻችሁን እንድትወጡ የወረዳው የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ያሳስባል ፡፡

28/10/2022

የክፍሉ የሳምንቱ መልዕክት
የአብክመ የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በተቋማት እና በየደረጃው ባሉት የአስተዳደር እርከኖች እያሳደረ ያለውን ዘርፈ ብዙ ተጽዕኖ ለመግታት ብሎም ለማስቆም የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎችን በማደራጀት እንቅስቃሴያቸው እያስተባበረ እና ክፍሎቹም የሚቻላቸውን ሁሉ እያደረጉ ቢሆንም በይ/ዴ/ወረዳ አስ/የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍል እንደወረዳ የሁሉንም ዜጋ እና ባለድርሻ አካላት አጋርነት ቅንጅት እና የጋራ የሆነ የንቅናቄ ትግል የሚጠይቁ በመሬት ካሳ ትመናና መሬት ምዝገባ፣ በኢንቨስትመንት ፈቃድ አሰጣጥ እና ስምሪት፣በግብርና ግብዓቶች ስርጭት፣በመታወቂያ እና መሸኛ አሰጣጥ፣በመንግስት ተሸከርካሪዎች ስምሪት፣ዘይትና ነዳጅ አጠቃቀም፣በትራፊክ ደህንነት ቁጥጥር፣በቤት ማህበራት አደረጃጀትና መኖሪያ ቦታ አሰጣጥ፣በትምህርት ማስረጃ አቀራረብና አያያዝ፣በመንግስት ሀብትና ንብረት አጠቃቀም፣በመንግስት የስራ ሰዓት አጠቃቀም፣በመንግስትና ህብረት ስራ ማህበራት የፋይናንሻያል ኦዲት አገልግሎት አሰጣጥ፣ በመሬት ዕቅድ አጠቃቀም፣በወጣት የስራ ዕድል ፈጠራ ተዘዋዋሪ ብድር አሰጣጥ፣ወረዳዊ በሆኑ ልዩ ልዩ የሃብትና የገቢ አሰባሰብ፣በእንስሳት መድሀኒት አቅርቦት፣ስርጭትና አጠቃቀም፣በስፖርት ሃብት አሰባሰብና በጀት አጠቃቀም፣በተፈናቃዮች ድጋፍና ዕርዳታ ስርጭት፣በካፒታል ፕሮጀክቶች ግንባታ የሚፈጸሙትን ብልሹ አሰራሮች፣ሙስናና የተደራጁ ሌብነቶችን ለመግታት ድርጊቶች ወደ ወንጀል ከመሸጋገራቸው በፊት በጅምርና በሂደት ላይ እንዳሉ ምስጢራዊ በሆነ ጥቆማና መረጃ አሰጣጥ እንዲመክኑ በማድረግ የወረዳችን ማህበረሰብ የድርሻችንን እንድንወጣ ሳምንታዊ የጥሪ መልዕክታችንን እያስተላለፍን ስልክ 0583381119 email - [email protected]
መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የይ/ዴ/ወ/አስ/የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍል
አዴት

Send a message to learn more

Address

Adet
Adet

Telephone

+251941483605

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yilmana Ethics Liason Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yilmana Ethics Liason Office:

Share