ቤተንዳ ጉራጌው

ቤተንዳ ጉራጌው በዚ ፔጅ ስራ በነፃ ማስታወቂያም ይሁን የፈለጋቹት ነገር ፕሮሞሽን መስራት ለምትፈልጉ በነፃ አዉሩኝ 09 13 07 37 63 whatsup hi በሉኝ

12/07/2025
‎ሐምሌ 5/11/2017ዓ.ም (ወልቂጤ)‎‎የማስ ስፖርት ከአካላዊ እንቅስቃሴ ባሻገር አብሮነትን እና ወንድማማችነትን ለማጠናከር ያለው ድርሻ የጎላ መሆኑ ተገለጸ።‎‎በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ...
12/07/2025

‎ሐምሌ 5/11/2017ዓ.ም (ወልቂጤ)

‎የማስ ስፖርት ከአካላዊ እንቅስቃሴ ባሻገር አብሮነትን እና ወንድማማችነትን ለማጠናከር ያለው ድርሻ የጎላ መሆኑ ተገለጸ።

‎በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ሳምንታዊ_የማስ ስፖርት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርሃግብር ለመጀመሪያ ጊዜ በጉብርየ ክፍለ ከተማ በሌተናል ጀነራል ወልደስላሴ በረካ መታሰቢያ ሀውልት አደባባይ በደማቅ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል።

‎የማስ ስፖርት ከአካላዊ እንቅስቃሴ ባሻገር ለአብሮነት እና ለወንድማማችነት ያለው ድርሻ የጎላ በመሆኑ ስፖርቱን ማደበር እንደሚገባ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር አስታወቁ፡፡

‎በመርሀግብሩ ላይ የወልቂጤ ከተማ አመራሮች እና የክፍለከተማ አመራሮች ፣የአካል ብቃትና ጤና ሰልጣኝ ወጣቶች ፣የቴኳንዶ ሰልጣኝ ወጣቶች፣ የበጎ አድራጎት ክበባትና ሌሎችንም ፣ፐፕሊክ ሰርቫንትና ሁሉም የክፍለ ከተማችን ወጣቶችና ነዋሪዎች እየተሳተፉበት ይገኛል።

‎ዝርዝር መረጃው ተከታትለን የምናደርስ ይሆናል።

የሀምሌ ዝናብ ቪትዝ ማዝነብ ጀመረ  በሉኝ
11/07/2025

የሀምሌ ዝናብ ቪትዝ ማዝነብ ጀመረ በሉኝ

ሐምሌ  4/2017 ዓ.ም [ወልቂጤ] ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ስፓርት ባህላችን በማድረግ ማዘውተር እንደሚገባ ተገለፀ። በነገው እለት በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በጉብርየ ክ/...
11/07/2025

ሐምሌ 4/2017 ዓ.ም [ወልቂጤ]

ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ስፓርት ባህላችን በማድረግ ማዘውተር እንደሚገባ ተገለፀ።

በነገው እለት በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በጉብርየ ክ/ከተማ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል የሚያሳትፍ የማስ ስፖርት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ይካሄዳል።

በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ጽህፈት ቤት አዘጋጅነት በየ15ቀኑ በተለያዩ ቦታዎች የሚካሄደው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በነገው ዕለት በጉብርየ ክ/ከተማ ስለሚካሄድ የከተማ ነዋሪዎች ተሳታፊ እንዲሆኑ ጽህፈት ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።

ነገ ከማለዳው 12:00ሰዓት ጀምሮ ታላቅ የማስ እስፖርት ፕሮግራም ስለሚካሄድ ሁላችንም እንገናኝ መቅረት በፍጹም አይታሰብም።!!

"ሠላም ለሀገራችን"

👉 ዌብሳይት፦ http://www.wolkitecityadministration.gov.et
👉 https://www.facebook.com/profile.php?id=100071941941290

👉 ዩቲዩብ ፦https://youtube.com/.c?si=rqFMyMVDSkYdKny1

👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/wcagca

👉 tiktok.com/.city.gov
👉instagram::https://www.instagram.com/wolkite_city_gov.tcommun/profilecard/?igsh=MW1uMW43ZTl5MHAwNg==

👉X :-https://x.com/WolkiteA67?t=hnyplUuDhg31lig5TCpw1w&s=09

👉ኢ_ሜይል፦ [email protected]" rel="ugc" target="_blank">[email protected] ይጎብኙ

👉 ስልክ፦ +251113659879

 ‼️••~••~••~••~•••~•••~••~••~••~••የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የኮሪደር ልማት ሀብት አሰባሰብ ቻሌንጅን ተጠናክሮ ቀጥሏል‼️    #4000ብር እንዲሁም   በልማቱ ተማርኮ በ...
11/07/2025

‼️
••~••~••~••~•••~•••~••~••~••~••

የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የኮሪደር ልማት ሀብት አሰባሰብ ቻሌንጅን ተጠናክሮ ቀጥሏል‼️

#4000ብር እንዲሁም በልማቱ ተማርኮ በራስ ተነሳሽነት #10000ብር የልማት ድጋፍ ጥሪ ተቀብለው “ለወልቂጤ ከተማ ኮሪደር ልማት”
የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ቻሌንጁን ተቀላቅለዋል።

#ለከተማው የልማት ስራ ላይ ላደረጉት ተሳትፎ በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ስም ከልብ እናመሰግናለን 🙏🙏

🕊እኔም ለከተማዬ🕊
•~•~••~••~••~••~•
አንተስ…?
አንቺስ…?
እርስዎስ…?

11/07/2025

እዚህ ፔጅ ላይ ደስ ማይላቹ ነገር ካለ ንገሩኝ #በአላህ #በእግዛብሔር ብያቹሀለሁ ምንም like እያገኘ አደለም

የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ከ17 እና ከ20 አመት ቡድኖችን የመያዝ ግዴታ አለባቸው - ፌደሬሽኑ*******************በ2018 ዓ.ም ሁሉም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ከ17 እና ከ...
10/07/2025

የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ከ17 እና ከ20 አመት ቡድኖችን የመያዝ ግዴታ አለባቸው - ፌደሬሽኑ
*******************

በ2018 ዓ.ም ሁሉም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ከ17 እና ከ20 አመት በታች ቡድኖች የመያዝ ግዴታ እንዳለባቸው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አሳስቧል።

የሊጉ አሰልጣኞች እና ረዳት አሰልጣኞች ደረጃም ለ2018 ብቻ ዝቅተኛው የካፍ ቢ ፈቃድ መሆን እንዳለበትም ነው ፌደሬሽኑ ያሳሰበው፡፡

ውል ያላቸው አሰልጣኞች ግን በያዙት ፈቃድ እንደሚቀጥሉም ይፋ ተደርጓል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ክለቦች ለ2018 የውድድር ዘመን ሊያሟሏቸው የሚገቡ መስፈርቶች አስመልክቶ ያወጣውን የምስል መግለጫ ይመልከቱ፡-

በአንተነህ ሲሳይ

😱
10/07/2025

😱

በዞኑ ችግኝ የመትከል፣ የመንከባከብና ጠብቆ የማቆየት የማህበረሰቡን እሴት በመጠቀም ከመትከል ባለፈ የተተከሉ ችግኞች የጽድቀት መጠናቸው ከፍ እንዲል ሁሉም የተጠናከር ስራ መስራት እንዳለባቸው...
10/07/2025

በዞኑ ችግኝ የመትከል፣ የመንከባከብና ጠብቆ የማቆየት የማህበረሰቡን እሴት በመጠቀም ከመትከል ባለፈ የተተከሉ ችግኞች የጽድቀት መጠናቸው ከፍ እንዲል ሁሉም የተጠናከር ስራ መስራት እንዳለባቸው የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ላጫ ጋሩማ አሳሰቡ።

ሐምሌ 3/2017 ዓ.ም

የ2017 ዓ.ም ዞናዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በጉራጌ ዞን ቸሃ ወረዳ የጀካ ቀበሌ ተካሂዷል።

በዘንድሮ አመት በዞኑ ከ114 ሚሊዮን በላይ የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተተከለ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ የአረንጓዴ አሻራ ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት የጉራጌ ማህበረሰብ ችግኝ የመትከል፣ የመንከባከብና ተፈጥሮን የመጠበቅ የቆየ ባህል እንዳለው አመላክተዋል።

በዚህም በዞኑ ከ3 ሺህ 2 መቶ ሄክታር መሬት በላይ ጥብቅ ደኖች መኖራቸውን ያነሱት አቶ ላጫ ይህም የማህበረሰቡ ደን ጠብቆና ተንከባክቦ የማቆየት እሴቱ ማሳያ ነው ብለዋል።

በዞኑ የማህበረሰቡ የቆየ እሴት አጠናክሮ ለማስቀጠልና የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል በየአመቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን በመትከልና በመንከባከብ በርካታ ስራዎች እንደሚሰሩም ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል።

በዚህም የዞኑ የደን ሽፋን ከ25 ከመቶ በላይ መሆኑንም አመላክተዋል።

ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን የጽድቀት መጠናቸው ከፍ እንዲል ችግኝ በወቅቱ ከመትከል ባለፈ የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብና የመጠበቅ የማህበረሰቡ የቆየ እሴት ማጠናከር ይገባል ነው ያሉት።

ተፈጥሮ የመጠበቅ ስራ ተፈጥሮአዊ ብቻ ሳይሆን የፈጣሪም ትዕዛዝ በመሆኑ ተፈጥሮን የመጠበቅ፣ የመንከባከብና ለቀጣይ ትውልድ ማሸጋገር ስራ ላይ ሁሉም ኃላፊነቱ ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳደሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በበኩላቸው በዞኑ በዘንድሮ አመት ከ114 ሚሊዮን በላይ የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተተከለ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ከነዚህም ከ14 ሚሊዮን በላይ የቡና፣ ከ11 ሚሊዮን በላይ የመኖና 2 ነጥብ 4 የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን አንስተዋል።

የጉራጌ ማህበረሰብ ችግኝ የመትከልና የመንከባከብ የቆየ እሴት እንዳለው በዞኑ ለዘመናት ተጠብቀው የቆዩ የደን ማሳዎች ማሳያ ናቸው ያሉት አቶ አበራ የአሁኑ ትውልድም የቀድሞ የማህበረሰቡን እሴት ለማስቀጠልና ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ በዘርፉ የተጠናከረ ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

በዞኑ በእስካሁኑ የተተከሉ ችግኞች የጽድቀት መጠናቸው ከ92 ከመቶ በላይ መሆኑን ጠቁመው ማህበረሰቡ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ከመስራት ባለፈ ችግኝ በመትከላቸው የአፈር ለምነትና ምርትና ምርታማነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።

በዞኑ በሁሉም መዋቅር የተጀመረው የአረንዴ አሻራ ተግባር በማጠናከር የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከልና የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ መጠበቅና መንከባከብ ላይ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።

የቸሃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጥላሁን ሽምንሳ በወረዳው በዘንድሮ አመት ከ13 ነጥብ 4 በላይ የተለያዩ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተተከለ ይገኛል ብለዋል።

ከዚህ ቀደም በወረዳው የተተከሉ ችግኞች የአፈር ለምነትና ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው ያነሱት አቶ ጥላሁን የጽድቀት መጠናቸውም ከ85 ከመቶ በላይ መሆኑን ተናግረዋል።

በወረዳው ማህበረሰቡ ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከና የመጠበቅ ስራ አጠናክረው እንዲያስቀጥሉም አንስተዋል።

በወረዳው የጆካ ቀበሌ ችግኝ ሲተክሉ አግኝተን ያነጋገርናቸው አርሶ አደሮች እንዳሉት ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች የአፈር ለምነት ከማስጠበቃቸውም ባለፈ ምርትና ምርታማነት እንዳሳደገላቸው አንስተዋል።

በዘንድሮ አመት የተተከሉ ችግኞችም ከእንሰሳትና ከሰው ንክኪ ነጻ እንዲሆኑ የመንከባከብና የመጠበቅ ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

የዞኑ ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ

ታላቅ የምስራች!   | ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ታሪካዊ ምዕራፍ ተቀዳጀ፡ የመጀመሪያው የአንጎል ዕጢ ቀዶ ህክምና በተሳካ ሁኔታ አከናወነ!ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔ...
10/07/2025

ታላቅ የምስራች!

| ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ታሪካዊ ምዕራፍ ተቀዳጀ፡ የመጀመሪያው የአንጎል ዕጢ ቀዶ ህክምና በተሳካ ሁኔታ አከናወነ!

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ታላቅ ስኬት በማስመዝገቡ ኩራት ይሰማዋል፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የተደረገው የአንጎል ዕጢ ቀዶ ህክምና በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል! ይህ ታሪካዊ ክስተት ለማህበረሰባችን የምንሰጠው ልዩ የህክምና አገልግሎት ትልቅ መሻሻል ማሳያ ነው።

ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ቁርጠኛ ሰራተኞች በሙሉ ላቅ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ለመስራት ያላችሁ የማያወላውል ቁርጠኝነት በእውነትም ህይወትን እየለወጠ ነው። በሆስፒታላችን አገልግሎት እምነት ላሳዩን ታካሚ እና ቤተሰቦቻቸው ከልብ እናመሰግናለን።

በዚህ ታሪካዊ ቀዶ ህክምና የተሳተፉት ባለሙያዎች የሚከተሉት ናቸው፦

ዶ/ር ተመስገን ወልዴ-የአንጎል እና የህብለሰረሰር ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት

ዶ/ር አክበረት ለሜሳ (የቀዶ-ህክምና ረዚደንት)
የአንስቲዚያ ቡድን: ሙሁዲን፣ ታምሩ፣ አባይነሽ፣ መሀመድ
የነርሲንግ ቡድን: ብርሀኑ፣ነጋ፣ነፃነት፣ብርቱካን

Congratulations!!!

Historic Milestone at Wolkite University Comprehensive Specialized Hospital: First Brain Tumor Surgery!

Wolkite University Specialized Hospital is proud to announce a monumental achievement: the successful performance of it’s first-ever brain tumor surgery! This landmark event represents a significant advancement in delivering specialized medical care to our community.

We extend our deepest commendation to the entire dedicated staff of Wolkite University Hospital. Your unwavering commitment to excellence is truly transforming lives. Our sincere gratitude also goes to the patient and their family for placing their trust in our services.

Key participants in this groundbreaking surgery included:

Neurosurgeon: Dr. Temesgen Wolde
Assistant: Dr. Akberet Lemesa (GSR-3)
Anesthesia: Muhudin,Tamiru, Tajir, Cherinet, Abaynesh, Mohammed
Nursing team : Birhanu, Nega, Netsant, Birtukan

Address

Adis

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቤተንዳ ጉራጌው posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category