Bediru

የሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ግንባታ ፕሮጀክት በተያዘለት ግዜ ገደብ ለመጠናቀቅ በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ ይገኛል - ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን=====ነሀሴ 16/2017 የሀላባ ኢንተርናሽናል ስ...
22/08/2025

የሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ግንባታ ፕሮጀክት በተያዘለት ግዜ ገደብ ለመጠናቀቅ በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ ይገኛል - ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን
=====

ነሀሴ 16/2017 የሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ግንባታ ፕሮጀክት በተያዘለት ግዜ ገደብ ለመጠናቀቅ በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ እንደሚገኝ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ገለጹ።

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳ ክብር አቶ ሙህዲን ሁሴን የሚመራ ልኡክ በማልት ወዳዱ በሀላባ ህዝብ ተሳትፎ እየተገነባ ያለውን የሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ያለበትን ደረጃ ተመልክቷል።

በዚህ ወቅትም የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን እንደገለጹት ታሪካዊ የሆነው በልማት ወዳዱ በሀላባ ህዝብ ተሳትፎ እየተገነባ ያለውን የሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ግንባታ ፕሮጀክት ሂደት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ይገኛል ብለዋል።

የስታዲየሙ ግንባታ ሲጠናቀቅ ለአካባቢው ኢኮኖሚ እና ቱሪዝም ዘርፍ መነቃቃት ተጨማሪ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን ሁሴን እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ በተያዘለት ግዜ ገደብ እስኪጠናቀቅ ድረስ የህብረተሰብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።

ይህን ትልቅ ፕሮጀክት የዞኑ የህብረተሰብ ክፍል ርብርብ በማድረግ አሻራውን አሳርፎ የተጀመረው ግንባታ በተያዘለት ግዜ ገደብ ለመጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ የእግር ኳስ ተጫዋቾች የሚፈልቁበትና የስፖርት ቤተሰብ በብዛት ያለበት መሆኑን ጠቅሰው፣ ስታዲየሙ በአካባቢው መገንባቱ ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል።

በህዝብና በመንግስት ትብብር እየተገነባ ያለው የስታዲየም ፕሮጀክት እንዲጠናቀቅ ህዝቡ የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

በሁሉም ህብረተሰብ ክፍል እየተሳተፈ የሚገኘው ይህ ታሪካዊ ፕሮጀክት እንዲሳካ በኩላቸውን አስተዋጽኦ እየበረከቱ ይገኛሉ ብለዋል።

በዚህም የዞኑ ህዝብን ጨምረው ከሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጪ የሚኖሩ የብሄሩ ተወላጆችና ወዳጆችን አቶ ሙህድን ሁሴን ምስጋና አቅርበዋል።

በሹኩር ሀ/ሀሰን

22/08/2025
22/08/2025
✍️👉 ።👉የሀላባ ህዝብና የሀገር የኩራት ምንጭ የሆነው ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ በህዝቡ የጋራ ጥረትና በወዳጆች አጋርነት እየተካሄደ ነው። የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የከተማዋ ነዋሪዎች እና...
22/08/2025

✍️👉 ።

👉የሀላባ ህዝብና የሀገር የኩራት ምንጭ የሆነው ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ በህዝቡ የጋራ ጥረትና በወዳጆች አጋርነት እየተካሄደ ነው። የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የከተማዋ ነዋሪዎች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተባበረ ኃይል የስታዲየሙን እውን መሆን በተግባር በመደገፍ ላይ ይገኛሉ። ይህ ታላቅ ህዝባዊ ተሳትፎ የአካባቢውን ጠንካራ የጋራ ራዕይ፣ የህብረት ኃይልን እና የመተባበር መንፈስን በግልጽ የሚያሳይ ልዩ ምሳሌ ነው። ስታዲየሙ የህዝቡ የጋራ ባለቤትነት ስሜት ፍሬ ነው።

👉ይህ ስታዲየም ለሀላባ ቁሊቶ ከተማ የስፖርት፣ የባህልና የኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ መሠረት ነው። ለብዙ ሺህ ወጣቶች የስፖርት ክህሎቶቻቸውን የሚያዳብሩበት፣ ተሰጥኦአቸውን የሚያሳድጉበትና ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ የሚቀሰቅስ ማዕከል ከመሆኑም በላይ፣ ለከተማዋ ኢኮኖሚ የገቢ ምንጭ ይሆናል። የስታዲየሙ መገኘት ብቁና ስኬታማ ትውልድ በማፍራት የአገርን አጠቃላይ እድገት ለማፋጠን ጉልህና ዘላቂ አስተዋጽኦ ያበረክታል።

👉የስታዲየሙ ግንባታ የሀላባ ህዝብ ሁሉን አቀፍ ልማት አንፀባራቂ ማሳያ ነው። ከስታዲየሙ ጋር ተያይዞ በመንገድ መሠረተ ልማት፣ በህንፃ ልማት (እንደ ሆቴሎችና መዝናኛዎች) እና በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች የሚፈጠረው የኢንቨስትመንት ዕድገት ከተማዋን ወደ ዘመናዊና ተስፋ ሰጪ የንግድና የቱሪዝም ማዕከልነት ያሸጋገራታል። ይህ ታላቅ ፕሮጀክት ሀላባ በዙሪያዋ ላሉ ከተሞች የቅርብ ጊዜ የልማት ምሳሌ እንድትሆን ያደርጋታል፤ እንዲሁም የከተማዋን መልካም ገጽታ ይገነባል።

👉የሀላባ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ለከተማዋና ለነዋሪዎቿ ብሩህ የወደፊት ተስፋን ይወክላል። በዚህ ዘመናዊ ማዕከል የሚካሄዱ ዓለም አቀፍ የስፖርት ውድድሮች፣ ታላላቅ የባህል በዓላት፣ ኮንሰርቶች እና ማህበራዊ አገልግሎቶች ለከተማዋ አዲስ የእድገት ምዕራፍ የሚከፍቱ ከመሆናቸውም በላይ፣ የስራ ዕድሎችን በመፍጠርና የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ በማሻሻል በህዝቡ ውስጥ የከፍተኛ ስኬት እምነትንና ብሩህ ተስፋን ያጎለብታል።

✍️በከፍተኛ ተስፋና በህዝብ የጋራ ኃይል የተቀጣጠለው ይህ ታላቅ ፕሮጀክት ሀላባን በባህል፣ በስፖርትና በኢኮኖሚ ዘርፎች ወደ አዲስ የዕድገትና የብልጽግና ዘመን ያሸጋግራታል።

19/08/2025
18/08/2025
18/08/2025

Address

Alaba K'ulito

Telephone

+251916545320

Website

https://www.facebook.com/m.bediru1

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bediru posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Bediru:

Share