Alexo Media Network

Alexo Media Network Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Alexo Media Network, Alaba K'ulito.

ሥሉጥ ከተማበከተማ የመሰረተ ልማት አገልግሎቶችን ሥሉጥ ማድረግ ወጪ ቆጣቢ ቀልጣፋ አገልግሎት ነዋሪዎች እንዲያገኙ ያስችላል፡፡ በሥሉጥ ከተሞች ነዋሪዎች ዉል ለመስጠትና ለመቀበል በአካል መገኘ...
16/11/2025

ሥሉጥ ከተማ

በከተማ የመሰረተ ልማት አገልግሎቶችን ሥሉጥ ማድረግ ወጪ ቆጣቢ ቀልጣፋ አገልግሎት ነዋሪዎች እንዲያገኙ ያስችላል፡፡ በሥሉጥ ከተሞች ነዋሪዎች ዉል ለመስጠትና ለመቀበል በአካል መገኘት አይጠበቅባቸዉም፡፡ የንግድ ስራ ለመጀመር አብዛኛዉን ሂደት በአካል ለመቅረብ አይገደዱም፡፡ የመንግሥት ግዥ ሂደቶች አካላዊ ግንኙነቶችን በመቀነስ ወይም በአካል ሳይገኙ እንዲከዉኑ ያስችላል፡፡

ሥሉጥ ከተሞች አገልግሎታቸዉ ከዚህም በላይ ነዉ፡፡ ዘላቂ የከተማ ልማትን ያረጋግጣል፡፡ አረንጓዴ መሰረተ ልማት ለማስፋፋት ይጠቅማሉ፡፡ እንዲሁም ኃይል ቆጣቢ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የአካባቢና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃን ያሻሽላሉ፡፡ ለአየር ንብረት ለዉጥ የማይበገር ከተማን ለመገንባት ሥሉጥ የከተማ መፍትሄዎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸዉ፡፡ ሥሉጥ ከተሞች ህይወት እንዲኖራቸዉና የሰዉ ልጅ ህይወቱንና ስራዉን በረጋ መንፈስ እንዲመራ፣ ለአረንጓዴ ቦታና ለህዝብ ቦታ ልማቶች ትልቅ ቦታ ይሰጣሉ፡፡

የከተሞች ሥሉጥ መሆን ምቹ የፈጠራ ሥነ ምህዳር ይፈጥራል፡፡ የዲጂታል ፈጠራን ያጎለብታል፡፡ የመደመር መንግሥት እሳቤን ያስፋፋል፡፡ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ኢንዱስትሪዎችን እድገት ያፋጥናል፡፡ በዚህም እዉቀት መር ኢኮኖሚ ለመገንባት ያስችላል፡፡

በአጠቃላይ ሥሉጥ ከተሞች በመረጃ የተደገፉ መፍትሄዎችን ይሰጣሉ፡፡ በዲጂታል ቴከኖሎጂና በኔትዎርክ በተገናኙ ሥርዓቶች ተጠቅመዉ የከተማ ልማት ራዕይን ዉጤታማ፣ ዘላቂና ሁሉን አካታች ያደርጋሉ፡፡ የነዋሪዎችን፣ የኩባንያዎችንና የማህበረሰቡን ፍላጎቶችንና ግቦች ለማሳካት የሚያስችል አቅም ይፈጥራሉ፡፡ ሥሉጥ ከተሞች ለቀጣይ ዘመን ዕድሎችና ተግዳሮቶች ዝግጁ የሆነ ከተማ ይፈጥራሉ፡፡ የዲጂታል ሽግግሩን እዉን በማድረግ፣ ኢኮኖሚዉ ከዲጂታል ኢኮኖሚ ወደ እዉቀት መር ኢኮኖሚ ሽግግር እንዲያደርግ ያስችላሉ፡፡

ከተሞቻችንን በአዲሱ ዘመን እሳቤና ተግባር ማልማትና ፈጣን እድገት ማረጋገጥ አለብን፡፡ ያሉንን የመሰረተ ልማት አቅሞች አሟጠን መጠቀምና ኋላ በቀረንባቸዉ ፈጥኖ መልማት አለብን፡፡ ከተሞቻችን ከዲጂታል ዘመን እድል እንዲቋደሱ ከፈለግን በፍጥነት ሥሉጥ ማድረግ ይገባል፡፡ ለዚህም መሳካት የከተሞች አስተዳደር በመደመር መንግሥት ዕሳቤ መቃኘት አለበት፡፡

የመደመር መንግሥት ገጽ 238

16/11/2025
27/10/2025
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በሸዋኮ ቀበሌ ቆካንቴ ልማት ህብረት ሞዴል ሆኖ ተመረቀ።ጥቅምት 17/2018 በሀላባ ዞን ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ መምሪያ የሁለተኛ ዙር...
27/10/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በሸዋኮ ቀበሌ ቆካንቴ ልማት ህብረት ሞዴል ሆኖ ተመረቀ።

ጥቅምት 17/2018 በሀላባ ዞን ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ መምሪያ የሁለተኛ ዙር ሞዴል ልማት ህብረት ማስመረቂያ እና ሶስተኛ ዙር ሞዴል ልማት ህብረት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በሸዋኮ ቀበሌ የሞዴል ቀበሌ ምረቃ ፕሮግራም በደማቁ ተከናውኗል ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ሀላፊና ሰራተኛ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ባይዴ ሙንድኖ በሴቶች ሞዴል ምረቃ ወቅት እንደተናግሩት፡- ሴቶች በተለይ ከተሞች ውስጥ በሚኖሩ በሴቶች አደረጃጀቶች ላይ ንቁና ጠንካራ ተሳታፊ በመሆን በተለይ በኢኮኖሚው ዘርፍ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን እንደ ቁጠባ መቆጠብና፤ በአትክልት በፍራፍሬና በባልትና ምርቶች ላይ በመሳተፍ ዕድሎችን በመጠቀም ግንባር ቀደም መሆን እንዳለባቸው ገልጻለች ።


አክለውም ባደረጉት የመስክ ምልከታ ወቅት
ባዩት ነገር ተደስተው እኛ ሴቶች እንችላለን ስለዚህ በሁሉም ፓኬጆች ውጤታማነታቹሁ ኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ወደ ገበያ በአዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎች እየተቀበላችሁ እና ቁጠባቹን እያስጋቹሁ መቀጠል አላባቹሁ ብላዋል።

የሀላባ ዞን ሴቶችና ህጻናት መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ እመቤት ጀማል በበኩላቸው የሴት ልማት ህብረት ሞዴል ካደረጋቸው ተግባሮች መካከል በአከባቢ ፅዳት፣ የደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ፣ በመስራት መጠቀም በመቻላቸው ፣ መንደሮቹ ከጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች ነፃ በማድረግ ፣ የሌማት ትሩፋትና፤ንብ በማነብና ምግቤን ከጓሮዮ ፕሮግራሞችን በመተግበር በየ መኖሪያ ግቢያቸው የጓሮ አትክልት ማልማት መቻላቸው ከብዙ በጥቂቱ እንደሚገኝበት በቤት ለቤት ጉብኝት ለማረጋገጥ መቻላቸውን ገልጸዋል ።

ሞዴል የሴቶች ህብረት በተለያዩ የስራ ዘርፎች ራሳቸው በማብቃት እና መንግስት በተለያዩ ድጋፎች ሴቶችን ተጠቃሚ የሆኑበትን ፕሮግራሞች ፓኬጆች በትኩረት እየሰራ በመሆኑ በቀጣይ ሴቶች በሁሉም ሁለንተናዊ ዘርፍ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚጠበቅባቸው እና ለዚህም በማህበራዊ በኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳታፊ መሆን እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የመንግሰት ዋና ተጠሪ አቶ በክሪ አብደላ በበኩላቸው የሴቶች ልማት ህብረት አደራጃጀት በመጠናከር ሁለተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ ይጠበቅብናል ሲሉ ተናገረዋል

አያይዘውም በግብርና፣በጤና፣በህገወጥ ከሰዎች ዝውውር ጋር ተያይዞ፣ከትምህርት ጋር በተያይዘ ሰፋ ያለ ሀሳብ የሰጡ ሲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላቶች ተግባራትን ሲመሩ በቅንጅት እንደሚመሩ አሳስበዋል ።

የሀላባ ዞን ፍትህ መምሪያ ሀላፊ አቶ ገራሙ ሱንክቻ በበኩላቸው ሰዎች ትምህርታቸውን በመቆረጥ ህገወጥ ስድት እየተገዙ መሆናቸውን አንስተው ልጆች በትምህርት እራሳቸው አሻሽለው በተለያዩ ስራ ዘርፎ ተሰማርተው እራሳቸውን መቀየር እንዳሚችሉ አስገዝበዋል ።

በመጨረሻም በዓመቱ አስተዋጾ ላደረጉ አካላቶች በሙሉ የእውቅና የሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል

በፕሮግራሙ ላይ የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሀላፊ አቶ ሀጂ ኑርዬ፣የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ምክትልና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አብዲ መሀመድ፣የከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ምክትልና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሁሴን፣የዌራ ዲጆ ብልጽግና ፓርቲ ምክትል አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሱራጅ ጎድሶ የዞንና የወረዳ እስትሪንግ ኮሚቴዎች ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል ።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል !!

27/10/2025
💥ፈተናን_እንደ ጥሩ እድል በመጠቀምና በእጃችን ያሉንን ፀጋዎች በመገንዘብና በመጠቀም የተገኙ ስኬቶችን ለማወቅ የትላንትና የዛሬዋን የስምቢጣን ጉዞን መመልከት ይገባናል።💥✅  ዛሬና ትላንትና💥...
12/10/2025

💥ፈተናን_እንደ ጥሩ እድል በመጠቀምና በእጃችን ያሉንን ፀጋዎች በመገንዘብና በመጠቀም የተገኙ ስኬቶችን ለማወቅ የትላንትና የዛሬዋን የስምቢጣን ጉዞን መመልከት ይገባናል።💥✅
ዛሬና ትላንትና💥✅

03/10/2025
“የቀይ ባህርና የአሰብ ወደብ ጥያቄን በየትኛውም መነፅር ትክክል እንዳልሆነ ለመቀላመድ መሞከር ባንዳነት ነው” - የመከላከያ ሚኒስቴር“የቀይ ባሕር እና የአሰብ ወደብ ጥያቄን በየትኛውም መነፅ...
27/09/2025

“የቀይ ባህርና የአሰብ ወደብ ጥያቄን በየትኛውም መነፅር ትክክል እንዳልሆነ ለመቀላመድ መሞከር ባንዳነት ነው” - የመከላከያ ሚኒስቴር

“የቀይ ባሕር እና የአሰብ ወደብ ጥያቄን በየትኛውም መነፅር ትክክል እንዳልሆነ ለመቀላመድ መሞከር ባንዳነት ነው ሲል” የመከላከያ ሚኒስቴር ተናገረ።

ተቋሙ ዛሬ መስከረም 17/1018 ዓ.ም በይፋዊ የማኀበራዊ ገጹ “ወደን እና ፈቅደን ስለምንሞትላት ኢትዮጵያችን ጠንቅቀን እናውቃለን” በሚል ርዕስ ባሰፈረው መልዕክቱ ነው ይህን የገለጸው። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ስለማረጋገጥ የሚያትተው የመከላከያ ሚኒስቴር ጽሑፍ፤ የቀይ ባሕር እና የአሰብ ጉዳይ ላለፉት 30 ዓመታት የኢትዮጵያ ሕመም ሆኖ እንደቆየ ያስረዳል።

ኢትዮጵያ ከቀይ ባሕር መገለሏ እና የአሰብን ወደብ ማጣቷ “የታላቅ ሀገርነቷን ክብር አሳንሷል፤ የጂኦ ፖለቲካ ብሄራዊ ወሳኝ ጥቅሟን ቀምቷል” በማለት ያትታል። ይህን ጉዳይ አስመልክቶ “የኢትዮጵያ ወታደሮች የቀይ ባሕርን ጥያቄ በዓለም አደባባይ በይፋ መጠየቁ በታላቅ የደስታ ስሜት ሞልቶናል” ማለቱን ተመልክተናል። የመከላከያ ሚኒስቴር በዛሬው መልዕክቱ ሰራዊቱ “ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መረጋገጥ የትኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ለሰከንድ አያቅማም” የሚል ማረጋገጫን ሰጥቷል።

በባለፈው የጷግሜ ወር የተመረቀውን የሕዳሴውን ግድብ በመጥቀስ “የቀይ ባሕር ጉዳይም ዕውን የማይሆንበት ምክንያት እንደሌለ በጽኑ እናምናለን” በማለት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ አቋሙን ገልጿል። በመሆኑም "የቀይ ባሕር ብሎም የአሰብ ወደብ ጥያቄን በየትኛውም መነፅር ትክክል እንዳልሆነ ለመቀላመድ መሞከር ከባንዳነት ውጭ አንዳች ውኃ የሚያነሳ አመክንዮ ሊኖረው አይችልም” ሲል መከላከያ ሚኒስቴር ጠንከር ያለ መልዕክቱን አስተላልፏል።

“እኛ ፖለቲከኞች አይደለንም” ያለው ሚኒስቴሩ ነገር ግን “ስለኢትዮጵያችን ብሔራዊ ጥቅም መረጋገጥ ወደን ፈቅደን ስለእሷ ስንሰየፍላት ዐውቀናት” ነው ብሏል።

Address

Alaba K'ulito

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alexo Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share