Alamata Press

Alamata Press Alamata Press is a social media platform, providing information, socio economic & political analysi

01/07/2025

ሰበር
በሻዕቢያና ፋኖ በሚደገፈው በTDF እና በፌድራል መንግስት በሚደገፈው በTPF መካከል ወጅራት አካባቢ ዛሬ በሞርተር ጦርነት ጀምረዋል።

ራያ ወሎ ነው ። ወሎ አማራ ነው ። አማራም ወሎ ነው ። አገው ፣ አርጎባውና ኦሮሞውም ወሎ ናቸው ። ስለዚህ እኛ  ወሎዬዎች ነን በሚለው በውቢቷ የራዮች መዲና በአላማጣ ስም       በማድረ...
30/06/2025

ራያ ወሎ ነው ። ወሎ አማራ ነው ። አማራም ወሎ ነው ። አገው ፣ አርጎባውና ኦሮሞውም ወሎ ናቸው ። ስለዚህ እኛ ወሎዬዎች ነን በሚለው በውቢቷ የራዮች መዲና በአላማጣ ስም በማድረግ ይወዳጁን 🙏

ውቢቷ ራያ አላማጣ ከተማ 👇

የልቤን መልካም መሻት ያሟላችልኝ ቅድስት ድንግል ማርያም የእናንተንም ትሙላላችሁ ።
28/06/2025

የልቤን መልካም መሻት ያሟላችልኝ ቅድስት ድንግል ማርያም የእናንተንም ትሙላላችሁ ።

28/06/2025

“ አንዳንዴ ጥፋትህ ብቻ ሳይሆን
እላፊ መልካምነትህም እንደ ወንጀል ይቆጠራል ያውም በራስ ወገኖችህ ”🙆‍♂️

የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) ከራያ አላማጣ፣ አላማጣ ከተማ፣ ራያ ባላ፣ ኮረም ከተማ፣ ኦፍላ እና ዛታ ወረዳዎች ከተውጣጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያይተዋል...
27/06/2025

የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) ከራያ አላማጣ፣ አላማጣ ከተማ፣ ራያ ባላ፣ ኮረም ከተማ፣ ኦፍላ እና ዛታ ወረዳዎች ከተውጣጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያይተዋል።

የምክክሩ ተሳታፊዎች ከ1983 ጀምሮ በአያቶቻችን እና በአባቶቻችን ርስት መሬቱ የእኛ ነው ለቃችሁ ውጡ ስንባል ኖረናል ነው ያሉት። እኛ ባለርስቶቹ ግን ወጡ አላልናቸውም፤ ምክንያቱም ኢትዮጵያዊ ነን ብለዋል።

የህውሐት ኃይል ከአንድ ዓመት በፊት ዳግም ወሮናል ያሉት ተሳታፊዎቹ ወደ ራያ ምድር ሲገባ በወረራ ነው፣ ይህ ሊነገራቸው ይገባል ብለዋል። በተፈናቃይ ስም ወረራ መፈጸሙን ገልጸዋል። በወረራ የገባው ታጣቂ ይውጣልን፣ በተፈናቃይ ስም የገባውም ተጣርቶ የሕዝብ ቅቡልነት እንንዲኖረው ሊደረግ ይገባል ነው ያሉት።

የህውሐት ኃይሎች አካባቢያችንን በድጋሚ በመውረር ግፍ እየፈጸሙብን፣ እየዘረፉን ነው ብለዋል። ልጆቻችን በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማር አለባቸው በማለታችን ትምህርት እንዲቋረጥ ኾኗል ነው ያሉት።

የፌደራል እና የክልሉ መንግሥት መፍትሔ እንዲሠጧቸውም ጠይቀዋል። የደኅንነት ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባም አንስተዋል።

ጥያቄያችን በሕግ አግባብ ዘላቂ መልስ እስከሚያገኝ ትምህርት ይጀመርልን፣ የጸጥታ ኃይሎች ደኅንነታችን ይጠብቁልን ያሉት ተሳታፊዎቹ የህወሐት ታጣቂ ቡድን ከአካባቢው እንዲወጣም ጠይቀዋል።

ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖችን መንግሥት ድጋፍ ሊያደርግላቸው እንደሚገባም አንስተዋል። አካባቢው ተረጋግቶ ወደ ቤታችን መመለስ እንፈልጋለን ነው ያሉት።

የባዕዳን ተላላኪ የኾነው እና በስማችን የሚነግደው ጽንፈኛ ኃይል የማንነት ጥያቄያችን መልስ እንዲዘገይ ምክንያት ኾኗልና ድርጊቱን እናወግዛለን ብለዋል።

የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) የተነሱ ጥያቄዎች እና ችግሮች በሚመለከታቸው መዋቅሮች መፍትሔ እንዲያገኙ የክልሉ መንግሥት እንደሚሠራ አስታውቀዋል።

የወሰን እና የማንነት ጥያቄው በዘላቂነት መልስ እንዲያገኝ ዋናው ተዋናይ ሕዝቡ መኾኑንም ገልጸዋል። ሕዝቡ ሚናውን እንዲወጣም አሳስበዋል።

በመጀመሪያ ዙር ከትግራይ ክልል ተመልሰው በሀገር ሽማግሌዎች እና ታዋቂ ሰዎች ልየታ የገቡ ተፈናቃዮች በአማራ ክልል መንግሥት እውቅና የተፈጸመ መኾኑንም ገልጸዋል። ከዚያ በኋላ የተፈጸመው ግን ህወሐት በወረራ መልክ የፈጸመው መኾኑን ተናግረዋል።

የፌደራል መንግሥት ተፈናቃዮች ይመለሱ ከማለቱ በፊት የክልሉ መንግሥት አጣርቶ የያዘው ቁጥር እና ተመለሱ የተባሉት ቁጥር ምጥጥን በሦስቱ አካላት የተጣራ ባለመኾኑ ቅዲሚያ መጣራት አለበት ነው ያሉት።

የህወሐት ታጣቂ ወረራ ሲፈጽም የተፈናቀሉ ወገኖች ሁኔታዎች እስከሚረጋጉ ድረስ ቆቦ ከተማ እንዲጠለሉ መደረጉንም ገልጸዋል። ነገሮች ሲስተካከሉ እና የደኅንነት ስጋት ሲቀረፍ ወደቤታቸው እንደሚመለሱም አንስተዋል።

ጉዳዩ ሰላማዊ መፍትሔ ያገኝ ዘንድ የፌደራል መንግሥት፣ የክልል መንግሥት እና ኮሚቴዎች በየድርሻቸው እየሠሩ መኾናቸውንም ተናግረዋል።

"መንግሥት ዛሬን ብቻ ሳይኾን ነገን ታሳቢ አድርጎ እየሠራ ነው" ያሉት ምክትል ርእሰ መሥተዳድሩ ለተፈረሙ ውሎች ዋጋ የሚሰጥ እና ለዘላቂ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት የሚጨነቅ መኾኑን ገልጸዋል። ለዘላቂ አብሮነት እንቅፋት ከሚሆኑ አካሄዶች መጠንቀቅ እንደሚገባም ተናግረዋል።

ውሾች ይጮኻሉ  #ግመሎች  ይጓዛሉ ። መሪው ግን ይችላል!!! ራዮች እንችላለን 👌
26/06/2025

ውሾች ይጮኻሉ #ግመሎች ይጓዛሉ ።

መሪው ግን ይችላል!!! ራዮች እንችላለን 👌

"የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ የማንነት ጥያቄ ተገቢ መኾኑን እናምናለን።  ሰው ከመሬት በላይ ከፍ ብሎ መታየት አለበት። የወልቃይትን ሕዝብ ሕዝቤ ነው ብሎ መቀበል ይገባል። የትግራይ ሕዝብ አጀንዳ...
23/06/2025

"የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ የማንነት ጥያቄ ተገቢ መኾኑን እናምናለን። ሰው ከመሬት በላይ ከፍ ብሎ መታየት አለበት። የወልቃይትን ሕዝብ ሕዝቤ ነው ብሎ መቀበል ይገባል።

የትግራይ ሕዝብ አጀንዳ የሰላም አጀንዳ ነው። የህውሓት መሪዎች የትግራይ ሕዝብ ፍጹም የተለያዩ አካላት ናቸው። ሰላምን ለመፍጠርም ሁለቱን አካላት ለየብቻ መመልከት ጠቃሚ ነው።

የማንነት ጥያቄ መኖሩን እናምናለን፣ ጥያቄው ግን በሕጋዊና በፍትሐዊ መንገድ መመለስ አለበት። ጥያቄው የግለሰብ ጥያቄ ባለመኾኑ የሕዝቡን ድምጽ መስማት ይገባልም።"

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ በዛሬው እለት በወልቃይት ሰቲት ሁመራ ተገኝተው ካስተላለፉት ንግግር የተወሰደ።

 #40 ዙር ነው ድጉ በትሩ መዋጣ ፤ወሎ ነው አምሳያው የራያ አላማጣ ።     @አባግርሻ ራያ  አዝለሎም ስበር 💪            ያዕስ አባው ❤
22/06/2025

#40 ዙር ነው ድጉ በትሩ መዋጣ ፤
ወሎ ነው አምሳያው የራያ አላማጣ ።
@አባግርሻ ራያ አዝለሎም ስበር 💪
ያዕስ አባው ❤

ከታሪክ ማህደር ✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️በ1984ዓ.ም የአላማጣ ከተማ ወጣቶች ሰሜን ወሎን ወክለው አአ ስታዲየም ስፖርት ውድድር ላይ ሲሳተፉ ።ከብዙዎቹ በጥቂቱ 1. ከ 03 ንጉስ  ካ...
18/06/2025

ከታሪክ ማህደር
✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️
በ1984ዓ.ም የአላማጣ ከተማ ወጣቶች ሰሜን ወሎን ወክለው አአ ስታዲየም ስፖርት ውድድር ላይ ሲሳተፉ ።ከብዙዎቹ በጥቂቱ
1. ከ 03 ንጉስ ካሳየ ታረቀ
2.ከ 02 ቀበሌ የሺ ወንድሙ መኮነን
3.ከ 01 ቀበሌ ሓድሽ ሽሞይ
4.ከ 04 ቀበሌ ኪሮስ ለገሰ
5. ሰሎሜ ዱባለ
6. አምሳል ተፈራ/ቆቦ
7. ጣዕመ አብርሃ
ይህ አንዱ የማንነታችን ማሳያ ነው። ወሎየነት ተገደን አጥተነው የነበረ።በዓመታት ትግል መልሰን ያገኘነው ተፈጥሯዊ ማንነታችን ነው።

ማንነት ወይ ሞት 💪💪💪

@ባራንቶ አባ ሴሩ

15/06/2025

እስራኤል አፈር ድሜ ብትበላ ወይም የኢራንን አንገት አንቃ ከስር ፈሷን ብትቀዳ😁ኢራን ብትወቀጥ ወይም እስራኤል አናቷ ከላይ እንደ እባብ ቢቀጠቀጥ😁 እኛ ኢትዮጲያውያን ምን ቤት ነን ርስ በርስ የባለጌ ስድብ የምንሰዳደበው??☺️ይልቅስ ጦርነቱ በእኛ ኑሮ እና ዘንድሮ ላይ የሚያመጣው ተጨማሪ ጣጣ ላይ ብንወያይ አይሻልም ?
ኢራን እየተፋለመች ያለችው ከቅድመ-እስልምና በፊት የነበረውን የታላቁን የፐርሺያ ኢምፓየር ዝናዋን
ለመመለስ ነው።እስራኤልም የራሷን እና የአጋሮቿን ሀያልነት ለማስቀጠል ነው።በቃ ጉዳዩ እምነት እና ማንነትን ሽፋን ያደረገ የጥቅም ግጭት ነው።እኔን ብቻ ይድላኝ።እኔ ብቻ ልከበር ነው።የእኛ ቲፎዞነት ግን ባዶ ስሜት ነው።ድንቁርና ነው።የአለምን አሰራር አለማወቅ ነው።መጀመሪያ የቤታችንን ቆሻሻ እናፅዳ።
Miko zen

Address

Alamat'a

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alamata Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Alamata Press:

Share