Alamata Press

Alamata Press Alamata Press is a social media platform, providing information, socio economic & political analysi

የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ ለማስመለስ ብዙ ርቀት ተጉዘናል ።በጠንካራ የህዝብ ትግል የማንነት ጥያቄው ወደ ማይቀለበስበት ደረጃ ከፍ በማድረግ ጥያቄው ከራያ ህዝብ ጥያቄ መሆን አልፎ የመላው ...
09/06/2026

የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ ለማስመለስ ብዙ ርቀት ተጉዘናል ።በጠንካራ የህዝብ ትግል የማንነት ጥያቄው ወደ ማይቀለበስበት ደረጃ ከፍ በማድረግ ጥያቄው ከራያ ህዝብ ጥያቄ መሆን አልፎ የመላው አማራ የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ጥያቄ ወደ መሆን ተሸጋግሯል ። ይህ በጎ ጅምር ቢሆንም የራያ ህዝብ በየቀኑ የተለያየ የፖለቲካ ፍላጎት ባላቸው አካላት ከመገደል ልናቆመው ግን አልቻልነም ።

👉 ተባብረን የዕድሜ ዘመን የራያ ህዝብ ጠላት የሆነው ትህነግ ከመታገል ይልቅ ከራያ ህዝብ ፍላጎት በተቃራኒ በሆነ መንገድ ልዩነቶችን በመፍጠር የህዝባችን መከራ እያራዘምነው እንገኛለን ። በዚህም በየቀኑ ወጣት እያለቀ ህዝብ እየተሰቃየ እኛም ነብስ ይማር ማለት ሁኗል ስራችን ። ይህ የተለመደ አካሄድ ህዝባችን ከማስጨረስ በስተቀር ለራያ ህዝብ ከሞት መታደግ አልቻለም ።

👉 አሁንም አልመሸም በርካታ ልስተካከሉ የሚችሉ ነገሮች በግዜ ማስተካከል ከተቻለ ህዝባችን ከተጨማሪ ጥፋት መታደግ እንችላለን ። የራያ ህዝብ ልዩነቱን አጥብቦ በህውሃት ላይ ካልተነሳ የራያ ህዝብ ችግር መቼም ልቀረፍ አይችልም ። የፖለቲካ ፍላጎት ያላችሁ አካላት የፖለቲካ ጥያቄ ወይም እንቅስቃሴ አስፈላጊ በሚሆንበት ግዜ ያኔ አስተሳሰባችሁ ወይም ርዕዮት አላማችሁ በግዜው ትሰብካላችሁ ። አሁን ግን የተጋረጠብን የህልውና ችግር ላይ በማተኮር ህዝባችን ልንታደገው ይገባል ።

👉ሞት ሰባኪዎች (ግጭት ጠማቂዎችም ) ከራያ ህዝብ መሞትና መፈናቀል የምታገኙት እውቅናም ይሁን ጥቅም መልሶ እናንተን የሚያጠፋ በመሆኑ ልዩነት መስበክ ትታችሁ በጋራ ለመነሳት ሞክሩ ።

ራያ የሁሉም ተወላጅ ናት ። የሁላችንም አስተዋጽኦ ትሻለች ። ምርጫው ውሳኔው ለህዝባችን ትተን በጋራ ጉዳይ በጋራ እንነሳ ። ለሞተው ወንድማችን ነብስ ይማር 😢 ለመላው ቤተሰብ መፅናናቱን ተመኘን ። ነብስ ይማር 😢

ባራንቶ አባ ሴሩ

የማንደራደርባቸው ቀይ መስመሮች ሊኖሩን ይገባልየራያ ህዝብ እያደረጋቸው ላሉ ሁሉን አቀፍ የህልውና ትግሎች እንዲሁም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከግፍ አገዛዝ ተላቆ በመረጠው አስተዳደር ራሱን በራ...
08/06/2026

የማንደራደርባቸው ቀይ መስመሮች ሊኖሩን ይገባል

የራያ ህዝብ እያደረጋቸው ላሉ ሁሉን አቀፍ የህልውና ትግሎች እንዲሁም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከግፍ አገዛዝ ተላቆ በመረጠው አስተዳደር ራሱን በራሱ የሚያስተዳድርበትን ህዝባዊ ጥያቄ እልባት እንዲያገኝ የሚከተሉትን እሴቶች ወይንም ቀይ መስመሮች ሊተገብር ይገባል ።

➥ ራያነት ፦ ይህ ተፈጥሯዊ ማንነታችን ነው።የትግሉ ምሰሶ ወሎየነት ነው።

➥ አንድነት ፦ የሁለንተናዊ ጥቃት ሰለባ የሆነውን የራያ ህዝብ እና የህልውና ታጋዮችን አንድነት መጠበቅ የግድ ይላል ።

➥እውነትን መናገርና እውነተኛ ትግል ማድረግ :- ትልቁ ዋጋ ሊከፈል የሚገባው ለእውነትና ስለእውነት መሆን አለበት።ትግሉ የህልውና ነው ፤ ስለዚህ ለድብብቆሽ ፤ ለአሉባልታ ፤ ለተራ ብሽሽቅና ለአስመሳይነት ፈፅሞ ጊዜና ቦታ ሊኖረን አይገባም ።

➥ መደማመጥ :- በከፍተኛ ትዕግስትና በመደማመጥ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጋራ መፍታት ግድ ይላል ።

➥ ሀሳብን በሀሳብ መሞገት ቁልፍ የችግሮቻችን መፍቻ መንገድ ማድረግ ተገቢ ነው ።

➥ በልዩነት ማመን :- የልዩነት መኖር ተፈጥሯዊ ነው ይሁን እንጅ በልዩነት ተከባብሮ በአላማ አንድ መሆን ያስፈልጋል በጎጥ መከፋፈልን ሳይሆን በህወሓት ለተጨቆነውን ህዝባችንን ነፃ ለማውጣት ፤ በመጋገር ፤ በእውቀት ፤ በመረዳዳት አንድ ሆነን መታገል አለብን ።

➥ ምክንያታዊ መሆንና ለመርህ መገዛት ፤ ጠላትንና ወዳጅን መለየት

➥ ሰማዕትን ማክበርናመዘከር : - የራያ ግዠጀግኖች ለሞቱለት አላማ እስከመጨረሻው እንድንፀና ጊዜው ይጠይቀናል ።

➥ በአላማ መፅናት : - ተስፋ ቆራጮች ፤ ተሸናፊዎችና ተንበርካኪ አለመሆን መርሃችን ይሁን ።

➥ በራያ ህዝብ ላይ በየቀኑ እየደረሰ ያለውን ሁሉን አቀፍ ስርዓታዊ ጥቃት ደጋግሞ ለአዕምሮ መንገር ያስፈልጋል ፤ እልህ እና ቁጭት እንዲኖር ይኑረን ፤ የአባቶቻችን የአመራር ጥበብና እውቀት መቀበልና ማጎልበት ያስፈልጋል ።

ክብርና ሞገስ ለትግላችን ሰማዕታት 🇪🇹
ራያ ወሎ ነው 🇪🇹

@የራያው መብረቅ

28/05/2026
ራያ ላይ የቤተክርስቲያን ቅርሳቅርስ እየተዘረፈ ነው ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የተገነጠለውና በወያኔ ታዝሎ የገባው   ቡድን አባላት በግልጽ   ላይ ግልፅ ዘረፋ እየፈፀሙ ይገኛሉ ። ዕቃ ...
27/05/2026

ራያ ላይ የቤተክርስቲያን ቅርሳቅርስ እየተዘረፈ ነው

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የተገነጠለውና በወያኔ ታዝሎ የገባው ቡድን አባላት በግልጽ ላይ ግልፅ ዘረፋ እየፈፀሙ ይገኛሉ ። ዕቃ ቤቱን በማስገደድ ቁልፍ በመቀማት በውስጥ የነበሩ ንብረቶች ተዘርፈዋል ። ከተዘረፉ ንብረቶች መካከል

1. የተለያዩ ቅርሳቅርሶች ተዘርፈዋል ።
2. ከ3ቱ ቤተክርስቲያን የተሰበሰበ ጤፍ ከ20 ኩንታል በላይ ጤፍ ተዘርፏል ።
3. የቤተክርስቲያን ማስቀደሻ ግብር ስንዴ ከ5 ኩንታል በላይ ተዘርፏል ።
4. ገና ውላቸው ያልጨረሱ በሁለገብ ትምህርት የሚገኙ ህንፃዎች ልማት ባንኩ ጨምሮ በማስገደድ ከ300 ሺህ በላይ የአንድ ወር ኪራይ ተቀብለው ወስደዋል ።
5. ቃለ አዋጁ የማይፈቅደው እያንዳንዱ የሰበካ ጉባኤ አባል 10 ሺህ ብር እንዲከፈላቸው ተወስኗል ።
6. ገብረ የውሀንስ የሚባል ግለሰብ ተፈናቅየ በነበረበት ሰዓት ያልተከፈለኝ የ3 አመት ደሞዝ ይከፈለኝ ብሎ በመጠየቁ የመንበረ ሰይጣን የወረዳ ቤተክህነቱ እንዲሰጠው ወስነዋል ። በአጠቃላይ ቤተክርስቲያኗ በተደራጁና በወያኔ እየተዘረፈች ትገኛለች ።
👉 ይህን እያስፈፀሙ ያሉ የሰበካ ጉባኤ አባላት

1.
2.
3.
4.
5. /መንቀል_ንጉስ _አባል
6.

እነዚህ የአከባቢ ተወላጅ የሰበካ ጉባኤ አባላት ቤተክርስቲያን እንድትዘረፍና የተዘረፈው ለግላቸውና ለወያኔ ለጦርነት እንዲውል እያደረጉ ይገኛሉ ። ከላይ የተጠቀሳችሁ ግለሰቦችና ቤተሰቦች እጃችሁን ከቅድስት ቤተክርስቲያን እንድታነሱ እናሳውቃለን ።

መላው ህዝበ ክርስቲያን አመታዊ ሆነ የተለያዩ ክፍያዎች የምትከፍሉ የከፈላችሁት ለነዚህ ሆዳም ግለሰቦችና ለወያኔ እየሰጣችሁ መሆናችሁ አውቃችሁ የምትሰጡበት መንገድ አስተካክሉ ። በቅርቡ ወያኔ ከአከባቢው በፌዴራል መንግስት ተገዶ ይወጣል ። የራያ ሀገረስብከት ወደነበረበት ይመለሳል ። በመንበረ ሰይጣን ተወክላችሁ ቤተክርስቲያን እየዘረፋችሁ ያላችሁ ግለሰቦች ከተጠያቂነት አትድኑም ።

መልዕክቱ ለሁሉም አድርሱ

@ባራንቶ

ማንም እንዳይቀር‼️🏆 ታሪካዊ የእንብላ ድግስ ጥሪ ለአላማጣ ወረዳ የመድፈኞቹ (የንጉሡ ክለብ) ደጋፊዎች በሙሉ! 🏆 ዓመታትን ሙሉ “አርሰናል ዋንጫ አያነሳም እሱኮ ፆመኛ ነው እያሉ በየአደባባ...
23/05/2026

ማንም እንዳይቀር‼️

🏆 ታሪካዊ የእንብላ ድግስ ጥሪ ለአላማጣ ወረዳ የመድፈኞቹ (የንጉሡ ክለብ) ደጋፊዎች በሙሉ! 🏆

ዓመታትን ሙሉ “አርሰናል ዋንጫ አያነሳም እሱኮ ፆመኛ ነው እያሉ በየአደባባዩና በየDstv ቤቱ ና በተለያየ ቦታ ሲያበሻሽቁን፣ በባዶ ተስፋ ሊያሸማቅቁን የሞከሩ የሌሎች ክለብ ደጋፊዎችን አንገት ያስደፋ ታሪካዊ የእንብል ድግስ እነሆ ተዘጋጅቷል።

ይህ የድል ማዕድ የንጉሡ የአርሰናል ደጋፊዎች በኩራትና በደስታ የሚፈነድቁበት ዕለት በመሆኑ፣ በ Dj davo ማራኪ ስራዎች ከ 8 : 00 ሰዓት ጀምሮ በዳውን ታውን ላወንጅ በደማቅ ይከበራል ማንም እንዳይቀር ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ፈጥነው ቦታ የያዙ 🙏

ማሳሳቢያ!
ለጎረቤት ክለብ ደጋፊዎች፦ የድግሱን ተካፋይ እንዲሆኑ በክብር ጠርተነዎታል

ቦታ down town

ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊታችን ጋር በመሆን "ለመጭው ትውልድ የማንነት ነጻነትን እናወርሳለን"ራያ ወሎ ነው💪🇪🇹💪🇪🇹💪🇪🇹
17/05/2026

ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊታችን ጋር በመሆን "ለመጭው ትውልድ የማንነት ነጻነትን እናወርሳለን"

ራያ ወሎ ነው💪🇪🇹💪🇪🇹💪🇪🇹

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የጸጥታ አመራሮች እና  የሰሜን ወሎ ዞን አመራሮች ከራያ 3ቱ ወረዳዎች የሰላም አስከባሪ አባላት ጋር በጮቢ  ግንባር ተወያዩ።     ጮቢ ግንባር ፥ ግንቦት ...
16/05/2026

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የጸጥታ አመራሮች እና የሰሜን ወሎ ዞን አመራሮች ከራያ 3ቱ ወረዳዎች የሰላም አስከባሪ አባላት ጋር በጮቢ ግንባር ተወያዩ።

ጮቢ ግንባር ፥ ግንቦት 8/2018 ዓ/ም(አላማጣ ከተማ መንግስት ኮሚኒኬሽን)፦በዛሬው ዕለት ማለትም ግንቦት 8/2018 ዓ/ም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሚሊሻ የምልመላና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ፣የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ኮምሽን እንዲሁም የሰሜን ወሎ ዞን የሰላምና ጸጥታ ሃላፊ ፣ የሴሜን ወሎ ዞን አደጋ መከላከል መምሪያ ሃላፊ እንዲሁም የሶስቱ ወረዳዎች የወረዳ አመራር ጮቢ ግንባር በመሄድ፥ የሰላም አስከባሪ አባላት ጋር በወቅታዊ ሁኔታና በቀጠናው ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።የአላማጣ ከተማ ፣ የራያ አላማጣ እና የራያ ባላ የሚሊሻ አባላት በአንድ ግንባር ለቀጠናዊ ሰላምና ለህልውናቸው ሲሉ እንደተደራጁ ይታወቃል።

ስለዚህ በዛሬው ዕለት የክልልና የዞን የጸጥታ አመራሮች እንዲሁም የሶስቱ የራያ ወረዳዎች የወረዳ አመራሮችም ጭምር በጋራ "በተባበረ ክንድ ለማንነትና ለህልውና ቃል_ኪዳን" በሚል እሳቤ የጋራ ውይይት አድርገዋል።

ከውይይቱ በተጨማሪ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የምልመላና ስልጠና መምሪያ ሀላፊ "እናተ ለራያ ህዝብ ሁሉን አቀፍ ልዕልና ዘብ ሁናቹህ በሰከነ የሞራል ልዕልና ዳብራቹህ ፣ በራያ ሰማይ ስር ለራያ ህዝብ ዘብ በመሆን ለህዝባቹህ አሌንታ እንደምትሆኑ ምንም ጥርጥር የለንም መንግስትም ከጎናቹህ ነው።"ሲሉ ለሰላም አስከባሪው የሞራል ግንባታ ፈጥረውለታል።

በተጨማሪም "የራያ ህዝብ ከገጠመው የከፋ አደጋ ለመላቀቅ መደራጀት ፣ አንድነቱን ማጎልበትና ማዳበር ነገ የማይባል ፥ ግዜ የማይሰጥ አንገብጋቢ ተግባር ነው።" ሲሉ አጽንዖት ሰጥተውበታል።

ለዘለቄታዊ ሰላምን ማስፈንና ለተጨቆነ ህዝብ መከታም ጭምር ነው።

!

በአላማጣ ከተማ እየታየ ያለው የመሬት ወረራ ግዜውን በዉሉ ያላገናዘበ ነው ✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️መሬት መሸንሸን ፣ ሊዝ ማጫረት ፣ ሊዝ ማስከፈል ፣ ግብር ማስከፈ...
13/05/2026

በአላማጣ ከተማ እየታየ ያለው የመሬት ወረራ ግዜውን በዉሉ ያላገናዘበ ነው
✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️
መሬት መሸንሸን ፣ ሊዝ ማጫረት ፣ ሊዝ ማስከፈል ፣ ግብር ማስከፈል ፣ መሬት ማካተት ፣ ስም መቀየር ፣ ኢንቨስትመንት መቀበል ፣ የቀበሌ ቤቶች ወደ ግል ማዞር ፣ ታራሽ መሬቶች ላይ ቤት መገንባት እና ሌሎች መሬት ነክ ጉዳዮች በራያ 6ቱ ወረዳዎች የተከለከሉ ናቸው ። በዚህ ሰዓት ከላይ የተዘረዘሩ ተግባራት አውቆም ይሁን ሳያውቅ የሚፈፅም አካል ተጠያቂ ነው ። የአላማጣ ከተማ መሬት በውል የታወቀ በተለያየ ሰነዶች የተያዘ ስለሆነ ግዜ ተመቸን ብላችሁ የመንግስት መሬት እየተቀራመታችሁ ያላችሁ አካላት ከተጠያቂነት አታመልጡም ። በዚህ ሰዓት ከትህነግ ጋር ወግኖ የትህነግ መንግስትነት እውቅና ሰጥቶ መሬት ነክ ጉዳዮች የሚፈፅም የሚያስፈፅም አካል ከራያ ህዝብ ፍላጎት በተቃራኒ የቆመ መሆኑ መታወቅ አለበት ።

በዚህ ሰዓት መሬት ለመጫረት ሰነድ እየገዛችሁ ያላችሁ አካላት በህገወጥ ተግባር እየተሳተፋችሁ መሆናችሁ አውቃችሁ ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ እናሳውቃለን ።

Address

Alamat'a

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alamata Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Alamata Press:

Share