16/04/2025
ከመጋቢት 30 የተጀመረው በልማት እና በአካባቢ ጉዳዮች ላይ ምክክር አመርቂ ለውጦችን እያመጣ ነው:: በዚህ መሰረት በሚያዚያ 8 ቀን ከዞኑ እና ከወረዳው ሲቪል ሰርቫንት ጋር የተደረገው ምክክር ትልቅ የእሳቤ ለውጥ አምጥቷል:: በዚህ መድረክ የክልሉ የብሔር ብሔረሰቦች ዋና አፈ ጉባኤ ክቡር አቶ አዳማ ትንጳዬ, ኮሚሽነር ፍስሃ እና የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ያስተላለፉት ዋና ዋና ፍሬ ሃሳቦች: በአካባቢው ስለተፈጠረው ዘግናኝ ድርጊት ሁሉም ሰው መፀፀት አለበት, እንዲህ አይነት ድርጊት ዳግም እንዳይከሰት ሁሉም ሰው እጁን መሰብሰብ አለበት, ለተፈጠረው ቀውስ እጃቸው ያለበት ሁሉ ላይ የሕግ የበላይነት እንደሚረጋገጥባቸው, የተጉዱትን ሕብረተሰብ መልሶ የማቋቋም ሥራ በሙሉ በአጥፊዎች እና በሕዝቡ እንደሚሰራ, ከእርቅ በፊት ወንጀለኞች ተላልፎ መሰጠት እንዳለበት, የተዘረፈው ንብረት መመለስና የወደመው ንብረት በሙሉ መተካት አለበት የሚል ጠንከር ያለ መልዕክት አስተላልፈዋል:: አያይዞም ለዲራሼ ወረዳ ልማት እንቅፋት የሚሆን ሁሉ ጠላት ነውና እርምጃ ይወሰድበታል::
በሌላ በኩል ለአካባቢው ትርምስ ምክንያት ነው ተብሎ ስለ የተለዩት:- የጉማይዴ ማንነት (ወረዳ) አስመላሽ ጉዳይ የሞተን ፈረስ መጋለብ እንደሆነ, -የወየሳ ደን ውስጥ መግባት የሞት ወጥመድ መርገጥ እንደሆነ, -የቀጠናው ህገ ወጥ ትጥቅ አሁን በህግ መልክ መያዝ እንዳለበት, -ከሰገን ዙሪያ ወረዳ ባልተገባ መንገድ ወደ ጋርዱላ ዞን የገቡ ከ400 መቶ በላይ ሰራተኞች የሌላ ሕዝብ በጀት ለደመወዝ እየተከፈላቸው ነገር ግን ከተማ ተቀምጦ አርሶ አደሩን ለጥፋት የሚያደራጁ, መዋጮ ከፍለው መሳሪያና ጥይት የሚገዙ ላይ የሕግ እርምጃ እንደሚወሰድ, - የተዛባ ትርክት እየፈጠሩ ውዥምብር በሚፈጥሩት በግጭት ነጋዴዎች (ከሰገን ዙሪያ ወረዳ አምፆ የመጣው ኃይል እና አንዳንድ አቅጣጫ የጠፋው የጋርዱላ ዞን ተወላጅ) እና ፀረ ሠላም ኃይሎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልፁአል::
ስለዚህ ሁሉም ሰው ከዚህ እኩይ ተግባር ራሱን ሰብስቦ መንግስት በሚያስቀምጠው የልማት አቅጣጫ ልክ አስተዋፅኦ ማበርከት እንዳለበት ተግባብተው በቀጣይ የማጥራት ሥራዎች ላይ ሲቪል ሰርቫንቱ ከመንግስት ጎን በመቆም ሙያዊ እና ቴክኒካዊ እገዛ እንደሚያደርግ ተስማምተዋል::