Asteryo Media Media - አስተርዮ ሚዲያ

Asteryo Media Media - አስተርዮ ሚዲያ በዚህ የፌስ ቡክ ገፅ መንፈሳዊ ፣ ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ ኩነቶች የዜና ዘገባዎች ይተላለፋሉ።

17/12/2025

ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ማጠናከሪያና

አላማው ታኅሣሥ 29 ቀን 2018 ዓ/ም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን አስመልክቶ በደ/ኃ/ቅ/ገብርኤልና ደ/መ/ቅ/ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ዓለመ ብርሃን ሰንበት ት/ቤትና በመንበረ ጵጵስናው የሚገኙ የሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ሰንበት ትምህርት ቤት ሕብረት በጋራ በመሆን ላዘጋጁት ትልቅ የዝማሬ መርሃ ግብር በዕለቱ ታላላቅ መምራንና ዘማሪያን ስለ ሚጋበዙ አንድም ዝግጅቱን በመቀጠልም እንዲህ አይነት መርሃ ግብሮች እንዲቀጥሉ የሰንበት ትምርት ቤቶቾን ለማጠናከር ያለመ ነው።

በመሆኑም ስብሐታት ዝማሬ ዛሬ ታኅሣሥ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2:30 ጀምሮ አዳሩን መሉ በአርባ ምንጭ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከሚገኘው ማህበረ ቅዱሳን መሰብሰቢያ አዳራሽ

▶️የቀጥታ ስርጭቱ፦ በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሚዲያ
▶️በግናይ የደ/ኃ/ቅ/ገብርኤልና ደ/መ/ቅ/ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ሚዲያ

በ tik tok ,youtub ,facebook ከስር ባስቀመጥናቸው ሊንኮች እየገባችሁ like share copylink በማድረግ አጋርነታችሁን በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።

ሰንበት ትምህርት ቤቱ ያዘጋጀውን ስብሐታት ዝማሬን መደገፍ ለምትፈልጉ

▶የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000021470019
የደ/ኃ/ቅዱስ ገብርኤልና ደ/መ/ቅዱስ ሚካኤል አብያተክርስቲያናት ሰበካ

▶️ለመደወል

📲0982348956
📲0928016945
📲0910782374
📲0940577551
📲0910321824

👉የደ/ኃ/ቅ/ገብርኤልና ደ/መ/ቅ/ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ዓለመ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ያግኙን፤

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/gamoazhsi

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.com/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/gamoha

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

17/12/2025
17/12/2025
14/12/2025

ታላቅ የንግስ በዓል ጥሪ !!

በጥንታዊው ኤሊ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም

እግዚአብሔር የላከው መልአክም ከአናንያና ከአዛርያ ከሚሳኤልም ጋር ወደሚነደው ወደ እሳቱ ምድጃ ወርዶ በጕድጓድ ያለውን እሳት መታው ትን.ዳኔኤል ፫፥፵፮

ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል በብሉይ ኪዳን የተነገረለት ታላቅ ተአምር አለው። የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ላቆመው የወርቅ ምስል ያልሰገዱትን ሦስቱን ቅዱሳን ሕፃናት ሲድራቅ፣ ሚሳቅና አብደናጎን ወደሚነድ እሳት ውስጥ ጥሏቸው ነበር።

ቅዱስ ገብርኤል ግን ከሰማይ ወርዶ የነደደውን እሳት አበረደው፤ በምትኩም ቀዝቃዛ ነፋስ የሚነፍስበት እንደ ጠል ቦታ አደረገው። ሕፃናቱም ምንም ሳይጎዱ በእሳቱ መካከል ሆነው እግዚአብሔርን አመስግነዋል። ይህ ታላቅ የማዳን ተግባሩ የቅዱስ ገብርኤልን ኃያልነት ያሳያል።

ይህን ታላቅ የማዳን ተአምር በማሰብ፣ በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በዳራ ማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኘው በኤሊ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ታላቅ የንግስ በዓል በድምቀት ይከበራል።

ከዋዜማው ጀምሮ ከታኅሣሥ ፲፰ እና ፲፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም በኤሊ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፣ ተገኝታችሁ የበረከቱ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ እርስዎና ቤተሰብዎ፣ ወዳጅ ዘመድዎ ሁሉ በአክብሮት ተጋብዘዋል!

የቅዱስ ገብርኤል በረከትና ምልጃ አይለያችሁ!

የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጽ/ቤ

ታኅሣሥ ፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ያግኙን፤

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/gamoazhsi

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.com/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/gamoha

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

14/12/2025

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የማኅበረ ቅዱሳን አባል በታጣቂዎች ተገደሉ።
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ታኅሣሥ ፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

የኅዳር ጽዮን ማርያምን በዓል በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥር በምትገኘው በሐረቶ ማርያም በዓሉን አክብረው ሲመለሱ ሻንቡ ከተማ መዳረሻ ሲደርሱ የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ እና በርካታ የሀገረ ስብከቱ ሠራተኞችና ወጣት የማኅበራት አገልጋዮች በሕገ ወጥ ታጣቂዎች መወሰዳቸው ይታወቃል።

ሌሎቹ ተፈትተው ቆይተው ወደ ቤተሰቦቻቸው የተመለሱ ሲሆን በትናንትናው ዕለት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ኡፋ እና የማህበረ ቅዱሳን አገልጋይ የሆኑት ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ በሕገ ወጥ ታጣቂዎች መገደላቸው ተገልጿል::

መረጃው የEOTCTV ነው

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ያግኙን፤

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/gamoazhsi

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.com/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/gamoha

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

14/12/2025
14/12/2025

የማኅበራዊ ሚዲያ መበራከት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስፈላጊነት
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ታኅሣሥ ፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

የማኅበራዊ ሚዲያ መበራከት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተልዕኮዋን በዘመኑ መንገድ እንድትፈጽም የሚያስችላት ቁልፍ ጉዳይ ነው።

፩.የቤተ ክርስቲያንን ድምፅ ከፍ ማድረግ

ማኅበራዊ ሚዲያ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የራሷን ታሪክ እንድትገነባ ይረዳታል። ብዙ መድረኮችን መጠቀም እና ይዘትን ማብዛት ለሚከተሉት ያግዛል፡

ቤተ ክርስቲያን ይዘቷን ስታበዛ፣ ምዕመናን ከቤተ ክርስቲያን ሥርዓት የወጡ (ከሐሰተኛ) ትምህርቶች ይልቅ ትክክለኛውንና ኦርቶዶክሳዊ ትምህርትን እንዲያገኙ ዕድሉ ይሰፋል።

ብዙ ሰዎች በተለያየ የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ላይ ስለሚገኙ (ለምሳሌ አንዳንዶቹ ፌስቡክ ላይ፣ ሌሎቹ ቴሌግራም ወይም ዩቲዩብ)፣ በሁሉም መድረክ ላይ መገኘት ሁሉንም ምዕመናን ለመድረስ ያስችላል።

የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ፣ ታሪካዊ እና ባህላዊ እሴቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታዩበትን መንገድ ይከፍታል።

፪.የተወሰኑ ቡድኖችን መድረስ

የተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች ለተለያዩ ዕድሜና ፍላጎት ያላቸው ሰዎች ያገለግላሉ። ይህ መበራከት ለቤተ ክርስቲያን ልዩ ዕድል ይፈጥራል፡

ወጣቶች በብዛት የሚጠቀሙባቸውን እንደ ቲክቶክ ወይም ኢንስታግራም ያሉ መድረኮችን በመጠቀም ወንጌልን ዘመኑ በሚፈልገው ቅርጽ ማድረስ።

▶ዩቲዩብ (YouTube): ረጅም ስብከቶችና ጥናቶችን ለማቅረብ።

▶ቴሌግራም (Telegram): ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እና የጽሑፍ ትምህርቶችን ለማሰራጨት።

▶ፌስቡክ (Facebook): ለሰፊው ሕዝብ መረጃና የሥርዓተ አምልኮ ቀጥተኛ ስርጭቶችን ለማድረግ።

ምዕመናን ጥያቄዎቻቸውን በአስተያየት መስጫ ወይም በግል መልዕክት የመጠየቅና ፈጣን ምላሽ የማግኘት ዕድላቸው ይጨምራል።

፫.የቤተ ክርስቲያንን አገልግልት ማሳደግ
የማኅበራዊ ሚዲያ መበራከት የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደራዊ እና ሰብአዊ አገልግሎት ያሻሽላል።

በኦንላይን የሚለቀቁ ትምህርቶችና ስብከቶች የቤተ ክርስቲያኒቱ ዲጂታል ቤተ መጻሕፍት ሆነው ለዘለቄታው ይቀመጣሉ። ምዕመናን በፈለጉት ጊዜ ተመልሰው ሊያጠኑ ይችላሉ።

ለግንባታ ወይም ለበጎ አድራጎት የሚሰበሰቡ ገንዘቦችን ጥሪ ማስተላለፍ እና የሂደቱን ግልጽነት ማሳየት።

መረጃን በመስመር ላይ ማግኘት ሲቻል፣ በቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪዎች ላይ የሚወድቀው ተደጋጋሚ የመረጃ ጥያቄዎች ጫና ይቀንሳል።

ማጠቃለያ

የማኅበራዊ ሚዲያ መበራከት ለቤተ ክርስቲያን ምንም አማራጭ የሌለው ዘመናዊ መንገድ ነው። ዋናው ዓላማ ቤተ ክርስቲያን በእግዚአብሔር የተሰጣትን የወንጌል አገልግሎት ተልዕኮ በዘመናዊው ዓለም ፍጥነትና ስፋት ማከናወን ነው። ቤተ ክርስቲያን የሚዲያውን ኃይል በመጠቀም የሰውን ልጅ መንፈሳዊ ፍላጎት መመለስ ትችላለች።

ቸር ያቆየን

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ያግኙን፤

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/gamoazhsi

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.com/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/gamoha

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

13/12/2025

አስደሳች የሚዲያ ጥቆማ !!

"ግናይ" የአርባ ምንጭ ደ.ኃ.ቅዱስ ገብርኤል እና ደ.መ.ቅዱስ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ሚዲያ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ታኅሣሥ ፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት አካል የሆነው "ግናይ" የአርባ ምንጭ ደ.ኃ.ቅዱስ ገብርኤል እና ደ.መ.ቅዱስ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ሚዲያ ገጽ ከፍቶ ወደ አገልግሎት ገብቷል። ይህ ገጽ በዋናነት ከሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ጋር በመተባበር የሚከናወኑ መንፈሳዊ እንቅስቃሴዎችን፣ አገልግሎቶችን እና ወቅታዊ ጉዳዮችን ለምዕመናን በጊዜና በፍጥነት ለማድረስ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ይህ አዲስ የተከፈተ የሚዲያ ገጽ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በያዘው የአስር አመት መሪ እቅድ ውስጥ የሚዲያ ተደራሽነትን ማስፋት እና መረጃዎችን በፍጥነት ወደ ምዕመናን ማድረስ የሚለውን ግብ ለማሳካት እንደሚያግዝ ተመላክቷል።

በዚሁ እቅድ መሰረት፣ በሀገረ ስብከቱ ስር የሚገኙ ሌሎች ወረዳ ቤተ ክህነቶች፣ የተመረጡ አድባራትና ገዳማትም በቅርቡ የየራሳቸውን ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች እንደሚከፍቱ እና ወደ ስራ እንደሚገቡ ይጠበቃል።

ግናይ የአርባ ምንጭ ደ.ኃ.ቅዱስ ገብርኤል እና ደ.መ.ቅዱስ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ሚዲያ ከቁጫና ቁጫ አልፋ ፣ከኮንሶ ዞን ፣ከሠገን ፣ ከምዕራብ አባያ፣ከዳራማሎ ፣ ከገረሴና ቦንኬ ወረዳ ከአርባ ምንጭ ዙሪያና ጋጮ ባባ ወረዳዎች ቤተ ክህነት ከነዚህ ከ፯ቱ ወረዳ ቤተ ክህነቶች ሚዲያ ቀጥሎ በስምንተቻነት ከተከፈቱት ሚዲያዎች አንዱ ነው።

ግናይ የአርባ ምንጭ ደ.ኃ.ቅዱስ ገብርኤል እና ደ.መ.ቅዱስ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ሚዲያ ይፋ ባደረገው መልዕክቱ፣ ምዕመናን አዲሱን የፌስቡክ ገጽ like፣ share እና follow በማድረግ ድጋፋቸውን እንዲሰጡ "በእግዚአብሔር ስም" ጥሪ አቅርቧል።

ይህ ሚዲያ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት መመሪያ ሰጪነት ግናይ የአርባ ምንጭ ደ.ኃ.ቅዱስ ገብርኤል እና ደ.መ.ቅዱስ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት አስተዳደር ጽ/ቤት እውቅናና ፍቃድ የተከፈተ በመሆኑ፣ ምዕመናን የሚዲያው ተከታይ እንዲሆኑ እና እንዲያግዙም በአክብሮት ጥሪያችንን እናቀርባለን።

👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=61585160155928

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ያግኙን፤

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/gamoazhsi

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.com/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/gamoha

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

10/12/2025

አስደሳች የሚዲያ ጥቆማ !!

በጽሐ ሠናይ የአርባ ምንጭ ዙሪያና ጋጮ ባባ ወረዳዎች ቤተ ክህነት ሚዲያ የፌስቡክ ገጽ ይፋ ሆነ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ታኅሳስ ፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት አካል የሆነው በጽሐ ሠናይ የአርባ ምንጭ ዙሪያና ጋጮ ባባ ወረዳዎች ቤተ ክህነት ሚዲያ ገጽ ከፍቶ ወደ አገልግሎት ገብቷል። ይህ ገጽ በዋናነት ከሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ጋር በመተባበር የሚከናወኑ መንፈሳዊ እንቅስቃሴዎችን፣ አገልግሎቶችን እና ወቅታዊ ጉዳዮችን ለምዕመናን በጊዜና በፍጥነት ለማድረስ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ይህ አዲስ የተከፈተ የሚዲያ ገጽ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በያዘው የአስር አመት መሪ እቅድ ውስጥ የሚዲያ ተደራሽነትን ማስፋት እና መረጃዎችን በፍጥነት ወደ ምዕመናን ማድረስ የሚለውን ግብ ለማሳካት እንደሚያግዝ ተመላክቷል።

በዚሁ እቅድ መሰረት፣ በሀገረ ስብከቱ ስር የሚገኙ ሌሎች ወረዳ ቤተ ክህነቶች፣ የተመረጡ አድባራትና ገዳማትም በቅርቡ የየራሳቸውን ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች እንደሚከፍቱ እና ወደ ስራ እንደሚገቡ ይጠበቃል።

የበጽሐ ሠናይ አርባ ምንጭ ዙሪያና ጋጮ ባባ ወረዳዎች ቤተ ክህነት ሚዲያ ፣ከቁጫና ቁጫ አልፋ ፣ከኮንሶ ዞን ፣ከሠገን ፣ከምዕራብ አባያ፣ከዳራማሎ ፣ ከገረሴና ቦንኬ ወረዳ ቤተ ክህነቶች ከነዚህ ከስድስቱ ወረዳ ቤተ ክህነቶች ሚዲያ ቀጥሎ በሰባተኛነት ከተከፈቱት ሚዲያዎች አንዱ ነው።

የአርባ ምንጭ ዙሪያና ጋጮ ባባ ወረዳዎች ቤተ ክህነት ይፋ ባደረገው መልዕክቱ፣ ምዕመናን አዲሱን የፌስቡክ ገጽ like፣ share እና follow በማድረግ ድጋፋቸውን እንዲሰጡ "በእግዚአብሔር ስም" ጥሪ አቅርቧል።

ይህ ሚዲያ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት መመሪያ ሰጪነት የአርባ ምንጭ ዙሪያና ጋጮ ባባ ወረዳዎች ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እውቅናና ፍቃድ የተከፈተ በመሆኑ፣ ምዕመናን የሚዲያው ተከታይ እንዲሆኑ እና እንዲያግዙም በአክብሮት ጥሪያችንን እናቀርባለን።

👇👇👇👇👇👇👇??👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=61584625632509

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ያግኙን፤

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/gamoazhsi

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.com/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/gamoha

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

09/12/2025

የስብሐታት ዝማሬ ጥናት በአርባ ምንጭ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ኅዳር ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

የስብሐታት ዝማሬ ማብሠሪያ መርሐግብር ኅዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በቅዱስ ገብርኤል እና ቅዱስ ሚካኤል የልህቀት ት/ቤት ጊቢ የ7ቱ ሰ/ት/ቤት ስራ አስፈጻሚዎች እና አስተባባሪ ኮሚቴዎች በቦታው በመገኘት የስብሐታት ዝማሬ የመዝሙር ጥናት ተጀመረ።

የ7ቱ ሰ/ት/ቤት አባላት በጋራ በመሆን ያዘጋጁት የልደተ ክርስቶስን በዓል እልፍ በመሆን በዝማሬ ዋዜማው እለትን እናክብር በማለት በ ቀን 28/2018 ዓ/ም እንደሚካሄድ ገልጸዋል።

አርባምንጭ ከተማ የምትኖሩ ማኅበረ ምዕመናን በሙሉ! ይህ መንፈሳዊ ጥናት የሁላችንም ነውና፣ እየተገኛችሁ ዝማሬውን እንድታጠኑ እና በዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ኅብረት እንድትሳተፉ በታላቅ ደስታና ፍቅር ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ጥናቱ ዘውትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ሠርክ 11 : 00 - 12 : 30

▶መልእክቱን ሼር በማድረግ ይህ መንፈሳዊ ጥሪ ለሁሉም ይድረስ ዘንድ ተባበሩን!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ያግኙን፤

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/gamoazhsi

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.com/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/gamoha

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

Address

Arba Minch
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Asteryo Media Media - አስተርዮ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Asteryo Media Media - አስተርዮ ሚዲያ:

Share