Asteryo Media Media - አስተርዮ ሚዲያ

Asteryo Media Media - አስተርዮ ሚዲያ በዚህ የፌስ ቡክ ገፅ መንፈሳዊ ፣ ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ ኩነቶች የዜና ዘገባዎች ይተላለፋሉ።

17/10/2025

አስደሳች የሚዲያ ጥቆማ !!

የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት የፌስቡክ ገጽ ይፋ ሆነ
========
የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት አካል የሆነው የዳራ ማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት በይፋ የፌስቡክ ሚዲያ ገጽ ከፍቶ ወደ አገልግሎት ገብቷል። ይህ ገጽ በዋናነት ከሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ጋር በመተባበር የሚከናወኑ መንፈሳዊ እንቅስቃሴዎችን፣ አገልግሎቶችን እና ወቅታዊ ጉዳዮችን ለምዕመናን በጊዜና በፍጥነት ለማድረስ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ይህ አዲስ የተከፈተ የሚዲያ ገጽ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በያዘው የአስር አመት መሪ እቅድ ውስጥ የሚዲያ ተደራሽነትን ማስፋት እና መረጃዎችን በፍጥነት ወደ ምዕመናን ማድረስ የሚለውን ግብ ለማሳካት እንደሚያግዝ ተመላክቷል።

በዚሁ እቅድ መሰረት፣ በሀገረ ስብከቱ ስር የሚገኙ ሌሎች ወረዳ ቤተክህነቶች፣ የተመረጡ አድባራትና ገዳማትም በቅርቡ የየራሳቸውን ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች እንደሚከፍቱ እና ወደ ስራ እንደሚገቡ ይጠበቃል።

የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ ከቁጫና ቁጫ አልፋ ፣ከኮንሶ ዞን ፣ከሠገን ፣ከምዕራብ አባያ ከነዚህ ከአራቱ ወረዳ ቤተ ክህነቶች ሚዲያ ቀጥሎ በአምስተኛነት ከተከፈቱት ሚዲያዎች አንዱ ነው።

የዳራማሎ ወረዳ ቤተክህነት ይፋ ባደረገው መልዕክት፣ ምዕመናን አዲሱን የፌስቡክ ገጽ like፣ share እና follow በማድረግ ድጋፋቸውን እንዲሰጡ "በእግዚአብሔር ስም" ጥሪ አቅርቧል።

ይህ ሚዲያ በሀገረ ስብከቱ መመሪያ ሰጪነት በምዕራብ አባያ ወረዳ ቤተ ክህነት እውቅናና ፍቃድ የተከፈተ በመሆኑ፣ ምዕመናን የሚዲያው ተከታይ እንዲሆኑ እና እንዲያግዙም በአክብሮት ጥሪያችንን እናቀርባለን።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=61582382014530

17/10/2025

"መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ" የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ፀሐፊበገረሴ ዳምብሌ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ላይ ተገኝተው የሰጡት ቃለ ወንጌልና ቡራኬ

17/10/2025

የገረሴ ዳምብሌ ኦሳ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በላያቸው ላይ አድሮ በርካታ ገቢረ ተአምራት እያደረገላቸው ለብዙዎች ፈውስ ምክን...

16/10/2025

ከጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የተሰጠ የሀዘን መግለጫ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ጥቅምት ፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ አንቀላፍተው ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን። ኢየሱስ እንደ ሞተና እንደ ተነሣ ካመንን፥ እንዲሁም በኢየሱስ ያንቀላፉቱን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ያመጣቸዋልና። 1ኛ ተሰሎንቄ 4:13-14፦

የአርባ ምንጭ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል እና ደብረ መንክራት ቅዱስ ሚካኤል የሁለቱ አድባራት የዓለመ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ የነበረችው ወለተ ማርያም በዓለም ስሟ (ወ/ሪት ገነት ወንድሙ) በገጠማት ድንገተኛ ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እንገልጻለን።

ይህን አሳዛኝ ዕረፍተ ዜና ከሰማንበት ሰዓት ጀምሮ ልባችን ክፉኛ አዝኗል። እግዚአብሔር አምላክ የልጃችን ነፍስ በአብርሃም፣ በይስሐቅ እና በያዕቆብ አቅፍ በብርሃን ቦታ እንድታርፍ፣ጠ የምሕረትና የይቅርታ ባለቤት የሆነው አምላክ መንግሥተ ሰማያትን እንዲያወርሳት እየተመኘን እንጸልያለን።

ይህ ድንገተኛ ህልፈት ባስከተለው ከባድ ሐዘን ምክንያት፣ ለቤተሰቦቿ፣ ለወዳጅ ዘመዶቿ፣ እንዲሁም ለመላው የቅዱስ ገብርኤል እና የቅዱስ ሚካኤል አድባራት ማኅበረ ምእመናን ወምዕመናት መጽናናቱንና ኃይሉን እግዚአብሔር እንዲያድልልን እንለምናለን።

በተፈጠረው ድንገተኛ ህልፈት በሀገረ ስብከታችን ጽ/ቤት እና በምእመናን ስም የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን ለመግለጽ እንወዳለን።

የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት

እግዚአብሔር ነፍሷን በዕቅፉ ያኑር!

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ያግኙን፤

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

https://www.facebook.com/profile.ph

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/gamoazhsi

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.com/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/gamoha

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/.akababiw

16/10/2025
01/10/2025

ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የጋሞና አካባቢው የጎፋና ባስኬቶ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ለግንባታ የተሠራ ርብራብ እንጨት ተደርሞሶ ሕይወታቸውን ባጡ እና ጉዳት በደረሰባቸው ወገኖቻችን የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ገልጸው ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው ኢትዮጵያውያን መጽናናትን ተመኝተዋል።

የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሚዲያ - Gamo and surrounding zones diocese media

Address

Arba Minch
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Asteryo Media Media - አስተርዮ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Asteryo Media Media - አስተርዮ ሚዲያ:

Share