18/02/2026
👉👉👉
የነገዋን ተምሳሌት ሀገር በምርጫችን እንገነባለን!
ኢትዮጵያ የታላቅነት ታሪክ ያላት ብቻ ሳትሆን፣ የወደፊት ብሩህ ተስፋ ሰንቃ የምትጓዝ የሁላችንም ኩራት ናት። የብልፅግና እሳቤ ሀገራችንን በኢኮኖሚ የፈጠነች፣ በፖለቲካ የዳበረችና በዜጎቿ ሁለንተናዊ ክብር የታጀበች ተምሳሌት ለማድረግ ሌት ተቀን እየሰራ ይገኛል። ይህ ጉዞ ትላንትን ዛሬ ላይ እያከመ፣ ዛሬን ደግሞ ለነገዋ ጠንካራ ኢትዮጵያ መሰረት እየጣለ ያለ የለውጥ ጎዳና ነው።
መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የዴሞክራሲ ስርዓታችንን የምናፀናበትና የኢትዮጵያን የነገ እጣ ፈንታ በገዛ እጃችን የምንወስንበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው። በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው ይህ የለውጥ ጉዞ፣ በምርጫው በሚገኝ የህዝብ ውክልና ይበልጥ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። ድምፃችን ለቀጣይነት፣ ለልማትና ለሰላም የሚሰጥ ዋስትና በመሆኑ፣ በንቃት መሳተፋችን ለሀገራዊ ህልማችን መሳካት ቁልፍ ሚና ይጫወታል።
የነገዋ ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ፣ በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ተምሳሌትና የቴክኖሎጂ ማዕከል የመሆን ግብ አላት። በብልፅግና እሳቤ ውስጥ የሚገኙት ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስራዎች ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ምዕራፍ እያሸጋገሩ ይገኛሉ። ይህ የጋራ እይታችን የታላቅነታችን ማረጋገጫ ሆኖ ይቀጥላል።
ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገርነት የምናደርገው ጉዞ የተባበረ ክንድና የጋራ ራዕይን ይጠይቃል። በመጪው ምርጫ የምናሳየው ዲሞክራሲያዊ ጨዋነትና ለብልፅግና የምንሰጠው ድጋፍ ለልጆቻችን የምናወርሳትን የበለፀገች ሀገር እውን ያደርጋታል። ነገ ዛሬ ላይ ይገነባል፤ ኢትዮጵያም በልጆቿ ጥረትና በብልፅግና ጎዳና ወደ ከፍታ መውጣቷ አይቀሬ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በብልፅግና ፓርቲ መሪነት እውን ይሆናል።
የካቲት 11/2018 ዓ.ም
ዎምባ