Gamo tv

Gamo tv ይህ የጋሞ ተለቪዥን ትክክለኛ የፈስቡክ ገጽ ነው።ገጹን
ላክ፣ሸርና ኮሜንት በማድረግ፣ወቅታዊና እውነተኛ መረጃዎችን በየዕሌቱ ይከታተሉ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው ለሁሉም ክልሎች እና ለአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የመልካም ምኞት መግለ...
07/12/2024

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው ለሁሉም ክልሎች እና ለአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የመልካም ምኞት መግለጫ ስጦታ አበርክተዋል።

አርባምንጭ፤ ህዳር 28/2017 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)

በመድረኩ ላይ የአርባምንጭ ከተማ ከንቲባ አቶ ገዛኸኝ ጋሞ ወደ እንግዳ ተቀባይዋና ውቧ ከተማ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ከተማዋን ለነዋሪዎች ሳቢና ምቹ ለማድረግ የኮሪደር ልማትና ሌሎችም የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ምሽቱ በብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች የተለያዩ ሙዚቃዎች የደመቀ ሲሆን የእራት ፕሮግራምና የሙዚቃ ዝግጅቱ እንደቀጠለ ነው።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ በተገኙበት የብልፅግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምስረታ በዓል በአርባምንጭ ማዕከል በመከበር ላይ ይገኛል።አርባምንጭ ፣ኅዳር ...
26/11/2024

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ በተገኙበት የብልፅግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምስረታ በዓል በአርባምንጭ ማዕከል በመከበር ላይ ይገኛል።

አርባምንጭ ፣ኅዳር 17 I 2017 ዓ.ም (ጋሞ ቴቪ)

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ በተገኙበት የብልፅግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምስረታ በዓል "በህብር ወደ ኢትዮጵያ ልዕልና" በሚል መሪ ቃል በአርባምንጭ ማዕከል በመከበር ላይ ይገኛል።

በመረሀ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ በዓሉን ስናከብር ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክረን ለማስቀጠልና ጉድለቶችን ለማረም አመራሩ እና አባሉ ቃል በመግባት መሆን እንዳለበት አሳስበዋል።

ፓርቲው ዋልታ ረገጥነትን በማስወገድ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን በማስፈን በመደመር መንገድ የጀመረውን ጉዞ አጠናክሮ ሀገሪቱን ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማድረስ እየተጋ እንደሚገኝም ወ/ሮ ፀሐይ ገልጸዋል።

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይነህ አበራ በበኩላቸው ፓርቲው በሀገሪቱ ታሪክ ፍጹም ዴሞክራሲያዊ ምርጫ አካሂዶ በአብላጫ ድምጽ ሥልጣን ከያዘ በኋላ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነትና በጥራት በመጨረስ የተለያዩ ስኬቶችን ማስመዝገቡን ገልጸዋል።

አቶ አባይነህ አክለውም ፓርቲው እንደዞናችንም በቀደሙት ጊዜያት ያልተመለሱ የተለያዩ የህዝብ ጥያቄዎችን በመመለስ ህዝባዊነቱን ማሳየቱን ገልጸዋል።

በመድረኩ የፓርቲውን የአምስት ዓመት ጉዞ የሚዳስስ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበት ታዉቋል።

መርሃ ግብሩ በተለያዩ ሁነቶች ታጅቦ እየተከበረ የሚገኝ ሲሆን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ፣ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይነህ አበራ፣ የክልል፣ የዞንና ከሁሉም መዋቅር የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ አስተዳዳሪዎች፣ ከንቲባዎች፣ ደጋፊዎች፣ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል።

አርባምንጭ ከተማ ከሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት በኋላ ድል ቀንቶታልዛሬ በ10፡00 ሰዓት ከወልዋሎ አድግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር የተገናኙት አዞዎች 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል፡፡የአርባም...
23/11/2024

አርባምንጭ ከተማ ከሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት በኋላ ድል ቀንቶታል

ዛሬ በ10፡00 ሰዓት ከወልዋሎ አድግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር የተገናኙት አዞዎች 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል፡፡

የአርባምንጭ ከተማን የማሸነፊያ ግቦችን በፍቅር ግዛው በ 22'ኛው'ደቂቃ እንድሁም አህመድ ሁሴን 49ኛው ደቂቃ ኳስን ከመረብ አገናኝተዋል፡፡

ወጣቶች አሉታዊ ተፅዕኖ ያላቸዉ  መጤ ልማዶችን  በመተዉ ለሰላም  ዘብ መቆም እንዳለባቸው ተጠቆመ።አርባ ምንጭ ፤ ህዳር 13/2016 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን )የጋሞ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪ...
22/11/2024

ወጣቶች አሉታዊ ተፅዕኖ ያላቸዉ መጤ ልማዶችን በመተዉ ለሰላም ዘብ መቆም እንዳለባቸው ተጠቆመ።

አርባ ምንጭ ፤ ህዳር 13/2016 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን )

የጋሞ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ አሉታዊ ተፅዕኖ ያላቸዉ መጤ ልማዶችን ለመከላከል ዓላማ ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል ።

የመምሪያው ምክትል ኃላፊ አቶ ደረጀ ጳውሎስ መድረኩ አሉታዊ ተፅዕኖ ያላቸዉ መጤ ልማዶችን ለመከላከል ዓላማ ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሆኑን አስገንዝበዋል።

ወጣቱን ወደ ጥፋት የሚመሩ አደንዛዥ እፆችን ማምረት ፣ መነገድ ይሁን መጠቀም በወንጀል እንደሚያስጠይቅ ተጠቁሟል ።

ለሀገር እድገትና ብልጽግና የወጣቱ ሚና በተመለከተ በመድረኩ ተብራርቷል ።

በኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ አገአሁ ተሻገር የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገባ።አርባምንጭ፤ ህዳር 12/03/2017 ዓ.ም(ጋሞ ቴለቪዥን ) የ...
21/11/2024

በኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ አገአሁ ተሻገር የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገባ።

አርባምንጭ፤ ህዳር 12/03/2017 ዓ.ም(ጋሞ ቴለቪዥን )

የልዑክ ቡድኑ አባላት አርባምንጭ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በጋሞ ዞንና በአርባምንጭ ከተማ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ አባይነህ አበራን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎችና በጋሞ አባቶች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።

እንግዶቹ በአርባምንጭ ቆይታቸውም ለ19ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓል የተከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ብሎም እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎችን ይቃኛሉ።

ከአብይ ኮሚቴዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የስራ ውይይትና ግምገማ እንደሚያደርጉና የልማት ስራዎችንና የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎችን እንደሚጎበኙም ይጠበቃል።

በክልሉ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የወጪና ገቢ ኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ገለፀ።አር...
19/11/2024

በክልሉ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የወጪና ገቢ ኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ገለፀ።

አርባምንጭ፥ ህዳር 10/2017ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን )

"ኮንትሮባንድና ህገ- ወጥ ንግድን ለመከላከል እና የኤክስፖርት ምርት ማነቆዎችን ለመፍታት በጋራ እንረባረባለን!!" በሚል መሪ ሃሳብ የንቅናቄ መድረክ በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ጤናማ የገበያ ስርዓት ለሀገር ሉዓላዊነት ቁልፍ መሆኑን አመላክተዋል።

ህገ - ወጥ የነዳጅ ግብይት የኑሮ ውድነትን እያባባሰ ነው ያሉት አቶ ገብረመስቀል ግብረ-ሀይሉ ለጉዳዮ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ኮንትሮባንድ የንግድ ስርዓትን የሚያዛባና የውጪ ምንዛሪን የሚያሳጣ በመሆኑ ቅንጅታዊ አሰራር አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ገለቦ ጎልቶሞ ክልሉ ዘርፈ ብዙ አምራች መሆኑን ጠቁመው የሀገር ውስጥ ምርትን ማበረታት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በ2016 በጀት ከክልሉ ከተላኩ ምርቶች ከ53 ሚሊዮን ዶላር በላይ መገኘቱን ጠቅሰዉ ይህንን ይበልጥ ለማሳደግ ኮንትሮባንድ ተግዳሮት መሆኑንም ገልፀዋል።

በክልሉ ከፍተኛ የወጪና የገቢ ኮንትሮባንድ ዝውውር መስተዋሉን የገለፁት አቶ ገለቦ ከ972 ሚሊዮን 770 ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው እቃዎች ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል ።

የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ፍሬዘር ኦርካይዶ የኮንትሮባንድ ንግድ ከኢኮኖሚ ችግር ባሻገር በክልሉ እና በሀገር ደረጃ የሚያስከትለው ስጋት ከፍተኛ በመሆኑ ችግሩን ለመቅረፍ መርሃ-ግብሩ ወሳኝ ነው ብለዋል።

በኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድን መከላከል እና ወደ ውጪ በሚላኩ ምርቶች ዙሪያ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግ ተመላክቷል።

በመርሃ-ግብሩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ገብረ መስቀል ጫላን ጨምሮ የፌደራል፣ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የፀጥታ ዘርፍና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

Dugeha Tophphiya kilile payyateththa biiron  HIV Eedisenne hepitaytese  harge teqonne naago mac'aray 2016 bajete laytha ...
19/11/2024

Dugeha Tophphiya kilile payyateththa biiron HIV Eedisenne hepitaytese harge teqonne naago mac'aray 2016 bajete laytha ootho polonne oyqettida bajete laytha heedzdzu aginata halcho polo mixxi xeelo duulata Arba Minc'e kataman oothettishe dees.

Gaammo Arba Minc'e :Balbala 9/2017M.L( Gaammo Telebizhine)

Dugeha Tophphiya kilile payyateththa biiro kaalo kaappo Daanna Gaashsha Maatoosay duulatan beettidi hashshu saro yideta kiita aaththida gidishin, Eedise hargey salo sa'a deththan benippe doommidi haysa gaththo dereteththa kifileta shempo dhaysishe dizaysa yootida.

Tophphiyanka hargezi mala, zereththanne qoommo shaakkenna dalga gidida muruutancha gadaaddeta worshe dizaysi qasse ikkonoome , polettikaninne dereteththa bolla wolqama naaqo gaththishe dees gida.

Dugeha Tophphiya kililen ubba zonetankka qeeri naytaninne mac'c'ata bolla hargey dalga qoha gaththishe dizaysa yootidi, issi laytha giddon undena gidiza gadaaddeti hargen oyqettizaysanne delga asay qasse hargezan hayqizayasa malatida.

Duulatazan kililenne zoone dhoqqa kaappoti, payyateththa mac'ara kaappotinne oothanchati beettida.

በክልሉ አሪ ዞን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወነ የሚገኘው የልማት ተግባር የሚበረታታ እንደሆነ ተገለፀ።በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚዲያ ቱር እያደረገ የሚገኘው ልዑክ በኦሪ ዞ...
16/11/2024

በክልሉ አሪ ዞን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወነ የሚገኘው የልማት ተግባር የሚበረታታ እንደሆነ ተገለፀ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚዲያ ቱር እያደረገ የሚገኘው ልዑክ በኦሪ ዞን በጥላ ማኑፋክቸሪንግ አክስዮን ማህበር የበቆሎ ምርጥ ማባዣ ጣቢያንና የኮሪደር ልማትን ጎብኝቷል።

አርባምንጭ፥ ህዳር 06/2017 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)፦

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ አዜብ ዘውዴ የበርካታ ብሄረሰቦች መኖሪያ የሆነው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘርፈ ብዙ የልማት ስራ የሚሆን አመቺ ስነምህዳርና አየር ንብርት መታደሉን ገልፀዋል።

በክልሉ በሁሉም የልማት ዘርፎች የወጣቶችን ተሣትፎ በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወነው ተግባር አበረታች ለውጥ መታየቱንም አብራርተዋል።

በክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሣደግ በተሰጠው ትኩረት አመርቂ ውጤት እየታየ መገኘቱን ያስታወቁት ወ/ሮ አዜብ፤ የኣሪ ዞኑ መልካም ተሞክሮን ለአብነት አንስተዋል።

ክልሉ ለጠለቀ ማህበራዊ መስተጋብር መሠረት የሆኑ ማህበራዊና ባህላዊ እሴቶች ባለቤት መሆኑን ያስገነዘቡት ወ/ሮ አዜብ፤ የክልሉን እምቅ የተፈጥሮ ፀጋ በማልማት የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ቁርጠኝነትን ይጠይቃል ብለዋል።

የኣሪ ዞን የሚታወቀው በኮረሪማ ምርት እና ምርጥ ዘር አቅርቦት መሆኑን ያስታወቁት ወ/ሮ አዜብ፤ በየአካባቢው የሌማት ትሩፋትን በማጎለበት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር የገበያ ተኮር ግብርና ምርትን ማሣደግ የተቀናጀ ርብርብ እንደሚጠይቅ ተናግረዋል።

የኣሪ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አጣ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል በብዝሀ ባህልና ማህበራዊ እሴት የደመቀውን የዞኑን ህዝብ ያልተዳሰሰውን የተፈጥሮ ፀጋና ማህበራዊ ሀብት ለተቀረው ህዝብ ለማስተዋወቅ ሚናው የላቀ እንደሆነ አስገንዝበዋል።

በተለይም ከሀገራዊ ለውጥ ወዲህ የዞኑ ህዝብ የልማት ተሣትፎና ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው፤ በገጠሪቱ ዞኑ በስፋት የሚታወቀውን የቡናና ኮረሪማ ምርት ማሣደግና ከክልሉ ብዝሃ ማዕከላት መካከል አንዷ የሆነችውን የጅንካ ከተማን በህብረተሰብ ተሣትፎ በተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ ማስዋብ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

የኣሪ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታፈሰ ተስፋዬ የባካ ዳውላ ምርጥ ዘር አቅርቦት ማህበር በ15 ሄ/ር የእርሻ መሬት ምርጥ ዘር ብዜት በማከናወን ለአርሶ አደሩ እያሰራጨ መገኘቱ በዞኑ የግብርና ልማትን ከማጠናከር ረገድ የጎላ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

አቶ አውግቸው ዘውዴ የባካ ዳውላ ምርጥ ዘር ብዜት ማህበር ሰብሳቢ ሲሆኑ፤ መንግስት ያመቻቸውን የ15 ሄ/ር የእርሻ መሬት በመጠቀም በህብረተሰቡ ፍላጎት መሠረት ምርጥ ዘር እያባዙ እንደሚያሰራጩ ተናግረዋል።

19ኛውን የብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓልን አስመልክቶ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚዲያ ቱር እያደረጉ የሚገኙ ባለሙያዎች በአርባምንጭ ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ተግባራትን ጎብኝተዋል።...
14/11/2024

19ኛውን የብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓልን አስመልክቶ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚዲያ ቱር እያደረጉ የሚገኙ ባለሙያዎች በአርባምንጭ ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ተግባራትን ጎብኝተዋል።

አርባምንጭ፥ ህዳር 5/2017 ዓ/ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)፦

ልዑካኑ በአርባምንጭ ከተማ የሚገኘውን ቤሬ የሐር ጥጥ ልማት ፕሮጀክቶችን የጎበኙ ሲሆን ፕሮጀክቱ በሀገር ደረጃ ብቸኛ ሲሆን አሁን ላይ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ እንደሚገኝም የድርጅቱ ባለቤት አቶ ገለታ ኃይሉ አብራርተዋል።

የሚዲያ ልዑካኑ በጋሞ ልማት ማህበር በ705 ሄክታር ማሳ በተቀናጀ ግብርና እየለማ የሚገኘውን የአዝርዕትና ሆሊቲ ካልቸር ሰብል ተመልክተዋል።

ልማት ማህበሩ ከግብርና ስራ ባሻገር በእንስሳት ልማት፣ በአዞ ራንች፣ በጋራዥ አልግሎት እና በማይክሮ ፋይናንስ እንዲሁም በኮንስትራክሽን ዘርፍ በርካታ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝ በልማት ማህበሩ የሰው ሀብት ልማት አስተዳዳሪ አቶ ካተኔ ካውሌ ገልፀዋል።

ልማት ማህበሩ የሚያመርታቸውን የሰብል እና የፍራፍሬ ምርትን ለማዕከላዊ ገበያ እያቀረበ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።

ልኡካኑ የግል ባለሀብት የሆኑት ወ/ሮ የአይን አበባ አስፋው በ6 ወራት ውስጥ ያለሙትን የአትክልትና ፍራፍሬ ማሳ ጎብኝተዋል።

ባለሀብቷ ከዚህ ቀደም የግለሰብ ማሳ ተከራይተው ሲሰሩ የነበረ ቢሆንም ውጤታማነታቸውን የተመለከተው የጋሞ ዞን አስተዳደር በኢንቨስትመንት 10 ሄክታር ማሳ እንደሰጠቻው ገልፀው፤ አሁን ላይ ለ62 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል እንደፈጠሩ ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን ክልሉን የሰላም የመቻቻልና የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አስገንዝበው፤ የጉብኝቱ ዓላማ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወነ ያለውን ለማመላከት ነው ብለዋል።

እንደ ሀገር ከተረጂነት ለመላቀቅ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ በክልሉ በሁሉም የልማት ዘርፎች ለማጠናከር በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ኃላፊዋ አብራርተዋል።

በክልሉ መላውን ህብረተሰቡ በማስተባበር ሁለንተናዊ ለውጥ ለማምጣት በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

የጋሞ ልማት ማህበር የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ የሚበረታታ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ማህበሩ ለአርሶ አደሩ ምርጥ ዘር ከማቅረብ ባሻገር የገበያ ትስስር እየፈጠረ መገኘቱ በይበልጥ መጎለበት የሚገባ ተግባር እንደሆነም ገልፀዋል።

የአርባምንጭ አለም አቀፍ ስቴድየም ግንባታ 40 በመቶ ደረሰለስቴድየሙ ግንባታ ገቢ የማሰባሰብ ስራን የሚሰራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ ለመግባት በዛሬው እለት የመግባቢያ ሰነድ ተፈርሟል።በካፍ ስ...
12/11/2024

የአርባምንጭ አለም አቀፍ ስቴድየም ግንባታ 40 በመቶ ደረሰ

ለስቴድየሙ ግንባታ ገቢ የማሰባሰብ ስራን የሚሰራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ ለመግባት በዛሬው እለት የመግባቢያ ሰነድ ተፈርሟል።

በካፍ ስታንዳርድ እየተገነባ የሚገኘው 3 ቢሊየን ብር ወጪ የተመደበለት የአርባምንጭ አለም አቀፍ ስቴድየም ግንባታ 40 በመቶ መድረሱ ተገልጿል።

ስቴድየሙ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ እስከ 30ሺ ሰው የመያዝ አቅም እንዳለው የተገለፀ ሲሆን የፊፋ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ፣ የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታዎችን ፣ የካፍ ልዩ ልዩ ውድድሮች ፣ የቻን ውድድር እንዲሁም የኢትዮጵያ ሊጎችን እንደሚያስተናግድም ተነግሯል።

ይህ በካፍ ስታንዳርድ እየተገነባ እንደሚገኝ የተገለፀው የአርባምንጭ አለም አቀፍ ስቴድየም ባሳለፍነው አመት ሀምሌ ወር ላይ እንደተጀመረ የተገለፀ ሲሆን በቀጣይ አንድ አመት ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት ይሰጣል ተብሏል።

ለስቴድየሙ ግንባታ ገቢ የማሰባሰብ ስራን የሚሰራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ ለመግባት በዛሬው እለት የመግባቢያ ሰነድ ተፈርሟል።

ስቴድየሙ በውስጡ ለሚድያ አጋዥ አገልግሎቶች የሚውሉ መለማመጃ ሜዳ ፣ 12 የተጫዋቾችና የሚዲያ ታናሎች ፣ ፓርኪንግ ፣ ኢንዶር ጌሞች ፣ መልበሻ ክፍሎች ፣ ቢሮዎች እና መስብስቢያ አዳራሾች ፣ ዶፕንግ መቆጣጥሪያ ክፍሎች ፣ መጫወቻ ሜዳ፣ መሮጫ ትራክ እና ማሟሟቅያ ስፖርት ፊልድ ፣ ሼድ ያላቸው መቀመጫዎች፣ የህዝብ መገልገያዎች፣ መፀዳጃዎች፣ ህክምና ማዕከል፣ ግዙፍ ስክሪን ፣
የደህንነት መቆጣጠሪያ መሳሪያዎች እና ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን ያሟላ እንደሆነ ተነግሯል።
via: South Ethiopia Regional State Office Of The President

ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የ7 መቶ 38 ሚሊዮን ዶላር ብድር አጸደቀች የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ኛው መደበኛ ስብሰባ የደቡብ ሱዳን የብድር ጥያቄ ተቀብሎ አጽድቋል፡፡ምክር ቤቱ...
05/11/2024

ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የ7 መቶ 38 ሚሊዮን ዶላር ብድር አጸደቀች

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ኛው መደበኛ ስብሰባ የደቡብ ሱዳን የብድር ጥያቄ ተቀብሎ አጽድቋል፡፡

ምክር ቤቱ 738 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር ብድር ስምምት ያጸደቀ ሲሆን ብድሩ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳንን ለማስተሳሰር የሚረዳ 220 ኪሎ ሜትር ለመንገድ ግንባታ የሚውል መሆኑ ተመላክቷል።

የብድር ስምምነቱ የአምስት አመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ10 ዓመት የሚመለስ ሲሆን ብድሩ የሚመለሰው በካሽ ወይም እስከ ፖርት ሱዳን ድረስ በሚቀርብ ድፍድፍ ነዳጅ እንደሆነ ተገልጿል።

የደቡብ ሱዳን ብሔራዊ የሽግግር ህግ አውጪ ምክር ቤት የገንዘብ ስምምነቱን በሰኔ ወር 2016 አጽድቆ የነበረ ሲሆን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስቴር በወቅቱ፤ የመንገድ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን መካከል እያደገ ያለውን ትብብር እና የጋራ ተጠቃሚነት ግንኙነት የሚያሳይና የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነትን ለማጠናከር ያለመ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የብድር ስምምነት የተፈራረሙት እ.ኤ.አ በግንቦት ወር 2023 ለድንበር ተሸጋሪ መንገድ ግንባታ ይውላል በሚል እንደነበር ይታወሳል፡፡


Address

Gamo
Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo tv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share