24/07/2026
ክልሉ በበጀት ዓመቱ 13 ሚሊዮን የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ጎበኙ ።
አርባ ምንጭ ፡ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም (ጋሞ ቴቪ)
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባኤ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የክልሉን መንግስት የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም ሪፖርት በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ጥላሁን ከበደ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ ከሀገር ውስጥና ጎብኚ 978 ሚሊዮን ገቢ የተገኘ ሲሆን አፈፃፀሙን ከ100% በላይ ማሳደግ ተችሏል።
የማዜና የማጎ ብሔራዊ ፓርኮችን ህልውና ለማስጠበቅ በኃይለማሪያምና ሮማን ፋውንዴሽን እንዲሁም በዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በተደረገ የ3 ሚሊዮን ብር በጀት ድጋፍ በጎፋና አሪ ዞኖች ለ330 የህግ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል ብለዋል።
አክለውም በጥበቃ ረገድም 1 ሺህ 765 ነጥብ 36 ሺህ ሰዓት (82%) ሰዓት ተኮር ቁጥጥር የተደረገ ሲሆን፤ ህገ-ወጥ ተግባራትን በ55% መቀነስ እና ከህገ-ወጥ ድርጊት ነፃ የሆነ የፓርኮች ሽፋን 60% በማድረስ ውጤታማ ሥራ ተከናውኗል ነው ያሉት።
በተጨማሪም 12 የሰፈራና እርሻ ሥራ ቅኝቶች የተካሄዱ ሲሆን፤ በዱር እንስሳትና መኖሪያቸው ላይ የሚደርሱ አደጋዎችንና ግጭቶችን የመከላከል ዝግጁነትን 40% ማሳደግ ተችሏል።
የዱር እንስሳት ጤና ክትትል 11 ዙር እና የመጨ አረም ቁጥጥር 4 ጊዜ ለማካሄድ ታቅዶ ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ ማከናወን የተቻለ ሲሆን፤ በዚህም የጥበቃ ቦታዎች ሽፋኑን 47.5% እንዲሁም ያገገሙ የዱር እንስሳት መኖሪያዎች ሽፋኑ 40% ላይ ደርሰዋል።
በይመኙሻል ዮሴፍ