GAMO TV

GAMO TV ይህ የጋሞ ቴሌቪዥን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ፣ ሼርና ኮሜንት በማድረግ ወቅታዊና እውነተኛ መረጃዎችን በየዕለቱ ይከታተሉ!
(1)

የኮሪደር ልማት አካል የሆነው ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራት ዝርጋታ በአርባምንጭ ከተማ በከፊል
29/05/2026

የኮሪደር ልማት አካል የሆነው ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራት ዝርጋታ በአርባምንጭ ከተማ በከፊል

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በአርባ ምንጭ ከተማ በአባያ ሐይቅ የሞጨ ደሴትን ጎበኙ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በክልሉ በጋሞ ዞን በአርባ ምንጭ ከተማ በጋሞ ልማት ማህበር በመልማት ላ...
29/05/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በአርባ ምንጭ ከተማ በአባያ ሐይቅ የሞጨ ደሴትን ጎበኙ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በክልሉ በጋሞ ዞን በአርባ ምንጭ ከተማ በጋሞ ልማት ማህበር በመልማት ላይ ከሚገኙ አዳዲስ የቱሪስ መዳረሻዎች እጅግ ውብና ማራኪ የሆነውን በአባያ ሐይቅ የሞጨ ደሴት ጎብኝተዋል፡፡

በአባያ ሐይቅ ላይ ከሚገኙ 11 ደሴቶች አንዷ የሆነችው ሞጨ ደሴት፤ እጅግ ማራኪ የሆነ ገፅታን የታላበሰችና ድንቅ ተፈጥሮን የታደለች ሲሆን፣ ጎብኝዎች በደሴቷ እጀግ ውብ መልክዓምድርን ከዱር እንስሳት ሀብት፤ ከጀልባ ላይ ሽርሽር እና ከድንቅ የባህል ተሞክሮ ጋር በጣምራ የሚያገኙ መሆኑ ቆይታቸውን እጅግ አስደሳችና አይረስ ያደርገዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ጎብኚዎች በደሴቷ በሚያደርጉት ቆይታ በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የሆነውን የአርባ ምንጭ አዞ ራንች የሞጎብኘት ድርብ ዕድል የሚያገኙበት ድንቅ የቱሪስት መዳረሻ ነው፡፡

የጋሞ ልማት ማህበር የአባያና የጫሞ ሐይቆች የተፈጥሮ ፀጋ ለቱሪዝም ልማት ለማዋል በስፋት እየሰራ ሲሆን፤ ወደ ሞጨ ደሴት የሚደረገውን ጉዞ ዘመናዊና ምቹ ለማድረግ “ባይራ 2018” የተሰኘች ዘመናዊ ጀልባ ወደ ስራ ማስገባቱ ታውቋል።

የክልሉ መንግስት ለቱሪዝም ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት አዳዲስ የቱሪዝም መስህብ ስፍራዎችን የመለየት እና የማልማት እንዲሁም የቱሪስት መዳረሻ ስፋራዎች የማስፋት ስራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ ሲሆን፤ በዘርፉ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በእጅጉ ያበረታታል፡፡

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

29/05/2026

C'iishshata giigiso Qeera gallassi wontappe 3:00 saaten ubba wode kaallite!

29/05/2026

የመስህብ ቅኝት በቅዳሜ መዝናኛ ይጠብቁን

ወጣቱ በአካለና በአዕምሮ ብቁ ሆኖ እንዲያድግ የስፖርታዊ ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንባታቸው ለስፖርቱ እድገት አስፈላጊ መሆናቸው ተጠቆመአርባምንጭ : ግንቦት 21 / 2018 ዓ.ም. (ጋሞ ቴቪ)...
29/05/2026

ወጣቱ በአካለና በአዕምሮ ብቁ ሆኖ እንዲያድግ የስፖርታዊ ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንባታቸው ለስፖርቱ እድገት አስፈላጊ መሆናቸው ተጠቆመ

አርባምንጭ : ግንቦት 21 / 2018 ዓ.ም. (ጋሞ ቴቪ)

በአርባምንጭ ከተማ የኮሪዴር ልማት አካል የሆኑ ስፖርታዊ ማዘውተሪያ ስፍራዎች በከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት እየተገነቡ ይገኛሉ

አስተያየታቸውን ለጋሞ ቴሌቪዥን የሰጡት የአርባምንጭ ከተማ ባህልና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጻራ ወጣች በአካልና በአዕምሮ ብቁ ሆነው እንዲያድጉ የስፖርታዊ ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

በአሁኑ ሰዓት ወጣቱ የማህበራዊ ሚዲያ ጥገኛ ከመሆን ወጥተው ስፖርት በመስራት ጤናውን ጠብቆ ጊዜውን አልባለ ቦታ ከማሳለፍ እንድቆጠቡ እንደሚረዳም ተናግረዋል።

በከተማው በርካታ የእግር ኳስ ተጫዋቾች የሚፈልቁት መሰል ስፖርታዊ ማዘውተሪያዎች በአግባቡ ባልበጁበት አቧራማና ጠጠር ሜዳዎች እንደነበር የሚያስታውሱት የጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ አሰልጣኝ ማቴዎስ ለማ እየተገነቡ የሚገኙ ማዘውተሪያ ስፍራዎች ለከተማው ወጣቶች ተስፋን የሚሰጥ እንደሆነ ገልፀዋል።

የአርባምንጭ ከተማ በሁሉም አቅጣጫ በከፍተኛ ሁኔታ እየለማች ትገኛለች የምትለው የቀድሞ የአርባምንጭ ከተማ ተጫዋች ምስር ላቀው ነች።

የከተማዋ ሁለንተናዊ እድገት አግራሞት እንደፈጠረባት ገልፃ ሁሉን ያማከለ እጅግ ዘመናዊ ማዘውተሪያ ስፍራዎች በከተማዋ ሁሉም ስፍራዎች መገንባታቸው ለእግር ኳሱ እድገት ጉልህ አስተዋፆ እንዳለው ትናገራለች ።

የከተማው የቀድሞ ተጫዋቾች በበኩላቸው የማዘውተሪያዎቹ መገንባታ ለወጣቱ ትውልድ ብሩህ ተስፋን ይዞ የመጣ መሆኑን ገልፀዋል።

የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎችም በስፖርታዊ ማዘውተሪያዎች መገንባት የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።

ሴቶችን ያላካተተ ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ውጤታማ ሊሆን አይችልም -  ዶ/ር ባይሳ ፈዬአርባ ምንጭ :- ግንቦት 21 / 2018 ዓ.ም. (ጋሞ ቴሌቪዥን)  የጋሞ ልማት ማህበ...
29/05/2026

ሴቶችን ያላካተተ ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ውጤታማ ሊሆን አይችልም - ዶ/ር ባይሳ ፈዬ

አርባ ምንጭ :- ግንቦት 21 / 2018 ዓ.ም. (ጋሞ ቴሌቪዥን)

የጋሞ ልማት ማህበር IDH ከተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ዓለም አቀፍ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የስርዓተ ፆታ አካቶ ስልጠና ተጠናቋል።

ስልጠናውን የሰጡት የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሶሻል አንትሮፖሎጂ መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር ባይሳ ፈዬ
ሴቶችን ያላካተተ ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በአንድ እጅ እንደማጨብጨብ ነው
ብለዋል።

ዶ/ር ፈይሳ አክለውም ሴቶች ባሉበት ቦታ እውቀት ላይ የተመሠረተ አበርክቶ እንዲያደርጉ ለማድረግ የፆታ እኩልነት ማሳደግ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።

የተሰጠው ስልጠና በተሰማሩበት የሙያ መስክ የሚፈልጉትን ጠይቀው እንዲያገኙ የሚያስችላቸው መሆኑን ገልፀዋል።

ስልጠናው ሴቶች በራስ የመተማመን ደረጃቸው ከፍ እንዲል ብሎም በኢኮኖሚ ብቁ እንዲሆኑ ለማስቻል ያለመ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሺዮሎጂና ሶሻል አንትሮፖሎጂ መምህርት ባንቺደሩ አወል በበኩላቸው ሴቶች ስለስርዓተ ፆታና ስለእኩልነት በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው በማድረግ ብቁ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ከፍ ማድረግ የሁሉም አካላት ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የጋሞ ልማት ማህበር የፕሮግራምና ፕላን ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምሰገድ ሉቃስ የስርዓተ ፆታ ጉዳዮችን የተቋሙ ስትራቴጂክ እቅድ አካል በማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

አክለውም ስርአተ ፆታን በሁሉም ፕሮግራሞች እና ፕላን ውስጥ ማካተት ለውጤታማነት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።

IDH በዞኑ በርካታ የልማት ተግባራትን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን በተለይ በግብርናው ዘርፍ ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት የአፍሪካ ስርዓተምግብን ለመቀየር አንግቦ እየሰራ ያለ ድርጅት መሆኑን የምትናገረው IDH ዓለማቀፍ ግብረሰናይ ድርጅት ወይዘሪት እንቁ ገላነህ ናት።

የምርጥ ዘር ብዜት በማስፋፋት የአርሶ አደሩ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምርና በኢኮኖሚ ራሱን እንዲችል ከማድረግ በተጓዳኛ የግብርናው ጀርባ አጥንት የሆኑት ሴቶችን በማሳተፍ እየሰራ እንደሆነ ጠቁመዋል።

በስልጠናው ከጋሞ ዞንና አርባ ምንጭ ከተማ ሰቶችና ህጻናት መምሪያ፣ የዞኑ የስራ ዕድል ፈጠራ መምሪያ የዞኑ ግብርና መምሪያ፣ እንዲሁም የጋሞ ልማት ማህበር ሴት ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

29/05/2026

በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የአርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለዜጎች ፈጣንና ጥራት ያለው አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ተገለፀ

ድንገተኛ የተፈጥሮ አደጋዎችን በዘላቂነት ለመቀነስ፣ ሳይንሳዊ የመከላከል ዘዴዎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ተገለፀ ።አርባምንጭ፦ ግንቦት 21/2018ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)የደቡብ ኢትዮጵያ...
29/05/2026

ድንገተኛ የተፈጥሮ አደጋዎችን በዘላቂነት ለመቀነስ፣ ሳይንሳዊ የመከላከል ዘዴዎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ተገለፀ ።

አርባምንጭ፦ ግንቦት 21/2018ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ከተለያዩ ዞኖች፣ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ለተውጣጡ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ባለሙያዎች በአርባምንጭ ከተማ ስሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቅቋል ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ዘርፍ
ተወካይ አቶ መስፍን ባልቻ በማጠቃለያው በአሁኑ ወቅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለምን እየተፈተነ መሆኑን አስገንዝበዋል ።

በተለይ ባለፉት ሶስት ዓመታት የአየር ንብረት ለውጥ
በክልሉ ያሳደረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል ።

በክልሉ የሚስተዋሉ ድንገተኛ የተፈጥሮ አደጋ ስጋቶችን
በዘላቂነት ለመቀነስ፣ ሳይንሳዊ የመከላከል ዘዴዎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ገለፀዋል ።

የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራን የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚ በሚያሳድግ መልኩ መጠቀም እንደሚገባ አሳስበው
በክልሉ ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ መጠበቅና ማልማት ያስፈልጋል ብለዋል ።

በየደረጃው የሚሰሩ የተፋሰስ ልማት ስራዎች የአካባቢ ስነ-ምህዳርን መጠበቅ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ እንዲያተኩሩ አስረድተዋል ።

ሰልጣኞች ከስልጠናው ያገኙትን ክህሎት ወደ መረት በማውረድ የአርሶ አደሩን ኑሮ በዘላቂነት ከማሻሻል ረገድ የበኩላቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል ።

የተፈጥሮ ሀብትን በሳይንሳዊ መንገድ ለመጠበቅ አቅም የፈጠረላቸው መሆኑን የስልጠናው ተሳታፊዎች ገልጸዋል ።

ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጎን ለጎን የአርሶ አደሩን ገቢ ማሳደግ በሚያስችሉ አማራጮች በቂ ክህሎት ያገኙበት መሆኑንም አስረድተዋል።o

የኢትዮጵያ ስታቲስትክ አገልግሎት ለጋሞ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች ከስምንት መቶ ሺ ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገአርባምንጭ : ግንቦት 21 / 2018 ዓ.ም. (ጋሞ ...
29/05/2026

የኢትዮጵያ ስታቲስትክ አገልግሎት ለጋሞ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች ከስምንት መቶ ሺ ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

አርባምንጭ : ግንቦት 21 / 2018 ዓ.ም. (ጋሞ ቴቪ)

በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ በደረሰውየ መረት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የሚውሉ የተለያዩ የሰብዓዊ ድጋፎች ተጠናክረው ቀጥለዋል።

ድጋፉን ያስረከቡት የኢትዮጵያ ስታቲስትክ አገልግሎት የዋና ዳይረክተር ጽ/ቤት ኃላፍና አባላት ናቸው።

የኢትዮጵያ ስታቲስትክ አገልግሎት የዋና ዳይረክተር ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ አብነት ሀዋስ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት በአደጋው ተጎጂዎች ቤተሰብ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀው ከመላው የስታስቲክ ቤተሰቦች የተሰበሰበውን ከስምንት መቶ ሃያ ሁለት ሺ በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

ገንዘቡ ከደረሰው አደጋ አንፃር ለወገኖቻችን በቂ ባይሆንም ለመጀመሪያ ዙር የሚውል ድጋፍ መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይም ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተው ድጋፉ ከቀያቸዉ የተፈናቀሉትን መልሶ ለማቋቋም እንደሚውል ተናግረዋል።

በተፈጥሮ አደጋ የተፈናቀሉ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም በሚካሄዱ ቀጣይ ስራዎች ሁሉ እንደሚሳተፍ ተናግረዋል።

ድጋፉን የተረከቡት የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ ተስፋፅዮን ዘነበ ለተደረገው ሰብዓዊ ድጋፍ በጋሞ ዞን አስተዳደር ስም ልባዊ ምስጋና አቅርበው በአደጋው ከ500 በላይ አባወራዎች መፈናቀላቸውንና በርካቶችም ለህልፈት መዳረጋቸውን ተናግረዋል።

የጉዳቱ መጠንም ከፍተኛ በመሆኑ በቀጣይም ሰብዓዊ ድጋፎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን መልሰን እስክናቋቋም ድረስ እንዲሆን ጠይቀዋል።

የጋሞ የሀገር ሽማግሌዎችም ለተደረገላቸው ድጋፍ ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።

28/05/2026

በአርባምንጭ ከተማ እየተገነቡ ያሉ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በከፊል

በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የአርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለዜጎች ፈጣንና ጥራት ያለው አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ተገለፀ ።‎አርባምንጭ፡- ግንቦት 20/2018 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪ...
28/05/2026

በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የአርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለዜጎች ፈጣንና ጥራት ያለው አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ተገለፀ ።

አርባምንጭ፡- ግንቦት 20/2018 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)

ከአገልግሎት ተጠቃሚዎች መካከል አቶ ሚኪያስ ገብረ ሳሙኤል እና አቶ ታደለ ኤርሚያስ የተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ተቋሙ በአቅራቢያቸው መኖሩ ከአላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንደታደጋቸው ተናግረዋል፡፡

‎በአገልግሎቱ የአርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሹፌር ሱንኩሮ ተቋሙ ለዜጎች መደበኛና አስቸኳይ ፓስፖርት ያለምንም እንግልት እየሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል ።

‎ተቋሙ እነዚህን አገልግሎቶች በአምስት ቀናት ወስጥ ለዜጎች እንደሚሰጥ ነው ኃላፊው ያብራሩት ።

‎ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው ኢንተርኔትን በመጠቀም የተቋሙን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉበት አሰራር መዘርጋቱን አስረድተዋል፡፡





Address

Arba Mintch

Telephone

+251468812386

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when GAMO TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to GAMO TV:

Share