GAMO TV

GAMO TV ይህ የጋሞ ቴሌቪዥን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ፣ ሼርና ኮሜንት በማድረግ ወቅታዊና እውነተኛ መረጃዎችን በየዕለቱ ይከታተሉ!

በዞኑ ባህላዊ እሴቶች ሳይበረዙ ለትውልድ ለማስተላለፍ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለፀአርባ ምንጭ ፡ መስከረም 19 / 2018 ዓ.ም. (ጋሞ ቴሌቪዥን)በጋሞ ዞን ባህላዊ እሴቶችን በማልማትና በማስ...
29/09/2025

በዞኑ ባህላዊ እሴቶች ሳይበረዙ ለትውልድ ለማስተላለፍ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ

አርባ ምንጭ ፡ መስከረም 19 / 2018 ዓ.ም. (ጋሞ ቴሌቪዥን)

በጋሞ ዞን ባህላዊ እሴቶችን በማልማትና በማስተዋወቅ
ሳይበረዙ ለትውልድ እንዲተላለፉ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ደምሴ አድማሱ ገለጹ።

የጋሞ ብሄረሰብ ዘመን መለወጫ ዮ- ማስቃላ በዓል በዞኑ ካምባ ዙሪያ ወረዳ ባልታ ቀበሌ በድምቀት ተከብሯል፡፡

በበዓሉ መልዕክት ያስተላለፉት የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ደምሴ አድማሱ እንዳሉት በዞኑ የሚገኙ ባህላዊ እሴቶችን ለማልማትና ለማስተዋወቅ በትኩረት እየተሠራ ነው።

ይህ ጥረት ባህላዊ ይዘታቸው ሳይበረዝ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስችል ገልፀዋል፡፡


ከዞኑ 42 ደሬዎች አንዱ በሆነው ባልታ ቀበሌ የተከበረው የዮ ማስቃላ በዓል ህብረተሰቡ ባህሉንና ወጉን ጠብቆ በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አድምቆ ማክበሩን አስረድተዋል።

ይህም ልዩ ደስታን እንደፈጠረባቸው ዶክተር ደምሴ ተናግረዋል፡፡

አክውም በዓሉ በደመቁ ተከብሮ በሠላም እንዲጠናቀቅ ላደረጉ አካትም ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

‎የጋሞ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሀኪሜ አየለ በበኩላቸው የጋሞ ህዝብ ዘመን መለወጫ በዓል ያዘኑ የሚጽናኑበት፤ የተጣሉ የሚታረቁበትና የይቅርታ በዓል ነው ብለዋል፡፡

በዓሉም ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለእንስሳትም የጥጋብና የደስታ በዓል መሆኑን አስረድተዋል።

አባቶቻቸውን የሚሰሙና የሚያከብሩ ወጣቶች የወጡት ከመሰል በአላት መሆኑን የሚስረዱት አቶ ሀኪሜ ወጣቶች ከአባቶቻቸው የወረሱት ባህል ሳይበረዝ እንዲቀጥል የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

የጋሞ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ሞናዬ ሞሶሌ ከዮ-ማስቃላ ክዋኔዎች አንዱ የሆነው የሽማግሌዎች ምርቃት በባህሉ መሠረት ኃላፊነት በተሰጣቸው የአገር ሽማግሌ የሚከወን ሲሆን "ፑስኬ" በመባል እንደሚታወቅ ተናግረዋል።

የሶፌ ስርዓት በባልታ መስቀል ከሚዘወተሩ ክዋኔዎች መካከል አንዱ እእደሆነም ጠቅሰዋል።

በሶፌ በዓመቱ ጋብቻ የፈጸሙ ሙሽሮች በባህላዊ አልባሳት ደምቀው ከዘመድ ከጓደኞቻቸው ጋር የሚገናኙበትና ከማህበረሰቡ የሚቀላቀሉበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የጋሞ ዱቡሻና ዱቡሻ ወጋን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

በዚሁ የዮ-ማስቃላ በዓል የካባ ዙሪያ ወረዳ ባልታ ቀበሌና አካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡

"የማከም እርካታና ገንዘብ የማግኘት እርካታ ፍጹም የተለያዩ ናቸው" ዶክተር ፍጹም ጌታሁን በፈርጦች ፈለግ ክፍል ሁለት
29/09/2025

"የማከም እርካታና ገንዘብ የማግኘት እርካታ ፍጹም የተለያዩ ናቸው" ዶክተር ፍጹም ጌታሁን በፈርጦች ፈለግ ክፍል ሁለት

"የማከም እርካታና ገንዘብ የማግኘት እርካታ ፍጹም የተለያዩ ናቸው" ዶክተር ፍጹም ጌታሁን የዶክተር ፍጹም ስፔሻሊቲ ክሊኒክ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ በፈርጦች ፈለግ ክፍል ሁለት

በጋሞ ዞን በካምባ ዙሪያ ወረዳ ባልታ ቀበሌ ዮ ማስቃላ በዓል በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል፡፡አርባ ምንጭ ፡  መስከረም 18/2018ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)በየዓመቱ ባህላዊ እሴቱን በጠበ...
29/09/2025

በጋሞ ዞን በካምባ ዙሪያ ወረዳ ባልታ ቀበሌ ዮ ማስቃላ በዓል በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል፡፡

አርባ ምንጭ ፡ መስከረም 18/2018ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)

በየዓመቱ ባህላዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ የሚከበረው የጋሞ ብሄረሰብ የዮ ማስቃላ የዘመን መለወጫ በዓል በባልታ ቀበሌ ኮይራ ገበያ ላይ በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡

ዮ ማስቃላ በዓል በጋሞዎች ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠውና የህዝቡን ባህል፣ ወግ፣ እሴትና ልማድ ከፍ አድርጎ የሚያጎላ ክዋኔ ነዉ፡፡ ‎

‎ዮ...ማስቃላ ከትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣ፤ የጋሞ ህዝብ የአሮጌ ዓመት ማብቂያና ወደ አዲስ ዓመት መሸጋገርያቸውን የሚያበስሩበት ነው።

በበዓሉም የዞንና የወረዳው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የአካባቢው ተወላጆች አንዲሁም ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ አንግዶች ታድመዋል።

የጋሞ ዞን  ከፍተኛ  የመንግስትና የፓርቲ የስራ ኃላፊዎች ባልታ ገቡ‎አርባምንጭ፦ መስከረም 19/2018 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)የጋሞ ዞን  ከፍተኛ  የመንግስትና የፓርቲ የስራ ኃላፊዎች በካን...
29/09/2025

የጋሞ ዞን ከፍተኛ የመንግስትና የፓርቲ የስራ ኃላፊዎች ባልታ ገቡ

‎አርባምንጭ፦ መስከረም 19/2018 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)

የጋሞ ዞን ከፍተኛ የመንግስትና የፓርቲ የስራ ኃላፊዎች በካንባ ዙሪያ ወረዳ የሚከበረውን የዮ ማስቃላ በዓል ለመታደም ባልታ ገቡ

‎ልዑካኑ በስፍራው ሲደረሱ የካንባ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች ፣ የጋሞ አባቶች እና የአከባቢው ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የጋሞ ዞን አስተዳደር ለ4 አመት የሚቆይ የብዝሀ ሕይወት  ፕሮጀክት ስምምነት አካሄደአርባምንጭ፦ መስከረም 19/2018 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)የጋሞ ዞን አስተዳደር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደ...
29/09/2025

የጋሞ ዞን አስተዳደር ለ4 አመት የሚቆይ የብዝሀ ሕይወት ፕሮጀክት ስምምነት አካሄደ

አርባምንጭ፦ መስከረም 19/2018 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)

የጋሞ ዞን አስተዳደር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግና ለ4 አመታት የሚቆይ የብዝሀ ሕይወት ፕሮጀክት ከብዝሀ ሕይወትና የዘላቂ ልማት ኤክስፐርት ከሆኑት ከሚ/ር ፒተር ኒውሊንገር (Mr Peter Neulinger) ጋር ስምምነት ተፈራርመዋል።

ጋሞ ዞን በግብርናው እጅግ ሰፊ እምቅ አቅም እና የተለያዩ የአየር ንብረት እና የመሬት አቀማመጥ ያለው በመሆኑ በዋና ዋናዎቹ የግብርና አቅሞች እና ገጽታዎች ዙሪያ ከብዝሀ ሕይወትና የዘላቂ ልማት ኤክስፐርት ከሆኑት ከፒተር ኒውሊንገር ጋር መክረዋል።

በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ የጋሞ ዞን ካለው እምቅ የተፈጥሮ ሀብት አሁን ላይ እየተፈጠረ ካለው ምቹ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ለአርሶ አደሩ ህብረተሰብና ለኢንቨስተሮች ጥሩ አጋጣሚን ይፈጥራል ብለዋል።

ስምምነቱ የጋሞ ዞን የብዝሀ ሕይወት ጥበቃና ዘላቂ ልማት ፕሮጀክት በማዘጋጀት እና በመተግበር ረገድ ፓርቲዎቹ የትብብር ማዕቀፍ ለመዘርጋት ያለመ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ፕሮጀክቱ ከአፍሪካ ህብረት እና ከሌሎች ሀገራት ጋር በጋራ የሚሰራ መሆኑን ጠቁመው 5 ሚሊዮን ዩሮ ካፒታል የያዘ ፕሮጀክት መሆኑንም ገልፀዋል።

ዋና አስተዳዳሪው አክለውም በአከባቢ ጥበቃና በመልሶ ማልማት፣ ማህበረሰቡን መሰረት ያደረጉ የአስተዳደር ዘዴዎችን ማዳበር፣ አርሶ አደሩ ምርትን በስፉትና በጥራት እንዲያመርት የገበያ ትስስር መፍጠር፣ ሳይንሳዊ፣ አስተዳደራዊና የማህበረሰብ አቅሞችን ማዳበርን ጨምሮ ማህበረሰቡን በስፉት ተጠቃሚ በሚያደርጉ ጉዳዮች ላይ እንደሚሰራም አመላክተዋል።

ለትምህርት ዘመኑ የትምህርት ዘርፍ ስራዎች ውጤታማነትና ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ     ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ወቅቱ...
29/09/2025

ለትምህርት ዘመኑ የትምህርት ዘርፍ ስራዎች ውጤታማነትና ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ወቅቱ በየደረጃው ባሉ የትምህርት ዕርከኖች የትምህርት ዘመኑ የመማር ማስተማር ስራ ጅማሮ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ለትምህርት ዘመኑ የትምህርት ስራዎች ውጤታማነት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ርብርብ በማድረግ የትምህርት ጥራትን የማሻሻል፤ ትውልድን በተሻለ መሠረት ላይ የማነፅ እና ለተሻለ ውጤት የማብቃት የተጀመሩ ተግባራትን በማጠናከር የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ሁለንተናዊ ብልጽግናን የማረጋገጥ ራዕይ ለሰነቀ ሀገር እና መንግስት የትምህርት ዘርፍ ውጤታማነትን ማረጋገጥ ለነገ የማይባል ተግባር ሊሆን ይገባል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የክልሉ መንግስት በማህበራዊ ልማት ዘርፍ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች ትምህርት ቀዳሚው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ ባለፉ ጊዜያት እንደ ሀገር ያጋጠመን የትምህርት ስብራት ለማከም በህብረተሰቡ ግንባር ቀደም ተሳትፎ በተከናወኑ የትምህርት ተደራሽነትን የማሳደግ እና የትምህርት ጥራትን የማሻሻል ዘርፈ ብዙ ስራዎች አበረታች ውጤት መገኘቱንም ገልጸዋል፡፡

ትምህርት በበቂ ዕውቀትና ክህሎት የተገነቡና በመልካም ስነምግባር የታነጹ የዛሬ ሀገር ገንቢዎችንና የነገ ሀገር ተረካቢዎችን በማፍራት ጠንካራ ሀገር ለትውልድ የማሻገር ታላቅ ተግባር ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ለዘርፉ ውጤታማነት የሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡

በክልሉ የህብረተሰቡ የትምህርት ልማት ተሳትፎ በተለይም ትምህርት ቤቶችን በመጽሐፍትና ሌሎች ግብዓቶች የማጠናከር፤ የማደስና አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን የመገንባት ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣ መሆኑንም ጠቅሰው፤ በተያዘው የ2018 የትምህርት ዘመንም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ለተማሪዎች ውጤታማነት ማደግ እና የትምህርት ጥራት መረጋገጥ የግብዓት መሟላት ቁልፍ ጉዳይ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በዚህ ረገድ በክልላዊ የአንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ ኢንሼቲቪ እና በሀገራዊው የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተገኙ ስኬቶች ተሞክሮን ቀምሮ ማላቅ ይገባል ብለዋል፡፡

በትምህርት ዘመኑ የተማሪዎችን ውጤታማነት ለማሳደግ በቀዳሚነት የተማሪ ወላጆች፤ መምህራን እና በየደረጃው ያለው የትምህርት ዘርፍ አመራር የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ከወዲሁ ሊወጡ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

በተለይ የተሟላ ዕውቀትና ክህሎት ያለው፤ መልካም ስነምግባርና ስብዕናን የተላበሰ ዜጋ ማፍራት የሚቻለው የቀለም አባት የሆኑት መምህራን የተጣለባቸውን ከፍተኛ ኃላፊነት በአግባቡ ሲወጡ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ እንደተለመደው ከምንም በላይ ቅድሚያ ለትውልዱ በመስጠት በትጋት እንዲሰሩ ከአደራ ጭምር ጠይቀዋል፡፡

በክልሉ ለተማሪዎች ውጤታማነት ማደግና በተለያዩ ምክንያቶች ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ ለማድረግ ከሚከናወኑ በርካታ ስራዎች መካከል ከ873 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተደራሽ ያደረገ የትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር አንዱ መሆኑንም ጠቅሰው፤ በትምህርት ዘመኑ ለታለመው የማህበረሰብ አቀፍ የምገባ ፕሮግራም ስኬት በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡

ርዕሰመስተዳድር ጽ/ቤት

‎Arba Minc'e kataman dumma dumma dichcha oothota oothishe diza"FE" eqotay masqala baala gaaso oothidi  Arba Minc'e kaata...
27/09/2025

‎Arba Minc'e kataman dumma dumma dichcha oothota oothishe diza"FE" eqotay masqala baala gaaso oothidi Arba Minc'e kaataman diza 200ppe bolla wolqay bayna dere asatas maada gishides.

‎Arba Minc’e: Gustama 17,2018 M.L Gaammo Telebizhine

‎ Arba Minc'e katama ayson pilxigina parte tashe xaappo keeththa kaapponne kawo gisha M/ro Kaassaye Lisaaneworqa gida mala maada gishoy kiya oothoppe aadhidi dereteththa issippeteththaka minthizaysako.

‎Arba Minc'e katama ayson oothanchatanne dereteththa wuda xaafo keeththa kaappo M/ro Tasfaye Abineta banta baggara katama aysoy oothishe diza kiyateththa oothoti ashoppe aadhidi shempoka ufaysizaysako gidosona.

‎"FE" eqota kaappo Daanna Alemu Derejjey banta baggara ha maada gishon beettidi habba masqala baalas gaththides gishe kiita aaththidi masqala baalay wolqay bantaytara issippeteththan gididi maadeteththan bonchiza baala gididaysa yootida.

‎Gujjidi ha kehateththa oothon derezi maadetana mala koshshes giidi ha maada gishon hashetidayta galatidosona.

‎Ha maado gisho maaran go'ettida Arba Minc'e katama de'anchatika immettida maadon ufaytidaysa malattidi maado oothidaytaska galata shiishida.

የጋሞ ማስቃላ በዓልን አስመልክቶ የጋሞ ቴለቪዥን ድርጅት ለአቅመ ደካሞችና ለአረጋውያን የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።አርባ ምንጭ፦ መስከረም 16/2018ዓ.ም(ጋሞ ቴሌቪዥን)እርስ በርስ የመረዳዳት ...
27/09/2025

የጋሞ ማስቃላ በዓልን አስመልክቶ የጋሞ ቴለቪዥን ድርጅት ለአቅመ ደካሞችና ለአረጋውያን የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

አርባ ምንጭ፦ መስከረም 16/2018ዓ.ም(ጋሞ ቴሌቪዥን)

እርስ በርስ የመረዳዳት እና የመተጋገዝ ባህላችን ማሳደግ ለሁለንተናዊ ብልፅግና ወሳኝ መሆኑን ተገልጿል ።

በእለቱ የጋሞ ቴለቪዥን ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ማንጉዳይ መርጮ ለአቅመ ደካሞችና ለአረጋዊያን ድጋፍ በማድረጋቸው መደሰታቸውን ገልፀው በዓሉ የደስታ የሰላም የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል ።

አክለዉም በዓሉን ስናከብር በአንድነት፣በመተባበር፣ በመቻቻል ረጂ ያጡትን በመርዳትና በጎ ሥራዎችን በመሥራት መሆን እንዳለበት መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል። ከዚህ በተጨማሪ የጋሞ ቴሌቪዥን መሰረቱ ጠንካራ እንዲሆን የሁሉም ሰዉ ርብርብና ድጋፍ ወሳኝ ስለሆነ በአገር ዉስጥም ከአገር ዉጭም ላሉ የጋሞ ቴሌቪዥን ተመልካቾች አስፈላጊዉን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

በመጨረሻም ዓመቱ ኢትዮጵያ ወደተሻለ ከፍታ የሚትወጣበት፣ በአባይ ግድብ የተሠራዉ ድል በቀይ ባህር የባህር በር የሚደገምበትና ሌሎች የተጀመሩና ሊጀመሩ የታቀዱ አገራዊ ፕሮጀክቶች ተሠርተዉ የሚጠናቀቁበት ዓመት እንዲሆን መልካም ምኞታቸዉን ገልፀዋል።

በስፍራው የአርባ ምንጭ ከተማ ሰራተኛና ማህበራዊ መምሪያ ኃላፊ ተወካይ ፤ የውሃ ምንጭ ቀጠና ሊቀመንበርና ሌሎችም የዉሃ ምንጭ ቀጠና አሰተባባሪ አካላት ተገኝተዋል ።

ድጋፍ የተደረገላቸው አካላት በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልፀው በዓሉ የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የጋሞ ዞን  የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃኪሜ አየለ የደመራና መስቀል በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ:-እንኳን ለመስቀል በዓ...
26/09/2025

የጋሞ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃኪሜ አየለ የደመራና መስቀል በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ:-

እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ!

የተከበራችሁ የክርስትና እምነት ተከታዮች እና መላው ኢትዮጵያውያን ፣ የመስቀል በዓል በፍቅር፣ በሰላም እና በደስታ በሚከበርበት በዚህ ልዩ ወቅት፣ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ!

መስቀል የክርስቶስን ስቅለት የምናስብበት፣ የይቅርታን እና የተስፋን ብርሃን የምንመለከትበት ታላቅ በዓል ነው። ይህ ታላቅ በዓል የጋሞ ህዝብን ጨምሮ ለመላው የሀገራችን ህዝቦች የደስታ፣ የፍቅርና የወንድማማችነት መገለጫ ነው።

የመስቀል በዓልን ስናከብር፣ የሰላም፣ የትብብርና የአንድነት እሴቶቻችንን አጠናክረን፣ በዞናችን እና በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ የልማትና የብልፅግና ጉዞዎችን በአብሮነትና በጋራ ተነሳሽነት እንድንደግፍ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

በዓሉን ስናከብር፣ ለሰላማችን መረጋጋት የደከሙትን እና የልማት ሥራዎቻችን ተጠቃሚ እንዲሆኑ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ያደረጉትን ሁሉ በማሰብ፣ በጎ አድራጎትን እና መተዛዘንንም እናስቀድም!

የተባበረን ጥረት ውጤት የሆነው ብልፅግናችን እንዲያብብ፣ መስቀል የሰላም፣ የመግባባትና የፍቅር መነሻ ይሁንልን።

መልካም በዓል!

አቶ ሃኪሜ አየለ
የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ
መስከረም 16/2018 ዓ.ም

ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸውን ህዝባዊ በዓላትንና እሴቶችን ጠብቆ ለቀጣይ ትውልድ ከማስተላለፍ ረገድ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ።ከዮ-ማስቃላ እሴቶች መካከል ተጠቃሽ የሆነው የ"ሶፌ...
26/09/2025

ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸውን ህዝባዊ በዓላትንና እሴቶችን ጠብቆ ለቀጣይ ትውልድ ከማስተላለፍ ረገድ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ።

ከዮ-ማስቃላ እሴቶች መካከል ተጠቃሽ የሆነው የ"ሶፌ'' እና የ"ካሎ" ልጆች ''ዶንጎ ካሳ'' ስነ ስርዓት በቆጎታ ወረዳ በድምቀት ተከናውኗል።

አርባምንጭ፥ መስከረም 16፣ 2018 ዓ/ም(ጋሞ ቴሌቪዥን)፦

የዮ-ማስቃላ እሴቶችን ለማልማትና ለማስተዋወቅ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጋሞ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ሞናዬ ሞሶሌ ተናግረዋል።

የጋሞ ህዝብ የበርካታ ባህላዊ እሴቶች ባለቤት መሆኑን ጠቁመው፤ ዮ- ማስቃላን ከዱቡሻ ዎጋ ጋር በማስተሳሰር በዩኒስኮ ለማስመዝገብ የተጀመረው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በዞኑ ያሉ መሰል ባህላዊና ማህበራዊ እሴቶች የሚደምቁባቸውን ህዝባዊ በዓላት ለቱሪስት መስህብነት በማዋል የኢኮኖሚ ምንጭ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራም ገልፅዋል።

የዮ-ማስቃላ አካል የሆነው በዓመቱ የተጋቡ ሙሽሮች ወደ ዶርቦ ዱቡሻ በመሰብሰብ ከህዝብ ጋር በይፋ የሚተዋወቁበትና በውበትና ደም ግብዓት አድናቆት የሚያገኙበት የ"ሶፌ" ስነ ስርዓት በደማቅ ሁኔታ መከናወኑን የቆጎታ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ታከለ ገልፀዋል።

ልጆች በለጋ ዕድሜያቸው የማህበረሰቡን ወግና ስርዓት ተምረው እንዲያድጉ የሚያግዝና ትኩረት የሚሰጠው የካሎ ልጆች ባህላዊ ስርዓት መከናወኑንም አስታውቀዋል።

ስርዓቱ ሳይበረዝ ለመጭው ትውልድ እንዲተላለፍ የመጠበቅና የማስተዋወቅ ስራ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

ዮ-ማስቃላ በዓል በህዝቦች ዘንድ ማህበራዊ መስተጋብርን የሚያጠናክር ድንቅ እሴቶችን የተጎናፀፈ መሆኑን የበዓሉ ታዳሚዎች ተናግረዋል ።

‎በአርባ ምንጭ ከተማ የደመራ ሥነ ሥርዓት በሰላማዊ ሁኔታ ተጠናቋል።‎‎የ2018ዓ.ም የጌታችንና የመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ደመራ በዓል በአርባምንጭ ከተማ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ...
26/09/2025

‎በአርባ ምንጭ ከተማ የደመራ ሥነ ሥርዓት በሰላማዊ ሁኔታ ተጠናቋል።

‎የ2018ዓ.ም የጌታችንና የመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ደመራ በዓል በአርባምንጭ ከተማ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

‎በአሉ በፀሎት፣በምስባክ፣በዝማሬ እና በተለያዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች ተከብሮ ውሏል።

‎በሥነ ሥርዓቱ የሃይማኖት አባቶች፣የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ፣ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና ምእመናን የተገኙ ሲሆን በፀሎት ተጠናቋል።

ህዝበ ክርስቲያኑ ደመራና መስቀልን ሲያከብር በትህትናና ፍቅር ሊሆን ይገባል - ብጹዕ አቡነ ኤልያስ‎ ‎‎አርባ ምንጭ መስከረም 16 / 2018 ዓ.ም. (ጋሞ ቴሌቪዥን)፦ ‎‎የደመራና መስቀል ...
26/09/2025

ህዝበ ክርስቲያኑ ደመራና መስቀልን ሲያከብር በትህትናና ፍቅር ሊሆን ይገባል - ብጹዕ አቡነ ኤልያስ


‎አርባ ምንጭ መስከረም 16 / 2018 ዓ.ም. (ጋሞ ቴሌቪዥን)፦


‎የደመራና መስቀል በዓል ሥነ-ሥርዓት በአርባ ምንጭ ከተማ ሲቀላ ፈለገ ዮርዳኖስ ህዝበ ምዕመኑ በተገኘበት በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።


‎የጋሞና አከባቢው ዞኖች የጎፋና ባስኬቶ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ ኤሊያስ ህዝበ ክርስቲያኑ በዓሉን ሲያከብር ከመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተማረውን ትህትናና ፍቅር በመተግበር እንዲሆን መክረዋል።

ብጹዕነታ የደመራና የመስቀል በዓል መንፈሳዊና ታሪካዊ ዳራ አስተምረዋል።


‎የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ደምሴ አድማሱ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያዊነትና በአብሮነት እሴት የምትታወቅ መሆኗንም ገልፀዋል።


‎የመስቀሉ መንፈሳዊ ትርጉም አንዱ ስለሁሉ የከፈለው ዋጋ መሆኑንም ተናግረዋል።


‎በዓሉ ሲከበር ሰላምን ለማጽናት፣ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት እና ወደ ላቀ ተስፋ መሸጋገር በመትጋት ሊሆን እንደሚገባም አስረድተዋል።


‎ለሰላም፣ ለልማት እና ለአብሮነት ቤተክርስቲያኗ እያደረገች የምትገኘውን አስተዋጽኦ እንድታጠናክርም ጥሪ አቅርበዋል።


‎የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ ዶክተር መስፍን መንዛ መስቀል ጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች ዋጋ የከፈለበትና ቤዛነቱን የገለጠበት እንደሆነ ተናግረዋል።


‎ደመራ የአብሮነትና የትብብር ማሳያ ነው ያሉት ከንቲባው በዓሉ የመቻቻል እሴት ማሳያም እንደሆነ ገልጸዋል።


‎አርባ ምንጭ የቱሪስት መስህብ መዳረሻ ፣የህብረ ብሄራዊነት መገለጫ መሆኗኖም ከንቲባው አብራርተዋል።


‎የመስቀልና ደመራ በዓል በዩኔስኮ እንደተመዘገበ አስታውሰው በዓሉ ለከተማዋ ቱሪዝም ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነም ዶክተር መስፍን ተናግረዋል።

Address

Arba Mintch

Telephone

+251468812386

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when GAMO TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to GAMO TV:

Share