GAMO TV

GAMO TV ይህ የጋሞ ቴሌቪዥን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ፣ ሼርና ኮሜንት በማድረግ ወቅታዊና እውነተኛ መረጃዎችን በየዕለቱ ይከታተሉ!

07/08/2025

'የሠላም ማይክሮ ፋይናንስ አክሲዮን ማህበር' ስራ ለመጀመር የሚያሰፈልጉ ቅድመ ዝግጅቶችን ማጠናቀቁ ተገለፀ።


የኩልፎ ወንዝ ዳር ልማት በአርባምንጭ ከተማ
07/08/2025

የኩልፎ ወንዝ ዳር ልማት በአርባምንጭ ከተማ

የኮሪደር ልማት - በአርባምንጭ ከተማ
07/08/2025

የኮሪደር ልማት - በአርባምንጭ ከተማ

ፀጋዎችን ወደ ውጤት በመቀየር የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ማሳደግ ይገባል- ዶክተር ደምሴ አድማሱ አርባምንጭ :- ነሔሰ 1/2017 ዓ /ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)"ትጋት ለላቀ ስኬት" በሚል መ...
07/08/2025

ፀጋዎችን ወደ ውጤት በመቀየር የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ማሳደግ ይገባል- ዶክተር ደምሴ አድማሱ

አርባምንጭ :- ነሔሰ 1/2017 ዓ /ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)

"ትጋት ለላቀ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የነበረው የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት ፈጻሚ ዝግጅት መድረክ ተጠናቋል ።
የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ደምሴ አድማሱ በወቅቱ እንዳሉት፣ የፓርቲና መንግስት ዕቅዶችን ለማሳካት ሁሉም በየደረጃው መረባረብ አለበት።

በየአከባቢው ያሉ ፀጋዎችን ወደ ውጤት በመቀየር ህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ መትጋት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል ።

የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሀኪሜ አየለ በበጀት ዓመቱ በብልፅግና ፓርቲ መሪነት የተመዘገቡ ውጤቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
የታዩ ድክመቶችን ለማረም መረባረብ ያስፈልጋል ብለዋል።

በየደረጃው የተለዩ ዕቅዶችን ከግብ ለማድረስ ሁሉንም አቅሞችን መጠቀምና ህዝቡን በተገቢው ማሳተፍ እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል።

የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ ጋሞ በበኩላቸው፣ አመራሩ ለተግባር ውጤታማነት ቁርጠኛ መሆኑን አለብት ብለዋል፡፡
የህዝብ ተጠቃሚነትን ማዕከል ያደረጉ ሥራዎች ላይ ትኩረት መስጠት እንደሚያስፈልግም አስረድተዋል ።

የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተመስገን እዩኤል ፥ ጠንካራ ፓርቲ ለመፍጠር አደረጃጀቶችን ማጠናከር ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል፡፡
በመድረኩ ማጠቃለያ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ መዋቅሮችና ተቋማት የዋንጫና ምስክር ወረቀት ተበረክቷል ።

07/08/2025

የጋሞ ልማት ማህበር አርባ ምንጭ እርሻ ልማት ቅኝት በጋሞ ቴቪ

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/gamotv2023
ዩቲዩብ- https://www.youtube.com/watch?v=ON_IiPGDg-4
ቴሌግራም - // t.me/gamotv123
ትክቶክ -https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1...
ትዊተር - https://twitter.com/GamoTv

07/08/2025

የኢችአይቪ/ኤድስ ቫይረስ አሁንም ትኩረት የሚሻ ጉዳይ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለፀ፡፡

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ 200ሺህ ዜጎች የኤችአይቪ/ኤድስ ምርመራ ማድረጋቸው ተመላክቷል፡፡

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/gamotv2023
ዩቲዩብ- https://www.youtube.com/watch?v=ON_IiPGDg-4
ቴሌግራም - // t.me/gamotv123
ትክቶክ -https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1...
ትዊተር - https://twitter.com/GamoTv

‎"ትጋት ለላቀ ስኬት" በሚል መሪ ቃል  የሚካሄደው ውይይት እንደቀጠለ ነው፡፡‎‎አርባምንጭ:- ነሔሰ 1/2017 ዓ/ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)‎የጋሞ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት "ትጋት ለ...
07/08/2025

‎"ትጋት ለላቀ ስኬት" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ውይይት እንደቀጠለ ነው፡፡

‎አርባምንጭ:- ነሔሰ 1/2017 ዓ/ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)

‎የጋሞ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት "ትጋት ለላቀ ስኬት" በሚል መሪ ቃል የ2017 ዓ/ም ዕቅድ አፈጻጸም ግምግማ እና የ2018 ዓ/ም ዕቅድ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ የፓርቲ አፈጻጸም ሪፖርት እና ቀጣይ ዕቅድ ዙሪያ ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡


"ትጋት ለላቀ ስኬት" በሚል መሪ ሀሳብ  የጋሞ ዞን   ብልፅግና  ፓርቲ  ቅርንጫፍ  ጽ/ቤት የውይይት መድረክ ተሳታፊዎች የችግኝ ተከላ እና የመስክ ምልከታ አካሄዱ።አርባምንጭ፣ ነሐሴ 1/20...
07/08/2025

"ትጋት ለላቀ ስኬት" በሚል መሪ ሀሳብ የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የውይይት መድረክ ተሳታፊዎች የችግኝ ተከላ እና የመስክ ምልከታ አካሄዱ።

አርባምንጭ፣ ነሐሴ 1/2017 ዓ.ም(ጋሞ ቴሌቪዥን)፦

የውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች በጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙርያ ላንቴ ቀበሌ ኤፃ ተፋሰስ ላይ የአረንጓዴ አሻራቸውን ያኖሩ ሲሆን የመስክ ምልከታም አካሂደዋል።

በትላንትናው እለት "ትጋት ለላቀ ስኬት" በሚል መሪ ሀሳብ የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2017 የፓርቲ ስራዎች እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2018 ፈፃሚ ዕቅድ ማዘጋጃ ዞናዊ መድረክ ሲካሄድ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው እለትም የችግኝ ተከላ እና የመስክ ምልከታን ጨምሮ የማጠቃለያ መድረክ እንደሚካሄድ ይጠበቃል።

የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተሻሻለ የግብርና አሰራር በማስፈን፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ፣ የውሃ ሃብትንና የብዝሃ ህይወት ጥበቃን በማረጋገጥ ዘላቂ ተጠቃሚነትን እንደሚያስገኝና፣ በተጨማሪም ብዝሀ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የራሱን አስተዋጽኦ በማበርከት እረገድም የማይተካ ሚና እንዳለው ተመላክቷል።

በመረሃ ግብሩም የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀኪሜ አየለ፣ የዞኑ ም/ል አስተዳዳሪ አቶ መኮንን ቶንቼ ፣ የዞኑ ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ገዛኃኝ ጋሞ ፣የዞኑ ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ተመስገን እዩኤልን ጨምሮ የዞኑ የሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር ፣ የብልፅግና ፓርት ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል ።

'የሠላም ማይክሮ ፋይናንስ አክሲዮን ማህበር' ስራ ለመጀመር የሚያሰፈልጉ ቅድመ ዝግጅቶችን ማጠናቀቁ ተገለፀ።‎‎አክሲዮን ማህበሩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንዲሟሉ የግድ የሚላቸው ጉዳዮችን ሙ...
06/08/2025

'የሠላም ማይክሮ ፋይናንስ አክሲዮን ማህበር' ስራ ለመጀመር የሚያሰፈልጉ ቅድመ ዝግጅቶችን ማጠናቀቁ ተገለፀ።

‎አክሲዮን ማህበሩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንዲሟሉ የግድ የሚላቸው ጉዳዮችን ሙሉ በሙሉ ማሟላቱን ተከትሎ በቅርቡ ስራ ይጀምራል ተብሏል።

‎አርባምንጭ፤ ሐምሌ 30/2017 ዓ.ም (ጋሞ ቴሌቪዥን)

‎የሠላም ማይክሮ ፋይናንስ አክሲዮን ማህበር ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢና የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) እንደገለፁት አክሲዮን ማህበሩ በታህሳስ 5 የመስራች ጉባኤ ካደረገ ጀምሮ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ሠርቷል።

‎የመተዳደሪያ ደንብን በተገቢው አዘጋጅቶ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማስገባት፣ የዋና ስራ አስፈፃሚ ቅጥር እና ቢሮ የማደራጀት ጉዳዮች ጊዜ የሚፈልጉ እንደነበር ዶክተር ደምሴ ጠቅሰው አሁን የሥራ አስፈፃሚ ቅጥር ተፈፅሞ በብሔራዊ ባንክም ተቀባይነት ማግኘቱንና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሙሉ በሙሉ መጠናቀቃቸውን አመላክተዋል።

‎አክሲዮን ማህበሩ አርባምንጭ ከተማን ጨምሮ በመነሻው ሦስት ቅርንጫፎችን ከፍቶ ወደ ስራ እንደሚገባ የተናገሩት የቦርዱ ሰብሳቢ ሰባት የተለያዩ የስራ መምሪያ ማንዋሎች መዘጋጀታቸውን በመግለፅ አክሲዮን ማህበሩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንዲሟሉ የግድ የሚላቸው ጉዳዮችን ሙሉ በሙሉ ማሟላቱን ተከትሎ በቅርቡ ስራ ይጀምራል ብለዋል።

‎አባላቱ ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው መነሻ በላይ የሆነ ከ81 ሚሊዮን ብር በላይ አክሲዮን በመግዛት ተቋሙን ለዚህ ማብቃታቸው ትልቅ አቅም ነው ያሉት ዶክተር ደምሴ ቀድሞ እንደክልል በስፋት ይሰራ የነበረው ኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ወደ ባንክ በማደጉ ሊፈጠር የሚችልን ክፍተት የሚሞላ እንደሆነም ተናግረዋል።

‎የተቋሙ ወደ ስራ መግባት በተቋሙ ቆጥበውና ተበድረው የስራ ዕድል መፍጠር ለሚያስቡ በርካታ ስራ ፈጣሪዎች ትልቅ ዕድልን ይዞ የመጣና ለወጣቱም የስራ ዕድልን የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።

‎ዶክተር ደምሴ በመግለጫቸው የጋሞ ልማት ማህበር ቦርድ አባላትን ጨምሮ ለተቋሙ እዚህ ደረጃ መድረስ አስተዋፅዖ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበው ህብረተሰቡም ተቋሙን የራሱ በማድረግ እንዲቆጥብ፣ እንዲበደርና እንዲገለገልበት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል በቅንጅት መስራት ይገባልአርባ ምንጭ :- ሃምሌ 30 /11/2017 ዓ.ም. (ጋሞ ቴሌቪዥን)‎ ‎ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ተቋማት በጋራና በተቀና...
06/08/2025

ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል በቅንጅት መስራት ይገባል

አርባ ምንጭ :- ሃምሌ 30 /11/2017 ዓ.ም. (ጋሞ ቴሌቪዥን)


‎ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ተቋማት በጋራና በተቀናጀ አግባብ ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ።

በጉዳዩ ላይ በአርባ ምንጭ ከተማ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አብዮት ሸጋው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በክልሉ ሕገ ወጥ ሰዎች ዝውውር ለመቀነስ በትኩረት እየተሰራ ነው።

በክልሉ በአብዛኛው በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚደረጉ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር በህገወጥ ደላሎች የሚፈጸም ነው ብለዋል።

አካላዊ ጉዳት እንደሚደርስባቸውም ተናግረዋል።


‎ችግሩን ለመከላከል ከተለያዩ ድርጅቶች በጋራ ለማህበረሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ነው የገለጹት።


‎ወጣቶች ያሉንን ፀጋዎችን በአግባቡ በመጠቀ በአገራቸው ሰርተው እንዲለወጡ መክረው መንግስት የስራ ዕድል ለማመቻቸት በትኩረት እንደሚሠራ አክለዋል።


‎በስልጠናው ከተሳተፋት መካከል ለጋሞ ቴሌቪዥን አስተያየታቸውን የሰጡ ወይዘሮ ሰናይት ገብረስላሴ ከሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ጋር ተያያዞ ከስልጠናው የጠለቀ ዕውቀት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

የሰዎች ዝውውር ለመከላከል የተለያዩ ተቋማት
‎በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ አመላክተዋል።

‎ወይዘሮ ዘኒት አህመድ በበኩላቸው የተሻለ ኑሮ ፍለጋ በሚል በህገወጥ መንገድ ለሚጓዙ የግንዛቤ ማስጨበጫ መስጠት ይገባል ይላሉ።

‎ህገወጥ የሰዎች ፍልሰትን ለመግታት ክልላዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ንደሚያስፈልግ የተናገሩት ደግሞ አቶ ግርማ ብርሃኔ ናቸው።

‎ዜጎች በአቋራጭና በአጭር ጊዜ ሀብት ለማፍራት በሚል ተሰፋ ለሕገወጥ ደላሎች መጋለጥ እንደሌለባቸው መክረዋል።

‎ይኸው ስልጠናው ለሦስት ተከታታይ ቀናት ነው የተሰጠው።

ብቁ ተተኪ ትውልድ በማፍራት ሂደት የህፃናት ፓርላማ ሚና የጎላ ነው - ወይዘሮ ሂሩት ማሞአርባ ምንጭ :- ሃምሌ 30 /11/2017 ዓ.ም. (ጋሞ ቴሌቪዥን)‎ ሀገር ተረካቢ ብቁ ትውልድ በማፍ...
06/08/2025

ብቁ ተተኪ ትውልድ በማፍራት ሂደት የህፃናት ፓርላማ ሚና የጎላ ነው - ወይዘሮ ሂሩት ማሞ

አርባ ምንጭ :- ሃምሌ 30 /11/2017 ዓ.ም. (ጋሞ ቴሌቪዥን)


ሀገር ተረካቢ ብቁ ትውልድ በማፍራት ሂደት የህፃናት ፓርላማ ሚና የጎላ መሆኑን የጋሞ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሂሩት ማሞ ገለጹ።


‎የመምሪያው የ2017 በጀት ዓመት የህፃናት ፓርላማ ዕቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት ተካሂዷል።


‎የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ ሂሩት ማሞ እንዳሉት የህፃናትን ሁሉ አቀፍ ተሳታፊነት እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሴቶች ሴክተር ብቻ የሚተገበር አይደለም።

‎የህፃናት መብትና ደህንነት የተከበረበት፣ ስብዕናቸው የጎለበተበትና የስርዓተ-ጾታ እኩልነት የሰፈነበት ዞን ለማየት መምሪያው ራዕይ አስቀምጦ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም ኃላፊዋ አብራርተዋል።


‎ለስኬታማነቱ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተግባርና ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባልም ብለዋል።


‎የጋሞ ዞን ህፃናት ፓርላማ ጽህፈት ቤት ዋና አፈጉባኤ ህጻን ሜሮን ወንዱ የህፃናት መብት ኮንቬንሽን በተደራጀ መልኩ ህፃናት ሀሳባቸውን እንዲገልፁ እና ተሳትፏቸውን እንዲያዳብሩ እንዳደረገ አመላክተዋል።


‎መረሃ ግብሩ ባለፉት 9 ወራት በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ገንቢ የሆነ ውይይት ተደርጎበታል።


‎በመድረኩ የህፃናት ፓርላማ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችን የመተካካት ሥራ ተካሂዷል።


‎በዚህ መሰረት የህፃናት ፓርላማ ዋና አፈጉባኤ ህፃን አሰግድ አለማየሁ እንዲሁም ህፃን ዲቦራ ጌታቸውን ምክትል አፈጉባኤ በመሆን ተሰይመዋል።


‎በመድረኩ በዞኑ የሚገኙ የህፃናት ፓርላማዎች አመራሮች፣ የሴቶችና ህፃናት ጽ/ቤት ኃላፊዎችን ጨምሮ የሚመለከታቸው ተሳትፈዋል።


Gaammo zoone qeeri nayta parlaama xaafo keeththay 2017 M.L moodenne 7-tho yuusho duulatay Arba Minc'e kataman doomettide...
06/08/2025

Gaammo zoone qeeri nayta parlaama xaafo keeththay 2017 M.L moodenne 7-tho yuusho duulatay Arba Minc'e kataman doomettides.

‎Arba Minc'e :- Lame 30/2017 M.L (Gaammo Telebizhine)

‎Duulata dooyo haasaya oothida Gaammo zoone mac'c'atanne qeeri nayta wuda kaaleththo kaappo M/ro Maammo Hiiruta dereteththay nayta maatanne saroteththa naagisanaas wuday xeellizaytara hasheteththan c'ora oothoti oothettishe gam'ides gidosona.

‎Gaammo zoone qeeri nayta parlaama xaafo keeththa ayfe dere duuna Wondu Meeronay dumma dumma hanotan kezzida nayta maatay bonchetana mala issippeteththaninne hasheteththan oothana besses gides.

‎Duulatan laythan oothettida oothota kaalli xeelon mino bagga mintheththizanne shugo miyeta giigissiza qofata iriporte shiiqin iza yuushon zoreteththi oothettes geetettidi naagettes.

‎Duulatan Gaammo zoone mac'c'atanne, qeeri nayta kaaleththo kaappo M/ro Maammo Hiiruto gujjidi, zoonezan beettiza ubba woradatappenne katama aysota qeeri nayta parlaama zore keeththa kaappotinne nayta parlaama dere duunatinne wuday bana gelthizayti beettida.

Address

Arba Mintch

Telephone

+251468812386

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when GAMO TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to GAMO TV:

Share