Gamo Bayira Media Network

Gamo Bayira Media Network ቤተሰብ ይሁኑ የሀገራችንን መልካ ምድር እንወቅ እናሳውቅ

በፈጣንና ወቅታዊ መረጃ የበለጸገ ማህብረሰብ እንፍጠር!

በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ 👇👇
Gamo Bayira Media Network
(1)

ከፋፋዩ የልብወለድ ማንነት ህልመኛው ላይመለስ ተወገደ በጠንካራው ህዝብ ትግል ቦታ ያጣው ቁህዴፓ ህዝቡ አንቅሮ ስተፋና በምርጫ ካርዱ ስቀጣው መዘረሩን  አሻፈረኝ ብልም ስንፈቱን በግድ እንድቀ...
16/06/2026

ከፋፋዩ የልብወለድ ማንነት ህልመኛው ላይመለስ ተወገደ

በጠንካራው ህዝብ ትግል ቦታ ያጣው ቁህዴፓ ህዝቡ አንቅሮ ስተፋና በምርጫ ካርዱ ስቀጣው መዘረሩን አሻፈረኝ ብልም ስንፈቱን በግድ እንድቀበል ተገዷል።

የጋሞን ህዝብ አንድነቱን የሚፈታተነው ዘንዶው ተቀጥቅጦ ሞተ፤ ህዝቡም አረፈ!

አበቃ 🙏

እንኳን ደስ አላችሁ አለን #

16/06/2026
ድምፃዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየበባህል ሙዚቃዎቹ የሚታወቀው ድምፃዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ኢቢሲ ከወዳጆቹ እንዳረጋገጠው ድምፃዊው ባደረበት...
15/06/2026

ድምፃዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በባህል ሙዚቃዎቹ የሚታወቀው ድምፃዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ኢቢሲ ከወዳጆቹ እንዳረጋገጠው ድምፃዊው ባደረበት ሕመም በሕክም እና ሲረዳ ቆይቶ ነው በዛሬው ዕለት ያረፈው።

በባህላዊ ሙዚቃዎቹ ይበልጥ የሚታወቀው ድምፃዊ ሰማኸኝ በለው፣ ከሙዚቃው ውጭም በትወና ይሳተፍ ነበር።

ድምፃዊ ሰማኸኝ ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት ነበር።

እኛም ለቤተሰቡ፣ ለወዳጆቹ እና አድናቂዎቹ መጽናናትን እንመኛለን።

መረጃ ፦ ኢቢሲ

በአርባምንጭ ከተማ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መስጠት ተጀመረ  ~ሰኔ 8/2018 ዓ.ም በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በዛሬው ዕለት በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች መስጠት...
15/06/2026

በአርባምንጭ ከተማ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መስጠት ተጀመረ

~ሰኔ 8/2018 ዓ.ም

በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በዛሬው ዕለት በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች መስጠት ተጀምሯል።

የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 8 ጀምሮ ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚሰጥ መሆኑን የተናገሩት የከተማው ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አብርሃም አምሳሉ በከተማው በሚገኙ 10 የመፈተኛ ጣቢያዎች 3 ሺ 708 ተማሪዎች ፈተና ላይ መቀመጣቸውን ገልጸዋል።

ኩረጃን የሚፀይፍ ትውልድ ከማፍራት አኳያ በትኩረት እየተሰራ መቆየቱን ተናግረው ፈተናው የፈተና አስተዳደር ሥርዓትን የጠበቀና ከኩረጃ በፀዳ ሁነታ እየተሰጠ እንዳለ አስረድተዋል።

በፈተናውም በ2018 የትምህርት ዘመን በመደበኛውና በማታው ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ክልላዊ ፈተናውን እየወሰዱ ነውም ብለዋል።

ይህን ተከትሎ ፈተናው ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ በቂ የፀጥታ አካላት በየትምህርት ቤቱ መመደባቸውን ጭምር ጠቁመዋል ።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ባለሙያ አቶ ፍቅረ ወ/ዮሐንስ ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ በቂ ሥራዎች እየተሰሩ መቆየቱን ገልጸዋል።

ለተማሪዎች፣ለፈታኝ መምህራን፣ለ ሱፐርቫይዘሮች፣ለጣቢያ ሀላፊዎች፣ለፀጥታ አካላት በቂ ኦርንቴሽን መስጠቱን ተናግረው ፈተናው ከኩረጃ የፀዳ እንዲሆን በአንድ መቀመጫ አንድ ተማሪ ብቻ እንድቀመጥ የማድረግ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለት መሰጠት የተጀመረው የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ተጠይቀዋል።

ክልል አቀፉ የ6ኛ ክፍል ፈተና በጋሞ ዞን በሁሉም አካባቢዎች እየተሰጠ ይገኛል​  ሰኔ 8/2018 ​የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በጋሞ ዞን በሁሉም አካባቢዎች ዛሬ ረፋድ 2፡30 ጀምሮ እየ...
15/06/2026

ክልል አቀፉ የ6ኛ ክፍል ፈተና በጋሞ ዞን በሁሉም አካባቢዎች እየተሰጠ ይገኛል

​ ሰኔ 8/2018

​የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በጋሞ ዞን በሁሉም አካባቢዎች ዛሬ ረፋድ 2፡30 ጀምሮ እየተሰጠ መሆኑን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።

​ፈተናውን በዞኑ ጨንቻ ከተማ አስተዳደር ጨንቻ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገኘት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢሳይያስ እንድሪያስ እንዲሁም የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር አዲሱ አዳሙ በጋራ አስጀምረውታል።

​የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ኢሳይያስ እንድሪያስ በወቅቱ እንደገለጹት ዘንድሮ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 126 ሺህ ተማሪዎች የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናን የሚወስዱ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 75 በመቶ ያህሉን ወደ ቀጣዩ የትምህርት ደረጃ ለማሳለፍ ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል።

​በክልሉ በ768 የፈተና ማዕከላት ለሚሰጠው ለዚሁ ፈተና 4 ሺህ 953 ፈታኝ መምህራን፣ የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችና ሱፐርቫይዘሮች የተመደቡ ሲሆን፥ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ ወደ ሥራ መግባታቸውንም አቶ ኢሳይያስ ጠቁመዋል።

​ኃላፊው አክለውም፥ ፈታኝ መምህራንና ሌሎች አስፈጻሚ አካላት ፈተናው በሚሰጥበት ወቅት ከፍተኛ የኃላፊነት መንፈስ በመሰነቅ ሂደቱ ፍጹም ከኩረጃ የጸዳ እንዲሆን መሥራት እንዳለባቸው አሳስበው ተማሪዎችም ተረጋግተው በራሳቸው እውቀትና አቅም ብቻ እንዲሠሩ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

​የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር አዲሱ አዳሙ በበኩላቸው በዞኑ በአጠቃላይ 26 ሺህ 637 ተማሪዎች የ6ኛ ክፍል ፈተናውን እየወሰዱ እንደሚገኙ ገልጸው፥ ለዚህም 198 የፈተና ማዕከላት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።

​ተማሪዎች ሳይደናገጡና ተረጋግተው የተሰጣቸውን ሰዓት በአግባቡ በመጠቀም ፈተናቸውን እንዲሠሩ አስቀድሞ ሰፊ የግንዛቤና የስነ-ልቦና ዝግጅት ሥራ መሠራቱን የገለጹት ዶ/ር አዲሱ፤ በዘንድሮው ዓመት ወደ ቀጣዩ ክፍል የሚያልፉ ተማሪዎች ቁጥር ከፍተኛ እንደሚሆን እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።

​(ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)

ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ያስገነባው  የኮንሶ ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ  ተመርቋል። ~ሰኔ 07/2018ዓ.ም  የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሐዋሳ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ታደሠ መርዕ...
14/06/2026

ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ያስገነባው የኮንሶ ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ ተመርቋል።

~ሰኔ 07/2018ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሐዋሳ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ታደሠ መርዕድ በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከሚገኙ 8 መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች የኮንሶ መቆጣጠሪያ ጣቢያ የላቀ አፈፃፀም በሁሉም ዘርፎች ማስመዝገቡን ተናግረው ጣቢያውን ማቋቋም ለሀገሪቱም ሆነ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት ላቅ ያለ ጠቀሜታ መኖሩን ገልፀዋል።

በዚህ አመት ብቻ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከ3.2 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት የኮንትሮባድ እቃ መያዙን የተናገሩት አቶ ታደሰ በኮንሶ ጉሙሩክ መቆጣጠሪያ ደግሞ ከ1 ቢሊዬን ብር በላይ የሚገመት የኮንትሮባንድ እቃ መያዙንም አስታውሰዋል።

ይህ የተገነባው ህንፃም ኮሚሽኑ የጀመራቸውን ህገ ወጥ የንግድ ቁጥጥርን በማሳለጥ የድርሻውን እንደሚወጣም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሸነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) በበኩላቸው ሀገሪቱ የጀመረቻቸው ሁሉ አቀፍ የኢኮኖሚ ለውጦች ተግዳሮት እንዳይገጥመው እየተሰራ መሆኑን ተናግረው ለዚህም ህገ ወጥ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን በተደራጀና በሰለጠነ መንገድ መግታት ያስፈልጋልም ብለዋል።

ከ2011 ዓ ም ጀምሮ ኮሚሽኑ ኢትዮጰያ የሚትፈልገውን ተቋም ለመገንባት ራዕይ በመያዝ በርካታ ለውጦችን ማምጣት መቻሉን ገልፀዋል።

ኮንሶ ላይ የተገነባው መቆጣጠሪያ ጣቢያ ለሀገር ግንባታና ዕድገት ጉልህ ድርሻ እንዳለው አረጋግጠዋል።

የሀገሪቱን ህግና ስርዓትን ለማስከበር፣ የገቢ አቅምን ለማሳደግና ንግድ ስርዓቱን ለማዘመን ኮሚሽኑ እየተጫወተ የሚገኘው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ያስረዱት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጰያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፌ-ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳኤ ናቸው።

የክልሉ መንግስት ኮሚሽኑ እያደረገ ለሚገኘው እንቅስቃሴ አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርግ ገልፀው ሀገሪቱበ የተያያዘችውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ማገዝ ያስፈልጋልም ብለዋል።

በዛሬው እለት የተመረቀው የኮንሶ ጉምሩክ ኮምሽን በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ባለቤትነት በታደለ ገብሬ ግንባታ ተቋራጭነት እና ከዲዛይን ጀምሮ ግንባታ ቁጥጥርና የኮንትራት አስተዳደር ሥራዎች በደቡብ ኢትዮጵያ የዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅቱ የተከናወነ ነዉ ።

በመርሃ ግብሩ መጨረሻ ለስራው ስኬታማነት ጉልህ ሚና ለተጫወቱ አካላት የዕውቅና ሽልማት ተሰጥቷል።

በጋሞ ዞን ከ46 ሺህ በላይ ተማሪዎች የሚፈተኑበት የ2018 ዓ.ም ክልል አቀፍ ፈተና ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለፀበጋሞ ዞን የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና የፈተና ስርቆትን ለመከላከል የሚያስችሉ...
14/06/2026

በጋሞ ዞን ከ46 ሺህ በላይ ተማሪዎች የሚፈተኑበት የ2018 ዓ.ም ክልል አቀፍ ፈተና ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለፀ

በጋሞ ዞን የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና የፈተና ስርቆትን ለመከላከል የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀው የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናዎችን ለመስጠት ሙሉ ዝግጁነት መኖሩን የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።

​የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲሱ አዳሙ በሰጡት መግለጫ ዘንድሮ በዞኑ በሁለቱም ደረጃዎች በአጠቃላይ 46,354 ተማሪዎች ለክልል አቀፍ ፈተና እንደሚቀመጡ ገልጸዋል።

ፈተናው ፍፁም ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ስኬታማ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ ከዞን እስከ ወረዳ ካሉ ባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ የውይይትና የዝግጅት መድረኮች መካሄዳቸውንም ኃላፊው ጠቁመዋል።

​እንደ ኃላፊው ገለፃ የፈተና ሂደቱ ተማሪዎች በተረጋጋ መንፈስ እውቀታቸውን እንዲመዝኑ ለማድረግ በሁለት ዙር ተከፍሎ የሚከናወን ሲሆን ፦

​የ1ኛ ዙር የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ ሲሆን፤ በዚህ ፈተና ላይ 26,637 ተማሪዎች ይሳተፋሉ። ለዚህም በዞኑ ስር የሚገኙ 543 ትምህርት ቤቶች የተለዩ ሲሆን፣ ሂደቱን በተሳለጠ መልኩ ለመምራት 198 የፈተና ማዕከላት ተደራጅተው ዝግጁ መደረጋቸውን ኃላፊው አብራርተዋል።

​የ2ኛ ዙር የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ደግሞ ከሰኔ 11 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ ይሆናል። በዚህ ፈተና ላይ 19,717 ተማሪዎች የሚፈተኑ ሲሆን፤ ፈተናው በ446 ትምህርት ቤቶች ውስጥ ላሉ ተማሪዎች በ159 በተመረጡ የፈተና ማዕከላት ውስጥ እንደሚሰጥ አቶ አዲሱ አስታውቀዋል።

የ​መምሪያ ኃላፊው አቶ አዲሱ አዳሙ በመግለጫቸው ማጠቃለያ ላይ፤ “ፍትሃዊ እና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም!” የሚለውን መሪ ቃል በተግባር ለማዋል የፈተና ማዕከላትን ደህንነት ከማስጠበቅ ጀምሮ የፈተና አስፈጻሚዎችና ታዛቢዎችን ስምሪት የማስተካከል ስራ በልዩ ትኩረት መከናወኑን ገልጸዋል።

ተማሪዎችም በቀሩት ጥቂት ቀናት ራሳቸውን ለፈተናው ብቁ አድርገው እንዲያዘጋጁና ወላጆችም ለልጆቻቸው አስፈላጊውን የሞራልና የጥናት ጊዜ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ሰኔ 7/2018
(ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)

የጥበብ ልኬት እና የለውጥ ችሎታ​አንድ አርቲስት ለሚወደው ስራ የሚከፍለው መስዋዕትነት፣ ገጸ-ባህሪያትን በውስጡ አዋህዶ በመቅረጽ የሚያሳየው ጥበብ እውነተኛ የኪነ-ጥበብ መገለጫ ነው።በፎቶው ...
14/06/2026

የጥበብ ልኬት እና የለውጥ ችሎታ

​አንድ አርቲስት ለሚወደው ስራ የሚከፍለው መስዋዕትነት፣ ገጸ-ባህሪያትን በውስጡ አዋህዶ በመቅረጽ የሚያሳየው ጥበብ እውነተኛ የኪነ-ጥበብ መገለጫ ነው።

በፎቶው ላይ የምናያት ቲክቶከሯ ዩቲናስ የዘመነ ማንነቷን ወደ ሙሉ ለሙሉ ሌላ ገጸ-ባህሪ በመቀየር የምታሳየው ትወና፣ የተመልካችን ልብ የመግዛት ልዩ አቅሟን ያሳያል።

​ብዙዎች "እሷ አይደለችም እሷ ነች" እያሉ የሚጠራጠሩት የዚች ጎበዝ ቲክቶከር የመቀያየር (Transformation) ችሎታ ስለደነቃቸው ነው።

ይህ የመገረም ስሜት የራሷን የጥበብ ጥግ በሌላ ከፍታ ላይ እንደምትገኝ ማሳያ ነው። ከዘመናዊው ገጽታ ወደ ጥልቅ የገጠር ስሜት መሸጋገር፣ የሰው ልጅን ስሜት በብቃት መጫወት የሚችሉ ጥቂት አርቲስቶች ብቻ የሚችሉት ብቃት ነው።

​ዩቲናስ ሆይ! ጥበብሽ፣ ትጋትሽ እና ገጸ-ባህሪያትን ህያው የማድረግ ችሎታሽ ለብዙዎች ትምህርት፣ ለአድናቂዎችሽ
ደግሞ መደነቂያ ነው። ቀጥይበት እንላለን!

መረጃ ቲዩብ

14/06/2026

ዶክተራ ተርጓሚ አግኝታለች 😆😆

14/06/2026

Address

Arba Minch
Arba Mintch

Telephone

+251925705694

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Bayira Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gamo Bayira Media Network:

Share