Gamo Bayira Media Network

Gamo Bayira Media Network ቤተሰብ ይሁኑ የሀገራችንን መልካ ምድር እንወቅ እናሳውቅ

በፈጣንና ወቅታዊ መረጃ የበለጸገ ማህብረሰብ እንፍጠር!

በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ 👇👇
Gamo Bayira Media Network
(1)

  የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ ዛሬ ይጀምራል!)በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ዛሬ፣ ረቡዕ ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም ይጀመራል።በአርባ...
19/08/2026

የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ ዛሬ ይጀምራል!)

በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ዛሬ፣ ረቡዕ ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም ይጀመራል።

በአርባምንጭ ከተማ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አብርሃም አምሳሉ እንዳስታወቁት፣ ምዝገባው ከነሐሴ 13-30/2018 ይካሄዳል።

በከተማዋ ባሉ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ፋይዳ መታወቂያ ይዘው እንዲገኙ እና ከ1ኛ–12ኛ ክፍል ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ነባርና አዳዲስ ተማሪዎች በተቀመጠላቸው ቀን የተማሪ ካርዳቸውን በመያዝ በወቅቱ እንዲመዘገቡ መምሪያው አሳስቧል።

የወላጆች ሚናም ወሳኝ ነው! ወላጆች ልጆቻቸውን በተጠቀሱት ቀናት በፍጥነት በማስመዝገብ፣ ትምህርት በወቅቱ እንዲጀመርና የትምህርት ብክነት እንዳይፈጠር የበኩላቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ መምሪያው ጥሪ አቅርቧል።

📚 ልጆቻችንን በወቅቱ እናስመዝግብ፤ የትምህርት ጊዜን እንጠብቅ!

አርባምንጭ ከተማ ትምህርት መምሪያ

እንኳን ለ3ኛ ዓመት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምስረታ ቀን አደረሳችሁ ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም እንኳን ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 3ተኛ ዓመት የምስረታ ቀን በሠላም አደረሰን አደረሳችሁ። ባለፉት...
18/08/2026

እንኳን ለ3ኛ ዓመት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምስረታ ቀን አደረሳችሁ

ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም

እንኳን ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 3ተኛ ዓመት የምስረታ ቀን በሠላም አደረሰን አደረሳችሁ።

ባለፉት ሦስት የለውጥ እና የሥራ ዓመታት ክልላችን የሕዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ፣ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እና ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማስመዝገብ በርካታ ስትራቴጂያዊ ስኬቶችን አስመዝግቧል።

የ3 ዓመታት አበይት የትኩረት አቅጣጫዎቻችን ቀዳሚው
ዘላቂ ሰላምና አብሮነት ሲሆን በዚህም የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶችን በማጠናከርና ውይይቶችን በማስፋፋት የፀና ሰላምና የሕግ የበላይነት ተረጋግጧል።

ከመሠረተ ልማትና አገልግሎት አንፃር የገጠርና የከተማ መንገድ ዝርጋታዎች፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታዎች እንዲሁም የትምህርትና የጤና ተቋማት ተስፋፍተው ለሕዝቡ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ።

ከኢኮኖሚና የሥራ ዕድል አኳያ ግብርናን ማዘመን ኢንቨስትመንትን መሳብ እና ለአካባቢው ወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድሎችን መፍጠር ተችሏል።

የክልላችን የወደፊት ጉዞ የህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነት፣ የልማትና የብልጽግና መሠረት ሆኖ ይቀጥላል!

እንኳን ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት 3ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አደረሳችሁ!

የሠላም፣ የመቻቻል እና የብልፅግና ተምሳሌት ክልል ደቡብ ኢትዮጵያ

Ethiopia Regional State!👏

18/08/2026
"አዲስ ተስፋ ለሲቀላው አባት! የጤና ተቋማትን በማስተባበር የመኖሪያ ቤት ግንባታ በይፋ ተጀመረ" 🌟የአርባ ምንጭ ከተማ ጤና መምሪያ በሲቀላ ክፍለ ከተማ ለሚኖሩ አንድ አቅመ ደካማ አባት ጥራ...
18/08/2026

"አዲስ ተስፋ ለሲቀላው አባት!
የጤና ተቋማትን በማስተባበር የመኖሪያ ቤት ግንባታ በይፋ ተጀመረ" 🌟

የአርባ ምንጭ ከተማ ጤና መምሪያ በሲቀላ ክፍለ ከተማ ለሚኖሩ አንድ አቅመ ደካማ አባት ጥራቱን የጠበቀና ዘላቂ የሆነ የመኖሪያ ቤት ግንባታ በይፋ አስጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የከተማው ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አይሶጼ ሂሎታ እና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ጌታቸው እንደገለጹት፤ አቅም የሌላቸውን ወገኖች መደገፍና ሰብአዊነትን ማጠናከር የሕዝቡ ልዩ መገለጫ ነው። ቀደም ሲል በአንድ ጀንበር ከሚሠሩ የጭቃ ቤቶች ወጥቶ አሁን ላይ ጥራትን መሠረት ያደረጉ ቋሚ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑንና በዚህ ክረምት የተጀመሩ ቤቶች በአጭር ጊዜ ተጠናቀው እንደሚረከቡ ገልጸዋል።

የከተማው ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር አንተነህ ካሣዬ በበኩላቸው፤ ግንባታው የጤና ተቋማትንና ማናጅመንቱን በማስተባበር የሚከናወን መሆኑን ጠቅሰው፣ ቤት ሲጠናቀቅም ሙሉ የቤት ቁሳቁስ ተሟልቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ርክክብ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።

መምሪያው ከቤት ግንባታው በተጨማሪ የደም ልገሳ፣ የችግኝ ተከላና የማስ ስፖርት መርሃ ግብሮችን ማከናወኑንና የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራትን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

በተደረገላቸው ድጋፍ የተደሰቱት የሲቀላ ክፍለ ከተማ ነዋሪው አቅመ ደካማ አባት

📍 አርባ ምንጭ፣ ኢትዮጵያ #የክረምትበጎፈቃድ #ሰብአዊነት #አርባምንጭ

በክልሉ የማዕድን አለኝታ ምርምር ውጤት ማረጋገጫ ወርክሾፕ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተጀመረ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማዕድን ባለስልጣን ትብብር በክልሉ የማዕድን ...
18/08/2026

በክልሉ የማዕድን አለኝታ ምርምር ውጤት ማረጋገጫ ወርክሾፕ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተጀመረ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማዕድን ባለስልጣን ትብብር በክልሉ የማዕድን አለኝታ ጥናት የምርምር ውጤት ማረጋገጫ ወርክሾፕ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።

በወርክሾፑ መክፈቻ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሄለን ዮሀንስ እንዳሉት ምርምሩ የተካሄደው በክልሉ ደቡብ ኦሞ፣ አሌ እና ጎፋ ዞኖች በሚገኙ ማሌ፣ ገዋዳ ዙሪያ እና መሎኮዛ ወረዳዎች ነው።

ጥናቱ በግንባታ እና የጌጣጌጥ ማዕድን ሀብቶች ላይ ትኩረት ማድረጉን ጠቅሰዋል።

በክልሉ ዘርፉን ለማልማት እየተሠራ መሆኑን ዳይሬክተሯ ጠቅሰው፣ለዚህም በጥናት የተደገፈ ስራ መጀመሩን አመልክተዋል።

የክልሉ የርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ እና የአማካሪዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ቦሻ ቦምቤ መንግስት ማዕድንን አንዱ የልማት ትኩረት አድርጎ እየሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ሀብቱን በሚገባ በማልማት ረገድ ዩኒቨርሲቲዎችና ማህበረሰቡ ከመንግስት ጋር ይበልጥ በቅንጅት መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ኢንጂኒየር አብደላ ከማል ዩኒቨርሲቲው የክልሉ ሀብት ለድህነት ቅነሳ እንዲውል በጥናት የተደገፉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በወርክሾፑ ሌሎች የክልል እና የፌዴራል ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ ምሁራን እየተሳተፉ ነው።

"መጣና በዓመቱ... ኧረ እንደምን ሰነበቱ!" ቡሄ - ከክረምት ጨለማ ወደ መስከረም ብርሃን*****************የክረምቱ ቅዝቃዜ ማብቂያ ሲቃረብ የፀሐይ ብርሃን ምድርን ዳግም ማሞቅ ሲጀ...
18/08/2026

"መጣና በዓመቱ... ኧረ እንደምን ሰነበቱ!" ቡሄ - ከክረምት ጨለማ ወደ መስከረም ብርሃን
*****************

የክረምቱ ቅዝቃዜ ማብቂያ ሲቃረብ የፀሐይ ብርሃን ምድርን ዳግም ማሞቅ ሲጀምር፣ የኢትዮጵያዊነት ማህበራዊ ትስስር እና የመንፈሳዊነት ህብረ-ቀለም የሆነው የቡሄ (ደብረ ታቦር) በዓል መቃረቢያው እና ዋዜማው ላይ "መጣና በዓመቱ... ኧረ እንደምን ሰነበቱ!" የሚለው የታዳጊዎች ጭፈራ በያካባቢው መታየት ይጀምራል።

በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን በመላው ኢትዮጵያውያን ዘንድ በታላቅ ደስታ የሚከበረው "ቡሄ" የብርሃንና የተስፋ ማበሰሪያ ከመሆኑም በላይ፣ ትውልድን ከሀገር ፍቅር እና ከአብሮነት እሴት ጋር የሚያስተሳስር ታላቅ ህዝባዊ ሀብት ነው።

በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮታዊ ብርሃን በደብረ ታቦር ተራራ ላይ መገለጡን በማሰብ "ደብረ ታቦር" ተብሎ የሚከበረው ይህ በዓል፤ "ቡሄ ካለፈ የለም ክረምት" እንደሚባለው የዝናብና የጨለማው ወቅት ማለፉን፣ የልምላሜና የብርሃን ዘመን መምጣቱን ያበስራል።

የታዳጊዎች የሆያ ሆዬ ጭፈራ፣ በቃጫ አምሮ እና ተገምዶ የሚሰራው የጅራፉ ድምጽ፣ ከእምዬ ጓሮ የሚያውደው የሙልሙሉ ሽታ የቡሄ በዓል የብዙዎቻችን የልጅነት ትዝታ ማህደር ነው።

እኛ ኢትዮጵያውያን የተጋመደ ማንነት እና አንድነት እንዳለን በግልጽ ከሚያመለክቱ እሴቶቻችን አንዱ የሆነው "ቡሄ" በአንድ አካባቢ እና ቋንቋ ብቻ የታጠረ አለመሆኑ በግልጽ ይታያል።

ታዳጊዎችና ወጣቶች በየቡድን ሆነው
"ሆያ ሆዬ ሆ
ሆይ የኔ ጌታ፤ ሆ
ጌታ ለጌታ ፤ ሆ
ቡሄ በሉ ፤ ሆ
ልጆች ሁሉ ሆ " ...
እያሉ በዱላ እና በከበሮ የታጀበ ውብ ዜማ በየደጁ ሲያዜሙ፣ እናቶች ደግሞ በኮባ ተጠቅልሎ የተጋገረውን ልዩ መዓዛ ያለው "ሙልሙል" ዳቦ ያድሏቸዋል አልያም ለጨፈሩ ልጆች በጋራ የሚካፈሉት ጥቂት ገንዘብ ከአባቶች ምርቃት ጋር እንካችሁ ይሏቸዋል።

በአማራ ክልል በደብረ ታቦር፣ በሰሜን ወሎ፣ በጎጃም፣ በሸዋ፣ በወሎና በሌሎችም የሀገሪቱ ክፍሎች በደመቀ ሁኔታ የሚከበር ቢሆንም፣ እሴቱ ግን የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ ሀብት ነው።

የቡሄ በዓል በኦሮሚያ ክልልም የተለያዩ አከባቢዎች በተመሳሳይ "ኡኬ" (Ukee) በመባል ይታወቃል። በዓሉ ምሽት ላይ የሚከበር ሲሆን፣ ልጆቹ ከብቶችን በዜማ ያሞግሳሉ፤ ከበዓሉ ቀደም ብለው ልጆች ጅራፍ በማዘጋጀት ምሽት ላይ ተሰብስበው ጅራፍ ያስጮሃሉ፤ እንዲሁም ዱላ በመያዝ በየመንደሩ እየተዘዋወሩ ባለቤቶቹን በበጎ ስም በመጥራትና ውብ ግጥሞችን በመግጠም ያመሰግናሉ።

ይህ በዓል ልጆች ወዳጅነታቸውንና ጓደኝነታቸውን እንዲያጠናክሩ፣ የአካባቢያቸውንና ሁኔታ እንዲያውቁ፣ እንዲሁም ግጥም በመግጠም የዜማ ችሎታቸውን እንዲያዳብሩ ይረዳቸዋል።

በዚህን ወቅት ልጆች
"Ukee yaa ukee
Ukee bara kaanii
Kan miilli dagaanii
Ukee bara quufaa
Hindaaqqoo dhudhuufaa..."
እንዲህ እያሉ ያዜማሉ

ልጆች ሙልሙል ዳቦውን እየገመጡ በየሰፈሩ የሚገርፉት የጅራፍ ድምፅ የክረምቱን ጨለማ መገፈፍ የሚያበስር ሲሆን፣ በምሽት የሚለኮሰው ችቦ ደግሞ አካባቢውን በብርሃን ያሸበርቀዋል።

ይህ ከልጅነት ጀምሮ በልባችን የሚታተመው የማካፈል፣ የመተሳሰብ እና የእንግዳ ተቀባይነት ባህል፤ ህፃናት ስለ ሀገራቸው ፍቅር፣ ስለ ወገን ደስታ እና ስለ ህብረት ትልቅ ትምህርት የሚያገኙበት የቀደመ ማህበራዊ መሰረት ነው።

ቡሄ በዜማና በደስታ ብቻ የሚገለፅ ሳይሆን፤ የቤተሰብ ፍቅርን፣ የጎረቤት ትስስርን እና የህብረ-ብሄራዊ አንድነትን የሚያጠናክር ሌላኛው ድልድይ ነው።

የቡሄ በዓል መንፈሳዊ ጥልቀቱን ጠብቆ ከማህበራዊ ትስስር ማጠናከር ባለፈ፣ ለአገር ውስጥና ለውጭ ጎብኚዎች የማይረሳ ትዝታን የሚፈጥር፣ የቱሪዝም ኢኮኖሚን ከፍ የሚያደርግ እና የሀገራችንን በጎ ገጽታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ድንቅ ብሄራዊ ፀጋችን ነው።

የቡሄ በዓል በእናንተ አካባቢ ምን ተብሎ እንደሚጠራ በመልእክት መስጫው ላይ አጋሩን።

EBC-መዝናኛ #ቡሄ EBC-መዝናኛ #ቡሄ Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ

ቃልን በተግባር! ለአርባምንጭ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ የጀግኖች አሻራ ቀጥሏል! 🏟️✨ታሪክ የሚሰራው በወሬ ሳይሆን በተግባር ለሚያምኑ ውድ የሀገር ባለውለታዎች ነው! ለአርባምንጭ አለም ...
18/08/2026

ቃልን በተግባር!
ለአርባምንጭ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ የጀግኖች አሻራ ቀጥሏል! 🏟️✨

ታሪክ የሚሰራው በወሬ ሳይሆን በተግባር ለሚያምኑ ውድ የሀገር ባለውለታዎች ነው! ለአርባምንጭ አለም አቀፍ ስታዴየም ግንባታ የሚደረገው የ3ኛው ዙር የሀብት ማሰባሰብ ስራ በታላቅ መነሳሳት ቀጥሏል።

ታላቁ ባለሀብት አቶ ታረቀኝ ወርቁ ለዚህ ታሪካዊ ፕሮጀክት ያላቸውን የማይነጥፍ ፍቅርና ድጋፍ በድጋሚ አስመስክረዋል፦

* በ1ኛው ዙር፦ 1,000,000 (አንድ ሚሊዮን) ብር 💰
* በ2ኛው ዙር፦ 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር 💰
* አሁን በ3ኛው ዙር፦ ተጨማሪ 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ብር ገቢ አድርገዋል! 🙌

በአጠቃላይ 1.5 ሚሊዮን ብር በመለገስ ለህዝብና ለሀገር ኩራት መሆን ምን ማለት እንደሆነ በተግባር አሳይተውናል! ለአቶ ታረቀኝ ወርቁ ያለንን የላቀ ምስጋና እናቀርባለን። 👏🎈
የእርስዎስ ታሪካዊ አሻራ የት አለ? 🤔
ይህ ስታዲየም የሁላችንም ኩራት፣ የነገ ልጆቻችን መተነፈሻና ታላቅ የጋራ ስኬታችን ነው! የነገውን ታሪክ ዛሬ በጋራ ለመገንባት የእያንዳንዱ ዜጋ አስተዋጽኦ ወሳኝ ነው። እርስዎም ዛሬውኑ የበኩልዎን ድጋፍ በማድረግ ስምዎን በታሪክ ማህደር ላይ ይጻፉ!
👇 አሁኑኑ ድጋፍ ለማድረግ የባንክ አካውንታችን፦
👉 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000640532851
👉 የአካውንት ስም፦ ለአርባምንጭ አለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ
በህብረት ጀምረናል፣ በአንድነት እንጨርሳለን! 💪⚽

#ልማት #አንድነት

በህብረት ጀምረናል፣ በአንድነት እንጨርሳለን! 💪⚽የጋሞ ህዝብ ታላቅ ታሪክ የሚሰራው  በአንድ ልብ ሲቆም ነው! ከትውልድ ወደ ትውልድ የተሻገረው የመረዳዳት፣ የመተባበርና የጋራ ስራ ባህላችን ...
18/08/2026

በህብረት ጀምረናል፣ በአንድነት እንጨርሳለን! 💪⚽

የጋሞ ህዝብ ታላቅ ታሪክ የሚሰራው በአንድ ልብ ሲቆም ነው!

ከትውልድ ወደ ትውልድ የተሻገረው የመረዳዳት፣ የመተባበርና የጋራ ስራ ባህላችን የማንነታችን መገለጫ ነው።

ልማትን የመንግስት ብቻ ሳይሆን የራሳችን ሀላፊነት አድርገን በጉልበታችን፣ በእውቀታችንና በሀብታችን በተግባር አስመስክረናል።

ዛሬ ደግሞ ሌላ ታሪክ ለመስራት አዲስ ትልቅ ግብ ፊት ለፊት ቆመናል፤ የአርባምንጭ ዓለም አቀፍ ስታዲየምን ከግብ ማድረስ! 🏟️✨

ይህ ስታዲየም የጡብና የሲሚንቶ ህንፃ ብቻ አይደለም፤ የህዝባችን አቅም፣ የትውልድ ትሩፋትና የአንድነታችን መገለጫ ምልክት ነው። ዛሬ የምናቆመው ይህ ስራ ነገ ልጆቻችን በኩራት የሚመለከቱት ታሪክ ይሆናል።

ስታዲየሙን ማጠናቀቅ የሁላችንም የጋራ አላማና ሀላፊነት ነው!
የጋሞ ህዝብ አንድነቱ የጉልበቱ፣ ትጋቱ የልማቱ፣ የጋራ ራዕዩም የድሉ መሠረት ነው!

#ልማት #አንድነት

የገጠር ኮሪደር ልማት፡ የኢትዮጵያን ገጠር የሚቀይር አዲስ አቅጣጫ 🌾የመደመር መንግሥት ያስጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት የገጠርን ሀብት ወደ ምርት፣ ምርትን ወደ ገበያ፣ ገበያን ደግሞ ወደተሻ...
18/08/2026

የገጠር ኮሪደር ልማት፡ የኢትዮጵያን ገጠር የሚቀይር አዲስ አቅጣጫ 🌾

የመደመር መንግሥት ያስጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት የገጠርን ሀብት ወደ ምርት፣ ምርትን ወደ ገበያ፣ ገበያን ደግሞ ወደተሻለ የኑሮ ደረጃ በመቀየር ላይ ይገኛል። ገጠርን የምርት ቦታ ብቻ ሳይሆን ሰዎች በክብርና በጤና የሚኖሩበት ማዕከል ማድረግ ዋና ዓላማው ነው።

Gamo Bayira Media Network

የሌማት ትሩፋት በአርባ ምንጭ፦ የተስፋ ጭላንጭል በሮሆቦት ማህበርአርባ ምንጭ ከተማ በተለያዩ የልማት መስኮች እያስመዘገበች ካለችው እመርታ መካከል የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አንዱ ተጠቃሽ ...
18/08/2026

የሌማት ትሩፋት በአርባ ምንጭ፦ የተስፋ ጭላንጭል በሮሆቦት ማህበር

አርባ ምንጭ ከተማ በተለያዩ የልማት መስኮች እያስመዘገበች ካለችው እመርታ መካከል የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አንዱ ተጠቃሽ ነው። በተለይ በሼቻ ክፍለ ከተማ ውስጥ የተቋቋመው ሮሆቦት ከብት እርባታ ማህበር ለዚህ ጥሩ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።

ማህበሩ በ2018 ዓ.ም በዶይሳ አንድ ማዕከል በራስ ተነሳሽነት የተደራጀ ሲሆን፣ አባላቱ ገና ከጅምሩ የቦታ እጥረት ቢያጋጥማቸውም ከከተማው አስተዳደር ጋር በመተባበር ችግሩን በጋራ መፍታት ችለዋል። ይህም አርባ ምንጭ ላይ የህዝብና የመንግስት ተቋማት ተባብረው ሲሰሩ ምን ያህል ውጤት ማምጣት እንደሚቻል የሚያሳይ ተምሳሌት ሆኗል።

የአርባምንጭ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ጌታቸው ማህበሩን በጎበኙበት ወቅት እንዳረጋገጡት፣ የተጀመሩ የሌማት ትሩፋት ስራዎች ከወረቀት ያለፈ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው። ይህ ደግሞ አርባ ምንጭ ከንግግር ወደ ተግባር በፍጥነት እየተሸጋገረች መሆኗን ያመላክታል።

የሼቻ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ትዕግስት ፋሪሳ በበኩላቸው፣ ማህበራት የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች በመፍታት ሙሉ ድጋፍ የማድረግ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ይህ አካሄድ ወደፊትም ተጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ፣ ሌሎች ማህበራትም ተመሳሳይ እድል አግኝተው የከተማዋን የምግብ ዋስትና ማረጋገጫ ጥረት ሊያግዙ ይችላሉ።

በአጠቃላይ የሮሆቦት ማህበር ተሞክሮ የሚያሳየው አርባ ምንጭ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በኩል ወደ ላቀ ደረጃ እየተጓዘች መሆኗን ነው፤ ማህበራት በራሳቸው ተነሳሽነት ሲደራጁ አስተዳደሩም አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን ሲቀጥል ውጤቱ ይበልጥ ተስፋ ሰጪ ይሆናል።

ስንታየሁ - Sintayehu

Gamo Bayira Media Network

Address

Arba Minch
Arba Mintch

Telephone

+251925705694

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Bayira Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gamo Bayira Media Network:

Shortcuts

Share