Gamo nation

Gamo nation Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gamo nation, Digital creator, Arba Mintch.
(2)

የነኝህን እናት እና ልጅ  ቪድዮ በሰይፉ ሾው መመልከት ይከብዳል፣ ሰው በዚህ ልክ ክፋት ያውም በልጃቸው ልጅ ላይ መጨከንን ከየት አገኙት። ባልተቤቴ በተቀበረ ማግስት የባልተቤቴ የኮሜዲያን ወ...
15/12/2025

የነኝህን እናት እና ልጅ ቪድዮ በሰይፉ ሾው መመልከት ይከብዳል፣ ሰው በዚህ ልክ ክፋት ያውም በልጃቸው ልጅ ላይ መጨከንን ከየት አገኙት።

ባልተቤቴ በተቀበረ ማግስት የባልተቤቴ የኮሜዲያን ወንድወሰን አውራሪስ ቤተሰቦች ከቤት አስወጡኝ፤ የባልተቤቴን ስልክ የቀብሩ ዕለት ተቀበሉኝ ትቶልን ያለፈው ምንም ነገር የለም ፣ ለጊዜው ጓደኞቹ ባዘጋጁልን ጊዜያዊ ማረፊያ ውስጥ ነው ያለነው በማለት በተሰበረ አንደበት የወንዶሰን አውራሪስ ባልተቤት ተናግራለች።

ከኢትዮጲያዊነት ባህል እና ወግ ውጭ የሆነ ግፍ ነው የተፈፀመባቸው ልጅቱ በዚህ እድሜዋ ተስብራለች ከአባቷ ሞት በላይ ቤተሰቦቹ ሰብረዋታል፤ ስለዚህ ጉዳይ ለመፃፍም ቃል ያጥራል።

የኢትዮጲያን ህዝብ እርዳታ ይሻሉና ይታገዙ ዘንድ #ሸር በማድረግ ደጋግ ሰዎች ዘንድ ይድረስላቸውና ይረዱ መርዳት የምትችሉም ከታች በተቀመጠው አካውንት እና አድራሻ መጠቀም ትችላላችሁ።

ለመርዳት:-
Betelhem Hiluf
CBE 1000024737385
ስልከ 0910219309

የኢትዮጵያን ዘመነ አቆጣጠር እቀይራለሁ ያለው ዘመነ ቅዱስ ሔኖክ የተሰኘ መጽሐፍ ተመረቀ በኢትዮጵያ  የዘመን አቆጣጠር  በተለይም የጳጉሜን ወር ላይ ትኩረቱን ያደረገዉ የዲያቆን ወልደ ሰንበት...
14/12/2025

የኢትዮጵያን ዘመነ አቆጣጠር እቀይራለሁ ያለው ዘመነ ቅዱስ ሔኖክ የተሰኘ መጽሐፍ ተመረቀ

በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር በተለይም የጳጉሜን ወር ላይ ትኩረቱን ያደረገዉ የዲያቆን ወልደ ሰንበት "ዘመነ ቅዱስ ሔኖክ" የተሰኘዉ መፅሐፍ በዛሬዉ እለት መካኒሳ በሚገኘው የእህተ ማርያም አገልግል ሬስቶራንት ተመርቋል።

ይህን መፅሀፍ ለመፃፍ አራት ዓመታት እንደፈጀ እና ብዙ ጥናቶች የተለያዩ ጥንታዊ መፅሐፍትን እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ቻትጂቢቲን ጨምሮ ውጭ ሃገር የሚገኙ የመረጃ ምንጮችን እንደተጠቀሙ ተገልጿል።

የመፅሐፉ ዋና ትኩረት አሁን ኢትዮጵያ እየተጠቀመችበት ያለዉን የዘመን አቆጣጠር የሚዳስስ እና አቆጣጠሩ ሙሉ በሙሉ ከግብፅ የተወረሰ በመሆኑ እና በራሳችን የዘመን አቆጣጠር በመተካት ወደ ቀደመው ማንነታችን እንመለሳለን ሲሉ ተናግረዋል። መፅሐፉ ለአንባቢያን በአማርኛ ቋንቋ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን በጃፋር የመፅሃፍ መደብር ይገኛል ሲሉ ፀሃፊው ተናግረዋል።

ልክ የዛሬው ዕለት ታህሣሥ 4/1964 ዓ.ም ወደዚህ ምድር ተቀላቀልኩ። በጎውን፣ ክፉውን ሁሉ አሳይቶኝ፣ ዕድሜ እና ጤናን ሰጥቶኝ ለዚህ ቀን ለደረሰኝ እግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን ። መ...
13/12/2025

ልክ የዛሬው ዕለት ታህሣሥ 4/1964 ዓ.ም ወደዚህ ምድር ተቀላቀልኩ። በጎውን፣ ክፉውን ሁሉ አሳይቶኝ፣ ዕድሜ እና ጤናን ሰጥቶኝ ለዚህ ቀን ለደረሰኝ እግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን ። መልካሙን ሁሉ ለተመኛችሁልኝ ወዳጆቼ ክብረት ይስጥልኝ።

ለገሰ ቱሉ

አዶናይ በዋስ ተፈታ!Adonayy
13/12/2025

አዶናይ በዋስ ተፈታ!

Adonayy

ማን ያዉቀዋል 🤔
13/12/2025

ማን ያዉቀዋል 🤔

በአርባ ምንጭ ከተማ የስርቆት ወንጀል የፈፀመው ፖሊስ በሶስት አመት ከስድስት ወር ፅኑ እስራት ተቀጣ !!!  በቀን 16/03/2018 ዓ/ም ከረፋዱ በግምት 3:30  በሚሆንበት ጊዜ በአ/ምንጭ...
13/12/2025

በአርባ ምንጭ ከተማ የስርቆት ወንጀል የፈፀመው ፖሊስ በሶስት አመት ከስድስት ወር ፅኑ እስራት ተቀጣ !!!

በቀን 16/03/2018 ዓ/ም ከረፋዱ በግምት 3:30 በሚሆንበት ጊዜ በአ/ምንጭ ከተማ ነጭሳር ቀበሌ ልዩ ሥፍራ ጋሞ አደባባይ አከባቢ የግል ተበዳይን መስፍን ማሞን የት ልአድርስህ በማለት ባለ ሶስት እግር ባጃጅ ሠሌዳ ቁጥሩ ደ/ህ 33618 በሆነው በማሳፈር ወደ ኮንሶ አደባባይ አከባቢ ሌሎች ስርቆት ወንጀል የሚፈፅሙ ጓደኞችን ከኃላ በማሳፈር ከግል ተበዳይ ጓደኞቹ በማሰረቅ ንብረትነቱ የመስፍን ማሞ የሆነውን አይተል ስክሪን ታቺ (Itel screen touch) የዋጋ ግምቱ 14,000ብር(አስራ አራት ሺ ብር) የሚያወጣውን ሞባይል ስርቆው ካመለጠበት ፖሊስ ተከታትለው በመያዝ ምርመራ በማጣራት የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቤ ህግ ስልክ ዐ/ህግም ተከሳሹ ላይ በኢፌዲሪ ወ/ህግ አንቀጽ 32/3 እና 665/1ን በመተላለፍ በፈፀመው ስርቆት ወንጀል ክስ በመክፈት ለአርባምንጭ ከተማ መጀመሪያ ደ/ፍ/ቤት ስያስተላልፍ ፍ/ቤቱ ግራ ቀኙን ከመከራከር ቆይቶ ወንጀል ፈፃሚውን ያርማል ሌላውን ያስጠነቅቃል በማለት በቀን 03/04/2018 ዓ/ም በዋለው ወንጀል ችሎት ሶስት ዓመትከ 6ወር እንዲቀጣ መወሰኑን የሲቀላ ቀበሌ ፖሊስ ጽ/ቤት ታክቲክ ምርመራ ማስተባበሪያ ኃላፍ ረ/ኢ/ር ለማ ትላንቴ ገልጸዋል ።

◉ የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ ጉዳይ ፦ ሐላፊነቱን ወስጄ ፡ ከኦሮሚያ ክልል አመራሮች እና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክቡር  ፕሬዝዳንት አቶ ጥላሁን ከበደ ጋር በመሆን ፡ በጋራ ሰርተን ሐላፊነቱን...
13/12/2025

◉ የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ ጉዳይ ፦ ሐላፊነቱን ወስጄ ፡ ከኦሮሚያ ክልል አመራሮች እና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክቡር ፕሬዝዳንት አቶ ጥላሁን ከበደ ጋር በመሆን ፡ በጋራ ሰርተን ሐላፊነቱን ወስጄ ለእናንተ ሪፖርት አቀርባለሁ!

◉ ከአርባ ምንጭ - ጉጂ - ዲላ - አማሮ መንገድ ፡ አሁን ከሚሰራው በገጠር መንገድ ባለስልጣን ፡ የጠጠር መንገድ ተባብረን ወደ አስፓልት አሳድገን የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን እናጠናክራለን!

🗣 የኦሮሚያ ክልል ፕ/ት ኦቦ ሽመልስ አብዲሳ

አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጉዳዩን 'ጉዳዬ ነው' ብለው ይዘው መሄድ አለባቸውበአሁኑ ወቅት መንግስት የማሕበራዊ  ሚዲያ አልጎሪዝምን ተከትሎ ለአንዳንድ ጉዳዮች ትኩረት እንደሚሰጥ እሙን ነው። የኦሮሚ...
13/12/2025

አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጉዳዩን 'ጉዳዬ ነው' ብለው ይዘው መሄድ አለባቸው

በአሁኑ ወቅት መንግስት የማሕበራዊ ሚዲያ አልጎሪዝምን ተከትሎ ለአንዳንድ ጉዳዮች ትኩረት እንደሚሰጥ እሙን ነው።

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ወደ አርባምንጭ መምጣታቸውን ተከትሎ ከእንኳን ደህና መጡ ሙገሳ ጎን ለጎን በቀጥታ የኦሮሚያ ክልልን የሚመለከተውን የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ ውድመት ማስገንዘብ ተገቢ ነበር።

አቶ ሽመልስ ከኢትዮጵያ መረጃ ደህንነት ም/ዳይሬክተር አቶ ቴዘር ገ/እግዚአብሔር ጋር እንደመምጣታቸው የነጭ ሳር ጉዳዩ አሁንም የተሻለ ትኩረት የሚያገኝበት ተጨማሪ ዕድል አለው።

ርዕስ መስተዳድሩ በዛሬው ዕለት "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ቱሩፋቶች " በሚል ከአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ጋር ውይይት - አንደሚያደርጉ ተዘግቧል።

ለውይይቱ ተመርጣችሁ የምትገቡ ሰዎች - በሚሰጣችሁ ዕድል ከውዳሴው ቀነስ አርጋችሁ የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ ውድመት አንገብጋቢ መሆኑን እና የአርባምንጭ ከተማ ህልውና መሰረት መሆኑን ደጋግማችሁ ማስጨበጥ ይኖርባችኋል።

ፓርኩ ተገቢ ጥበቃ እና ልማት ቢደረግለት የጋም ፣ የኮሬ እና የጉጂ ሕዝቦችን የጋራ ተጠቃሚ እንደሚደረግ ማስገንዘብ እና አቶ ሽመልስ ጉዳዩን ጉዳዬ ብለው ይዘውት እንዲሄዱ ማድረግ ያስፈልጋል።

ከዛሬ 5 ዓመት በፊት ነጭ ሳር ፓርክ ውስጥ 1,100 ሕገ ወጥ አባወራ እንደሚኖር ፣ 110 ሺህ ከብት እንደተሰማራ የፓርኩ ሜዳማ ክፍል 50% በግጦሽ ፣ በሕገወጥ ሰፈራ ፣ በእርሻ እና በአደን እንደወደመ የተረጋገጠ መረጃ ቀርቧል። ጥፋቱ ዛሬ ላይ ከምን እንደ ደረሰ መገመት አይከብድም።

በፓርኩ ጉዳይ ለዓመታት እልፍ ውጤት - አልባ ስብሰባዎች ተደርገዋል። ግን ውጤት እስኪመጣ ድረስ በተገኙ ዕድሎች ሁሉ መጮህ ያስፈልጋል።

አሁንም ትኩረት ለነጭ ሳር ፓርክ !

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በአርባምንጭ ከተማ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አደረጉ።የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የ አቶ ቴዘር ገ/እግዛብሔር የ...
12/12/2025

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በአርባምንጭ ከተማ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አደረጉ።

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የ አቶ ቴዘር ገ/እግዛብሔር የኢትዮጵያ መረጃ ደህንነት ም/ዳይሬክተር ለይፋዊ ሥራ ጉዳይ አርባምንጭ ከተማ በዛሬው ዕለት አርባምንጭ ከተማ ገብተዋል።

ክቡር ርዕስ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በአርባ ምንጭ ከተማ በመንግስትና በሕብረተሰብ ተሳትፎ የተሰሩ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጉብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም የአርባምንጭ አለምአቀፍ ስታዲዬም ፕሮጄክት ግንባታ፣ የአርባምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት ገበታ ለትውልድ እና የጋሞ ባይራ አዳሪ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።

በከተማዋ እየተካሄዱ የሚገኙ ግዙፍ የልማት ሥራዎች አስመልክቶ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና የመንግስት ተጠሪ አተቶ ገ/መስቀል ጫላ፣የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ፣የከተማው ከንቲባ መስፍን መንዛ(ዶ/ር) የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምስ አድማሱ የፕሮጄክት ማናጀሮችና አስተባባሪዎች፣ የተቋማት ኃላፊዎች ገለፃና ማብራሪያ አድርገውላቸዋል።

ርዕስ መስተዳድሩ በነገው ዕለት "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ቱሩፋቶች " በሚል መሪ ቃል ከአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ጋር የሠላምና የአንድነት ኮንፈረንስ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

አ.ከ.መ.ኮ ✍️

የረዳት ኮሚሽነር   ስርዓተ ቀብራቸዉ በአርባምንጭ  ደብረ መድሃኒት  መዳነዓለም ካቴድራል ተፈጽሟል።ረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ ከአባታቸው ከአቶ  ሀብቴ  ቱሉ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ዲላሴ ...
10/12/2025

የረዳት ኮሚሽነር ስርዓተ ቀብራቸዉ በአርባምንጭ ደብረ መድሃኒት መዳነዓለም ካቴድራል ተፈጽሟል።

ረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ ከአባታቸው ከአቶ ሀብቴ ቱሉ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ዲላሴ ጮላ ህዳር 02/1955 ዓ.ም በጋሞ ዞን ቦንኬ ወረዳ ጮሾ ቀበሌ ተወለዱ።

ረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ቦንኬ ወረዳ ጋዜሶ አንደኛ ደረጃ እንድሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በካምባ ወረዳ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመከተልና በ1975 ዓ.ም ከሐዋሳ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም በመምህርነት ሙያ ተመርቀዋል።

ረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ በቀድሞው ጋርዱላ አዉራጃ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች በመምህርነትና በርዕስ መምህነት አግልግለዋል።

ረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ ወደ ተወለዱበት ቦንኬ ወረዳ በመመለሰም በተለያዩ የመንግስት ጽ/ቤቶችን በሃላፊነት ያገለገሉ ሲሆን፤

👉 ከ19994 ዓ.ም እስከ 1996 ዓ.ም ድረስ የቦንኬ ወረዳ ዋና አስተዳዳር ሆነው በታማኝነት ሕዝባቸውን አገልግልዋል።

👉 የአርባምንጭ ማረሚያ ተቋምን እስከ ረዳት ኮሚሽነሪነት ማዕረግ ድረስ በጡረታ እስከምገለሉ ድርስ በታማኝነት አገልግለዋል።

👉 ረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ ከምሰሩበት ተቋም በጡረታ ብግለሉም የቴጣሉትን በማስታረቅ መልካም ተግባራትን በመፈጸም እንድሁም ከጋሞ አባቶች በጋራ በመሆን በተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር የማስታረቅ ስራዎችን አከናውነዋል።

👉 ረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ በህይወት ዘመናቸው አስታራቂ ለሰዉ አዛኝ እና መልካም አባት ነበሩ።

👉 ረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ የሶስት ወንድና የአራት ሴት ልጆች አባት ነበሩ።

👉 ረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ በደረሰባቸው ድንገተኛ የጤና እክል የህክምና እርዳታ እያገኙ በተወለዱ 63 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

በረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ ስረዓተ ቀብራቸው የጋሞ ዞን ዋና አስተዳደር ዶ/ደምሴ አድማሱ፤ የአርባ ምንጭ ከተማ አሰተዳድር ከንቲባ ዶ/ር መሰፍን መንዛን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፍዎች፤ የሞያ አጋሮቻቸው፤ ቤተሰቦቻቸው እንድሁም አድናቂዎቻቸው በተገኙበት በአርባምንጭ ደብረ መድኃኒት መዳነዓለም ካቴድራል ተፈፅሟል።

የጋሞ ቴሌቪዥንም በረዳት ኮሚሽነር አበበ ሀብቴ ድንገተኛ ህለፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው በሙሉ መፅናናትን ይመኛል።

09/12/2025
ለ44 አመታት ኢትዮጵያ ልጆቿን አስተምሯል፤ አሁን የእሱ ልጆች ማን ያስተምራቸው? አንጋፋው የፍልስፍና መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ፔሌ ዳሮታ ህልፈተ ህይወት በተመለከተ በርካቶች ሀዘናቸውን ገልጸ...
09/12/2025

ለ44 አመታት ኢትዮጵያ ልጆቿን አስተምሯል፤
አሁን የእሱ ልጆች ማን ያስተምራቸው?

አንጋፋው የፍልስፍና መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ፔሌ ዳሮታ ህልፈተ ህይወት በተመለከተ በርካቶች ሀዘናቸውን ገልጸዋል።

ረዳት ፕሮፌሰር ፔሌ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና ትምህርት ክፍል ውስጥ ከጥቅምት 1974 ዓ.ም ጀምሮ በመምህርነት እና አማካሪነት ያገለገሉ ሲሆን በልዩ ትጋትና ቅንነት በርካታ ምሁራንን አፍርተዋል።

ትሁት፣ ሁሉንም የሚወድ፣ሙያውን ሳይሰስት የሚለግስ መምህር ነበር።

ልቡ ሳይሸፍት በአንጋፋው ዩኒቨርሲቲ ለ44 አመታት ያህል አገልግሏል።

ረዳት ፕሮፌሰር በአገልግሎት ዘመኑ ያተረፈው በትምህርቱ አለም የዘራው ዘር አንጂ ሀብት አይደለም።

ዘመኑን በሙሉ ለሰው ልጆች የሰጠ መምህር ነበር።

አሁን ረዳት ፕሮፌሰር ወደ አምላኩ ተጠርቷል።

ግን ለኛ ኢትዮጵያዊያን አደራ ትቶልን ነው ወደ አምላኩ የሄደው።

ፕሮፌሰር ፔሌ የትዳር አጋር ከሆነችው የሺሀረግ ኪዳኔ ያፈራቸው ሁለት መንቲያ ወንድ ልጆች አሏቸው።

እነዚህ የፕሮፌሰር ፔሌ መንትያ ልጆች አሁን 16 አመታቸው ላይ ይገኛሉ።

በትምህርታቸውም ጎበዝ እንደሆኑ የምትናገረው እናታቸው የሺሀረግ የልጆቹን ነገር አደራ ብላለች።

አሁን ሁለቱ መንትያ ልጆች አስረኛ ክፍል የደረሱ ሲሆን በደጋግ ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ።

ግን የትምህርት ቤት ክፍያ፣ የሰርቪስ ክፍያ፣ ምግባቸው፣ አልባሳታቸው ማን ይሸፍን ምክንያቱም አባታቸው አጥተዋልና።

ቤቷም ተገኝተን ያረጋገጥነው ይህንን እውነታ ነው።

እናታቸው የሺሀረግ ረዳት ፕሮፌሰር ከሞተ በኋላ ምንም መተዳደርያ የሌላት ሲሆን ሁለት መንታ ወንድ ልጆቻቸው የምታስተዳድርበት እጅ አጥሯታል። ፔሌም ጥሎላት የሄደው ጥሪት የለም።

በዚህም የኢትዮጵያዊያን ድጋፍ ትሻለች።

የፕሮፌሰር ፔሌ የትዳር አጋሩ እንደዚሁም የልጆቹ እናት የሆነችውን የሺሀረገ ኪዳኔን አገኝቶ መርዳት የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ ካለ ( መቄዶንያ ፊለ ፊት) የሚገኘው የካ ጣፎ ኮንዶሚኒየም ብሎክ 85 የቤት ቁጥር 12 ሄዶ ሊያገኛት ይችላል።

በተጨማሪም +251-989-062544 በግል የእጅ ስልኳን በመደወል ማነጋገር ይቻላል።

የሺሀረግ ኪዳኔን መርዳት የሚፈልጉ ኢትዮጵያዊያን ይህንን የእርሷን አካውንት መጠቀም ይችላል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000004412706

#ሼር

Address

Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo nation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share