Sintayehu Abayenh

Sintayehu Abayenh 👉ሚዲያን ለበጎ አላማ ብቻ እንጠቀም 🙏
(1)

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ለወጣቶች ስብዕና ልማት (Mindset) የተዘጋጀ ስልጠና መድረክ ተካሂዷል።‎ይህ...
15/10/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ለወጣቶች ስብዕና ልማት (Mindset) የተዘጋጀ ስልጠና መድረክ ተካሂዷል።

ይህ ስልጠና የወጣቱን የዕውቀት ደረጃቸውን ከፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን በተገቢው እንዲወጡና በፈጠራ ስራ ራሳቸውን እንዲያዳብሩ የሚረዳ ነው።

ዋና አላማውም
👉 የግለሰብ ፣የተቋማትና የሀገር ሠላም ፣ ለዉጥ ፣ልህቀትና ብልፅግና ለማረጋገጥ ወጣቶች ሚናቸውን እንዲወጡ ለማድረግ ፣
👉 በስብዕና የተካነ፣ በአፈፃፀም ብቁ ፣በአተገባበር የላቀ ፣ሠላምና ዕድገት ተኮር (Mindset) ያለው ወጣት ለመፍጠር፣
👉 የግለሰቦችና የማህበረሰብ አዕምሮ ዉቅር(Mindset) መቀየር፣
👉 የህዝብ የሥራ ትጋትና የሰላም ባህል ግንባታ እንዲጨምር ማስቻል፣
👉 የህዝብ በጎ ፈቃድና ማህበራዊ ኃላፊነት ስብዕና እንዲዳብር ማስቻል እና ከተግዳሮት (challenge) መማር የቻለ ወጣት መፍጠር ዋና ዋና አለን ያነገበ መድረክ ነው።

‎ባደጉ ሀገራት ሆነ ባላደጉ ሀገራት ይህንን ኃይል በአግባቡ መጠቀም፣ ስብዕና ግንባታ ላይ ውጤታማ እንዲሆኑ መስራት ሀገር ለምታስበው እድገትና ስኬት ቁልፍ ድርሻ ያለው በመሆኑ እንደሀገር ለወጣቱ ትውልድ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል።

‎የስብዕና ልማት ስራ አዲስ ባህል ሳይሆን በውስጣችን ያለውን እምቅ ኃይል፣ እውቀትና አቅም በመጠቀም ለሀገር ብልጽግና አሻራችንን የምናሳርፍበት ትልቅ መድረክ ነው ።

‎ ይህ የስብእና ልማት (Mindset) ስልጠና በነገው እለትም በጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ እና ከዘፈኔ ከተማ ለተወጣጡ ወጣቶች የሚሰጥ ሲሆን በቀጣይም በዞኑ በሌሎች መዋቅሮችም የሚቀጥል ይሆናል።

ከበሬ አጥንት የመኪና ፍሬን አካላትን የሚሰራው ስራ ፈጣሪ ወጣት የበሬ ስጋን ለምግብነት ከተጠቀምን በኋላ አጥንቱን ወደ ቆሻሻ መጣያ ማስወገድ ወይም ለውሻ መስጠት የተለመደ ነዉ። አንድ ወጣት...
15/10/2025

ከበሬ አጥንት የመኪና ፍሬን አካላትን የሚሰራው ስራ ፈጣሪ ወጣት

የበሬ ስጋን ለምግብነት ከተጠቀምን በኋላ አጥንቱን ወደ ቆሻሻ መጣያ ማስወገድ ወይም ለውሻ መስጠት የተለመደ ነዉ።

አንድ ወጣት ግን የሚጣለውን የበሬ አጥንት በመጠቀም የሰራው የፈጠራ ስራ ለበርካቶች የስራ አድል ፈጥሯል፡፡

ወጣቱ በሀይሉ ሰቦቃ ይባላል፡፡ በመካኒካል ኢንጂነሪንግ የመጀመሪያ ድግሪ አለው፡፡ በአዲስ አበባ የሚገኘው የአስኬማ ድርጅት መስራች ሲሆን ከልጅነቱ ጀምሮ ለሰዎች ችግር መፍትሄ መሆን ህልሙ እንነበር ይናገራል፡፡

ወጣቱ የመካኒካል ኢንጂነሪንግ ትምህርቱን መመረቂያ ፕሮጀክት ከአጥንት እና ከወዳደቁ ብረታብረትን በመጠቀም በመስራት ስራ ፈጣሪ ሆኗል።

ወጣቱ የመኪና ፍሬን አካላትን በሀገር ውስጥ ከበሬ አጥንት፣ ከወዳደቁ ብረታብረት እና ሴራሚክ በመስራት ከራሱ አልፎ ለሌሎች የስራ ዕድልን ፈጥሯል።

ተቋሙ የመኪና ፍሬን አካላቶችን ለማምረት የበሬ አጥንቶቹን ከተለያዩ የቄራ ድርጅቶች እና ስጋ ቤቶች የሚሰበሰብ ሲሆን የወዳደቁ ሴራሚክ እና ብረታብረቶችን ከማምረቻ ድርጅቶች እና ሻጮች እንደሚያገኝ ገልጿል።

ለምርቶቹ የሚጠቀሙት የአጥንት ክፍል ዳሌ አካባቢ ያለውን የበሬ ክፍል ሲሆን የአጥንቱን ባህሪ እና ጥንካሬ በማጥናት እንደሚለዩ ተናግሯል።

በወጣቱ የተቋቋመው አስኬማ ድርጅት 268 ሰራተኞችን የያዘ ሲሆን ከ6 ሺህ 400 በላይ ደንበኞች ምርቶቻቸውን እየተጠቀሙ እንደሚገኙ ገልጿል።

የተቋሙ መስራች ሀይሉ ሰቦቃ እንደሚለው ድርጅቱ ለመንገድ ግንባታ የሚያገለግሉ ማሽነሪዎች መለዋወጫ እቃዎችንም እየሰራ ሲሆን የISO ሰርተፍኬት ባለቤት መሆን መቻሉን ጠቅሶ የየዘገበው EBC ነው።

ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

14/10/2025

ኡፍ ክፕል 10 ተለቋል 🤣

👌👌
14/10/2025

👌👌

የ12 ዓመት ሴት ልጅ አስገድዶ የደፈረው የ65 ዓመት ጎልማሳ የHIV/AIDS ታማሚ በ23 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እሥራት ተቀጣየይርጋለም ከተማ ነዋሪ የሆነው አቶ ካሣሁን ናስር የተባለ ግለሰብ ...
14/10/2025

የ12 ዓመት ሴት ልጅ አስገድዶ የደፈረው የ65 ዓመት ጎልማሳ የHIV/AIDS ታማሚ በ23 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እሥራት ተቀጣ

የይርጋለም ከተማ ነዋሪ የሆነው አቶ ካሣሁን ናስር የተባለ ግለሰብ በቀን 6/12/2017 ዓ.ም በ12 ዓመት ሴት ልጅ አስገድዶ በመድፈሩ ፖሊስ በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማረጋገጡ የይርጋለም ከተማ አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት በቀን 4/2/2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ23 ዓመት ከስድስት ወር ፅኑ እሥራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ተከሳሹ በHIV/AIDS ታማሚ እንደነበረና ለ14 ዓመታት በይርጋዓለም ሆስፒታል ህክምናውን ሲከታተል መቆየቱን ፖሊስ ከሆስፒታሉ ያገኘውን መረጃ ለፍርድ ቤቱ ያቀረበ ሲሆን በዚህች ሴት ልጅ ሕይወት ላይ የደረሰው ተደጋጋሚ ጥቃት ሕብረተሰቡን አስቆጥቷል ሲል SBC ዘግቧል።

ክፕል 10 በጉጉት እየተጠበቀ ነው ጳውሎስ 🤣🤣
14/10/2025

ክፕል 10 በጉጉት እየተጠበቀ ነው ጳውሎስ 🤣🤣

በየ tiktok በየ YouTube በሁሉም social media ተኳኩላቹ በፊልተር ደማምቃቹ እየመጣቹ ለትዉልድ ስድብና መጨመላለቅ ከምታስተምሩት ይልቅ፡እንደነዚህ ልጆች ድራማ ይሁን ቲያትር ምን...
14/10/2025

በየ tiktok በየ YouTube በሁሉም social media ተኳኩላቹ በፊልተር ደማምቃቹ እየመጣቹ ለትዉልድ ስድብና መጨመላለቅ ከምታስተምሩት ይልቅ፡እንደነዚህ ልጆች ድራማ ይሁን ቲያትር ምንም ይሁን ምን የሚሰሩትም ነገር ባይገባኝ እንኳን ተመችተዉኛል ሌላዉ ቢቀር ያስቁኛል፡ይመቻቹ የምታቀርቡት ነገር አይለቅባቹ ብዬ መርቃቸዋለሁ😊

ግን ክፐል 10 መቆየቱ አሳስቦኛል የኢትዮጵያ ህዝብም አሳስቦታልና ጳውሎስ ክፑ አትሁን ለቀቅ በህግ አምላክ 🤣🤣😭

በደመወዝ ጭማሪ ሰበብ ዋጋ ያናሩ ከ57 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደለመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ተጨምሯል በሚል ሰበብ ዋጋ ያናሩ 57 ሺህ 212 ነጋዴዎች ላይ ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱ...
14/10/2025

በደመወዝ ጭማሪ ሰበብ ዋጋ ያናሩ ከ57 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

ለመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ተጨምሯል በሚል ሰበብ ዋጋ ያናሩ 57 ሺህ 212 ነጋዴዎች ላይ ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግመዋል።

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የንግድ ስርዓትና ላይሰንሲንግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤት አብዱል ሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) ባቀረቡት ሪፖርት በሩብ ዓመቱ ንግድን ሥርዓት ለማስያዝ የተለያዩ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን አብራርተዋል።

በዚህም ለመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ተጨምሯል በሚል ሰበብ ዋጋ ያናሩ 57 ሺህ ሺህ 212 ህገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

ዘገባዉ የኢትዮጲያ ፕረስ ድርጅት ነዉ

ጥቅምት 04/2018 ዓ/ም

14/10/2025

ዘንድሮ ብሶብናል ሆ

14/10/2025

👌👌👌❤
ሼር ይደረግ

14/10/2025

አርባ ምንጭ ሆኖ ሀይሚን የማያውቅ የለም 🙏

ኢትዮጵያ አሸንፋለች !!አሜሪካ ለግብፅ ያልተጠበቀ ምላሽ መስጠቷ ተሰምቷል።ግብፅ የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲያደርግ እየጠየቀች ባለችበት ወቅት ያልተጠበቀ ምላሽ ከአሜሪካ እን...
14/10/2025

ኢትዮጵያ አሸንፋለች !!

አሜሪካ ለግብፅ ያልተጠበቀ ምላሽ መስጠቷ ተሰምቷል።

ግብፅ የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲያደርግ እየጠየቀች ባለችበት ወቅት ያልተጠበቀ ምላሽ ከአሜሪካ እንዳገኘች ታውቋል።

በቅርቡ በፕሬዝደንት ትረምፕ የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ተደርገው የተሾሙት ማሳድ ቦውሎስ ሀገራቸው ኢትዮጵያ እና ግብፅ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ድጋፍ እንደምታደርግ ገልፀው የህዳሴ ግድብ ውዝግብ ፖለቲካዊ ሳይሆን ቴክኒካዊ ምላሽ እንዲያገኝ አሳስበዋል።

"ሁላችንም ጉዳዩ እንዲፈታ እና ለሁሉም ተቀባይ እንዲሆን እንፈልጋለን፣ በተለይ ደግሞ በቴክኒክ በኩል፤ ምክንያቱም ጉዳዩ የቴክኒክ ስለሆነ ቴክኒካዊ ምላሽ ያስፈልጋል" ሲሉ አል አረቢያ ለተባለው ሚድያ ተናግረዋል።

"አሁን ግድቡ ስለተጠናቀቀ እውን የሆነ ጉዳይ ነው፣ በዚህ መሬት ላይ ባለ እውነታ ዙርያ መፍትሄ ያስፈልጋል:ግድቡ ስላለቀ ፖለቲካ አታድርጉት" በማለት አሜሪካዊው ዲፕሎማት መናገራቸው

Address

Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sintayehu Abayenh posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share