Sintayehu Abayenh

Sintayehu Abayenh 👉ሚዲያን ለበጎ አላማ ብቻ እንጠቀም 🙏

አዲስ አበባ!!
06/09/2025

አዲስ አበባ!!

ስልክን ጨምሮ ማንኛውንም የኤሌክትሮኒክስ ቁስ ይዞ ወደ ትምህርት ቤት መግባት አይቻልም- ትምህርት ሚኒስቴርከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌት ...
06/09/2025

ስልክን ጨምሮ ማንኛውንም የኤሌክትሮኒክስ ቁስ ይዞ ወደ ትምህርት ቤት መግባት አይቻልም- ትምህርት ሚኒስቴር

ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌት እና የኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን ይዞ ወደ ትምህርት ቤት መግባት እንደማይቻል ትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ።

በተቀመጠው የትምህርት የጊዜ ሰሌዳ መሠረት፤ መስከረም 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ትምህርት ቤቶች ክፍት ሆነው መምህራንና ተማሪዎች ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

እንዲሁም ከመስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የ2018 የመማር ማስተማር ሥራ እንደሚጀመር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ አየለች እሸቴ ለኢዜአ አረጋግጠዋል።

ሁሉም ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕጻናትና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ወላጆች፣ መምህራንና ባለድርሻ አካላት የጀመሩትን የንቅናቄ ተግባር እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

ለዚህም የትምህርት ቤት ምዝገባን እስከ መጨረሻዋ ቀን ድረስ አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎች፤ ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌትና በትምህርት ሥራ ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩና አዋኪ የኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን ወደ ትምህርት ቤት ይዘው እንዳይገቡ በጥብቅ መከልከሉን አስታውቀዋል።

ጳጉሜን 1/2017 ዓ.ም

በማህበራዊ ሚዲያ በተለይ ቲክ ቶክን በመጠቀም ሰዎችን ሲያስፈራራና ሲዝት የነበረው በቲክቶክ ስሙ ቡራ ቡል (Burabull) ወይም ብሩክ ተስፋዬን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ...
06/09/2025

በማህበራዊ ሚዲያ በተለይ ቲክ ቶክን በመጠቀም ሰዎችን ሲያስፈራራና ሲዝት የነበረው በቲክቶክ ስሙ ቡራ ቡል (Burabull) ወይም ብሩክ ተስፋዬን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፤ ግለሰቡ ከዛቻ አልፎ በሁለት ሰዎች ላይ አካላዊ ጉዳት ማድረሱም በምርመራ ታውቋል፡፡
***
ቡራ ቡል (Burabull) ወይም ብሩክ ተስፋዬ ሰዎችን ስጋት ውስጥ የሚከቱ እና አስደንጋጭ የዛቻ ይዘት ያላቸውን እንዲሁም የፀጥታ አካላትን ስም የሚያጠለሹ መልእክቶችን በቲክቶክ ላይ ሲያሰራጭ ነበር፡፡

ግለሰቡ በሚለቃቸው ህገ-ወጥና ያልታረሙ መልዕክቶች ስጋት ውስጥ የገቡና አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰቦች ያቀረቡትን አቤቱታ መነሻ በማድረግ ፖሊስ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል፡፡

ግለሰቡ ከህግ ተጠያቂነት ለማምለጥ ወደ ትግራይ ክልል የሄደ ቢሆንም ከክልሉ ፖሊስ እና ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በቁጥጥ ስር ማዋል እንደተቻለ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎና ነገር መጠቀም እየተቻለ በተቃራኒው ህዝብን ስጋት ውስጥ የሚከቱ መልዕክቶችን ማሰራጨት ተገቢነት የሌለው ተግባር እንደሆነ ፖሊስ አስታውቆ መሰል ድርጊት የሚፈፅሙ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል፡፡

ጋሞ ልማት ማህበር ከኢንዶኔዢያ መንግሥት ጋር ስትራቴጂ አጋርነት በመፍጠር በአዞ ቆዳ ሽያጭ እና ምርጥ ዙሪያ በጋራ ለመሥራት ውይይት ማካሄዱን ገለፀ  ~~~~~~~~~~~~በኢትዮጵያ፣ በጂቡቱና...
06/09/2025

ጋሞ ልማት ማህበር ከኢንዶኔዢያ መንግሥት ጋር ስትራቴጂ አጋርነት በመፍጠር በአዞ ቆዳ ሽያጭ እና ምርጥ ዙሪያ በጋራ ለመሥራት ውይይት ማካሄዱን ገለፀ
~~~~~~~~~~~~
በኢትዮጵያ፣ በጂቡቱና በአፍሪካ ህብረት የኢንዶኔዢያ አምባሳደር ፋይዛል ቼሪ ሲድሃርታ የተመራ የልዑካን ቡድን በጋሞ ልማት ማህበር የአርባምንጭ እርሻ ልማት፣ ጋሞ ባይራ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የአርባምንጭ አዞ ራንች ጉብኝት አድርጓል::

የጋሞ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ዋኖ ዋሎሌ አጠቃላይ የልማት ማህበር እንቅስቃሴ ላይ ገለፃ አድርገዋል::

በተደረገው ውይይት ከአርባምንጭ አዞ ራንችጋር በትብብር በተለይ በአዞ ቆዳ ሽያጭ፣ በምርጥ ዘር ዙሪያ አብሮ ለመሥራት የጋራ መግባባት ላይ መደረሳቸውን ዶ/ር ዋኖ ተናግረዋል:: በተጨማሪ የባይራ አዳሪ ትምህርት ቤት ዲጅታላዝ ከማድረግ ባሻገር በቁሳቁስ ለመደገፍ ተስማምተዋል::

በጉብኝቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቦጋለ ቢታኔ ተግኝተዋል።

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!
ጳጉሜ 1/2017 ዓ.ም

የዶ/ር ስምዖን ሽብሩ  ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ።  የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው  በዛሬው ዕለት በአርባ ምንጭ መድኃኒያለም ካቴድራል ቤተክርስቲያን መካነ መቃብር ተከናውኗል። በሽኝት መርሃግብሩ ላይ ...
06/09/2025

የዶ/ር ስምዖን ሽብሩ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ።

የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው በዛሬው ዕለት በአርባ ምንጭ መድኃኒያለም ካቴድራል ቤተክርስቲያን መካነ መቃብር ተከናውኗል።

በሽኝት መርሃግብሩ ላይ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምስ አድማሱ፣ የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃኪሜ አየለ፣ ሌሎች አመራሮች፣ የስራ ባልደረቦቻቸው፣ ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ የአቶ ታገሰ ጫፎ ተወካይ፣ የጋሞ ዞን ከፍተኛ አመራሮች፤ ዶ/ር ደምስ አድማሱ፣ አቶ ሃኪሜ አየለ፣ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ከማል አብደላ፣ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌን ጨምሮ ሌሎች የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል።

ለጉምቱ ሰው ዶ/ር ስምዖን ሽብሩ ባሕላዊ የለቅሶ ስነስርዓት በርካታ ሕዝብ በተገኙበት ተከናውኗል።

መረጃው የዱቡሻ_ሚዲያ ነው
ጳጉሜ 1/13/2017 ዓ.ም

06/09/2025

ኧረ በሳቅ 🤣🤣 ገደለኝ
የተመታ

የአባይ ውሃ የኢትዮጵያውያን ሳንባና የልዕልናችንም መገለጫ ነው ! (በሰለሞን ኃይለኢየሱስ)ኢትዮጵያውያን የ14 ዘመናት ክራሞታችን ግድቡን በኩራት በመጨረስ ተቋጭቷልና እንኳንም ደስ ያለን !!...
06/09/2025

የአባይ ውሃ የኢትዮጵያውያን ሳንባና የልዕልናችንም መገለጫ ነው !

(በሰለሞን ኃይለኢየሱስ)

ኢትዮጵያውያን የ14 ዘመናት ክራሞታችን ግድቡን በኩራት በመጨረስ ተቋጭቷልና እንኳንም ደስ ያለን !! ከሊቅ እስከ ደቂቅ ሁላችሁም በአንድነት የነገውን የህልማችሁን ቋጠሮ ለመፍታት ከዕለት ጉርሳችሁና ከመቀነታችሁ ሳይተርፍ አባይን በመገደብ ሃገር ገንብታቹሃልና !

መላው የመከላከያ ፣ የደህንነትና የፖሊስ አባላት የጉባ በርሃና ሃሩር የካሳ ክፍያችሁን በግድቡ መጠናቀቅ ብስራቱን አሳይታችሁናልና ለክብራችሁ እጂ እንነሳለን !

የመጀመሪያው የግድቡ ስራ አስኪያጂ ኢንጂነር ስመኘው ነብስህ በአፀዱ ግርጌ ትሁን ስናወሳህ እንኖራለን !

ለግድቡ መጠናቀቅ የህይወት መሰዋዕትነት የከፈላችሁና አካላችሁን ያጣችሁ ዝንተ አለም በልባችን ጓዳ ትኖራላችሁ !

በየዘመናቱ ግድቡን በስራ አስኪያጂነት የመራችሁ ፣ የድርድሩን ሂደት ለፍሬ ያበቃችሁ ዲሎማቶቻችን ፣ ፀሃፍቶቻችን ፣ባለቅኔዎች ፣ አርቲስቶችና ተከራካሪዎቻችን ከፍ ያለ ምስጋናየን ተቀበሉኝ !

በዲፕሎማሲው አውታር የየትኛውም ሃገራት ቺፍ ዲፕሎማት መሪዎች ናቸው ! ዐቢይ አሕመድም የክፍለ ዘመኑ ቺፍ ዲፕሎማት ሆነው ታይተዋል !

በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከቋጥኝ የከበዱ ሴራዎችን በመቋቋም ግዙፉን ግድብ ግዘፍ በነሳ ሃሳብ በመምራት አፍሪቃውያን በተፈጥሮ ሃብታቸው መልማት እንደሚችሉ ግድቡን በማጠናቀቅ አሳይተዋልና እጂ እንነሳለን !

ይህ የዘመናት ቁጭት ያረበበበት ግድብ ከመሰረቱ የነበሩበትን ውስብስብ ችግሮች መንግሎ በመጣል እየበረታ የቀጠለውን የአለማቀፉ ማህበረሰብን ጫና ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ግልምጫና ግፊያ ፣ ኢትዮጵያ እንዳታድግና ዜጎቿም እንዳያልፍላቸው የተሸረቡ አታካች ጉዞዎችን ከመሰረቱ በጥበብ በመለየት ፣ የውሃ ፖለቲካና የዲፕሎማሲውን ውጊያ ፊት ለፊት በመምራት ለፋፃሜ እንዲበቃ አድርገዋልና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን በድጋሚ እናመሰግናለን !

አባይን የኢትዮጵያ መፃኢ እጣ ፋንታ ብይን ሰጭ እንደሚሆን በማመን የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ውጥን አሁን ላይ ሁኜ ሳስበው ብልህነታቸው ይደንቀኛል ።

የጃንሆይን ርዕይ በተግባር የገለጡት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ (ነብስ ይማር) መሰረት ድንጋዮን በማስቀመጥ ኢትዮጵያውያንን ከጫፍ እስከ ጫፍ ያነቃነቁበት መንገድም መሪዎቻችን ለሃገሬ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ምን ያህል ቀናኢ ልቡና እንዳላቸው ከፍ ያለ ትዕምርትን ይሰጠናል ።

በግድቡ ዙሪያ የሶስቱ ሀገራትን (የኢትዮጵያ ፤ ግብፅና ሱዳንን) የመርህ ስምምነት በማስኬድ የግድቡ ግንባታ የጋራ ተጠቃሚነትን እንደሚያሰፍን ሞግተው ያሟገቱንን የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝን ሚና መዘንጋትም ከቶውኑ አይቻለኝም ።

አባይ ከእንግዲህ የኢትዮጵያውን ሳምባ ፣ የልዕልናችንም መገለጫ ነው !

ኢትዮጵያ ለዘለአለም ትኑር !

ጃ !

ዘንድሮ ዮ ማስቃላ ልዩ ነው 💪 የዳውሮ  ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ዳዊት ገበየው  ከጋሞ ዞን የቀረበላቸውን "ዮ ማስቃላ" በዓል ላይ የመታደም ጥሪ ተቀበሉ።ጥሪውን የጋሞ ዞን ምክር ቤት ዋና ...
06/09/2025

ዘንድሮ ዮ ማስቃላ ልዩ ነው 💪

የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ዳዊት ገበየው ከጋሞ ዞን የቀረበላቸውን "ዮ ማስቃላ" በዓል ላይ የመታደም ጥሪ ተቀበሉ።

ጥሪውን የጋሞ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ክብርት ዓለሚቱ ዮሴፍ እና የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የፐብሊክ ሰርቪስ መምሪያ ኃላፊ አቶ መኮንን ቶንቼ አድርሰዋል።

ጥሪውን የተቀበሉት ዳውሮ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ዳዊት ገበየው ለመላው የጋሞ ዞን ህዝብ እንኳን ለ '' ዮ ማስቃላ '' በዓል በሠላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የጋሞ ዘመን መለወጫ '' ዮ ማስቃላ '' በዓል መስከረም 13 / 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር ታውቋል።

ምስጋና ለሚገባው 🙏ጎበዝ በረኛ ብዙ ድካምና ልፋት ይጠይቃል ።የኢትዮጵያ መድህን ድርጅት እና አሰልጣኝ ገብረመድህን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ትልቅ ችግር የሆነዉን ግብ ጠባቂ እጦት የቀረፈ ይ...
06/09/2025

ምስጋና ለሚገባው 🙏

ጎበዝ በረኛ ብዙ ድካምና ልፋት ይጠይቃል ።

የኢትዮጵያ መድህን ድርጅት እና አሰልጣኝ ገብረመድህን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ትልቅ ችግር የሆነዉን ግብ ጠባቂ እጦት የቀረፈ ይህን የመሰለ ጀግናና ገና ለሀገሩ ብዙ መስራት የሚችል በረኛ ብቁ ስላደረጉልን እናመሰግናለን 🙏

ተገልጦና ተነቦ የማያልቅ ብቻውን አንድ ቤተ-መጽሐፍት የሆነ ሠው ስለ  #አርባምንጭ  ከተማ ታሪክና መረጃ ማወቅ ከፈለክ  #ቾምቤ ጋ ተወዳጅ ያኔ ታሪክ ትጠግባለህ👉 #በፈጣሪ አሠፋ (ቾንቤ)(...
06/09/2025

ተገልጦና ተነቦ የማያልቅ ብቻውን አንድ ቤተ-መጽሐፍት የሆነ ሠው

ስለ #አርባምንጭ ከተማ ታሪክና መረጃ ማወቅ ከፈለክ #ቾምቤ ጋ ተወዳጅ ያኔ ታሪክ ትጠግባለህ

👉 #በፈጣሪ አሠፋ (ቾንቤ)(ቼ)🙏🏼🙏🏼🙏🏼🙏🏼

#ፈጣሪ እረጅም እድሜን ከጤና ጋር ያድልህ #ቼ

#ፓርክ ላንድ ኮሌጅ #1 🙏🏼

የፓርክላንድ ኮሌጅ በተለያየ ሙያ  ያሰለጠቸውን ከአንድ ሺህ በላይ ተማሪዎች ለሦስተኛ ዙር ዛሬ አስመርቋልበአርባምንጭ ከተማ የሚገኘው የፓርክላንድ ኮሌጅ ለሦስተኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስክ በ...
06/09/2025

የፓርክላንድ ኮሌጅ በተለያየ ሙያ ያሰለጠቸውን ከአንድ ሺህ በላይ ተማሪዎች ለሦስተኛ ዙር ዛሬ አስመርቋል

በአርባምንጭ ከተማ የሚገኘው የፓርክላንድ ኮሌጅ ለሦስተኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስክ በዲፕሎማ ደረጃ ሲሰለጠኑ የቆዩ ከአንድ ሺ በላይ ተማሪዎች የተለያዩ እንግዶችና የኮሌጁ መምህራን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ኮሌጁ ያከናውናቸው ተግባራት ገለጻ የተደረገ ሲሆን በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ካሰለጠናቸው የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችም እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል።

የጋሞ ዞን አስተዳደር የካቢኔ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጣሰው ከበደን ጨምሮ የዞኑና የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ተመራቂዎችና የተመራቂ ወላጆች በምረቃው ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ባህር ኃይል የባህረኞች የስልጠና ማዕከል ተመረቀ‼️በመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ የተገነባው የኢትዮጵያ ባህር ኃይል የስልጠና ማዕከል በጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ...
06/09/2025

የኢትዮጵያ ባህር ኃይል የባህረኞች የስልጠና ማዕከል ተመረቀ‼️

በመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ የተገነባው የኢትዮጵያ ባህር ኃይል የስልጠና ማዕከል በጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተመርቋል።

ኢትዮጵያ የቀደመ የቀይ ባህር ስመ ገናናነቷን ለመመለስ ዘረፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራች የምትገኝ ሲሆን የነዚህ ጥረቶች አካል የሆነው የባህር ኃይል የስልጠና ማዕከል የሰራዊቱ አዛዦች በተገኙበት ተመርቋል፡፡

ማዕከሉ የሰራዊት መኖሪያ ህንፃዎች፣ መማሪያ ክፍሎች፣ በኤሌክትሮ መካኒክ የሚሰራ መመገቢያ አዳራሽ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም እና ሌሎችንም አካቶ የያዘ ነው።
#ሟር

Address

Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sintayehu Abayenh posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share