Benishangul Gumuz Media

Benishangul Gumuz Media Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Benishangul Gumuz Media, Media/News Company, assosa, Asosa.

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ የክልሉን ህዝብና መንግስት የመረጃ ፍላጎት በጋዜጠኝነት መርህ ላይ የተመሰረቱ አስተማሪ፣አዝናኝ፣ አሳዋቂ ዜናዎች፣ ፕሮግራሞች እንዲሁም ዶክመንተሪዎች ሰርቶ በማቅረብ በኤሌክትሮኒከስ ሚዲያ እና በማህበራዊ ሚዲያ የአየር ሰዓት ሽፋን ለማዋል የተቋቋመ ድርጅት ነዉ።

የተፈጥሮ ጋዝ  -  አስፈላጊው የኢትዮጵያ የከርሰ ምድር ሀብትኢትዮጵያ የከርሰ ምድር ሃብቶቿን ከቀድሞው በተሻለ መንገድ እያለማች ወደመጠቀሙ ተሸጋግራለች፤ በተለይ የተፈጥሮ ጋዝ ሌላኛው የኢኮ...
17/10/2025

የተፈጥሮ ጋዝ - አስፈላጊው የኢትዮጵያ የከርሰ ምድር ሀብት

ኢትዮጵያ የከርሰ ምድር ሃብቶቿን ከቀድሞው በተሻለ መንገድ እያለማች ወደመጠቀሙ ተሸጋግራለች፤ በተለይ የተፈጥሮ ጋዝ ሌላኛው የኢኮኖሚ አቅም ማሳደጊያ መሆኑ ይገለፃል።

የኢትዮጵያ ነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ደስታው መኳንንት (ዶ/ር) በኢቢሲ ዳጉ ላይ ቀርበው በሰጡት ማብራሪያ፤ በርካታ ሀገራት ከድህነት የወጡት የተፈጥሮ ሀብታቸውን ተጠቅመው ነው ይላሉ።

ኢትዮጵያም የከርሰ ምድር ሀብቷን በስፋት ለመጠቀም የሚያስችሉ ሜጋ ፕሮጀክቶችን መጀመሯ ለእድገቷ መነሻ እንደሚሆናት ጠቁመዋል፡፡

የሥራ እድል ለመፍጠር እና ከድህነት ለመውጣት ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚጠይቁ ሥራዎች መከናወን እንደሚገባቸው ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት ለሀገሪቷ እድገት አስፈላጊ ኢንቨስትመንት መሆኑን ነው ያነሱት፡፡

እያደገ የመጣው ኢኮኖሚ የሚፈልገውን የኃይል አቅርቦት ለመሸፈን፣ በቅርቡ ግንባታው የተጀመረው የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት ትልቅ ሚና እንደአለውም አስረድተዋል።

ፕሮጀክቱ 1 ሺህ ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚያችል መሆኑንም አመላክተው፤ ይህም የኃይል አማራጭን እንደሚያሳድግ ነው ያስረዱት።

በ2017 ዓ.ም ብቻ ወደ ሀገር ውስጥ ከገባው 4.3 ቢሊየን ሊትር ነዳጅ ውስጥ አብዛኛው ለተሽከርካሪዎች ፍጆታ የዋለ ቢሆንም 8 በመቶው ለኢንዱስትሪ አገልግሎት መዋሉን አስታውሰዋል።

በመሆኑም ኢትዮጵያ ወደሥራ ያስገባችው የተፈጥሮ ጋዝ እና ሁለተኛ ዙር ፕሮጀክቱ የኃይል አቅርቦት አማራጭን በማስፋት የውጭ ምንዛሬ ወጪን የሚቀንስ መሆኑንም ተናግረዋል።
ይህም ለኢኮኖሚው እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት መገለጹን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።

በማህበረሰቡ ዘንድ የሚጠበቁ ሰብዓዊ አገልግሎቶችን ለማሟላት አበክሮ  እየሰራ መሆኑን ልማት ለሁሉም ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ገለጸ፡፡ድርጅቱም ንቁ ዜጋ ለማፍራት በከተማው ያሉ ሶስት ሁለተኛ ...
17/10/2025

በማህበረሰቡ ዘንድ የሚጠበቁ ሰብዓዊ አገልግሎቶችን ለማሟላት አበክሮ እየሰራ መሆኑን ልማት ለሁሉም ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ገለጸ፡፡

ድርጅቱም ንቁ ዜጋ ለማፍራት በከተማው ያሉ ሶስት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ 2 ሚሊየን ወጪ የተገዛ የኤሌክትሮኒክ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡

የልማት ለሁሉም ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ጀቤሳ ሰንበታ እንደገለጹት ድርጅቱ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎችን አካታች በማድረግ ንቁ ዜጋን ለማፍራት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ባላፉት አመታትም በክልሉ የነበረው የሰላም እጦት ተከትሎ ሰላምን ለማስፈንና የተፈናቀሉ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም የድርሻውን አስተዋጽዖ ሲያደርግ መቆየቱንም አስታውሰዋል፡፡

ድርጆቱ በሰብዓዊ መብት ላይም አትኩሮ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይም የወገናቸውን ድጋፍ የሚሹ ተማሪዎችን ከመደገፍ ባለፈ ለትምህርት ቤቶች ላይ የቁሳቁስ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ለዚህም በአሶሳ ከተማ ላሉ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ከ2 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው ስድስት የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን ድጋፍ አድርጓል ።

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ፍቃዱ በየነ እንዳሉትም የትምህርት ዘርፉን ለማዘመን በድርጅቱ በኩል ለተደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ ኡስማን እንዳሉት ደግሞ ድጋፉ በትምህርት ቤቶች እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮችን የሚቀርፍ መሆኑን ጠቁመው ክልሉም ሞዴል ትምህርት ቤቶችን ለማፍራት አትኩሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ድርጅቱ ንቁ ዜጋን ለማፍራት የጀመራቸውን ስራዎች ማስቀጠል እንዳለበትም ገልጸዋል።

ድጋፉን የተረከቡ መምህራን በበኩላቸው ድርጅቱ ከሚሰራቸው ዘርፈ ብዙ ስራዎች በተጨማሪ ብቁ ዜጋን ለማፍራት እየሰራ ያለውን ስራ እንዲያጠናከር ጠይቀዋል፡፡

በሞላሽ አሸንፍ

ላለፉት 10 ቀናት በንድፈ ሀሳብና በተግባር የወሰድነው ስልጠና ለቀጣይ ተልዕኮ ስንቅ ሆኖናል ሲሉ "የCaf D license" ሰልጣኞች ተናገሩ። ላለፉት 10ቀናት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽ...
17/10/2025

ላለፉት 10 ቀናት በንድፈ ሀሳብና በተግባር የወሰድነው ስልጠና ለቀጣይ ተልዕኮ ስንቅ ሆኖናል ሲሉ "የCaf D license" ሰልጣኞች ተናገሩ። ላለፉት 10ቀናት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አማካኝነት የተሰጠውን "የCaf D license" ስልጠና ተከትሎ የታዳጊዎች የስፖርት ፌስቲቫል ተካሃዷል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እግር ኳስ ፌደሬሽን ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የታዳጊዎች አሰልጣኞች "የCaf D license ስልጠና" ሰጥቷል።

ስልጠናውን አስመልክቶ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚድያ አስተያየታቸውን የሰጡ ሰልጣኞች እንዳሉት ላለፉት 10 ቀናት በንድፈ ሀሳብና በተግባር የወሰዱት ስልጠና
ግቡን የመታ ነበር ብለዋል።

ተተኪዎችን ለማፍራት ታዳጊዎች ላይ መስራት መሰረት መሆኑን የገለጹት ሰልጣኞቹ ለዚህም ስልጠናው አስፈላጊውን ዕውቀት እንዳስጨበጣቸው ጠቁመዋል።

በቀጣይም ወደየመጡበት አካባቢ ሲመለሱ ያገኙትን መሰረታዊ ዕውቀት ወደ ተግባር እንደሚቀይሩት ተናግረዋል ።

ስልጠናውን የሰጡት ኢንስትራክተር አለባቸው ተገኝ በበኩላቸው ሰልጣኞች በቆይታየው "ለ Caf D license" የሚያስፈልጋቸውን ክህሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል ።

ስልጠናው ተተኪዎችን ለማፍራት ታልሞ የተሰጠ መሆኑን የገለጹት ኢንስትራክተር አለባቸው ተገኝ ሰልጣኞችም ያገኙትን መሰረታዊ ክህሎት ወደ ተግባር እንዲቀይሩት አሳስበዋል ።

የክልሉ እግር ኳስ ፌደሬሽንም ስልጠናው በተግባር ላይ ለመዋሉ አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል ።

በስንታየሁ አድማስ

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የሀገርና የትዉልድ አደራን መወጣት ነው ሲሉ የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡እንደነዋሪዎቹ ገለጻ ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ላይ ያላት የባለቤትንት ...
17/10/2025

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የሀገርና የትዉልድ አደራን መወጣት ነው ሲሉ የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡

እንደነዋሪዎቹ ገለጻ ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ላይ ያላት የባለቤትንት ጥያቄ ዛሬ የተፈጠረ ሳይሆን በታሪክ ዓለም የሚያዉቀዉ ጉዳይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

የባህር በር ጉዳይ ጥያቄ ማንሳት ብቻ ሳይሆን ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ጥያቄዉ የቅንጦት ሳይሆን የኢትዮጵዊያን የህልዉና ጉዳይ መሆኑን የገለጹት ነዋሪዎቹ የዓለም ማህበረሰብም ይህንኑ ተገንዝቦ ጉዳዩ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ ከኢትዮጵያ ጎን እንዲቆም ጠይቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ ተመሳሳይ ጉዳይ የሆነዉንና የማይሞከር ይመስል የነበረዉን ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከመጀመር አልፎ ብዙ ተቃዉሞና ማስፈራራት ሳይበግራት እዉን ማድረጓ በእዉነታ ላይ ተመስርታ እንደምትራመድ ማሳያ ነዉም ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያዊያንም ዳግም አድዋ ተደርጎ በተቆጠረዉ የህዳሴ ግድቡ ላይ ያሳዩትን አንድነትና መተባበር አሁንም በኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ ላይ መድገም እንዳለባቸዉም አብራርተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማትና እድገት የማይፈልጉ አካላት በሚያነሱት የተሳሳተ ሀሳብ ተመርተዉ የባህር በር ጥያቄዉ ግጭት የመፈለግና አላስፈላጊ የሚመስላቸዉ ኢትዮጵያዊያንም ጉዳዩን በደንብ በማጤን አንድነታቸዉን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ምንም የግጭት ፍላጎት የሌላትና በመርህና በመነጋገር ላይ ተመስርታ ያለ አግባብ የሄደባትን የባህር በር ለማስመለስ እየተንቀሳቀሰች ነዉ ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ በዚህም ላይ እንደዜጋ የሚጠበቅባቸዉን ሁሉ ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸዉንም ገልጸዋል፡፡

ሪፖርተራችን ሙሉቀን ባልቻ እንደዘገበዉ፡፡

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዕድሚያቸው ከ1 ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት እየተሰጠ ያለው የወባ መከላከያ ክትባት በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ ...
17/10/2025

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዕድሚያቸው ከ1 ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት እየተሰጠ ያለው የወባ መከላከያ ክትባት በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረበ።

ቢሮው የክትባቱን አስፈላጊነትና ጠቀሜታ በሚመለከት ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር እንዳሉት የወባ በሽታ ስርጭቱ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ገልፀው ስርጭቱን ለመከላከል ኬሚካል የመርጨት፣ አጎበር የማሰራጨት፣ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማፋሰስ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

ህጻናትና የሚያጠቡ እናቶች ለወባ በሽታ ይበልጥ ተጋላጭ ናቸው ያሉት አቶ አብዱልሙኒየም ስርጭቱ ከፍተኛ በሆነባቸው አካባቢዎች እንደሀገር በ58 ወረዳዎች በክልሉ ደግሞ በ13 ወረዳዎች ላይ ዕድሚያቸው ከ1 ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት የወባ በሽታ መከላከያ ክትባትን መስጠት መጀመሩን አሳውቀዋል ።

የበወባ በሽታ መከላከያ ክትባቱ የሚሰጥባቸው ወረዳዎችን ጤና ሚኒስቴር ያለፉት 5 ዓመታትን ሪፖርቶች መነሻ በማድረግ መምረጡንም ምክትል ኃላፊው ገልጸዋል ፡፡

በተመሳሳይ ህጻናት በተወለዱ በ24 ሰዓታት ውስጥ የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባት እንደሚሰጥም ጠቁመዋል ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ እንዳሉት የወባ በሽታ በህብረተሰቡ ላይ እስከ ሞት የሚደርስ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ በህብረተሰቡ መዘናጋት እንደሌለበት አሳስበዋል፡፡

ሁሉም ባለድርሻ አካላትም ስለክትባቱ ጠቀሜታ ባገኙት ግንዛቤ ልክ ለስኬታማነቱ የሚጠበቅባቸውን ተሳትፎ ማድረግ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡

የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው መንግስት የዜጎችን ጤና ለማስጠበቅ ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ በክትባት መልኩ የሚሰጡ ህክምናዎች ተጠቃሽ ናቸው ብለው የወባ በሽታ መከላከያ ክትባቱ ሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ እንዲደረግ ጠይቀዋል ።

ዘገባው የሪፖርተራችን ሀና መንገሻ ነው ።

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበሩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለአሶሳ ከተማ አስተዳደር የአምቡላንስ ድጋፍ አደረገ። ‎በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበሩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት...
17/10/2025

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበሩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለአሶሳ ከተማ አስተዳደር የአምቡላንስ ድጋፍ አደረገ።

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበሩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሞጎስ ነገሮ በድጋፍ ርክክቡ ወቅት እንዳሉት ድጋፉ በከተማ አስተዳደሩ የሚስተዋለውን የአምቡላንስ ዕጥረት ለመቅረፍ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል ።

ማህበሩ በነፍስ አድን እና ሌሎች በጎ ተግባራት ላይ እየሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ ሞጎስ በዛሬ ዕለት የተደረገው የአምቡላንስ ድጋፍም አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አምቡላንሱም የጥራት ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን የገለጹት አቶ ሞጎስ ከተማ አስተዳደሩም ለታለመለት ዓላማ ብቻ መጠቀም እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

‎የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ካንቲባ ኢንጅነር ፍቃዱ በየነ የቀይ መስቀል ማህበር እያደረገ ላለው ሁለንተናዋ ድጋፍ አመስግነው ድጋፉ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኃላፊ ሲስተር ሲቱ አልበሽር በበኩላቸው በቀይ መስቀል ማህበር የተደረገው የአምቡላንስ ድጋፍ ተቋሙ ያለበትን የተሽከሪካሪ ችግር እንደሚያቃልልና የብዙ እናቶችን ስቃይ የሚቀንስ መሆኑን ገልጸው ለተደረገላቸው ድጋፍ አመስግነዋል፡፡

አምቡላንሱ ለታለመለት ዓለማው ብቻ እንደሚውልም አረጋግጠዋል፡፡

ከአምቡላንስ ድጋፉ ጎን ለጎንም ለማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳም የአምቡላንስና መድኃኒት ድጋፍ ተደርጓል፡፡

በሀይማኖት አዳሜ

የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር በፓዊ ወረዳ መካነ ሰላም ጤና ጣቢያ ለእናቶች ማቆያ ክፍል አገልግሎት የሚውል ከ9 መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።ማህበሩ ከUNFPA ባገኘው ...
17/10/2025

የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር በፓዊ ወረዳ መካነ ሰላም ጤና ጣቢያ ለእናቶች ማቆያ ክፍል አገልግሎት የሚውል ከ9 መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

ማህበሩ ከUNFPA ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ በፓዊ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ለመካነ ሰላም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ከ9 መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት የተለያዩ መገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ቀልቤሳ ተሬሳ፥ ማህበሩ በክልሉ በስድስት ወረዳዎችና በአንድ ከተማ አስተዳደር እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው፥ በተመረጡ ወረዳዎች የሚገኙ ጤና ጣቢያዎች ለወላድ እናቶች ምቹ አገልግሎት እንዲሰጡ ከማስቻል ባለፈ የተጠናከረ የጤና ትምህርት በመስጠት ረገድ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ማህበሩ ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራባቸው መስኮች መካከል በግጭትና ተያያዥ ችግሮች ጉዳት ለደረሰባቸው አካባቢዎች ጥራት ያለው የእናቶችና ህፃናት አገልግሎት መስጠት፣ ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች መቅጠርና የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን መስጠት መሆኑን አክለው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር በመካነ ሰላም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የእናቶች ማቆያ ክፍል ምቹ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማስቻል የመኝታ አልጋዎች፣ፍሪጅ፣ላውደሪ ማሽን፣ቴሌቪዥን፣የተሟላ የማብሰያ ቁሳቁስና የምግብ እህል ድጋፍ አድርጓል።

የፓዊ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ይርጋ አሰፋ እንደገለፁት ደግሞ፥ ወላድ እናቶች ወደ ጤና ተቋማት ሲመጡ እንደቤታቸው በመቁጠር በቆይታቸው ጤናማና ደስተኛ ሆነው እንዲመለሱ ለማስቻል ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

ጤና ጣቢያው በሙሉ አቅም አገልግሎት እንዲሰጥ የተጀመረውን ርብርብ ማህበረሰቡ ግቢውን በማስዋብና በመጠበቅ ሚናውን መወጣት እንዳለበት ዋና አስተዳዳሪው መልዕክት አስተላለፈዋል።

የፓዊ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ግዛቸው ላሎቶ፥ የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር ከUNFPA ጋር በመተባበር ያበረከተው ድጋፍ ህክምናው ለማሳለጥ ወሳኝ በመሆኑ ንብረቱን በአግባቡ በመያዝ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል ብለዋል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የእናቶችና ህጻናት ቡድን መሪ አቶ አለፎም ረዳ በበኩላቸው፤ማህበሩ እያደረገ ያለው ድጋፍ በክልሉ ውስጥ የእናቶችና ህጻናትን ጤና በዘላቂነት ለመጠበቅ በጤና ተቋማት ላይ የቁሳቁስ ዕጥረትን ከመቅረፍ ባለፈ እናቶች በሰለጠነ ባለሙያ እንዲወልዱ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በክልሉ በተጠመረጡ 11 ጤና ጣቢያዎች ላይ ለሚገኙ የእናቶች ማቆያ ክፍሎች በተሟላ አቅም ወደ ስራ እንዲገቡ የተደረገው መሰል ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውን የዞኑ ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዘግቧል።

17/10/2025

የቀን 6፡00 የአማርኛ ዜና ጥቅምት 07/2018 ዓ.ም

በከተማ አስተዳደሩ እየተባባሰ የመጣዉን የወባ በሽታ ስርጭት ለመግታት ሁሉም ማህበረሰብ በቅድመ መከላከል ስራዎች ላይ የበኩሉን ርብርብ እንዲያደርግ ተጠቆመ፡፡ በአሶሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መ...
17/10/2025

በከተማ አስተዳደሩ እየተባባሰ የመጣዉን የወባ በሽታ ስርጭት ለመግታት ሁሉም ማህበረሰብ በቅድመ መከላከል ስራዎች ላይ የበኩሉን ርብርብ እንዲያደርግ ተጠቆመ፡፡

በአሶሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ የመሰረታዊ ጤና አገልግሎት እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ቡድን መሪ አቶ ተፈሪ ገርቢ እንደተናገሩት በከተማ አስተዳደሩ በአሁኑ ሰዓት የታየዉ የወባ ስርጭት ባፉት 5 ዓመታት ዉስጥ ከነበረዉ ሁለት እጥፍ መሆኑን አስታዉቀዋል፡፡

ለአብነትም ባለፉት ሶስት ተከታታይ ወራት ዉስጥ የወባ ምርመራ ካደረጉ 29 ሺህ በላይ ታካሚዎች 10 ሺህ 3 መቶ ያህሉ ወባ እንደተገኘባቸዉ ገልጸዉ ከታካሚዎች ዉስጥ ደግሞ 23 በመቶዎቹ ህጻናት መሆናቸዉን ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይ እየታዩ ካሉ የወባ ተጠቂዎች ሁኔታ በከተማዉ የወባ ትንኝ መራቢያ አካባቢዎች መኖራዉን የሚያመላክት ነዉ ያሉት ቡድን መሪዉ በተለይም በከተማዉ እየተስፋፋ የመጣዉ የህዝብ ቁጥር መጨመር አባባሽ ስለመሆኑም አመላክተዋል፡፡

በከተማ አስተዳደሩ የሰልጋሉ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ ታሪኩ ለገሰ በበኩላቸዉ በጤና ጣቢያቸዉ በአራት ሳምንታት ከታከሙ 1ሺህ 9መቶ 70 ታማሚዎች 6መቶ 9ኙ ወባ እንደተገኘባቸዉ ገልጸዋል፡፡

በቁጥጥሩና በቅድመ መከላከሉ ረገድ በየእለቱ ታካሚዎች ዉጤታቸዉን በሚጠብቁበት ሰዓት የጥንቃቄ መልዕክቶች እተላለፉ ነዉ ያሉት ኃላፊዉ ያም ሆኖ የታማሚ ቁጥር እየጨመረ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ህብረተሰቡም የአካባቢ ቁጥጥር ስራዎችንና አጎበርን በአግባቡ እንዲጠቀም የጠቆሙት ኃላፊዉ በተለይም የበሽታዉ ምልክት ሲሰማቸዉ ጊዜ ሳይወስዱ ወደ ህክምና ተቋም በመምጣት ተገቢዉን ህክምና እንዲያገኙም አሳስበዋል፡፡

በሰልጋሉ ጤና ጣቢያ ሲገለገሉ ያገኘናቸዉ ታካሚዎችም በጤና ተቋሙ የሚሰጠዉ አገልግሎት ፈጣንና የተሻለ መሆኑን ገልጸዉ በተለይም የወባ በሽታ ሲገኝባቸዉ መድሃኒቱ በነጻ እንደሚሰጣቸዉ ተናግረዋል፡፡

የጤና ጣቢያዉ ከሚያስተናግደዉ ህዝብ ብዛትና ከሚሰጠዉ አገልግሎት አንጻር ተጨማሪ የህክምና መሳሪያዎች ተሟልተዉለት አገልግሎቱን አስፍቶ እንዲሰራ የሚመለከታቸዉ አካላት አስፈላጊዉን ትኩረት እንዲሰጡም ጠቁመዋል፡፡

ዘገባዉ የሪፖርተራችን ሙሉቀን ባልቻ ነዉ፡፡

ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በኩታገጠም ማልማት ከጀመሩ ወዲህ በግብርናው ዘርፍ የላቀ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን የአቡራሞ ወረዳ  አርሶ አደሮች ገለፁ።በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአቡራሞ ወረዳ በተ...
17/10/2025

ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በኩታገጠም ማልማት ከጀመሩ ወዲህ በግብርናው ዘርፍ የላቀ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን የአቡራሞ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአቡራሞ ወረዳ በተያዘው የመኸር እርሻ ከ125 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች በዘር መሸፈኑን የአቡራሞ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስታውቋል።

በአሶሳ ዞን የአቡራሞ ወረዳ ብልድግሉ ቀበሌ ሞዴል አርሶ አደር አለሚን መሀመድ ኩታገጠም የአስተራረስ ዘዴን መተግበር ከጀመሩ ወዲህ ውጤታማ እንዳደረጋቸው ገልፀዋል።

በዘንድሮው የመኸር እርሻም 15 ሄክታር የበቆሎ ማሳ በኩታ ገጠም በማልማት ጥሩ ውጤት እንደሚጠብቁ ይናገራሉ ።

ሌላኛው የዚሁ ቀበሌ ሞዴል አርሶ አደር ፋይሰል ኑሬን በበኩላቸው በቴክኖሎጂ ታግዘው መስራት በወረዳው ስኬታማ ከሚባሉ ሞዴል አርሶ አደሮች መካከል አንዱ መሆናቸውን ጠቅሰው የዘር ብዜትን በማባዛትም ከራሳቸው አልፈው ወደ ሌሎች የሀገራችን ክፍሎች እየላኩ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

አርሶ አደሩ አክለውም በአሁኑ ወቅት 10 ሄክታር የበቆሎ ማሳ ዘር ብዜትን ተጠቅመው በኩታ ገጠም እያለሙ መሆናቸውና ተናግረዋል ።

በአቡራሞ ወረዳ በተያዘው በ2017/2018 የምርት ዘመን በመኸር እርሻ ከ125 ሺህ በላይ ሄክታር የእርሻ ማሳ በተለያዩ የሰብል አይነቶች በዘር መሸፈናቸውንና ከዚህ ውስጥ ደግሞ ከ77 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም የለማ መሆኑን የወረዳው ግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አታላይ ደረጀ ገልፀዋል ።

ኃላፊው አያይዘውም የወረዳው አርሶ አደሮች ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂና ሜካናይዜሽንን የመጠቀም ባህል በማደጉ ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች የሚተርፉ ውጤታማ አርሶ አደሮች መፈጠራቸውን አስረድተዋል ።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባበክር ሀሚድ እንዳሉት ደግሞ አዳዲስ የእርሻ መሬቶችን በማዘጋጀት አርሶ አደሩ የተሻለ ምርት እንዲያገኝ በወረዳው ሰፊ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል ።

አርሶ አደሮች መሬት የምትሰጠውን ጥቅም የተረዱ በመሆናቸውንም ጠቅሰዋል ።

ሪፖርተራችን ሁሴን መሀመድ እንደዘገበው

17/10/2025

Arbic news 07 02 2018 E.C

17/10/2025

Benshangul news 07 02 2018 E.C

Address

Assosa
Asosa
251

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Benishangul Gumuz Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Benishangul Gumuz Media:

Share