Assosa Online

Assosa Online እውነተኛ ታማኝ እና ወቅታዊ መረጃዎችን እናደርሳለን፡፡

የጋዛ ተፈናቃዮችን በኢትዮጵያ ለማስፈር የቀረበውን እቅድ አሜሪካዊው ሴናተር ‹‹አሳፋሪና አሳዛኝ ነው›› አሉት፡፡ የአሜሪካው ሴናተር ክሪስ ዛን ሆለን ዛሬ በኤክስ ገፃቸው ላይ በፃፉት አስተያ...
19/07/2025

የጋዛ ተፈናቃዮችን በኢትዮጵያ ለማስፈር የቀረበውን እቅድ አሜሪካዊው ሴናተር ‹‹አሳፋሪና አሳዛኝ ነው›› አሉት፡፡ የአሜሪካው ሴናተር ክሪስ ዛን ሆለን ዛሬ በኤክስ ገፃቸው ላይ በፃፉት አስተያየት ፍሊስጤማዊያንን ከጋዛ አስወጥቶ በሌሎች አገራት ውስጥ ለማስፈር እቅድ መውጣቱን ማንበባቸውን ጠቅሰዋል፡፡

እስራኤል ባወጣችው በዚህ እቅድ መሰረት የጋዛ ተፈናቃዮችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በተወሰኑ አገራት ለማስፈር የአሜሪካን እገዛ መጠየቋን አውስተዋል፡፡ ሴናተሩ ጨምረውም ‹‹ይህ እቅድ አሳፋሪና አሳዛኝ ነው›› በማለት ተቃውሟቸውን ገልፀዋል፡፡

ሲቀጥሉም ‹‹ፍሊስጤማዊያንን ከጋዛ ለማንሳት በሚደረገው በዚህ ጥረት ላይ አሜሪካ ከማንም ወገን መቆም የለባትም፡፡ ለዚህ ድርጊትም አንተባበርም›› ብለዋል፡፡ የዲሞክራት ፓርቲ አባል የሆኑት እኚህ ሴናተር ለፍሊስጤማዊያን ድምፅ በመሆን ከዚህ ቀደም አስተያየት በመስጠት የሚታወቁ ናቸው፡፡

ዘ-ሐበሻ ዜና

የኮሪደር መብራቱ ተስተካክሏልስለ ፈጣን ምላሻቹህ እናመሰግናለንከተማችን በምሽት እንዲህ ጨረቃ ሁና ስናያት ልባችን ሀሰት ይደረጋል።
19/07/2025

የኮሪደር መብራቱ ተስተካክሏል
ስለ ፈጣን ምላሻቹህ እናመሰግናለን
ከተማችን በምሽት እንዲህ ጨረቃ ሁና ስናያት ልባችን ሀሰት ይደረጋል።

 ችግኝ ይዞ ታገቢኛለሽ ተጀምሯል ❤️🌳ፍቅር በዛፍ ተክል ታጅቦ!ቀድሞ ወንዶች የጣት ቀለበት ተንበርክከው "ታገቢኛለሽ?" ብለው የጋብቻ ጥያቄ የሚያቀርቡበት ልማድ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ደግሞ...
18/07/2025


ችግኝ ይዞ ታገቢኛለሽ ተጀምሯል ❤️🌳
ፍቅር በዛፍ ተክል ታጅቦ!

ቀድሞ ወንዶች የጣት ቀለበት ተንበርክከው "ታገቢኛለሽ?" ብለው የጋብቻ ጥያቄ የሚያቀርቡበት ልማድ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ደግሞ አዲስ እና ትርጉም ያለው አዝማሚያ እየተስተዋለ መጥቷል።

በምስሉ ላይ እንደምታዩት፣ አሁን አሁን ፍቅረኛሞች ችግኝ በመያዝ "ውዴ ታገቢኛለሽ?" እያሉ የጋብቻ ጥያቄያቸውን ማቅረብ ተጀምሯል።

18/07/2025

"ትራም የተመረጡት አሜሪካን ሊመሩ እንጂ የአለም ሀገራት ንጉሠ ነገሥት ሊሆኑ አደለም። በረባ ባልረባው የቀረጥ ጨዋታ ምክንያታዊ አይደለም።"
የብራዚል ፕሬዚዳንት

መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚገባበት እለት መሆኑ ተነገረየዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የፈተና ውጤት ጳጉሜ ላይ ይፋ ይሆናልየትምህርት ካላንደርን በአግባቡ...
17/07/2025

መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚገባበት እለት መሆኑ ተነገረ

የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የፈተና ውጤት ጳጉሜ ላይ ይፋ ይሆናል

የትምህርት ካላንደርን በአግባቡ አክብሮ በመስራት የፈተና ጊዜያትንም ላለመሻማት ከመስከረም ጀምሮ ጥብቅ አሰራር እንደሚኖር ተገልፆል።

እንደ ሀገር እኩል ውጤት ተናግሮ በእኩል ትምህርት ለማስጀመር ሲባል ቀሪ ያልተፈተኑ ተፈታኝ ተማሪዎችን ጠብቆ ማስጨረስ እንደሚገባ የተናገሩት የትምህርት ሚኒስትሩ በራሳቸው ፈቃድና ምክንያት አስቀድመው ፈተና ላይ ካልተቀመጡት በቀር ሌሎቹ የመመዘኛ መስፈርቱ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል።

, ትምህርት ሚንስቴር

ብዙዎችን ሲያከራክር የነበረው የገቢ ግብር አዋጅ ዛሬ ፀድቋል
17/07/2025

ብዙዎችን ሲያከራክር የነበረው የገቢ ግብር አዋጅ ዛሬ ፀድቋል

17/07/2025

የኮሪደሩ መብራት ምን ሁኖ ነው ፤ ሁለት ቀን በርቶ ጠፋ እኮ 🤔
ያላለቀ ነገር አለ እንዴ!?

አውሮፓ በገባ በ8ኛው ቀን በፆታዊ ትንኮሳ ፍርድ ቤት የቀረበው ኢትዮጵያዊየ38 አመቱ ኢትዮጵያዊው ስደተኛ  በእንግሊዝ በትምህርት ቤት ልጃገረዶች ላይ ፆታዊ ትንኮሳ ፈፅሟል በሚል ክስ ቀረበበ...
16/07/2025

አውሮፓ በገባ በ8ኛው ቀን በፆታዊ ትንኮሳ ፍርድ ቤት የቀረበው ኢትዮጵያዊ
የ38 አመቱ ኢትዮጵያዊው ስደተኛ በእንግሊዝ በትምህርት ቤት ልጃገረዶች ላይ ፆታዊ ትንኮሳ ፈፅሟል በሚል ክስ ቀረበበት

ሜልኦንላይን እንደዘገበው በሁለት ቀናት ውስጥ በሶስት የተለያዩ ወሲባዊ ጥቃቶች የተከሰሰው ስደተኛ፣ ወደ እንግሊዝ የገባው በትንሽ ጀልባ ስምንት ቀናት ቀደም ብሎ ነበር።

የ38 ዓመቱ ሀዱሽ ገብረስላሴ በኮልቼስተር ፍርድ ቤት በቀረበ ጊዜ፣ የትምህርት ቤት ልጃገረዶችን ዒላማ ያደረገ ተገቢ ያልሆነ ወሲባዊ ባህሪ ፈጽሟል በሚል በይፋ ክስ ተመስርቶበታል።

ፓርላማው ፍቃደኛ ከሆነ በስራ መውጫ ስዓት ፌስታል ይዘው ከሆቴል ተመላሸ ምግብ የሚለምኑ ሰራተኞች መኖራቸውን ማሳየት እንደሚችል የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ተናገረኮንፌዴሬሽን ...
14/07/2025

ፓርላማው ፍቃደኛ ከሆነ በስራ መውጫ ስዓት ፌስታል ይዘው ከሆቴል ተመላሸ ምግብ የሚለምኑ ሰራተኞች መኖራቸውን ማሳየት እንደሚችል የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ተናገረ

ኮንፌዴሬሽን ይህን ያለው በቅርብ ይጸድቃል ተብሎ በሚጠበቀው የፌዴራል ገቢ ግብር ማሻሽያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት ባካሄደበት ወቅት ነው፡፡

ከገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከሰራተኛው ለመቁረጥ የቀረበው ሃሳብ ውስብስብ የዋጋ ንረትን እና የድህነት መጠንን ያላገናዘብ ከመሆኑም በላይ ማጭበርበር ሳይኖር በአግባቡ ከደሞዙ ግብር የሚከፍለውን ሰራተኛ ከችግር የሚውጣ ሳይሆን ችግር ውስጥ የሚከት እንደሆነ የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ፕሬዘዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ተናግረዋል፡፡

ሰራተኛው በቀን አንድ ጊዜ በልቶ መዋል አልቻለም ያሉት ፕሬዝዳንቱ ምክንያቱ ደግሞ በርካታ ወጪዎች ስላሉበት ነው ብለዋል፡፡

ተቀጣሪው ሰራተኛ ህክምና ሄዶ መታከም የማይችልበት ሁኔታ ላይ ደርሷል ሲሉ ያስረዱት አቶ ካሳሁን እውነት ለመናገር አንድ ሰው በ5 ሺ ብር ደሞዝ ቤት ኪራይ ይከፍላል ፣ ይበላል፣ ልብስ ይለብሳል ፣ ህክምና ይሄዳል ብለዋል፡፡

ህክምናውን እንተው እየጸለየ ይኑር ፤ቤት ኪራይውንም እንተወው በበረንዳ በሰዎች ላይ በጥገኝነት ይኑር ግን በቀን አንድ ጊዜ እየበላ መኖር የለበትም ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

አንድ ድርጅት ከትርፉ 35 በመቶ ግብር ይከፍላል ያሉት የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ሰራተኛውም 35 በመቶ ይከፍላል ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

ነጋዴውም፣ ድርጅቱም ከትርፉ ነው እኮ 35 በመቶ የሚከፍለው ሲሉ ያስረዱት አቶ ካሳሁን ሰራተኛው ግን ከትርፉ ሳይሆን ከሚበላው ላይ ነው የሚከፍለው ይህ እንዴት እኩል ይሆናል ? ብለዋል፡፡

ስለሰዎች ስናስብ ልማት ለማስቀጠል ነው ያሉት አቶ ካሳሁን ልማት ያለ ሰው ሰው ያለ ልማት ሊኖሩ አይችሉም ሲሉ አስረድተዋል፡፡

ስለዚህም የሰራተኛውንም ጫና የመንግስትን ዓላማ ታሳቢ ያደረገ የግብር ምጣኔ መጣል አለበት ሲሉ ተናግረዋል፡፡

አሁን በማሻሻያው የግብር መነሻ 2000 ሺ ብር ሲሆን ምን ታሳቢ ተደርጎ ነው? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

አንድ ስልት ሲሰራ ሰውን ማኖር አለበት ያሉት አቶ ከሳሁን ይህ መነሻ ግን ታሳቢ አላደረገም ብለዋል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው እንደገና ከሚመለከታቸው ሰዎች ጋር ቢመካከር ሲሉ የጠየቁት አቶ ካሳሁን ፎሎ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ኑሮን አልቻሉም፤ ቋሚ ኮሚቴው ፍቃደኛ ከሆነ ከስራ ሲውጡ ፌስታል ይዘው ሆቴል አካባቢ ቆመው ሲለምኑ አብረን ማየት እንችላለን ብሏል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር በኩሉ አዋጁ በይድረስ ይድረስ የተዘጋጀ ሳይሆን ሁለት ዓመት ጥናት ተሰርቶበት የተዘጋጀ ማሻሻያ ነው ብሏል፡፡

 2 ልጆች ተጎደተዋልዛሬ ከሰዓታት በፊት፣  መዲናችን አዲስ አበባ ውስጥ ወጣቶች በቲክቶክ ላይቭ (TikTok Live) በቀጥታ ስርጭት ሲፋለሙና ሲጎዳዱ ታይተዋል። እነዚህ ወጣቶች በቡድን ተደ...
13/07/2025


2 ልጆች ተጎደተዋል

ዛሬ ከሰዓታት በፊት፣ መዲናችን አዲስ አበባ ውስጥ ወጣቶች በቲክቶክ ላይቭ (TikTok Live) በቀጥታ ስርጭት ሲፋለሙና ሲጎዳዱ ታይተዋል።

እነዚህ ወጣቶች በቡድን ተደራጅተው፣ ከተማዋ ውስጥ ግጭት ሲፈጥሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በቲክቶክ በቀጥታ ስርጭቱን ሲከታተሉ ቆይተዋል።

በዚህ ግዜ ወጣቱ ትውልድ በትጋት ሰርቶ ለራሱም ሆነ ለቤተሰቡ ብሎም ለአገሩ በሚጠቅምበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ አንዳንድ ወጣቶች የድሮውን "የ90ዎቹን ሙድ" እያራመዱ በቡድን ተደራጅተው ከተማዋን ማወክ እጅግ አደገኛ አካሄድ ነው።

ይህ ድርጊት የከተማዋን ሰላምና ፀጥታ ከማወኩም በላይ፣ ለከፋ ችግር ሊያመራ የሚችል በመሆኑ ትኩረት ያሻዋል።

የአሶሳ ከተማ የመጀመሪያ ዙር ኮሪደር ልማት በዓሁኑ ሰዓት የክልል እና ፌደራል ከፍተኛ ባለስልጣናት በተገኙበት እየተመረቀ ይገኛል።
12/07/2025

የአሶሳ ከተማ የመጀመሪያ ዙር ኮሪደር ልማት በዓሁኑ ሰዓት የክልል እና ፌደራል ከፍተኛ ባለስልጣናት በተገኙበት እየተመረቀ ይገኛል።

Address

Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Assosa Online posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Assosa Online:

Share