በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት''Prosperity Party Office"

25/08/2025

እንችላለን ካልን ሁሉንም እንችላለን…….ህዳሴ…. የኢትዮጵያውያን የአንድነት እና የጽናት ማሳያ

ሰው ተኮር ተግባር  ክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በምስራቅ መስቃን ወረዳ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው ።፡፡።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ነሐሴ 19/12/2017 ዓ/ም ...
25/08/2025

ሰው ተኮር ተግባር ክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በምስራቅ መስቃን ወረዳ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው ።

፡፡።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ነሐሴ 19/12/2017 ዓ/ም ( እንሴኖ )

ሰው ተኮር ተግባር ክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በምስራቅ መስቃን ወረዳ ተጠናክሮ ቀጥሏል በዛሬው ዕለት ከበጎ ፍቃደኞች በመተባበር በምስራቅ መስቃን ወረዳ በሀሙስ ገበያ ከተማ አቅመ ደካማ እናት አዲስ ቤት ገንብቶ ለመስራት በዛሬው ዕለት ስራው ተጀምሯል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ወጣቶችና እስፖርት ፅ/ቤት ኋላፊ አቶ አብዲ አወል ቤቱን ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በሁሉም ቀበሌ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው ተግባሩ አብሮነታችን የሚያጠናክር የህሊና እርካታ የሚያጎናፅፍ ነው ብለዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ወጣቶች ክንፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሽምሱ ሻፊ ቤቱን ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት የቀበሌው ወጣቶች በፓርቲያችን ዕሳቤ "ስው ተኮር ተግባር" ክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በማስተባበር መጀመራቸው የሚደነቅ ሲሆን ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ወጣቱ ከገጎናቸው ሆኖ አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ መቀጠል እንዳለበትና ተግባሩ በሌሎች ቀበሌ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ሀሙስ ገበያ ማዘጋጃ ሀላፊ አቶ ዋሲሁን ዘርጋ እንደገለፁት የዚህ የክረምት በጎ ተግባር ቀጣይነት ያለው በመሆኑም ወረዳችን ውስጥ የሚገኙ ሁሉም ወጣቶች ከዚህ በተሻለ በመረባረብ እና የምንደግፋቸው አረጋዊያንን ቁጥር በማብዛት ድጋፍ በማድረግ ሀላፊነታችንን መወጣት ይገባል በማለት ተናግረዋል፡፡

በዚህ የበጎ ተግባር ተጠቃሚ የሆኑት አሁን ላይ በተደረገው የቁሳቁስ ድጋፍ ቤታቸው እየተሰራ በመሆኑም እጅግ መደሰታቸውን ገልጸው ለበጎ ፍቃደኞች፣ ለአካባቢው ወጣቶች እንዲሁም ለወረዳው መንግስት ለማዘጋጃው ከልብ አመስግነዋል።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል ምስራቅ መስቃን ወረዳ አስተዳደር ወጣቶች እስፖርት ፅ/ቤት የ2017/18 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ የአንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት አፍ...
04/08/2025

በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል ምስራቅ መስቃን ወረዳ አስተዳደር ወጣቶች እስፖርት ፅ/ቤት የ2017/18 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ የአንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት አፍርሰው በአዲስ መልክ ገንብቶ ለመስራት በዛሬው ዕለት ስራው ተጀምሯል።

፡፡።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ሀምሌ 28/ 2017 እንሴኖ

በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት ከበጎ ፍቃደኞች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር በምስራቅ መስቃን ወረዳ በባቲ ልጃኖ ቀበሌ የአንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት አፍርሰው በአዲስ መልክ ገንብቶ ለመስራት በዛሬው ዕለት ስራው ተጀምሯል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር መሀመድ ሰብራላ በመርሀ ግብሩ ወቅት እንደተናገሩት የዘንድሮ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አረጋውያንን በመደገፍ እና አቅመ እንደዚህ አይነት ደካሞችን በመርዳት ወጣቶች የነቃ ተሳትፎ ሊኖራቸው እንደሚገባ ገልፀዋል።

ዋና አስተዳዳሪው አያይዘውም የወረዳው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ባህል ተደርጎ እየተሰራበት መሆኑን ገልጸው በቀጣይ በሁሉም አይነት ሰው ተኮር ተግባር ተደራሽ ለማድረግ የወረዳው ማህበረሰብ በጎዎች ከመንግስት ጋር በመሆን ተግባሩን ይበልጥ እንዲደግፍም ጥሪ አድርገዋል።

በዚህ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለተጠቃሚው ብቻ ሳይሆን ለአገልጋዩም የህሊና እርካታና የደስታ ምንጭ መሆኑንም አመላክተዋል።

እናታችን ያረፉበትም የነበረው ደሳሳ ቤትም እጅግ በጣም ያረጀና የተጎሳቆለ እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ በተደረገው የቁሳቁስ ድጋፍ ቤታቸው እየተሰራ በመሆኑም እጅግ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ተወካይ እንዳሉት በወረዳው በክረምቱ ወቅት የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባራት ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥቷል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ ፅ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መሃመድ ሃሚድ እንደገለፁት የሚከናወኑ የበጎነት ተግባር የመረዳዳትና የአብሮነት ባህላችን ለማሳየት እንደሆነና በይቻላል መንፈስ በሁሉም ሰው ውስጥ መረዳዳትና በመደጋገፍ የአቅመ ደካሞችን ለውጥ ለማምጣት እንደሆነ ተናግረው ሁላችንም የመደጋገፍ ባህላችን አጠናክረን ከቀጠልን ከዚህ የበለጠ ለውጥ ማምጣት ይቻላል ብለዋል፡፡

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና ዓቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ጥላሁን ብራቱ እንደገለፁት የዚህ የክረምት በጎ ተግባር ቀጣይነት ያለው በመሆኑም በወረዳችን ውስጥ የሚገኙ ሁሉም ወጣቶች ከዚህ በተሻለ በመረባረብ እና የምንደፋቸውን አረጋዊያንን ቁጥር በማብዛት ድጋፍ በማድረግ ሀላፊነታችንን መወጣት ይገባል በማለለት መልዕክታቸውን አሰተላልፈዋል

በመርሃ-ግብር የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ን ጨምሮ የምስራቅ መስቃን ወረዳ አስተባባሪዎች፣የወረዳው የህዝብ ም/ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ዓለሙ ግዛው እንዲሁም የወረዳው አጠቃላይ አመራርና የወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት የማኔጅመንት አካል ተገኝተዋል

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የምስራቅ መስቃን ወረዳ ወጣቶች ስፖርት ፅ/ቤት 2017 ዓ.ም የበጋ ወራት መዝጊያ እንዲሁም የክረምት ወራት መክፈቻ መድረክ አደረገ።።።...
04/08/2025

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የምስራቅ መስቃን ወረዳ ወጣቶች ስፖርት ፅ/ቤት 2017 ዓ.ም የበጋ ወራት መዝጊያ እንዲሁም የክረምት ወራት መክፈቻ መድረክ አደረገ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሃምሌ - 28/ 2017 ) እንሴኖ

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ " በሚል መሪ ቃል የምስራቅ መስቃን ወረዳ ወጣቶች ስፖርት ፅ/ቤት 2017 ዓ.ም የበጋ ወራት የወጣቶች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት መዝጊያና የ2017 የክረምት ወራት መክፈቻ ንቅናቄ መድረክ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር መሃመድ ሰብራላ መድረኩን የመፍክፈቻ ንግግር በማድርግ ያስጀመሩ ሲሆን።

በመድረኩም የወረዳው አስተባባሪ አካላቶች፣ የወርዳው እመራሮች፣ የሴክተር ሀላፊዎች፣የቀበሌ ስራ አሰኪያጅ እና ሊቀመንበር፣እንዲሁም በቀበሌው የወጣቶች ተወካይ ተገኝተዋል።

በመድረኩም የ2017 ዓ.ም የበጋ በጎ ፍቃድ የተግባር አፈጻጸም ሪፖርትና የ2017/18 ዓ.ም የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማብሰሪያ ተደርጓል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር መሃመድ ሰብራላ በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" የመድረኩ መሪ ቃል የተደርገው እንዳሉት በጎነት ለህሊና እርካታ እና ለራስ ጭምር መሆኑን ጠቅሰው ሰው ተኮር ተግባር የወጣቶች በጎ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልፀዋል።

በተጨማሪም አቅመ ደካማና አረጋውያንን ያማከለ ልማት በመስራት ለተተኪው ትውልድ አርአያ የሚሆን ተግባር መፈፀም እንደሚገባም ገልፀዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የፓለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ቢራቱ እንደገለፁት በበጋው የነበሩ ድክመቶችን በማረምና ጥንካሬዎችን በማስቀጠል በሁሉም የስምሪት መስኮች በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችን በነቂስ በማሳተፍ ቀድሞ ከነበረው በተሻለ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ የማስተባባር ስራ መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

በመሆኑም በወጣቶ እስፖርት ጽ/ቤት በ2017ዓ.ም በክረምትና በበጋ ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የተከናወኑ ተግባራት በተመለከተ በተለያዩ መስኮች ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝና እነዚህም በጤና ዘርፍ፤በመንገድ ዘርፍ፤በከተሞች የጽዳትና ውበት ልማት ተግባራት ፤በማህበረሰብ ልማት፣ድጋፍና እንክብካቤ አገልግሎት መስክ ፤
በወጣት አደረጃጀቶች እና የወጣት ማዕከላት ስብዕና ግንባታ አገልግሎት መስክ ፤በምግብ ዋስትናና በግብርና ልማት ድጋፍ መስክ፤ከት/ት ዘርፍ አንፃር ፤በደንና አካባቢ ጥበቃ አገልግሎት መስክ፤በስፖርትና በኪነ፣ በመንገድ ከፈታ እና ጥበብ፤ከሰላምና ጸጥታ አንጻር የተሰሩ ስራዎች እና ሌሎችንም የትኩረት መስኮች ላይ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።

በመጨረሻም በተለያዩ የበጎ አድርጎት ስራ ላይ ሲሳተፉ ለነበሩ ፅ/ቤቶች፣ቀበሌዎችና የአካባቢ ወጣቶች በምስራቅ መስቃን ወርዳ ዋና እስተዳዳሪ ዶ/ር መሀመድ ሰብራላ፣ በወረዳው የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ መሃመድ ሃሚድ እና በወርዳው የተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ዐለሙ ግዛው የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል።

በዕለቱም በዝግጅቱ የተገኙ አካላቶች የደም ልገሳ በማድረግ ሰብዓዊ ሃላፊነት በመወጣት በደም ለጋሹ ምንም ሳይጎድል፤ ውድ የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት መታደግ የሚያስችለው “ደም”፣ ልዩ ስጦታነቱን በመግለፅ “ደም በመለገስ አንድም ሰው በደም እጦት ምክንያት መሞት የለበትም በማለት ደም በመለገስ ሰብዓዊነትን አሳይተዋል ።
ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

የኢፌድሪ የሰላም፤ የፍትህና የሀገር መከላከያ ሚኒስትር መስሪያ ቤቶች  በምስራቅ ጉራጌ ዞን ምስራቅ መስቃን ወረዳ የአረጋውያን ቤት ግንባታ አስጀመሩ።(ሐምሌ 20/2017ዓ.ም )"በጎነትና አብ...
27/07/2025

የኢፌድሪ የሰላም፤ የፍትህና የሀገር መከላከያ ሚኒስትር መስሪያ ቤቶች በምስራቅ ጉራጌ ዞን ምስራቅ መስቃን ወረዳ የአረጋውያን ቤት ግንባታ አስጀመሩ።

(ሐምሌ 20/2017ዓ.ም )
"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሰጪ የመንግስት አካላትና የሰላም አምባሳደሮች በምስራቅ ጉራጌ ዞን ምስራቅ መስቃን ወረዳ ኢሌ ቀበሌ የተለያዩ ፕሮግራሞች አስጀመረዋል።

የኢፌድሪ የሰላም፤ የፍትህና የሀገር መከላከያ ሚኒስትር በመተባበር በምስራቅ መስቃን ወረዳ ለ9 አቅመ ደካማ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች የቤት ግንባታና ለ1ሺ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁሶች ድጋፍ በዛሬው ዕለት የተደረገ ሲሆን በቀጣይም ለ2ሺህ ተማሪዎች ድጋፍ እንደሚደረግ ተገልጿል።

የሚንስተር መስሪያ ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች በዞኑ "በመትከል ማንሰራራት" የአረንጓዴ አሻራ ልማት አሻራቸውን አኑረዋል።

በፕሮግራሙ የሰላም ሚንስትር ሚንስተር አቶ መሀመድ እድሪስ ፤የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ማርታ ላውጂ፤ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ፤ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ጫካ ጨምሮ የዞን፣የወረዳ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በኢሌ ቀበል የፌደራል 3 ሚኒስትር መስራ ቤቶች  በመትከል ማንሰራራት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም እና የበጎ ተግባር እየተካሄዱ ነው!!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።...
27/07/2025

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በኢሌ ቀበል የፌደራል 3 ሚኒስትር መስራ ቤቶች በመትከል ማንሰራራት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም እና የበጎ ተግባር እየተካሄዱ ነው!!

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ሀምሌ 20/2017 ዓ/ም በምስራቅ መስቃን ወረዳ በኢሌ ቀበል የፌደራል 3 ሚኒስትር መስራ ቤቶች በመትከል ማንሰራራት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም እና የበጎ ተግባር እየተካሄደ

በፕሮግራሙ የችግኝ ተከላ ይካሄዳል
ለ9 ለአቅመ ደካማ ሰዎች ቤቶች ይሰራል
2000 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቀስ ድጋፍ ይደረጋል።

በፍትህ ሚንስቴር ሚንሰተር የተመራ የመከላከያ፣ የሰላም፣ የፍትህ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ ''በመትከል ማንሰራራት'' በሚል መሪ ቃል የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሐግብር እያካሄዱ ይገኛል።

የሚኒስቴሮቹና የተጠሪ ተቋማቱ የስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩን እያካሂዱት ያለው ከክልሉ እና ከዞን ወረዳው አመራር አካላትና ወጣቶች ጋር በመሆን ነው።

በችግኝ ተካላው ስራ ላይ የፍትህ ሚኒስትር ፣ የሠላም ሚኒስትር ዲኤታ ፣ የመከላከያ ሚኒስትር ዲኤታ ፍትህ ሚኒስትር እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አመራሮች ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የዞን እመራሮች ይግኙበታል።

የአመራር አካላቱ ከችግኝ ተከላ ስራው በተጨማሪ በጎነት ለኢትዮጲያ ከፍታ በሚል መሪ ቃል የተለያዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችንም እንደሚያከናውኑ ተገልጿል።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

18/07/2025
በመትከል_ማንሰራራት"  የ2017ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ አንዱ አካል የሆነው የቡና የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በምስራቅ መስቃን ወረዳ በባቲ ፉጦ ቀበሌ የችግኝ ተከላመርሃ ግብር ተከናወነ  ።።...
16/07/2025

በመትከል_ማንሰራራት" የ2017ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ አንዱ አካል የሆነው የቡና የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በምስራቅ መስቃን ወረዳ በባቲ ፉጦ ቀበሌ የችግኝ ተከላመርሃ ግብር ተከናወነ ።
።።፡።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ሐምሌ 9/2017 ዓ/ም (የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

በመትከል_ማንሰራራት" የ2017ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ አንዱ አካል የሆነው የቡና የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በምስራቅ መስቃን ወረዳ በባቲ ፉጦ ቀበሌ የችግኝ ተከላመርሃ ግብር ተከናወነ ።

በዛሬው እለት በምስራቅ መስቃን ወረዳ በባቲ ፉጦ ቀበሌ በአርሶ አደር ፈቱ መሃመድ እና በአርሶአደር መሃመድ ጀማል በክላስተር (500 )አምስት መቶ የቡና ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተከናወነ

መርሃ ግብርን ያስጀመሩት የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አሰተዳዳሪ ዶ/ር መሀመድ ሰብራላ እንዳሉት በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታዎች ባብራሩበት ወቅት የችግኝ ተካላ ስራችን ለምግብነት የሚውሉ ተክሎች በስፋት መተከል እንዳለባቸውና እንዲሁም መትከል ብቻውን ወጤት ሳይሆ የእያንዳንዱ ችግኝ ፅድቀት መሆኑኑንም አስገንዝበዋል ።

በመርሃ -ግብሩ አጭር ገለፃ ያደረጉት የምስራቅ መስቃን ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት ም/ ኃላፊ አቶ ሁሴን መስጠፋ እንዳሉት በዚህ አመት እንደ ወረዳ በተለያዩ የቡና መንደሮች ከመመስረት ጋር በተያያዘ 600 አርሶ አደሮችን ያስተፋል ተብሎ ይጠበቃል።

ኃላፊው አያይዘውም በዛሬው እለትም በአ/አደር ፈቱ መሀመድና በአርሶ አደር መሀመድ ጀማል በተዘጋጀ የቡና ማሳ ላይ አዲሱ የቡና ኢንሼቲቭን መሰረት ተደርጎ አንድ አርሶ አደር 250 እና በላይ የቡና ችግኝ የመትከል ኢንሼቲቭ መሰረት ያደረገ የወረዳው አስተባባሪዎች የወረዳው አመራር አካላት እና የግብርና ጽ/ቤት ማኔጅመንት አካላት በተገኙበት 500 የቡና ችግኝ ተከላ ተከሄዷል ።

በቀጣይ ተከታታይ ቀናት በየቀበሌው የችግኝ ተከላው ይቀጥላል ብለዋል።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ''የፓርቲ ተቋም ግንባታ ለላቀ እምርታ'' በሚል መሪ ሀሳብ ለወረዳው ጠቅላላ አመራር ስልጠና መስጠት ጀመረ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።...
16/07/2025

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ''የፓርቲ ተቋም ግንባታ ለላቀ እምርታ'' በሚል መሪ ሀሳብ ለወረዳው ጠቅላላ አመራር ስልጠና መስጠት ጀመረ።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ሐምሌ 09/2017 ዓ/ም የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ''የፓርቲ ተቋም ግንባታ ለላቀ እምርታ'' በሚል መሪ ሀሳብ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ለወረዳው ጠቅላላ አመራር ስልጠና መስጠት ጀምሯል።

የስልጠናው ዋነኛ ዓላማም:- ለስራ የተነሳሳ፣ የሚመራውን ተቋም በብቃት የሚመራ አመራር መፍጠርና የፓርቲ ውጤታማነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያስችል የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠና እንደሆነም ተመላክቷል።

በአሁኑ ሰዓትም የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መሃመድ ሃሚድ ''መሰረታዊ የመሪነት ጥበብ እና አገልጋይ አመራር'' በሚል ርዕር የተዘጋጀ የስልጠና ሰነድ እያቀረቡ ይገኛል ።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በበጋው ወራት የተሰሩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና የክርምት የበጎ ስራ መነሻ ጠቋሚ እቅድ ተገመገመ።=====================ሀምሌ-07/2017ዓ.ም (የምስራቅ...
14/07/2025

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በበጋው ወራት የተሰሩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና የክርምት የበጎ ስራ መነሻ ጠቋሚ እቅድ ተገመገመ።
=====================
ሀምሌ-07/2017ዓ.ም (የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት አብይ ኮሚቴ አጠቃላይ የተከናወኑ የበጋ በጎ ፍቃድ ማጠቃለያ መዝጊያ ሪፖርት እና የ2017/2018 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መነሻ እቅድ ገምግሟል።

የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአብይ ኮሚቴ ሰብሳቢና የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና ዓቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ብራቱ በበጋው ወራት የተሰሩ የበጎ አገልግሎቶች አጠናክሮ በመቀጠል የበጎ ስራዎች ሰው ተኮር ተግባር መሆኑ በመጥቀስ የዘንድሮ ክርምት ከሌላ ጊዜ በተለየ ማህበረሰዋችን በሁሉም ዘርፍ በማሳተፍ ውጤታማ ስራ መስራት እንዳለብን ጠቁመዋል። እስካሁን በተሰሩ ስራዎች በሁሉም ዘርፍ ከእቅዳችን አንፃር የተቻለ መፈፀም ችለናል ብለዋል።አያይዘውም የአብይ ኮሚቴ አባላትን የበጎ ፈቃድ ባለ ድርሻ አካላትን አመስግነዋል።የቀጣይ የ2017/2018ዓም የክረምት በጎ ፈቃድ እቅድ መነሻ መገምገሙን ያነሱ ሲሆን በዚህም ከ14 በላይ ዘርፎች ላይ ርብርብ እንደሚደረግ እና ሌሎችንም አጋዥ ተቋማት እንደሚሳተፉ ገልፀዋል።

ሰብሳቢው ጥቅል በበጋው ወራት የነበሩ ክፍተቶች የ2017/18 የክረምቱ በጎ ፈቃድ የእቅድ አካል ተደርገው እንደሚመሩ የገለፁ ሲሆን በክረምቱ በጎ ፈቃድ በከፍተኛ ተግባር እንደሚሰራ ገልፀዋል።

በመጨረሻም ሰብሳቢው እንዳሉት በክረምቱ በጎ ፈቃድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፍትሃዊነትና ተደራሽነት ጥራትን ለማረጋገጥ በተደራጀ በአንድ ቋት ተቋቁሞ እንደሚመራ ገልፀዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት ም/ኃላፊ አቶ ሸረፋ አውላቸው እንደገለፁት
ሰው ተኮር ስራዎችን ውጤታማነት አጠናክሮ በማስቀጠል ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚያስፈልግና በበጋው ወራት የተሻሉ ስራዎችን መሠራታቸውን የገለፁ ሲሆን በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሁሉንም ትብብር የሚጠይቅ ስራ መሆኑን ገልፀው የቀጣይ የ2017/2018 መነሻ እቅዱ በየጊዜ እየተሻሻለ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

የአብይ ኮሚቴ አባላትም ሪፖርት አፈፃፀማቸውን አቅርበው ሰፊ የሆነ ውይይትና አስተያየት የሰጡ ሲሆን በሂደቱም ሪፓርት በየ15 ቀን በዚህ ልክ ተገናኝተን መገምገሙ የስራችን ቅልጥፍና ወሳኝ መሆኑ መግባባት ተፈጥሯል።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ  በህብረተሰብ ተሳትፎ ሲገነባ የነበረው  ግንባታው ተጠናቆ በዛሬው እለትየወጃ ንቡር  ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ መርቆ ስራ አ...
12/07/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ በህብረተሰብ ተሳትፎ ሲገነባ የነበረው ግንባታው ተጠናቆ በዛሬው እለትየወጃ ንቡር ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ መርቆ ስራ አስጀመረ

ሀምሌ 5/2017 እንሴኖ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ በህብረተሰብ ተሳትፎና በክልሉ መንግስት ገንዘብ ወጪ የተገነባውን የንቡር ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ስራ አስጀመረ።

ለሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ግንባታው የአካባቢው ህዝብና የክልሉ መንግስት ከ13ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጋቸው ተገልጿል።

የጤና ተቋሙን መርቀው ስራ ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የብልጽግና መንግስት የህብረተሰቡን የጤና ሽፋን ለማሳደግና የተቀላጠፈ የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል።

የክልሉ መንግስት 17 መሰል ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላዎችን በመንግስትና በህዝብ ድጋፍ ለማሰራት እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም ገልጸው ፣ህብረተሰቡ ለአዳዲሶቹ ተቋማት የጎደሉ ቁሳቁሶችን ለማሟላት እንዲረባረብም ጥሪ አቅርበዋል።

የአካባቢው ህዝብ የተገኘውን ሰላም በመጠበቅና በማጽናት ልማቱን እንዲያፋጥንም አቶ ሳሙኤል አሳስበው ፣የጤና ተቋሙ በአጎራባች የሚገኙ ህዝቦችን ጭምር ተጠቃሚ የሚያደርግና የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን የሚያጎለብት ትልቅ ተቋም መሆኑንም አስታውቀዋል።

ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላው ለምስራቅ መስቃን ወረዳ፣ለአጎራባች የማረቆ ልዩ ወረዳ ቀበሌያትና ለኦሮሚያ ክልል አጎራባች ቀበሌያት ህዝቦች የተሻለ የጤና አገልግሎት እንደሚሰጥም አቶ ሳሙኤል ገልጸዋል።

ንቡር ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ በምስራቅ ጉራጌ ዞን ምስራቅ መስቃን ወረዳ ወጃ ቀበሌ ይገኛል።

ለጤና ተቋሙ ግንባታ የአካባቢው ህዝብ ከ8 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ በገንዘብ፣በጉልበትና በሀሳብ ወጪ ያደረገ ሲሆን የክልሉ መንግስትም ለተቋሙ ግንባታ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ አድርጓል።

ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላው የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ኢንሼቲቭ የሆነው የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት አካል መሆኑም ተመላክቷል።

ከፍተኛ አመራሮቹ ከጤና ተቋም ምረቃው በኋላ የምስራቅ መስቃን ወረዳን የልማት ስራዎች የሚያሳይ አውደ ርዕይ በመመረቅ የአረንጓዴ አሻራቸውን በሁሉ አቀፍ ጤና ኬላው ግቢ ውስጥ አኑረዋል።

ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላውን መርቀው ስራ ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን፣የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ፣የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መለሰ ጫካ፣፣ከፍተኛ የክልሉ ጤና ቢሮ የስራ ሃላፊዎች፣የዞኑና የወረዳው አመራሮች ናቸው።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት በቀጣይ የ90 ቀን የንቅናቄ የማስፈፀምያ ዕቅድ ከወረዳው አጠቃላይ አመራር በተገኘበት ኦረንቴሽን መድረክ  ተካሄደ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።...
22/06/2025

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት በቀጣይ የ90 ቀን የንቅናቄ የማስፈፀምያ ዕቅድ ከወረዳው አጠቃላይ አመራር በተገኘበት ኦረንቴሽን መድረክ ተካሄደ ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።

14/10/2017 ዓ.ም

የቀጣይ 90 ቀን ከሚሰሩ ተግባራት መካከል በዋናነት ከስራ እድል ፈጠራ ተግባር ፣በወረዳ አንድ ፕሮጀክት በተቀመጠለት ጊዜ ማጠናቀቅ እና በሌሎች ፕሮጀክቶች፣በመኸር ሥራዎች ፣በበልግ ሥራዎች የበጎ ፈቃድ ስራዎች የኑሮ ማረጋጋት የገቢ አሰባሰብ ስራና፣ በ5ሚልዮን ኢንኮደርስ፣ በፉይዳ መታወቅያ ፣

ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በቀጣይ ቀናት ዕቅድ በማድረግ በልዩ ሁኔታ ተግባራቶቹ እንዲፈፀሙ እቅዱ ተፈፃሚ ሚሆንበት የ90 ቀን ሰነዱ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

ከአረንጓዴ አሻራ የልማት ስራዎች ጋር ተያይዞ ወጣቶችና ሴቶችን በማነቃነቅ ተግባሩን ውጤታማ ለማድረግ መስራት እንደሚያስፈልግ ፣ሌማት ትሩፋትም ዘርፍም አበረታች ውጤቶች መታየታቸውን ተጠቅሰው የስኬቶቹን አቅሞች ተጠቅሞ የዘጠና ቀናት የክረምት ስራዎቻችንን ውጤታማ ቀናት ዕቅድ ለማድረግ መረባረብ እንደሚገባ በውይይቱ ተነስቷል።

በመኸር ስራዎች ስኬታማነት ግብዓት ከማሟላትና ክትትልና ድጋፍን ከማጠናከር ባሻገር በተፈጥሯዊና ሌሎች ምክንያቶች በበልግ ሥራዎች ማከናወን የማካካሻ ዕቅድ በማዘጋጀት በመኸር ማካካሻ ልንሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በውይይቱ የ90 ቀን እቅድ ተግባራትን አመራሩ አስተሳስሮ በመስራት በሁሉም ተግባር የሚፈለገውን ውጤት ማስመዝገብ አለበት ተብልዋል።

አመራሩ ወቅቱ የሚፈልገው የአመራር ስምሪት በመውሰድ ታቅደው እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በጥራት እና በውጤት መታጀብ እንዳለበት በዕቅድ ግምገማው ተመላክቷል።

በቀሪ 90 ቀናት በዋናነት የመኸር ልማት፣ የአሬንጓዴ አሻራ፣ የበጎ አድራጎት ሥራዎች፣ የሠላም እሴት ግንባታ ማፅናት ፣
ሌሎች ተግባራት በከፍተኛ ኃላፊነት በመፈፀም ዓመታዊ አፈፃፀማችን ግቦቻችን ማሳካት ይገባል።

ከመልካም አስተዳደር ጋር ተያይዞ በፍትህና በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት በወረዳው ያለውን አንፃራዊ ሰላም የማፅናት ተግባሮች በቁርጠኝነት መሰራት እንዳለበት፣

በውይቱ አመራሩ ተግባራትን አስተሳስሮ በመስራት በሁሉም ተግባር የሚፈለገውን ውጤት ማስመዝገብ እንዳለበት፣

አመራሩ ወቅቱ የሚፈልገው የአመራር ስምሪት በመውሰድ በ90 ቀን ታቅደው እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በጥራት እና በውጤት መታጀብ እንዳለበት በዕቅድ ግምገማው ቀርቧል።

በመጨረሻም የ90ቀን እቅድ መሠረት በማድረግ ለቀጣይ ሥራዎች ዝርዝር የተግባር አቅጣጫዎች ተቀምጠው ውይይቱ ተጠናቋል።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

Address

Awassa

Telephone

+251964476649

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት:

Share