በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት''Prosperity Party Office"

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በቀጣይ ቀናት በሚሰጠው የጠቅላላ የብልጽግና ፓርቲ አባላት ስልጠና እና የሚደረጉ የሕዝብ መድረኮችን አስመልክቶ ለአጠቃላይ ለወረዳው አመራሮች...
13/12/2025

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በቀጣይ ቀናት በሚሰጠው የጠቅላላ የብልጽግና ፓርቲ አባላት ስልጠና እና የሚደረጉ የሕዝብ መድረኮችን አስመልክቶ ለአጠቃላይ ለወረዳው አመራሮች ኦረንቴሽን ሰጠ።

ታህሳስ 04/2018 ዓ.ም

"በመደመር መንግስት ዕይታ የዘርፎች እመርታ!" በሚል መሪ ርዕስ ላይ በቅርቡ ጠቅላላ አመራሩ ሰፊ ስልጠና መውሰዱ ይታወቃል።

ይህንኑ ስልጠና ለአጠቃላይ ለወረዳው ውስጥ ያሉ ጠቅላላ የፓርቲው አባላትን ለማሰልጠን ያለመ የቅድመ_ዝግጅት ለአጠቃላይ አመራሩ ኦረንቴሽን ተሰጥቷል።

እንደሚታወቀው የብልጽግና ፓርቲ በተከታታይነት የአመራሩና የአጠቃላይ አባላት የፓለቲካ አቅም የሚገነቡ ወቅታዊና ዕውቀትን የሚያስጨብጡ የተለያዩ ስልጠናዎችን በተከታታይ እያወረደና እያሰለጠነ ይገኛል።

በዚህም መሰረት በፓርቲው የሚወርዱ ወቅታዊ ሀገራዊ ፣ አከባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን በመተንተንና በማካተት የወረዳው የፓርቲ አባላት አቅም ለመገንባትና ለማብቃት በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን እና ይህም በቀጣይ የበለጠ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተነስቷል።

መድረኩን የመሩት የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድኑር ስርሞሎ እንደ ወረዳ የፓርቲ አባላት አቅም የሚገነቡ ስልጠናዎች ከአመራሩ በተጨማሪ ጠቅላላ አባላት ላይም በልዩ ትኩረት መሰራት እንዳለበት አብራርተው ሁሉም የወረዳው አመራር በቁርጠኝነት ተግባራቶቹን ማሳካት እንደሚጠበቅ ለአመራሩ አሳስበዋል።

በመድረኩ ላይ የተሳተፉት ጠቅላላ የወረዳው አመራሮች ለስልጠናው የሚያስፈልጉ ከስልጠናው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ጀምሮ ስልጠናው በስኬት ለማጠናቀቅ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የወረዳው ረዳት የመንግስት ተጠሪና የፓለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ብራቱ በመድረኩ ተገኝተው ፣ ስልጠው ልዩ ፖለቲካዊ ትርጉም ተሰጥቶት መመራት ያለበት መሆኑን አንስተዋል ፣ መድረኮቹ የተሳኩ እንዲሆኑ በሁሉም ማህበራዊ መሰረቶች ተደራጅተው የሚገኙ የፓርቲ አባላት ስልጠናው አንድም አባል ሳይንጠባጠብ በተገቢው በሁሉም መድረኮች በጥብቅ ዲሲፕሊን እንዲሰጥ አቅጣጫ አስቀምጠው የተለያዩ ስልጠናውን የሚመሩና አሰልጣኞች እና #የተለያዩ ንዑሳን #ኮሚቴዎችን አሳውቀው ኦረንቴሽኑ ተጠናቁዋል።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር በምስራቅ መስቃን ወረዳ  በባቲ ፋጦ ቀበሌ ለሚገኘው  የንጋት ጮራ 1ኛ እና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከአንድ መቶ ሃያ ሺ ብር በላይ ወጪ በማድረግ 473 የመ...
12/12/2025

የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር በምስራቅ መስቃን ወረዳ በባቲ ፋጦ ቀበሌ ለሚገኘው የንጋት ጮራ 1ኛ እና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከአንድ መቶ ሃያ ሺ ብር በላይ ወጪ በማድረግ 473 የመማሪያ መጽሐፍት ድጋፍ አደረገ!!

ታህሳስ 3/2018

ጉልባማ በምስራቅ መስቃን ወረዳ በባቲ ፋጦ ቀበሌ ለሚገኘው የንጋት ጮራ 1ኛ እና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከአንድ መቶ ሃያ ሺ ብር በላይ ወጪ በማድረግ 473 የመማሪያ መጽሐፍት ድጋፍ አደረገ፡፡


በስፍራው በመገኘት የመፅሐፍት ርክክቡን ያደረጉት የጉልባማ ዋና ዳይሬክተር አቶ ቅባቱ ተሰማ እንደገለፁት ጉልባማ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ከሐገር ውጪ ያሉ ተወላጆችን ጭምር በማስተባበር በርካታ ጥረቶችን ሲያደርግ መቆየቱንና ገልፀው።

በቅርቡም ወረዳዎች ከአባላቶቻቸው በሰበሰቡት ገቢ ከ 1ኛ-8ኛ ክፍል የመማሪያ መጽሐፍትን በኢትዮጵያ የትምህርት መርጃ መሳርያዎች ማምረቻ ድርጅት በማሳተም ማሰራጨት መቻሉን የገለጹ ሲሆን

በቀጣይም የትምህርት ማህበረሰቡ የልማት ማህበሩ አባል በመሆን አዳዲስ አባላትን በማፍራትና የአባልነት መዋጮዎችንም በአግባቡ በመሰብሰብ መሰል ድጋፎች ተጠናክረው የሚቀጥሉበት ሁኔታ ላይ በንቃት መሳተፍ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል፡፡

በተመሳሳይ ወረዳውን በመወከል በስፍራው ተገኝተው በተደረገው ድጋፍ የተሰማቸውን ደስታ የገለፁት የምስራቅ መስቃን ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ የሁኑት አቶ ከድር አደም ይህ ድጋፍ እጅግ አበረታች መሆኑን በመግለጽ መሰል ድጋፎች በሌሎች መስኮችም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡

በመጨረሻም የትምህርት ቤቱ ም/ር/መምህር የሆኑት አቶ ክፍሌ ግዛው እንደገለፁት ትምህርት ቤቱ ከፍተኛ የሆነ የመጽሐፍት እጥረት ችግር ያለበት ሲሆን በተለይም የሰባተኛ እና የስምንተኛ ክፍል መማሪያ መጽሐፍት ከተማሪዎች አልፎ ለመምህራን እንኳን ለማድረስ የተቸገሩበት ሁኔታ ውስጥ እንደነበሩ እና አሁን የነዚህ መጽሐፍት ድጋፍ ትልቅ ችግር ሊቀርፍ እንደሚችል ገልፀዋል፡፡

በርክክቡ ወቅት የጉልባማ የማኔጅመንት አባላት፣ የወረዳው የማህበሩ አስተባበሪ እና የሚመለከታቸው አካላት በጋራ በመሆን የትምህርት ቤቱንም ነባራዊ ሁኔታ ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡ ሲልጨየዘገበው የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮምንኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው

የምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የእህል አሰባሰብ ከቀበሌ  ወደ ወረዳ ማዕከል ርክክብ ማድረግ ተጀመረ  ።።።።።።።።።ታህሳስ 2/ 2018የምስራቅ ጉራጌ...
11/12/2025

የምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የእህል አሰባሰብ ከቀበሌ ወደ ወረዳ ማዕከል ርክክብ ማድረግ ተጀመረ
።።።።።።።።።
ታህሳስ 2/ 2018

የምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የእህል አሰባሰብ ስራን ተከትሎ እያንዳንዱ የወረዳችን አባውራ አርሶ አደሮች የአቅማቸውን ድጋፍ እያረጉ ሲሆን

በዚህም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመጠባበቂያ የሚሆን የእህል አሰባሰብ በዛሬው ዕለት ይመርዋጮ 2ተኛ ይመርዋጮ 3ኛ ቀበሌ እህል በመሰብሰብ ወደ መጋዘን አስረክበዋል።

በዚህም የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር መሀመድ ሰብራላ ይመርዋጮ 2ተኛ ቀበሌ ነዋሪዎች በእህል አሰባሰብ ስራው ላይ ባደረጉት ተሳትፎ እጅግ አመስግነው ቀጣይነት ያለው እንዲሆን እና ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚደረገው መተጋገዝ የራስን ችግር በራስ ከመፍታት ባለፈ በሁሉም ቀበሌ ተጠናክሮ እንደሚጥልም ጠቁመዋል።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የመከላከያ ምልመላ አብይ ኮሚቴ  የአፈጻጸም ግምገማ አካሄደ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ታህሳስ2/2018 ዓ/ምበምስራቅ ጉራጌ ዞን ​የምስራቅ መስቃን ...
11/12/2025

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የመከላከያ ምልመላ አብይ ኮሚቴ የአፈጻጸም ግምገማ አካሄደ።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ታህሳስ2/2018 ዓ/ም

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ​የምስራቅ መስቃን ወረዳ ወረዳ የመከላከያ ሠራዊት ምልመላ አብይ ኮሚቴ የወረዳውን የ2018 በጀት ዓመት የመከላከያ ምልመላ አፈጻጸም ሪፖርት ተገምግሟል።

በወረዳው የተከናወኑ የመከላከያ ሠራዊት ምልመላ ሂደት አፈጻጸም ስራዎች ተገምግምዋል።

​በሂደቱ የታዩ ጠንካራ ጎኖች እንዲቀጥሉ እና ክፍተቶች እንዲስተካከሉ አቅጣጫ ማስቀመጥ እንደሆነ ተገልጿል።​

የአቅድ አፈፃፀም የወረዳው ምልመላ ከዕቅድ አንፃር ምን ደረጃ መሆኑን በቀጣይ ምን ከምልመላ አንፃር የሚሰሩ ስራዎች የመድረኩ አስፈላጊነት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ እና የኮሚቴው ሰብሳቢ የሆኑት መሀመድ ኑር ስርሞሎ ተናግረዋል።

​ሀላፊው አክለው በቀጣይም ምልመላውን በላቀ ጥንቃቄ እና ግልጽነት ለማካሄድ የጋራ አቋም በመያዝ በሀገር መከላከያ ደረጃ ወረዳውና እንደሀገር ያለውን ድርሻ ከፍ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

በምስራቅ መስቃን ወረዳ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሥራ ይፋዊ ማስጀመሪያ መርሃ -ግብር ተካሄ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ታህሳስ 1/2018  የየበጋ መስኖ ስንዴ መንግስት በሰጠው ል...
10/12/2025

በምስራቅ መስቃን ወረዳ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሥራ ይፋዊ ማስጀመሪያ መርሃ -ግብር ተካሄ።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ታህሳስ 1/2018

የየበጋ መስኖ ስንዴ መንግስት በሰጠው ልዩ ትኩረት የሀገር ውስጥ ፍላጎት አልፎ ኤክስፖርት ወደ ማድረግ የተሻገርንበት፣ ተረጅነትን በማስቀረት የፖለቲካና የኢኮኖሚ ስብራታችን ያከምነብት መሆኑም ተመላክቷል ።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ በዛሬው እለት ማስጀመሪያ የተደረገበት ኦቻ ገነሜ ቀበሌ በሠብል ልማት የሚታወቁ በበጋ መስኖ ከፍተኛ አቅም ያለው ትርፍ አምራች አርሶ አደሮች ያለበት እንደሆነ ተገልፅዋል።

አካባቢው ብሎም እንደ ወረዳ የምርታማነት አቅማችሁ አጠናክረው በማስቀጠል ብልፅግናን በቤተሠብ ደረጃ በማረጋገጥ በአገር ኢኮኖሚ ላይ አስተዋፅኦ ማድረግ እንዳለባቸው ተመላክቷል።

ከበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በተጎዳኝ የመደበኛውም የመስኖ ልማቶች አስፍተው እንዲያለሙ በማመላከት ከመንግስት የሚጠበቀው የግብዓትና ግብዓቶት አቅርቦት የማመቻቸትና የሙያዊ ድጋፋ እንደማይለያቸው ተገልጿል።

የበጋ መስኖ ስንዴ በክላስተር ደረጃ በማልማት በዘንደሮ ዓመትም በላቀ መልኩ ለመፈፀም የእርሻ ዝግጅ ከማድረግ፣ የማዳበሪያ የምርጥ ዘርና ሌሎችም ግብዓቶች በተሟላ መልኩ እንዲቀርብ በበቂ ሁኔታ መሠራቱን አስታውቀዋል።

የበጋ መሥኖ በአመት 2ጊዜና ከዚያ በላይ እንድናመርት በማስቻል ከራስ ፍጆታ አልፎ ትርፍ ምርት ለውጭ ገበያ እስከ ማቅረብ ያስቻለ ሀገራዊ ስኬት እንዳስገኘ ተገልጿል

ወረዳው ያለው የመሬት ሀብትና የህብረተሠቡ የመልማት አቅም በማቀናጀት ብልፅግናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጥረት እያደረግን እንገኛለን ብለዋል።

ስንዴን በመስኖ ለማልማት እየዘሩ ያገኘናቸው አርሶ አደርች በቆሎ ዘርተው ባነሱበት መሬት አርሰውና አለስልሰው ስንዴ እየዘሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

በዕለቱ 5 ሄክታር መሬት በላይ ስንዴን በክላስተር በማልማት አርሶ አደሮቹ ተጨማሪ ምርት ለማግኘት እየሠሩ እንዳሉ ተናግረዋል።

በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የወረዳው አስተባባሪዎችና አመራሮች፣ የወረዳው እና የቀበሌው አመራሮች እንዲሁም አርሶ አደሮች በእርሻ መስኩ በመገኘት ተሣትፈዋል።

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት like shere follow ያድርጉ 👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=10006508462855

08/12/2025
"የኢትዮጵያውያን ቀን" በሆሳእና የማለዳ ድባብ **************በ20ኛው የብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን የማጠቃለያ ዝግጅት ላይ ዛሬ ሕዳር 29 በድምቀት የሚከበረው  "የኢትዮጵያው...
08/12/2025

"የኢትዮጵያውያን ቀን" በሆሳእና የማለዳ ድባብ
**************

በ20ኛው የብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን የማጠቃለያ ዝግጅት ላይ ዛሬ ሕዳር 29 በድምቀት የሚከበረው "የኢትዮጵያውያን ቀን" በሆሳእና ከተማ በድምቀት በመካሄድ ላይ ነው።

ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የባህል አምባሳደሮች በሆሳዕና ከተማ የተለያዩ ባህላዊ ትዕይንቶችን አቀረቡ።''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በሆሳዕና ከተማ እየተከ...
07/12/2025

ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የባህል አምባሳደሮች በሆሳዕና ከተማ የተለያዩ ባህላዊ ትዕይንቶችን አቀረቡ።

''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ለሚገኛው ህዳር 29/2018 በዓል ከሀገሪቱ የተወጣጡ የባህል አምባሳደሮች የተለያዩ ትርኢቶችን በኮሎኔል በዛብህ አደባባይ አቅርበዋል።

ህዳር 28/2018) ''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በሆሳዕና ከተማ ለሚከበረው የ20ኛ የኢትዮጵያ የብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በተለያዩ መርሐ ግብሮች ከህዳር 25/2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲከበር መቆያቱ ይታወሳል።

ከሀገሪቱ የተወጣጡ ብሔር ብሔረሰቦች በኮሎኔል በዛብህ አደባባይ የየራሳቸውን ባህል የሚያንፀባርቁ ቱባ ባህላቸውን እና እሴታቸውን በተለያዩ ዜማዎች ባህላዊ ውዝዋዜዎች በአደባባዩ ለታዳሚዎች አቅርበዋል።

''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ያለው የ20ኛ የኢትዮጵያ የብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ህዳር 29/2018 ዓ.ም በአቢዮ ኤርሳሞ ስታዲየም ማጠቃለያ ያገኛል።

የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎችና ሌሎች የበዓሉ ተሳታፊዎችም በባህላዊ ትዕይንቶቹ በመቀላቀል በህብረ-ብሔራዊ አንድነት ደማቅ ድባብ መፍጠር ችለዋል።

ዴሞክራሲ፣ህብረ ብሄራዊ ፌደራሊዝም ፣የብዝሃነት አስተዳደርና የምርጫ ስርኣት.... በነገው እለት መላው ኢትዮጵያዊያን በሚሳተፉበት ደማቅ ዝግጅት የሚከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ፣ብሄረሰቦ...
07/12/2025

ዴሞክራሲ፣ህብረ ብሄራዊ ፌደራሊዝም
፣የብዝሃነት አስተዳደርና የምርጫ ስርኣት....

በነገው እለት መላው ኢትዮጵያዊያን በሚሳተፉበት ደማቅ ዝግጅት የሚከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ፣ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን የተለያዩ ዝግጅቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል።

በዛሬው እለት "በምክክር ቀን" ውሎ በሆሳዕና ከተማ የፌደሬሽን ምክር ቤት፣ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ፣ የህብረተሰብ ተወካዮች፣ ምሁራንና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በአዲሱ የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ዘመናዊ አዳራሽ ሲምፖዚየም እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህ ሲምፖዚየም አራት ምሁራን የጥናት ወረቀቶችን አቅርበዋል። ወረቀቶች በተለይ ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ በመነሳት "ዴሞክራሲና የፌዴራል ስርኣት አተገባበር በኢትዮጵያ" ፣ "የምርጫ ስርኣትና ህብረ ብሄራዊ ፌደራሊዝም በኢትዮጵያ" ፣ "ብዝሃነትና የብዝሃነት አስተዳደር" እንዲሁም ከክልሉ መነሻ "የጋራ እሴቶችና ጸጋዎች ለሁለንተናዊ ብልጽግና" በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበዋል።

የጥናት ወረቀቶቹ መድረክ በኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወ/ሮ እናታለም መለሰ የተመራ ሲሆን ወረቆቶቹ እንደ ሀገር ዴሞክራሲ፣ህብረ ብሄራዊ ፌደራሊዝም ፣የብዝሃነት አስተዳደርና የምርጫ ስርኣት ቁልፍ ጉዳዮች መሆናቸውን አመላክተዋል ።

"ዴሞክራሲና የፌዴራል ስርኣት አተገባበር በኢትዮጵያ" በሚል የጥናት ጽሁፍ ያቀረቡት አቶ በላይ ወዲሾ የሀገራት የዴሞክራሲ ስርኣት ተሞክሮዎችን አብራርተው አብሮነት፣ መግባባትና በጋራ ሀገርን መገንባት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል ። ለዚህ ስኬት ደግሞ ዴሞክራሲና ብዝሃነትን በአግባቡ የሚያስተናግድ የፌደራል ስርኣት ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው ብለዋል።

እንደ ሀገር በፖለቲካ ባህልና በጠንካራና ነጻ ተቋማት ግንባታ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ተቀራርቦ የመመካከር፣ የመተሳሰብ ባህልን ማጎልበት ወሳኝ ነው ብለዋል።

"የምርጫ ስርኣትና ህብረ ብሄራዊ ፌደራሊዝም በኢትዮጵያ" በሚል ጽሁፍ ያቀረቡት አቶ ማዕረጉ በዛብህ በበኩላቸው ከሀገር ተጨባጭ ሁኔታ የሚነሱ የምርጫ ስርኣቶች ለውጤታማ መንግስታት መመስረትና ውጤታማ መሆን ወሳኝ መሆናቸውን አስረድተዋል ።

ምህረቱ ሻንቆ(ዶ/ር) "ብዝሃነትና የብዝሃነት አስተዳደር" በሚል የጥናት ወረቀታቸው በብዝሃነት አያያዝና አስተዳደር ዙሪያ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ልዩነትንና አንድነትን በተጣጣመ መልኩ ማስተዳደር እንደሚገባ የጠቆሙት ብዝሃነት ምቹ ድምር መልካም እድሎችና ፈተናዎች አሉበት ብለዋል።

ለብዝሃነት አስተዳደር ስኬታማነት የማህበረሰብ ውቅር፣ የጋራ ህልምና የሀገራዊ አንድነት እሳቤ ጉዳዮች መታሰብ እንዳለባቸው ጠቁመዋል ።

እንደ ኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታም የብሄራዊና የብሄር ማንነትን አጣጥሞ መሄድ እንደሚገባ ዶ/ር ምህረቱ አስረድተዋል ።

"የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝቦች የጋራ እሴቶችና ጸጋዎች ለሁለንተናዊ ብልጽግና" በሚል የጥናት ወረቀት ያቀረቡት አክመል መሀመድ(ዶ/ር) እንደገለጹት የክልሉን ህዝቦች በጋራ ወደ ብልግጽና ሊያሻግሩ የሚችሉ ሀብቶች፣ ጸጋዎችንም ምቹ ሁኔታዎች እንዳሉ አብራርተዋል ።

በተለይም የክልሉ ህዝቦች ሁለንተናዊ ትስስር ፣ የስነ ልቦና አንድነት፣ ስራ ወዳድነትና በርካታ ጸጋዎች ክልሉ ለማዕከል ካለው ቅርበት ጋር ተዳምሮ የለውጥ ማዕከል የመሆን ሰፊ እድል እንዳለው ጠቁመዋል።

ይህም ብቻ ሳይሆን ክልሉ የበርካታ የቱሪስት መስህቦችና የልማት አማራጮች ባለቤት መሆኑን በጥናታቸው አመላክተዋል።

አስተያየታቸውን የሰጡ የሲምፖዚየሙ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ሀገራዊ ለውጡን በጋራ ሆኖ መደገፍና ዘላቂነቱን ማስጠበቅ ብቻ ሳይሆን ቡድኖች ከሀይል አማራጭ ወደ ዴሞክራሲና ሰላማዊ አማራጭ እንዲመጡ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

ለዚህ ደግሞ ተቀራርቦ መነጋገር፣ ህገ መንግስቱን ማስከበር፣ የጋራ መግባባትን መፍጠርና አንድነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል ። በተለይም ደግሞ በልዩነቶች ውስጥ ሆኖ ሀገራዊ አንድነትን ማጽናት፣ ፈተናዎችን በጋራ ሆኖ መመከት ወሳኝ እንደሆነ ገልጸዋል ።

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል "ጀምሮ የመጨረስ ተምሳሌታዊ ክልል" ነው፦ አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር‎‎ህዳር 28/2018 ዓ/ም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል "ጀምሮ የመጨረስ ተምሳሌታዊ ክልል" መ...
07/12/2025

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል "ጀምሮ የመጨረስ ተምሳሌታዊ ክልል" ነው፦ አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር

‎ህዳር 28/2018 ዓ/ም

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል "ጀምሮ የመጨረስ ተምሳሌታዊ ክልል" መሆኑን አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር አስታወቁ።

‎አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ያለውን 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ሲምፖዚየም በይፋ ከፍተዋል።

‎ሲምፕዚየሙ ምርጥ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ የሚያስችል፣ለጥናትና ምርምር ተጨማሪ ዕድል የሚፈጥርና ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን የሚያጠናክር ስለመሆኑም አፈ ጉባኤው ገልጸዋል።

‎ኢትዮጵያ ትልቅ ህዝብ ያላት ትልቅ አገር መሆኗን ያነሱት አፈጉባኤው ፣ዕቅዶቻችንና ተግባሮቻችን ሁሉ ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርጉ እንዲሆኑ መረባረብ ይገባል ብለዋል።

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 20ኛውን የኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በአጠረና በተሳካ መንገድ ለማዘጋጀት ላደረገው ጥረት አመራሩንና ህዝቡን አቶ አገኘሁ አመስግነዋል።

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ በዓሉ የአገራችንን ገጽታ ለዓለም የምናስተዋውቅበት፣
‎አብሮነታችንና አንድነታችንን የምናጠናክርበት፣የአገረ መንግስት ግንባታችንን የምናፋጥንበት ነው ብለዋል።

‎በዓሉ ተቀራራቢ አረዳድ በህብረተሰቡ ውስጥ ለመፍጠር የሚያስችልና ፣የአንድነታችንና የጥንካሬያችን መለያ ስለመሆኑም አብራርተዋል።

‎የርስ በርስ ትስስር የሚፈጥር፣የማህበረሰቡን የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል ማሳየት የሚያስችል፣ህብረ ብሄራዊ አንድነታችንን ለማጽናት የሚያስችል በዓል ስለመሆኑም አፈ ጉባኤ ፋጤ አብራርተዋል።

የፈጠራ ውጤቶች ወደ ችግር ፈቺነት በመቀየር የሥራ ዕድል ከመፈጠር ባሻገር ከውጭ የሚገቡ ልዩ ልዩ የቴክኖሎጂ ምርቶች ለመተካት የሚያስችል ሥራ መሥራት እንደሚገባ ተገለፀ። ህዳር 27/2018 ...
06/12/2025

የፈጠራ ውጤቶች ወደ ችግር ፈቺነት በመቀየር የሥራ ዕድል ከመፈጠር ባሻገር ከውጭ የሚገቡ ልዩ ልዩ የቴክኖሎጂ ምርቶች ለመተካት የሚያስችል ሥራ መሥራት እንደሚገባ ተገለፀ።

ህዳር 27/2018 ዓ/ም

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሳይንስ፤ ኢንፎርሜሽንና የቴክኖሎጂ መምሪያ "የቴክኖሎጂ ተቋም ግንባታ ለቀልጠፋ አገልግሎት እምርታ" በሚል ርዕሰ ሀሳብ እየሰጠ የቆየው የአድቫንስ ስልጠና ተጠናቋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሳይንስ፣ ኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ልክ የለሽ ከበደ በስልጠና ማጠቃለያው ላይ እንደተናገሩት በ3 አብይ ርዕሶች በዞኑ ለሚገኙ የከተማ እና የወረዳ መዋቅር አመራና ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው የተግባርና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና መጠናቀቁን ገልፀዋል።

በኢኮቴ፣ በሶፍትዌር ልማት እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ላይ ሲሠጥ የነበረው ስልጠና የዘርፉ ባለሙያዎች አዳዲስ እውቀት፤ ልምድና ክህሎት በማስገኘት በባለሙያዎችና በተቋማት ደረጃ ያሉ ክፍተቶች ማስተካከል የሚችል እውቀትና ክህሎት እንዲሁም የልምድ መጋራት ዕድል እንደፈጠረ ተናግረዋል።

የሳይንስና የቴክኖሎጁ የፈጠራ ውጤቶች ወደ ችግር ፈቺ ምርትነት በመቀየር በዘርፉ የሥራ ዕድል ከመፈጠር ባሻገር ሀገራችን በዶላር የምታስገባቸውን ልዩ ልዩ የቴክኖሎጂ ምርቶች ለመተካት የቤት ሥራ ወስዶ መሥራት እንደሚገባ አመላክተዋል።

ኃላፊዋ አክለውም ባሉን የቴክኖሎጂ መሳሪያዎችና የመምራት አቅም ፈጣራን በማከል ለህብረተሠባችን የዕለት ተዕለት ኑሮ እንዲሻሻል በተቋማት ደረጃ ፈጣንና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት ሠጪ ተቋም እውን እንዲሆን የበኩላችን ኃላፊነት እንወጣ ብለዋል።

ሥልጠናው በተግባር መስጠት እንዲቻል የቁሳቁስ የመጠቀም ፈቃድ ለሰጡት የቡታጅራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በአጠቃላይ የተሣካ ስልጠና እንድንሰጥ ለተባበሩ ተቋማትና ኃላፊዎች ላቅ ያለ ምስጋና ችረዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ምክር ቤት የማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ታሪኩ ደምሴ እንደ ሀገር ከተያዙት 5ቱ ኢኮኖሚያዊ የእድገት መሰሶዎች ቴክኖሎጂን ማሳደግ አንዱ መሆኑ በመጠቆም ሥልጠናው እንደ ዞን ልናሳካ ያቀድነው ሀገራዊ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ነው ብለዋል።

ከኢኮቴ ፈቃድ አሰጣጥና እድሳት ጋር የተነሱት ጉዳዮች ያለው የአሰራር ህግ ክፍተት በደንብ ተረጋግጦ እልባት እንዲያገኝ ከሚመለከታየው አካላት ጋር ይሰራል የሚል ምላሽ ለምድረኩ ሠጥተዋል።

የፈጠራ ሥራዎች ወደ ችግር ፈቺ ደረጃ የማሻገር ሥራ ሁሉም መዋቅሮች አቅደው ለውጤታማነቱ ሊሠሩ እንደሚገባ በአፅኖት ገልፀዋል።

እንደ ሀገር 100% ከሚፈፀሙ እቅዶች አንዱ የሆነው የኢትዮ ኮደረስ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ዜጎች ተጠቃሚ የማድረጉ ጉዳይ መረባረብ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።

የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ሥራዎች ማሳደግ በሚያስችሉ ዝርዝር ርዕሰ ጉዳዮች፤ ፈጠራን ለማበረታታትና ለመደገፍ፤ የፈጠራ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች ተጠቃሚነትና መብቶቻቸው ላይ የሚያጠነጥን ለባለድርሻ አካላቱ ግንዛቤ የሚያሲዝ ስልጠና በተለያዩ የዘርፉ ባለሙያዎች ተሠጥቷል።

ሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎችን የማሻሻልና በላቀ መልኩ ማዘመን የሚያስችሉ ጽንሰ ሀሳቦች በማስረጽ ሀገር በቀል እውቀቶች ጉልበት፣ ጊዜ፣ ምርታማነትን በማሳደግና ችግር ፈቺ በሆነ መልኩ በማልማት ለትውልድ ለማስተላለፍ የሚያስችል ስልጠና ተሠጥቷል።

መምሪያው ቢያንስ አንድ የፈጠራ ሥራ በአንድ መዋቅር እውን ለማድረግ ግብ አስቀምጦ እየሠራ እንዳለ በመጠቆም ዕቅዱ እንዲሳካ ተቋማትና የሚመለከታቸው አካላት ኃላፊነትና ትኩረት ሠጥቶ መፈፀም እንዳለባቸው ተመላክቷል።

በዞኑ በርካታ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች እንዳሉ የተገለፀ ሲሆን እነዚህን በሚያስፈልጋቸው ሁሉ በማገዝ የፈጠራ ሥራዎቻቸው በሙሉ አቅም ወደ ምርት እንዲገቡ የማድረጉን ሥራ የጋራ ጥረትና ሥራ እንደሚጠይቅ ተገልጿል።

ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በተቋምና በባለሙያዎች መካከል የመፈፀም አቅም የሚያሳድግና የሚያቀራርብ እንደሆነ ከሰልጣኞች ተገልጿል።

እንደ ምስራቅ ጉራጌ ዞን አንድ የተሟላ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል እውን በማድረግ ለዘርፉ ተመራማሪዎችና ፈጣሪዎች ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ሀሳብ ቀርቧል።

ሌላው በአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት እና በፐብሊክ ሰርቫንት መብትና ግዴታዎች ላይ ወጥ መረዳት በመፍጠር ለተግባር አጋዥ ስልጠና በተጓዳኝ ተሠጥቷል።

በስልጠና መጨረሻ የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት መምሪያው የፈፀማቸው ተግባራት ሪፖርት ቀርቦ በማስገምገም የቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጣል።

የአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት አሰራር ግልፅ መረጃ የሚሰጥ በመሆኑ ተቋማት ወጥነት ባለው መልኩ ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው ከመድረኩ ተሳታፊ ተመላክቷል።

በዕለቱ ለተነሱት ጥያቄና አስተያየቶች ከሚመለከታቸው አመራርና ባለሙያዎች ምላሽና ማብራሪያ በመሠጥ የስልጠና መድረኩ ተጠናቋል።

"ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ለሚከበረው 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ለማክበር ወደማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እያቀኑ ላሉ የኢፍድሪ ...
06/12/2025

"ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ለሚከበረው 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ለማክበር ወደማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እያቀኑ ላሉ የኢፍድሪ ፌደረሽን ም/ቤት ልዑኳን ቡድን ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበልና ሽኝት ተደረገላቸው

ህዳር 27/2018 ዓ/ም

የ.ኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፌደሬሽን ም/ቤት ዋና አፈ ጉባሄ የተከበሩ አቶ አገኘሁ ተሻገር እና የ.ኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፌደሬሽን ም/ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ዘህራ ሁመድ የተመራዉ የሉዑካን ቡድን በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ሲደርሱ የተከበሩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን፣ የተከበሩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ አቶ እንዳልካቸዉ ጌታቸዉ እና የምስራቅ ጉራጌ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ እና የብልፅግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ጫካ እና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች በፀጥታ አበላቶች ደማቅ አቀባበል በማድረግ ተሸኝተዋል።

Address

Awassa

Telephone

+251964476649

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት:

Share