17/10/2025
ግልፅ ምክር ለሌ/ጄ ታደሠ ወረደ ⏰ አሁን የት እንዳለህ እኛም አንተም እናውቃለን!
ከወንጀሉ ተጠያቂነት ለማምለጥ አዲስ ጦርነት በመጫር ላይ ያለው አሮጌው የህውሀት አንጃ የክልሉ ፕሬዘዳንት ጀነራል ታደሠ ወረደን እጅ የመጠምዘዝ ስራውን በሚገባ እየሰራ ነው። ህውሀት በክልሉ የሚያደርጋቸው የጦርነት ዝግጅትና ከግብፅና ከሻእቢያ ሰዎች ጋር እየሰራ ያለው አደገኛ ስራ ከክልሉ ፕሬዘዳንት ታደሠ ወረደ አይን የተሸሸገ አይደለም።
ምክሬ ይሄ ነው። ጀነራል ታደሠ ወረደ ከጦርነቱ በፊት ደብረፂዮንና የቡድኑ አባላት የተሳሳቱትን ስህተት አትድገም። የትግራይ ህዝብ ከዚህ በኋላ ጦርነትን የሚሸከምበት ጫንቃ የለውም። ትግራይ ላይ ያለህን ሃላፊነት ተጠቅመህ እየተጫረ ያለውን አደገኛ እሳት ቮልካኖ ከመሆኑ በፊት በማጥፋት ለትግራይ ህዝብ ውለታ ዋልለት። ይህን ሳታደርግ ቀርተህና አእምሯቸው በሻገተ በህውሀትና በሻእቢያ አዛውንቶች አኪጦፌላዊ ምክር ተገፍተህ ትገራይን ለጦርነት ዳግም ከዳረግካት ከታሪካዊ ተጠያቂነት እንደማታመልጥ የታወቀ ይሁን። እናት ዳግም አታልቅስ።