12/03/2026
ዉድ ኢትዮጵያዊያን ሀገር ዉስጥም ይሁን ከሀገር ዉጪ ያላችሁ፦ በጋሞ ዞን በደረሰ ጎርፍና የመሬት መንሸራተት አደጋ በርካታ ወገኖቻችን ከቤት ንብረታቸዉ ተፈናቅለዉ ይገኛሉ። ብዙ ወንድምና እህቶቻችን ህይወታቸዉን አጥተዋል። የደረሱበት የማይታወቅ ወገኖቻችን ቁጥርም ቀላል አይደለም። በመሆኑም ደጋግ ኢትዮጵያዊን ድጋፍ እንድታደርጉ ዘንድ እንጠይቃችኋለን። የጋሞ ህዝብ ከራሱ በላይ ለሌላዉ የሚያስብ፣ ኢትዮጵያ ሠላም እንድትሆን ዋጋ የከፈለ ህዝብ ዛሬ አደጋ ደርሶት የዉድ ኢትዮጵያን የድጋፍ እጅ ይሻል። የዓይነትም የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ይቻላል።
ፈጣሪ በምህረቱ ያስበን!