Aben K GEl

Aben K GEl ትላንትን በይቅርታ ታክመን ዛሬ በፍቅር ታጅበን ለነገ በተስፋ እናልፋለን። አሜን!!!!

21/01/2026

#ሙጋቤ ከተናገራቸው...ክፍል_3
1- ለነጫጭ መኪኖች ጥቁር ጎማ መጠቀም እስካልቆመ ድረስ ዘረኝነት አይጠፋም።

2- ከሌሎች ቀለማት በፊት ነጫጭ ልብሶችን አስቀድሞ ማጠብ እስካልቆመ ድረስ ዘረኝነት አይጠፋም።

3- ጥቁር ቀለምን ለመጥፎ ገድ፣ ነጭን ደግሞ ለሠላም ምልክት መጠቀም እስካልቆመ ድረስ ዘረኝነት አይጠፋም።

4- ጥቂር ቀለምን ለሐዘን፣ ነጭን ግን ለሠርግ መጠቀም እስካልቆመ ድረስ ዘረኝነት አይጠፋም።

5- ዕዳቸውን ያልከፈሉ ሰዎችን ከነጭ መዝገብ ይልቅ ጥቁር መዝገብ ላይ መመዝገብ እስካልቆመ ድረስ ዘረኝነት አይጠፋም።

6- በፑል ጨዋታ ላይ በነጭ ድንጋይ ጥቁር ድንጋዮችን መምታት እስካልቆመ ድረስ ዘረኝነት አይጠፋም።

~~~~~~~~~

7👉"በእርግጥ እኔ በበኩሌ ችግር የለብኝም። ምክንያቱም ተፀዳድቸ መቀመጫየን የምጠርገው በጥቁር ሳይሆን በነጭ ሶፍት ነውና!"

ስንተኛው ቁጥር እንደተመቻችሁ ኮመንት አድርጉ፡፡
ሀቅ እና ድንቅ

20/01/2026

“ቃና ዘገሊላ” ማለት ምን ማለት ነው? ምን ምን ተከናወነበት?
👉ሁሉን ነገር በመጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ እንየው👇

🔹 ቃና
ትርጓሜ፡ የተዘጋጀ ቦታ
መንፈሳዊ ትርጓሜ፡
👉 ተዘጋጀ ልብ
🔹 ዘገሊላ
ትርጓሜ፡ የተበተነ ክልል
መንፈሳዊ ትርጓሜ፡
👉 በኃጢአት የተበተነ ዓለም
👉 መደምደሚያ
ቃና ዘገሊላ ማለት፦
👉 በተበተነ ዓለም ውስጥ ያለ የተዘጋጀ ልብ።
3️⃣ ጋብቻው የሚያስተምረን
ጋብቻ = ክርስቶስ እና ቤተ-ክርስቲያን
ክርስቶስ በጋብቻ መገኘቱ፦
👉 ሕይወታችንን ሁሉ ለመባረክ መጣ
📌 ምክንያት፦
ክርስቶስ ከሕይወታችን ከገባ፣
ቤታችን፣ ስራችን፣ ግንኙነታችን ይባረካል።
4️⃣ ወይን ጠጅ መጨረሱ ምን ይመስላል?
ወይን ጠጅ መጨረሱ = የሰው ኃይል መጨረሻ
ብዙ ጊዜ እኛም እንዲህ እንላለን፦
👉 “ተስፋዬ ተሟጦ አልቋል”
👉 “ኃይሌ አበቃ”
📌 ነገር ግን፦
የሰው ነገር ሲያበቃ
👉 የእግዚአብሔር ሥራ ይጀምራል
5️⃣ የእመቤታችን ማርያም ትምህርት
“የሚነግራችሁን ሁሉ አድርጉ” (ዮሐ 2፡5)
👉 ይህ የኦርቶዶክስ መንገድ ነው፦
ምልጃ
ታዛዥነት
እምነት
6️⃣ ውሃን ወደ→ ወይን ጠጅ መቀየሩ (ዋና መልዕክት)
ውሃ = ደካማ ሕይወት፣ ሕግ፣ ድካም
ወይን ጠጅ = ጸጋ፣ ደስታ፣ አዲስ ሕይወት
👉 ክርስቶስ ሲገባ፦
ሐዘን ወደ→ ደስታ
ባዶነት ወደ→ ብዛት
ኃጢአት ወደ→ ጽድቅ
7️⃣ መደምደሚያ (Conclusion)
ወንድሞችና እህቶች ሆይ፣
ክርስቶስ ዛሬም በቃና ዘገሊላ ነው፤
👉 በልባችን ውስጥ።
❓ ልባችን ተዘጋጅቶ ነውን?
❓ ውሃችንን ለእርሱ ሞልተናልን?
👉 እርሱ ዛሬም
ውሃን ወደ ወይን ጠጅ ይለውጣል
ለእርሱ ክብር ይሁን። አሜን ✝️

06/12/2025

ሮበርት ሙጋቤ
1. ህይወትህ ትርጉም እንዲኖራት #ዓላማ ይኑርህ፡፡
2. የአንተነትህ ትልቁ ምዕራፍ ከእውቀትህ በላይ #ስራህ መሆኑን አትርሳ፡፡

3. ፈጣሪ ካልፈታው ገንዘብ ችግርህን አይፈታውም ፈጣሪ ካልሞላው ሰው ጎንህን አይሞላውም #ፈጣሪ ካልገለጸ እውቀት ጥበብ አይሆንም

4. ይቺ ዓለም ለሁሉም እኩል ናት፡፡ ዛሬ ብታገኝ ነገ ታጣለህ ዛሬ ብታሸንፍ ነገ ትሸነፋለህ፡፡ ለሁሉም ጊዜ አለው የሚባል መዶሻ አለ፡፡ መልካምነት ዋጋ ያስከፍልሃልና ሁሌም ፍጹም #መልካም ሰው ሁን

5. ንጹህ ልብ ልክ እንደ አበባ ናት! ፍሬ ባናገኝባትም #ውበቷ ግን እጅግ ማራኪ ነው፡፡
:
6. የውድቀት መጀመሪያው ራስህን #አዋቂና ብቸኛ አድርጎ ማሰብ ነው

6. ፍጻሜህ እንዲያምር ራስህን አታመጻድቅ ሁሌም ከስህተትህ ለመታረም ፈቃደኛ ሁን ጥፋትህን አሜን ብለህ መቀበልህ ክብርህን የሚጎዳብህ አይምሰልህ፡፡

7. ጠቢብ ሰው እንኳን ከራሱ ከሰው #ስህተት ተምሮ ራሱን ይጠብቃል ይመለሳልና፡፡

8. በህይወት ውስጥ አንዱ ሲታወር አንዱ መሪ መሆን አለበት

9. እውነትነ የሚናገር ሰው አፉ ክፉ ይመስላል #ልቡ ግን ንጹህ ነው

10. ህይወት በመደጋገፍ የተሞላች ናትና ወንድምህን #ከመርዳት ወደሗላ አትበል!

የትኛው አባባል ተመቻችሁ ???
__________________________

05/12/2025

ከአጎት ሮበርት ሙጋቤ ንግግሮች፦

1...ሴቶች በሙሉ የኤድስ መድሃኒት እስኪገኝ ድረስ የግብረ ስጋ ግንኙነት (S*x) አንፈጽምም ብለው ቢያምጹ ኖሮ ወንዶች በ30 ቀናት ውስጥ መድሃኒቱን ባገኙት ነበር።

2...ናይጄርያን የመሰሉ ብዙ ቋንቋዎች የሚናገር ህዝብ ያላቸው አገሮች መስማት የተሳነው ፕሬዝደንት ነው የሚያስፈልጋቸው።

3...አዳምና ሄዋን ቻይናዊያን ቢሆኑ ኖሮ፡ እስካሁን ድረስ ገነት ውስጥ በኖርን ነበር። ምክንያቱም የእጸ በለስ ፍሬውን ትተው እባቡን በበሉት ነበር።

4...ከአንድ ሰው በላይ የምታፈቅር ከሆነ፡ ውስጥህ ያለው ልብ ሳይሆን'memory card' ነው፡

5...አንዳንድ ጊዜ ወደ ኋላ መለስ ብለህ ስትመለከት ከእናትህ በላይ ለሴት ልጅ ገንዘብ የምታጠፋ ከሆነ ያኔ እጀ-ሰብ እውነት መሆኑ ይገባሃል።

6...አንዳንድ ሴቶችን ስትመለከት ጂም የሚሰሩ ይመስላሉ። ግን የጂምናዝየምን በር እንኳ አይተውት አያውቁም። ሆኖም ግን ከአንዱ ወንድ ወደ ሌላው ወንድ ለመሮጥ ሲሉ ቅርጻቸውን ይጠብቃሉ።

7...ትዳር እያለህ ከተማሪ ሴቶች ጋር መውጣት ደስ የሚልህ ከሆነ ለሚስትህ የተማሪ ዩኒፎርም ግዛላት፡፡

8...ሰይጣን ራሱ gay አልነበረም፡ ምክንያቱም እራቁቱን ከነበረው አዳም እራቁቷን የነበረችውን ሄዋንን ስለመረጠ፡፡

9...አስቀያሚ ከሆንክ አስቀያሚ ነህ ስለ ውስጣዊ ውበት አትናገር ምክንያቱም X-ray እያየን አይደለም የምንሄደው፡፡

10...አምላክ ምርጥ ተመራማሪ ነው፡፡ ምክንያቱም ከወንድ ልጅ የጎድን አጥንት ወስዶ ድምጽ ማጉያ (loud speaker) ፈጠረ፡፡

11...ዓለም አፍሪካን በድላታለች… ከአውሮፓ አንድ ነጭ ወደ አፍሪካ ከመጣ የውጪ ዜጋ ጎብኚ ይባላል። ከአፍሪካ አንድ አፍሪካዊ ወደ አውሮፓ ከሄደ ግን ህገ ወጥ ስደተኛ ይባላል፡፡

12...በግሩፕ ነጮች ወደ አፍሪካ ከመጡ ቱሪስት ይባላሉ፡፡ በብዛት አፍሪካዊያን ወደ አውሮፓ ከሄዱ ደግሞ ረፍዩጂስ (ስደተኞች) ይባለሉ።

13...ነጮች አፍሪካ ውስጥ መጥተው የአፍሪካዊያን አሰሪ ይሆናሉ፡፡ አፍሪካዊያን አውሮፓ ሄደውም የነጮች ሰራተኛ ነው የሚሆኑት።

14...አፍሪካ ውስጥ በስነ-ስርዓት የሚከበረው ማስጠንቀቂያ "battery low!"የሚለው ብቻ ነው።
©FB

በስንተኛው ቁጥር ላይ ያለው አባባል ተመቻችሁ?

♨️◁15 አስገራሚ ንግግሮች▷1. በጣም ብዙ የምትናገር ከሆነ ፤ ትዋሻለህ።2. በጣም ብዙ የምታስብ ከሆነ ፤ ድብርት ውስጥ ትገባለህ።3. በጣም ብዙ የምታለቅስ ከሆነ ፤ የአይን እይታህን ታጣ...
05/12/2025

♨️◁15 አስገራሚ ንግግሮች▷

1. በጣም ብዙ የምትናገር ከሆነ ፤ ትዋሻለህ።

2. በጣም ብዙ የምታስብ ከሆነ ፤ ድብርት ውስጥ ትገባለህ።

3. በጣም ብዙ የምታለቅስ ከሆነ ፤ የአይን እይታህን ታጣዋለህ።

4. በጣም ብዙ የምታፈቅር ከሆነ ፤ ማንነትህ ይጠፋል።

5. በጣም ብዙ ስለሰዎች የምታስብ ከሆነ ፤ ዋጋህን ሰዎች እያጡት ይመጣሉ።

6. በጣም ብዙ የምትጫወት ከሆነ ፤ አብዛኛውን ጊዜ ማንም ከቁምነገር አይቆጥርህም።

7. በጣም ብዙ የምታምን ከሆነ ፤ በሰዎች ትካዳለህ።

8. በጣም ብዙ የምትሰራ ከሆነ ፤ በውጥረት ትሞታለህ።

9. በጣም ብዙ የምትመገብ ከሆነ ፤ ከመጠን ያለፈ ውፍረት ውስጥ ትገባለህ።

10. በጣም ብዙ እንቅልፍ የምትተኛ ከሆነ ፤ ስራ ፈት ትሆናለህ።

11. በጣም ብዙ ገንዘብ የምታባክን ከሆነ ፤ የወደፊት ነገር ምንም አይኖርህም።

12. በጣም ብዙ ሜክፕ የምትጠቀም ከሆነ ፤ የአንተን ውበት እያጣኋው ትመጣለህ።

13. በጣም ብዙ ነገር የምትመለከት ከሆነ ፤ ትኩረትህን እያጣኸው ትመጣለህ ።

14. በጣም ብዙ ስለ ህይወት የምታስብና የምታሳድድ ከሆነ ፣ ሁሉንም ነገርህን ታጣለህ።

15. በጣም ብዙ ነገር የምትጠብቅ ከሆነ ፤ በጣም ትከፋለህ። በጣም ብዙ አትሁን ምክንያቱም ያ በጣም ብዙ ነገር ብዙ ይጎዳሀልና።

Address

Aroressa
Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Aben K GEl posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share