Sidama Media Service - SMS

Sidama Media Service - SMS Fast and real information for an active society

ባህላችንን የማያውቁ አካላት ባህላችንን እየጣሱ ሲሉ የሲዳማ አባቶች ተናገሩየሲዳማ የባህል እና የሃገር ሽማግሌዎች ከሲዳማ ባህል ውጪ በሆነ መልኩ የሲዳማ ህዝብንም ሆነ ባህል በማይወክል መንገ...
11/03/2025

ባህላችንን የማያውቁ አካላት ባህላችንን እየጣሱ ሲሉ የሲዳማ አባቶች ተናገሩ

የሲዳማ የባህል እና የሃገር ሽማግሌዎች ከሲዳማ ባህል ውጪ በሆነ መልኩ የሲዳማ ህዝብንም ሆነ ባህል በማይወክል መንገድ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን አወገዙ።

በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውን የሲዳማ ዘመን መለዋጫ (ፊቼ ጨምበላላ) በመጋቢት አጋማሽ በሲዳማ ክልል በሀዋሳ በደማቅ ሊከበር በቀን ተቆርጦለት እያለ በዓሉን ለማደብዘዝ እና ባህሉን ባልጠበቀ ስርዓት በሌለው መልኩ ከሰሞኑን በተለየዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የውሸት ወሬዎችን እና ግጭት እየሰበኩ ያሉ አካላትን የሲዳማ ሃገር ሽማግሌዎች ከባህል ያፈነገጡ ሲሉ ገልፀዋል።

የሲዳማ ህዝብ ለዘመናት ዋጋ ከፍሎ ያገኘውን የክልልነት ጥያቄ መልስ ዋጋ ለማሳነስ የህዝቡን ሰላምና ልማት ለማደፍረስ እየሰሩ ያሉ አካላት ህዝባችንን የማይወክሉ ለግል ፍላጎታቸው እና ጥቅማቸው ብለው የበርካታውን ህዝባችንን ጥቅም እና ፍላጎት የትግል ዋጋ ለማሳነስ እየሄዱ ያሉበት አካሄድ ከሲዳማ ባህል እና ቱሪፍት አንፃር አስነዋሪ መሆኑን የሀገር አባቶች ገልፀዋል።

ሲዳማ የሁሉንም ህዝብ እና ብሔር ብሔረሰቦች በማዕቀፍ በሰላም እና በአብሮነት እየኖረ ያለ ትልቅ ህዝብ ሲሆን “ጥያቄውም መልሱም” በባህል በስርዓት የተቃኘ እንጂ በስድብ የሚታወቅ ባለመሆኑ ከሰሞኑን በዚህ ድርጊት የተሳተፉ እየተሳተፉ ያሉ አካላትን አባቶች አውግዘዋል።

ህዝባችንን ከመላው በክልሉ ውስጥ ሆነ ክልሉ ውጪም ከአጎራባች ህዝቦቻችን ከሚገኙ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ጋር በሰላምና በደጋገፍ እየኖረ ያለ ህዝብ ሲሆን ይህንን የጠሉ አካላት የህዝባችንን ሰላም ለማደፍረስ ከጎረቤት እና አጎራባች ህዝቦቻችን ጋር ያለንን ወዳጅነት ጥርጣሬ ውስጥ ለመክተት እየሰሩ መሆናቸው የገለፁት የሃገር ሽማግሌዎች እኝህ ሃይላት የሲዳማ ህዝብ ጠላት፥ የሲዳማ ባህል ጠላት፥ የሲዳማ ህዝብ ስርዓት ጠላት፥ የሲዳማ ህዝብ ሰላም ጠላት ናቸውም ሲሉ የሲዳማ አባቶች (አያንቶች) ገልፀዋል።

ከቀናት በኋላ የሚከበረውን የሲዳማ ህዝብ ዘመን መለወጫ (ፊቼ ጨምበላላ) በዓልን በሰላም ለማክበር ህዝባችንን ከመንግስት ጋር እየሰራ ነው ያሉት የሃገር ሽማግሌዎች ሰላማችንን ባህላችንን ጠብቀን ስርዓታችንን አፅንተን እናከብራለን ብለዋል።

አክለውም በዚህ የውሸት ድርጊት እና ውሸቶች ተሳትፋችሁ የሲዳማ ህዝብ በማይወክል መንገድ ውስጥ ሆናችሁ የሲዳማ ሃላሌን (እውነትን) ተጣርሳችሁ ያላችሁ ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡም ሲሉም አሳስበዋል።

የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምበላላ በዓል አከባበር ዝግጅት አስመልክቶ ተገኙበት መድረክ ላይ የሃገር ሽማግሌዎች ይህንን መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጥፋትህ የስራ ሰው መሆንህ ነው፤ ከተረጂነት ህይወት ህዝብን ለማላቀቅ ያለ ዕረፍት መልፋትህ ነው፤ ለሀገርህ መልካም ራዕይ መሰነቅህ ነው። ወንጀልህ ፍቅርን እና ይቅርታን መስበክህ ነው።ሀጢአት...
17/01/2025

ጥፋትህ የስራ ሰው መሆንህ ነው፤ ከተረጂነት ህይወት ህዝብን ለማላቀቅ ያለ ዕረፍት መልፋትህ ነው፤ ለሀገርህ መልካም ራዕይ መሰነቅህ ነው። ወንጀልህ ፍቅርን እና ይቅርታን መስበክህ ነው።

ሀጢአትህ አምባገነንነትን የምትጠየፍ በታጋሽነትና ለሁሉም የቀረብክ ትሁትና ታጋሽ መሪ መሆንህ ነው። ድክመትህ በጉልበት የማታስብ፣ በመነጋገር፣ በመወያየትና ለሰላም በርህን ክፍት ማድረግህ ነው።

ጀግናው መሪያችን የጥላቻቸው መንስኤዎች እነዚህ ከሆኑ .!! እንግዳውስ እነዛ ያንተ ጠላቶች ብቻ ሳይሆኑ የህዝብም የሃገርም ጭምር ጠላቶች ናቸው።

ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎን ሳይረዱት፤ ሳይገነዘቡት፤ በውስን መረጃ አዛቢዎች የተዛባ መረጃ ቢሰራጭም እሱን የምናውቀው እንወደዋለን፤ እናከብረዋለን ዘግይተው የተረዱትም በፍቅር እንደሚደግፉት ብሎም እየደገፉት እንደሚገኝ ይታወቃል።

በሃገር መሪ ለዛውም ከጠባብ ዘረኝነት የነፃ ብሎም በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራ ህዝብ ደጀን፤ የህዝብ ጓደኛ የሆነ መሪ ላይ በውስን መሳሳቶች የተነሳውን ረብ የለሽ ወሬ ፍፁም ተቀባይነት የሌለው መሆኑ ይታወቃል።

ክብር አቶ አብርሃም በጎ ኅሊና እና ቅን ልቦና ያለው ሰው ብሎም በትክክለኛ መንገድ እየተጓዘ እንደሆነ ካወቀ፣ በጉዞው የሚገጥሙትን ፈተናዎችን እና ተግዳሮቶችን እንኳን በመልካም እየተረጎመ የሚያይ ነው።

ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ ማለት የልብ አድርስ የተግባር ሰው፣ ዝምተኛው መብረቅ እና ያልተዘመረለት ጀግና ይሉታል። ብዙ አይናገርም፣ የተናገረው ደግሞ ከመሬት ጠብ አይልም፤ ብዙ ከመናገር ብዙ መስራትን በመምረጡ ተመራጭ እና ድምፅ አልበው መብረቅ ቢባል ያንስበታል እንጂ አይበዘበትም ይላሉ ባልደረቦቹ።

ያለ ዕረፍት ሥራውንም በክህሎት፣ በብቃት፣ በዕውቀትና በቁርጠኝነት ተግባራትን ህዝባዊ በማድረግ ሰርቶ የሚያሰራ፣ ግንባር ቀደም መሪ የሆነ፣ ሐቀኛና ብልህ መሪ፣ በጠንካራ ስራ አስደማሚ የሆነ ብርቱ ሰው፣ ለህዝቦች መብትና ጥቅም አቅሙን በሙሉ አሟጦ ከአጋር ጓዶቹ ጋር ሳይሰለች ሌት ተቀን ሰርቶ የሚያሠራ ውጤታማ ብቁ ሰው ማለት አብርሃም ማርሻሎ ነው።

ለፍቶ ውጤታማ ተግባር መሥራት እና ማሳካት ጀግንነት ነው ያሳካውን ድል ማድነቅ ደግሞ መሰልጠን ነው!

አብርሽ የህዝባችንን አይን ብሌን ነው 🙏

በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በታላቅ ድምቀት ሲከበር የነበረው የጥምቀት በዓል በሰላም መጠናቀቁን የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ!!!ጥር 13/2015-ሀዋሳ-ሲዳማ-ኢትዮጵያ     ...
22/01/2024

በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በታላቅ ድምቀት ሲከበር የነበረው የጥምቀት በዓል በሰላም መጠናቀቁን የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ!!!

ጥር 13/2015-ሀዋሳ-ሲዳማ-ኢትዮጵያ
የሲዳማ-ሚዲያ-አገልግሎት

በመላው የክልሉ አከባቢ ሲከበር የነበረው የጥምቀት በዓል ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በሰላማዊ ሁኔታ ተከብሮ በሰላም ተጠናቅቋል። በክልሉ ውስጥ ከመላው አድባራት 147 የሚሆኑ ታቦተ ህጎች በሰላም በመውጣት አብዛኞቹ ወደ አድባረ ማደሪያቸው ተመልሰዋል።

የእምነቱ ተከታይ ምዕመን ብሎም የሌላው እምነት ተከታይ ምዕመናት በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ከፀጥታው ሃይል ጋር ከፍተኛ ትብብር ያደርጉ ሲሆን ለዚህም ምስጋና ይገባቸዋል ሲሉ የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞትዮስ ገልፀዋል።

በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ ለሃገር መከላከያ ሰራዊት ፣ ለፌደራል ፖሊስ ፣ ለብሄራዊ መረጃና ደህንነት አባላት ፣ ለክልሉ የፀጥታ ግብረ ሃይል ደከመን ሰለቸን ሳይሉ በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለወሰዱት ቁርጠኛ አቋም ከልብ ምስጋናቸውን አቀርበዋል።

ተጨማሪ የሚዲያ አውታሮች
instagram/
telegram/https://t.me/sidamamediaserviceSMS
Threads/https://www.threads.net/

የ2016 ዓ.ም የሲዳማ ጎፈሬ ካፕ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ምስጋናውን አቅርቧል።በሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና ...
26/09/2023

የ2016 ዓ.ም የሲዳማ ጎፈሬ ካፕ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ምስጋናውን አቅርቧል።

በሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና ጎፈሬ የስፖርት ትጥቅ አምራች ድርጅት የጋራ አዘጋጅነት ከመስከረም 5 ጀምሮ በ 8 ክለቦች መሀከል ሲካሄድ የሰነበተዉ የ2016 ዓ.ም የሲዳማ ጎፈሬ ካፕ በትላንትናው እለት በመቻል ስፖርት ክለብ አሸናፊነት ተጠናቋል።

ከዉድድሩ መጠናቀቅ በኋላ በዛሬው እለት የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ አንበሴ አበበ ዉድድሩ በሰላም ተጀምሮ በደመቀ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋናውን አቅርቧል።

በዚህም መሰረት የክልሉ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ አንበሴ አበበ ለተሳታፊ ቡድኖች ፣ ለዉድድሩ መሳካት ሜዳ በመፍቀድ አስተዋጽኦ ላበረከተዉ ሀዋሳ ዩንቨርስቲ ፣ በቴክኒካል ጉዳዮች አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦች ፣ ለዳኞች ፣ ለዉድድር ስነስርዓት ኮሚቴዎች ፣ ለፀጥታ ሀይሎች ፣ ለሚዲያ ባለሙያዎች ፣ ለቀይ መስቀሎች ፣ ለሲዳማ ቡና እና ለሀዋሳ ከተማ እግር ኳስ ክለብ የደጋፊዎች ማህበር ስራ አስፈፃሚዎች ፣ ለስፖርቱ ቤተሰቦች እና በተለያየ መንገድ ይህ ዉድድር በሰላም ተጀምሮ በደማቅ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በፌዴሬሽኑ ስም ምስጋናዉን አቅርቧል።

አቶ አንበሴ አበበ
የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት

መስከረም 15/2016 ዓ.ም
ሀዋሳ ፣ ሲዳማ ፣ ኢትዮጵያ

© Sidama Football Federation

ሜዳ ዉስጥ ታገቢኛለሽ ብሎ እሺታን አገኘ..በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘዉ ሲዳማ ጎፈሬ ካፕ የእግር ኳስ ዉድድር ላይ በዛሬው እለት ሲዳማ ቡና ከ ኡጋንዳዉ ኪያንዳ ቦይስ ጋር ባለዉ የምድብ...
20/09/2023

ሜዳ ዉስጥ ታገቢኛለሽ ብሎ እሺታን አገኘ..

በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘዉ ሲዳማ ጎፈሬ ካፕ የእግር ኳስ ዉድድር ላይ በዛሬው እለት ሲዳማ ቡና ከ ኡጋንዳዉ ኪያንዳ ቦይስ ጋር ባለዉ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ላይ ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት የሲዳማ ቡና ደጋፊ የሆነዉ ደግፌ ደምሴ ሜዳ ዉስጥ ለእጮኛዉ ቡቹ ተሾመ የታገቢኛለሽ ጥያቄ አቅርቦ እሺታን አግኝቷል።

Sidama Media ServiceSidama Media Service - SMSSMS

የእንግድነት ጥሪ ከብሄር ብሄረሰቦች ለሲዳማ መንግስት እና ህዝብ ተደረገ*************************  መስከረም4/2016ዓ/ምበትላንትናው እለት ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መቀመጫ ሶዶ...
15/09/2023

የእንግድነት ጥሪ ከብሄር ብሄረሰቦች ለሲዳማ መንግስት እና ህዝብ ተደረገ
*************************

መስከረም4/2016ዓ/ም

በትላንትናው እለት ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መቀመጫ ሶዶ የወላይታ ዞን የወላይታ ህዝብ ዘመን መለወጫ የሆነው የጊፋታ በዓል ላይ የሲዳማ ክልል መንግስት በክብር እንግድነት በልዑካን ቡድናቸው የግብዣ ጥሪ ለሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ፅ/ቤት ሃላፊ ለሆኑት አቶ ካሱ አሩሳ አስረከባቸው ተውቋል።

በተጨማሪም የኦሮሞ ህዝብ ታላቁ በዓል የሆነው ኢሬቻ በዓል ላይ ለመታደም የሲዳማ ክልል ወጣቶች(ኤጄቶች) እንቅስቃሴ መጀመራቸው ተሰምቷል።

የሲዳማ ህዝብ እና የኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ለዘመናት የቆየውን ይህን አብሮነት በተሻለ መልኩ መጠናከር አለበት በማለት እንቅስቃሴውን መጀመራቸውን ሚዲያችንን ከመረጃ ምንጮች ማግኘት ችሏል።

ይህን ጉዞ የሚያስተባብሩ አስተባባሪዎች ስለጉዞ ዝርዝር እና ግልፅ መግለጫ የሚሰጡ ሲሆን በዚህም የኢሬቻ በዓል ላይ የሲዳማ ወጣቶች ሊሳተፉ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።

Sidama Media ServiceSidama Media Service - SMSSMS

የብልፅግና ፓርቲ ሃገራዊ ስልጠና በአዳማ ከተማ ጠራ!!!******* መስከረም3/2016(ሃዋሳ)የብልፅግና ፓርቲ በፌደራል የመንግስት መዋቅር እና በክልል ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ሃላፊዎችንን ...
14/09/2023

የብልፅግና ፓርቲ ሃገራዊ ስልጠና በአዳማ ከተማ ጠራ!!!
*******

መስከረም3/2016(ሃዋሳ)

የብልፅግና ፓርቲ በፌደራል የመንግስት መዋቅር እና በክልል ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ሃላፊዎችንን በአዳማ ለ11 ቀን የሚቆይ ስልጠና መድረክ ጠርቷል።

ስልጠናው የአቅም ግንባታ መርህ ለማስጨበጥ የታቀደ ሲሆን ከሁሉም ክልሎች ሁሉም ከፍተኛ የቢሮ አመራሮች መገኘታቸው ደግሞ ከስልጠናው ባለፈ የስራ ልምድ ልውውጥ ለማድረግ መልካም መንገድ የሚከፍ መሆኑን የመረጃ ምንጮች ገልፀዋል።

Sidama Media Serviceለአዲስ አመት አዲስ ስጦታ የምስራች ይዘን  ብቅ ብለናል። ሲዳማ ሚዲያ ሰርቪስ አዲስ ሀገራዊ ሚዲያ ከሶስት ወር በላይ እራሱን ሲያደራጅ የነበረው ሚዲያችንን የ...
11/09/2023

Sidama Media Service

ለአዲስ አመት አዲስ ስጦታ የምስራች ይዘን ብቅ ብለናል። ሲዳማ ሚዲያ ሰርቪስ አዲስ ሀገራዊ ሚዲያ ከሶስት ወር በላይ እራሱን ሲያደራጅ የነበረው ሚዲያችንን የሲዳማ ሚዲያ ሰርቪስ ዛሬ ለአዲስ አመት አዲስ ስጦታ ብሎ በአዲስ አመት ወደ አንባቢያን በዲጂታል ሚዲያ ብቅ ብሏል።

የሲዳማ ህዝብ ድምፅ ሁለተናዊ ገፅታ ለአለም ህዝቦች ያስተጋባል ብለን የገነባነው ሚዲያችንን የሃገራችንን ባህል ወግ እና ስርዓት በተለይም ሲዳማ ሲዳማ በሚል ልዩ ለዛ ባላቸው ፅሁፍ ታሪክን እንቃኛለን ፈጣን ሃገራዊ ክልላዊ ዜናዎች የፖለቲካ ትንተና መዝናኛ ስፖርት በቅርቡ አድማሱን በሁሉም ዘርፍ እያሰፋ ለህዝብ ለመድረስ እቅድ ይዞ ስራው በይፋ ጀምሯል።

እንደ ህዝብ ዲጂታላይዝድ ሚዲያ ከመፍጠር አኳያ እና ፈጣን እና ትክክለኛ መረጃ ለነቃ ማህበረሰብ በሚል መፈክር ማህበረሰብ ለማንቃት የአንቂ ሚዲያ ቅርፅ ይዞ በዘመነ መልኩ 24 ሰዓት የመረጃ ምንጭ ለመሆን ሚዲያችንን Sidama Media Service ወደ አግልግሎት ገብቷል።

የተመረጡ ወጣቶች ያሳተፈው ይህ ሚዲያ በመንግሥትም ሆነ በህዝብ ዘንድ ያለውን የዲጂታል ሚዲያ አቅርቦት ችግር በተወሰነ መልኩ ሊቀርፍ ይችላል ተብሎ ይታመናል። ሚዲያው የአዲስ አመት ክስተት የሆነበት ምክንያት በአዲስ መንፈስ በአዲስ አብሮነት አዳዲስ መረጃዎች ለነቃው ህዝባችንን ለአዲስ አመት በስጣታ መልክ አቅረበነዋል።

ዛሬ የመጀመሪያ የሚዲችንን ስርጭት የበጎ እና በመልካም ምኞቶች መልካም ቃላቶች የተቀኙ መሆናቸው ሚዲያችንን ሁሌም ከጥላቻ ንግግር የፀዳ ብሎም በመልካም ዕሴት የተገነባ መሆኑን ለማረጋገጥ ታስቦ የተደረገ ነው።

ሲዳማ ሚዲያ ሰርቪስ በዲጂታላይዝድ የመረጃ ምንጮች ሲዳማን ብሎም ሃገራችንን ኢትዮጲያ ከአለም ለማስተሳሰር እቅድ ይዞ የተነሳ ሲሆን በቅርቡም ግቡን ለማሳካት በተለያዩ እንቅስቃሴዎች የሚያደርግ ሲሆን በዛሬው እለት ጷግሜ 6 2015 ዓ/ም ሚዲያችንን Sidama Media Service (SMS) የፌስቡክ ስርጭቱን መጀመሩን ስንገልፅ በደስታ ነው። ሚዲያው የህዝብ ነው ባለቤቱም ህዝብ ነው ምንጮም ህዝብ ነው በመረጃ የዘመነ ማህበረሰብ ለመፍጠር ዘውትር እንተጋለን።

እንኳን 2016 አመት በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞት እየገለፅን በአዲስ አመት አዲስ ስጦታ ሆኖ ለህዝቡ የመጣው የሲዳማ ሚዲያ ሰርቪስ ቤተሰብ እንድትሆኑ በትህትና እንገልፃለን።

መልካም በዓል!!!

Address

Hawassa
Awassa
1111

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama Media Service - SMS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sidama Media Service - SMS:

Share