17/07/2023
በአገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ዩኒቨርሲቲያችን በግምባር ቀደምትነት ተማሪዎችን በማሳለፉ እንኳን ደስ አለን፤ እንኳን ደስ አላችሁ።
**************************************
በአገር ዓቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በተተገበረው እና በዩኒቨርሲቲያችን ባሉ 8 ኮሌጆች፣ 2 ኢንስቲትዩቶችና 1 ትምህርት ቤት ስር በሚገኙ 73 ትምህርት ክፍሎች ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል።
በአጠቃላይ ካስፈተናቸው 3,089 ተማሪዎች ውስጥ 2,760(89.35%) ተፈታኞች በብቃት አልፈዋል። ፈተናውን ከወሰዱ 73 ትምህርት ክፍሎች መካከል 34 ትምህርት ክፍሎች ሙሉ በሙሉ (100%) አሳልፈዋል።
ከአጠቃላይ ተፈታኞች መካከል በመደበኛ መርሐግብር ካስፈተናቸው 2,919 ተማሪዎች 2,703 (92.6%) ያለፉ ሲሆን ቀሪዎቹ 170 ተማሪዎች በተከታታይ መርሐግብር ተፈተነው 57(33.53%) ፈተናውን በብቃት አልፈዋል።
ይህም ውጤት በአገሪቱ ካሉ አቻ ተቋማት ቀዳሚ ያደርገዋል።
በዚህም መላው የዩኒቨርስቲያችን ማህበረሰብና አጋሮቻችን ከፍተኛ ኩራትና ደስታ ተሰምቷቸዋል። የተገኘው ስኬት አበረታችና ለቀጣይ ትልቅ ኃላፊነትን የሰጠን ነው።
ስለሆነም ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች፣ የቴክኒክ ረዳቶች፣ የአስተዳደር ሠራተኞች፣ ትምህርት ሚኒስቴርና ሌሎች አጋር አካላት እንዲሁም መላ የትምህርት ቤተሰቡ በትብብር ያስመዘገባችሁት ውጤት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እንወዳለን።
*******************************
ለልህቀት እንተጋለን!
ህዝብና ዓለም ዓቀፍ ግኝኙነት ዳይሬክቶሬት
ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም
Congratulations on University of Gondar's University Exit Exam Achievements!!******************************
The Ethiopian University Exit Exam 2023 results have been announced.
Graduating students of the University of Gondar enrolled in 73 departments under 8 colleges, 2 institutes and 1 school, have been reported to have sat for the exam.
Of the total 3,089 prospective graduates who were registered, 2,760 (89.35%)have passed the exam. What is more, out of the 73 departments, 34 have got all of their examinees(100%) succeed in passing the exam.
Of the 2,919 examinees, registered under our regular programs, 2,703 (92.6%) have passed the exit exam. Besides, 57 (33.53%), out of the 170 graduating students under our continuing education programs, have passed the exam successfully.
These results put the University of Gondar on top of the list of similar higher education institutions in the country that have administered the exam.
Therefore, we would like to congratulate our students, teachers, parents, technical assistants, administrative staff, partners and the Ministry of on your collective achievement.
Our achievement is encouraging though, it leaves us with more responsibilities in the years to come.
******************
Devoted to Excellence!
Public and International Relations Directorate
July 09/2015