DNN Ethiopia

DNN Ethiopia ይኸ መድረክ አጫጭር ዜናዎችና መረጃዎች፣ የግል ትዝብቶች፣ እይታዎች እና የወደድኳቸው ሀሳቦች የሚፃፍበት ፤ የሚጋራበት ግላዊ ገፅ ነው።

በአሜሪካ ICE የተሰኘ የትራምፕ ሰደድ፣ አሜሪካዊ የICU ኔርስ ነፍስ በባሩዶቹ ለበለበከቤተሰቦቹ የተላለፈ መልእክት እንደሚከተለው ተላልፏል። ጥቃት ማድረስ ቀርቶ ራሱን መከላከል ወይም መረዳ...
25/01/2026

በአሜሪካ ICE የተሰኘ የትራምፕ ሰደድ፣ አሜሪካዊ የICU ኔርስ ነፍስ በባሩዶቹ ለበለበ

ከቤተሰቦቹ የተላለፈ መልእክት እንደሚከተለው ተላልፏል።

ጥቃት ማድረስ ቀርቶ ራሱን መከላከል ወይም መረዳት ወደማይችልበት ሁኔታ ላይ ካደረሱት በኋላ ከአራት በላይ የሚኾኑ የICE ወታደሮች ለምን በጥይት ደብድበው እንደገደሉት ሺ ጥያቄ አወጣሁ፣ አወረድሁ፤ ግን መልሱን አጣሁ።

በጥይቶች ተደብድቦ የተገደለውን ምስኪን የ37 ዓመት ልጅ (ከትራምፕ አኳያ) ወንድማችሁ ወይም ልጃችሁ አድርጋችሁ አስቡ!

አዲሷ የልማት ባንክ ፕረዚዳንት እመቤት መለሰ በልማት ባንክ የደረሱ ችግሮችን በዓለምዓቀፍ አማካሪ ድርጅት አስጠንተው ቅሬታቸውን በደብዳቤ ገለጹ፡፡ዶ/ር እመቤት መለሰ በቅርብ ጊዜ የልማት ባን...
09/12/2025

አዲሷ የልማት ባንክ ፕረዚዳንት እመቤት መለሰ በልማት ባንክ የደረሱ ችግሮችን በዓለምዓቀፍ አማካሪ ድርጅት አስጠንተው ቅሬታቸውን በደብዳቤ ገለጹ፡፡

ዶ/ር እመቤት መለሰ በቅርብ ጊዜ የልማት ባንክ ፕረዚዳንት ተደርገው በመንግስት የተሾሙ ሲሆን ወደ ልማት ባንክ ኃላፊነት ከመምጣታቸው በፊት የንብ ባንክ ፕረዚዳንትና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕረዚዳንት በመሆን አገልግለዋል፡፡

ወደ ልማት ባንክ ሲመጡ ስራ ከመጀመራቸው በፊት የባንኩን አጠቃላይ ሁኔታ በውስጥና በውጭ አጥኝወች ያስጠኑ ሲሆን በተለይም በዓለምቀፍ አማካሪ ድርጅት የተገኜው ግኝት እጅግ አስደንጋጭ ሆኖ ስላገኙት ግኙትን ለሚመለከታቸው ሁሉ እወቁልኝ በማለት በደብዳቤ አሳውቀዋል፡፡

ከችግሮቹ አንዱ የሆነው የባንኩ የተበላሸ ብድርን የሚመለከት ሲሆን በቀድሞው የልማት ባንክ ፕረዚዳንት በዶ/ር ዮኃንስ አያሌው የቀረበው የብድር ብልሽት መጠን 8 % ሳይሆን 52 % በመሆኑ ባንኩ ችግር ውስጥ ይገኛል፡፡ እስከ ሰኔ 30 ፣ 2023/2024 የባንኩ የተበላሸ ብድር (NPL) 52% ደርሶ ነበር፣ ይህም ከኢትዮጵያ የDFI መስፈርት (15%) በላይ ነው።

ዶ/ር እመቤት በጻፉት ደብዳቤ እንደገለጹት በዓለም አቀፍ ባለሙያ የተካሄደው AQR (Asset Quality Review) የጥናት ውጤት ባንኩን በከፍተኛ ሁኔታ የሚጎዳ ከባድ ችግሮችን አሳይቷል፡፡ በዚህም ምክንያት ባንኩ መደበኛ ስራወችን በተለይም የልማት ስራወችን ለመደገፍ የሚሰጡ ብድሮችን በተገቢው ሁኔታ እየሰጠ አይደለም፡፡

ከዚህ በፊት የነበሩ የባንኩ የፋይናንስ መግለጫዎች በተመርመሩበት ጊዜ የንብረት ጥራትን በትክክል አያሳዩም። የባንኩ የክፍያ መደበኛ ስርዓት መለያየት (Loan Classification/Staging) ከIFRS 9 መርሃ ግብር እና ከዓለም አቀፍ የክሬዲት መቆጣጠርያ መስፈርቶች ከፍተኛ ርቀት ያለው። እነዚህ ሁሉ ባንኩ ከፍተኛ የተበላሸ የብድር ቋት እንዳለው እና ችግሩን በግልጽ ያለማሳየት ሁኔታወች እንዳሉ ያሳያሉ።

በ2024 በዶ/ር ዮኃንስ የቀረበው የተሳሳተ ወይም ሆን ተብሎ የተዘጋጀ የፋይናንስ መግለጫ በቀረበው ሪፖርት እንደሚያሳየው እና እሳቸውም በፋና ቴሌቪዥን ቀርበው የባንኩን የብድር አመላላስ በተመለከተ የባንኩ ያልተመለሰ የብድር መጠን 8 % መሆኑን ገልጸው የነበረ ሲሆን እውነተኛውን መረጃ የደበቀ እና ባንኩን ለችግር ያጋለጠ ነው ሲሉ ዶ/ር እመቤት በደብዳቤያቸው ለሚመለከታቸው ሁሉ አሳውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት በአዋጅ ቁጥር 780/2013 መሰረት በዶ/ር ዮሃንስ አያሌው የአስተዳደር ጊዜ ለተፈጠሩ 32 ችግሮች የተለያዩ ቅጣቶችን ጥሎበታል፡፡ የብሄራዊ ባንክ ኃላፊወች የልማት ባንክ ዋና መስሪያ ቤት በመቅረብ ባደረጉት የመስክ ምልከታ የተከሰቱት ችግሮች ባንኩን ይዞት ሊወድቅ እንደሚችል በመረዳታቸው ነው ቅጣቱን ያሳለፉት፡፡ ከቅጣቱ በተጨማሪም ስራወቹን አስተካክሎ እንዲሰራ ከፍተኛ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶታል፡፡

ልማት ባንክ የተቋቋመው የሐገሪቱን የልማት ስራወች በተለይም ግብርና እና ኢንዱስትሪን ለመደገፍና ለማጠናከር ታልሞ የተቋቋመ ባንክ ሲሆን ከአላማው ውጭ በሆነ መንገድ ብድሮች ሲለቀቁ እና ገንዘቡ ሲባከን እንደነበር የሚታወቅ ነው፡፡

ዘጋቢው ንጉሴ ጌታቸው ሲኾን DNN Ethiopia ከአያለው መንበር ገፅ ላይ ነው ያገኘው።

በትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቀሌ ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ጎልተው መታየታቸውን ተከትሎ ውጥረት ነግሶ መዋሉን የዓይን ምስክሮች ለዶቼ ቬለ ተናገሩ ። ዛሬ ጠዋት የክልሉ ፕሬ...
05/12/2025

በትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቀሌ ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ጎልተው መታየታቸውን ተከትሎ ውጥረት ነግሶ መዋሉን የዓይን ምስክሮች ለዶቼ ቬለ ተናገሩ ።

ዛሬ ጠዋት የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤትን በመክበብ የተጀመረው የክልሉ ታጣቂ ቡድን እንቅስቃሴ፤ ከሰዓት በኋላ ላይ ድምጸ ወያኔን ጨምሮ ዋና ዋና የክልሉ ተቋማትን ወደ መቆጣጠር መሸጋገሩን የዓይን እማኖቹ አክለዉ ተናግረዋል።

አንድ ሌላ እማኝ በበኩላቸዉ «እርግጠኛ አይደለሁም ግን እንደሰማሁት የሁለት ወር ደሞዝ አልተከፈለንም የሚል ጥያቄ እንደያዙ ነው።» ብለዋል።

ዛሬ አስተያየታቸዉን ለዶቼ ቬለ የተናገሩ የዓይን እማኖጭ እንደነገሩን የታጣቂዎቹ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ፍላጎት እና ግብ እስካሁን የታወቀ ነገር የለም። የክልሉ ፕሬዚዳንት ያሉበት ተጨባጭ ሁኔታም በግልጽ አልታወቀም።

ከሁለት ወር ገደማ በፊት የትግራይ ኃይሎች አባላት የሆኑ ወታደሮች በመቀሌ ከተማ «የድሞዝ ጥያቄ» የሚል ለሦስት ቀናት የቆየ የጎዳና ላይ ተቃዉሞ ማድረጋቸው ይታወሳል።

በወቅቱ የታጣቂዎቹ ጎዳና መውጣት መቀሌን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች ውጥረት አንግሶ የነበረ ሲሆን የታጣቂ ቡድኖቹ ተወካዮች ከክልሉ መስተዳድር ጋር ተነጋግረው ለጥያቄው አልባት በማበጀታቸው ታጣቂዎቹ «ይቅርታ ጠይቀው» ጉዳይ እልባት ማግኘቱ ተዘግቦ ነበር።

ምንጭ:- ዶቼ ቬለ

አቶ ታዬ ደንደአ የሰባት ዓመት ከሁለት ወር እስር ተፈረደባቸውBBC
05/12/2025

አቶ ታዬ ደንደአ የሰባት ዓመት ከሁለት ወር እስር ተፈረደባቸው
BBC

29/11/2025
25/11/2025
በአዲስ አበባ የሞቱ ዶሮዎችን በማረድ እና በማሸግ ለተለያዩ ሱቆችና ሆቴሎች ለማከፋፈል ሲዘጋጁ የነበሩ ግለሰቦች ተያዙበአዲስ አበባ ከተማ በሾላ ገበያ የሞቱ ዶሮዎችን በማረድ እና በማሸግ ለተ...
20/11/2025

በአዲስ አበባ የሞቱ ዶሮዎችን በማረድ እና በማሸግ ለተለያዩ ሱቆችና ሆቴሎች ለማከፋፈል ሲዘጋጁ የነበሩ ግለሰቦች ተያዙ

በአዲስ አበባ ከተማ በሾላ ገበያ የሞቱ ዶሮዎችን በማረድ እና በማሸግ ለተለያዩ ሱቆችና ሆቴሎች ለማከፋፈል ሲዘጋጁ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አስታወቀ።

ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት የየካ ክ/ከተማ ወረዳ 08 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ከሰላም ፀጥታ ፅ/ቤት እና ከአዲስ አበባ ፖሊስ በጋራ በመሆን ባደረገዉ ድንገተኛ ኦኘሬሽን ነው።

በተደረገው ክትትልና የተቀናጀ ኦፕሬሽን ግለሰቦቹ የሞቱ ዶሮዎችን በማረድ እና በማሸግ ለተለያዩ ሱቆችና ሆቴሎች ለማከፋፈል ሲዘጋጁ በነበረበት ሁኔታ መያዛቸው ተጠቁሟል።

በዚህም የታሸገ ዶሮ በቁጥር መቶ 100 ተበልቶ ለመታሸግ የተዘጋጀ አርባ ሁለት 42 መያዝ መቻሉን ከባለሥልጣኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ምንጭ:- የአዲስ ስታንዳርድ

18/11/2025

🇧🇩 A court in Bangladesh on Monday sentenced ousted prime minister Sheikh Hasina to death for ordering a deadly crackdown on student-led protests last year. Hasina, who was sentenced in absentia after fleeing to India, was found guilty of crimes against humanity.

Read more ➡️ https://go.france24.com/mny

Address

Awassa

Telephone

+251913381675

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DNN Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to DNN Ethiopia:

Share