Tariku Donka

Tariku Donka God is omnipotent, omniscient, and omnipresent.

28/09/2025

#ደሙ ሀይል ጉልበቴ!

ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ የሴክተር ጉባኤ ።==============================="ከተሞች የአንድ ማህበረሰብ የዕድገት እና የብልፅግና ማሳያዎች በመሆናቸው የክልሉ ከተሞች የሚመሩ...
15/09/2025

ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ የሴክተር ጉባኤ ።
===============================
"ከተሞች የአንድ ማህበረሰብ የዕድገት እና የብልፅግና ማሳያዎች በመሆናቸው የክልሉ ከተሞች የሚመሩበት ስርዓት በልዩ ትኩረት መመራት ይገባል:-" አቶ አብርሃም ማርሻሎ

የሲዳማ ክልል ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ "የተደራጀ የህዝብ ተሳትፎ ለከተሞች ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ የ2018 በጀት ዓመት ሴክቶሪያል ጉባኤን እያካሄደ ይገኛል።

በሴክተር ጉባኤው ላይ በክብር እንግድነት በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ እንደተናገሩት ከተሞች የዕድገት እና የብልፅግና ማሳያዎች በመሆናቸው በክልሉ የሚገኙ ከተሞችን የምንመራበት መንገድ የተለየ ትኩረት ሰጥተን መምራት ይገባዋል በማለት የክልሉ ከተሞች ውብ ፣ያማሩ እና ለነዋሪዎች ተስማሚ እንዲሆኑ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት ሲከናወን መቆየቱን አንስተዋል።

ከተሞች የዕድገት፣የስራ ዕድል መፍጠሪያ ማዕከላት፣ ለነገው ትውልድ ዕውቀት መፍጠሪያ፣ በመሰረተ ልማት የተሟሉ እንዲሁም ለጤናማ ማህበረሰብ መፍጠር የበኩላቸውን ድርሻ የሚወጡ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ስራዎች በክልላችን ከተሞች መሰራት እንደሚገባቸው በማንሳት ይህንንም ለማሳካት የሚያስችል የተደራጀ የህዝብ ተሳትፎ በማካሄድ ለከተሞቻችን ልማት መፋጠን እና ማንሰራራት ሁሉም አመራር በቁርጠኝነት ሊንቀሳቀስ ይገባል በማለት ተናግረዋል።

የሴክተር ጉባኤውም ለክልሉ ከተሞች ልማት እና ማንሰራራት የሚረዱ ሃሳቦችን የሚፈልቁበት እንዲሆን እንዲሁም ለነገው ትውልድ የብልፅግና ማሳያ የሆኑ ከተሞች ለመገንባት አመራሩ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት የሚወስድበት እንደሆነ አሳስበዋል።

የክልሉ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አሻግሬ ጀንበሬ በበኩላቸው ከተሞች የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና የፖለቲካ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ማዕከላት በመሆናቸው ለክልሉ ከተሞች ማንሰራራት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተመራ እንደሚገኝ በመግለጽ በ2017 በጀት ዓመት በክልሉ በሚገኙ ከተሞች ተጨባጭ ለውጦች የተመዘገቡበት ዓመት እንደነበር አንስተዋል።

ኃላፊው አያይዘው ቢሮው በበጀት አመቱ በክልሉ ለከተሞች ዕድገትና ልማት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ሲከናውን መቆቱን ጠቅሰው በክልሉ በሚገኙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራ፣ የልማታዊ ሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ከተረጂነት ለማላቀቅ የሚያስችሉ ስራዎች፣ከተሞች በፕላን የሚመሩ እንዲሆኑ እንዲሁም ሌሎች ከከተማ ልማት ስራዎች ጋር የተያያዙ ስራዎች በሰፊው ሲሰሩ መቆየታቸውን በማንሳት በ2018 በጀት ዓመት የከተሞች ሁለንተናዊ ልማትን የሚያፋጥን የክልሉ ከተሞች የከተሜነት ፍኖተ ካርታ ተግባራዊ እንደሚደረግም ጠቅሰዋል።

በሴክተር ጉባኤው ላይ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም፣ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ እንዲሁም የክልሉ ከተሞች የከተሜነት ፍኖተ ካርታ ቀርቦ ሰፊ ውይይት በማካሄድ በአፈጻጸማቸው የተሻሉ መዋቅሮች የእውቅና መርሐ ግብር ይካሄዳል።

በጉባኤው ላይ የክልል፣ የዞን፣ የሀዋሳ ከተማ እንዲሁም የወረዳዎችና የከተሞች አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

የሲዳማ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞች በአለታ ወንዶ ከተማ ለወላጅ አጥ ሕጻናት የትምህርት ቁሳቁስ እና ለአረጋዊን የምግብና የተለያዩ አልባሳት ድጋፍ አደረጉ።አለታ ...
04/09/2025

የሲዳማ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞች በአለታ ወንዶ ከተማ ለወላጅ አጥ ሕጻናት የትምህርት ቁሳቁስ እና ለአረጋዊን የምግብና የተለያዩ አልባሳት ድጋፍ አደረጉ።

አለታ ወንዶ፣ ነሐሴ 29/2017 ዓ.ም የሲዳማ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞች በደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ከተማ አስተዳደር ለወላጅ አጥ ሕጻናት የትምህርት ቁሳቁስ እና አቅመ ደካማ ለሆኑ አረጋዊያን የምግብና የተለያዩ አልባሳት ድጋፍ በማድረግ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሥራ አከናዉነዋል።

አመራሮቹና ሠራተኞቹ ለሕጻናቶቹ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሥራ ያከናወኑት ሕጻናቶቹ በ2018 ትምህርት ዘመን በመማሪያ ቁሳቁስ እጦት ምክንያት ወደ ት/ቤት ሳይገቡ እንዳይቀሩ በሚል እሳቤ መሆኑ ተገልጿል።

የድጋፍ ቁሳቁሱንና አልባሳቱን የሲዳማ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አሻግሬ ጀንበሬ እና የከተማዉ ከንቲባ ሳሙኤል ቦጋለ ሰጥተዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የቢሮዉ ምክትል ኃላፊዎች፣ ደቡባዊ ሲዳማ ዞን እና የአለታ ወንዶ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የቢሮዉ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሮች እና ሰራተኞች እንዲሁም ሌሎች ተገኝተዋል።

በዚሁ ጊዜ የቢሮ ኃላፊ አቶ አሻግሬ ጀንበሬ ከቢሮዉ፣ ከዞኑ፣ ከከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና ሠራተኞች ጋር በመሆን በከተማዉ ማዘጋጃ ቤት በተዘጋጀዉ ቦታ ችግኞችን በመትከል የአረንጓዴ ልሜት አሻራቸዉን አኑረዋል።

31/08/2025

ለዛሬ የመድረሰ ምስጢር የጌታ ምህረት ብቻ ነው ፡፡

29/08/2025
24/08/2025

“እርሱ አስቀድሞ ወዶናልና እኛ እንወደዋለን።”
— 1ኛ ዮሐንስ 4፥19

17/08/2025

“ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ።”
— ኤፌሶን 5፥16

Address

Awassa

Telephone

+251916367938

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tariku Donka posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tariku Donka:

Share