Tariku Donka

Tariku Donka God is omnipotent, omniscient, and omnipresent.

08/08/2025
06/08/2025

“የእግዚአብሔር መንገድ ሁሉ ቸርነትና እውነት ነው። ቃል ኪዳኑንና ምስክሩን ለሚጠብቁ።”
— መዝሙር 25፥10

እኔም ለነገ ትውልድ የሚተላለፊ አሻራዬን አሳርፍያለሁኝ::''           _ Legacy!         ዞን_ይርጋዓለም! #700ሚ #8ሚ #1.5ሚ #118,000 ችግኝ
31/07/2025

እኔም ለነገ ትውልድ የሚተላለፊ አሻራዬን አሳርፍያለሁኝ::''
_ Legacy!
ዞን_ይርጋዓለም!
#700ሚ
#8ሚ
#1.5ሚ
#118,000 ችግኝ

27/07/2025

“ኢየሱስም፦ እርሱ ደግሞ የአብርሃም ልጅ ነውና ዛሬ ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል”
@ ሉቃስ 19፥9

በከተሞች ቀጣይነት ያለው ዕድገት እንዲመዘገብ የተጀመረዉ የክትትልና ድጋፍ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።                                                    ...
22/07/2025

በከተሞች ቀጣይነት ያለው ዕድገት እንዲመዘገብ የተጀመረዉ የክትትልና ድጋፍ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።
አቶ አሻግሬ ጀንበሬ ቢሮ ኃላፊ

የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ የ2017 በጀት አመት በክልሉ በሚገኙ ከተሞች ሲያካሂድ በቆየዉ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት የነበሩ ጥናካሬዎች እና ጉድለቶች ላይ ያተኮረ ግምገማ አካሂዷል።

የግምገማ መድርኩን የመሩት የቢሮ ኃላፊ አቶ አሻግሬ ጀንበሬ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ የተካሄደዉ የክትትልና ድጋፍ ሥርዓታችን ከተለመደዉ አካሄድ ወጣ ባለ መንገድ ቴክኒካል ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ የቢሮ አመራሩ ተጠያቂነት ያለዉን አሰራር ዞኖችን ተከፋፍሎ በመመደብ የታችኛዉ መዋቅር ተቋም ግንባታ ላይ ያተኮረ የድጋፍ ስራ ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል።

አመራሩ ባደረገዉ ክትትልና ድጋፍ ዉጤታማ የሆኑ ለዉጦች የታዩ መሆኑን ጠቅሰዉ በተፈጠረ የህዝብ ንቅናቄ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን በመሰለፍ በጉልበቱና በገንዘቡ የልማት ሥራዎቹን ከማገዝ ባለፈ እጅግ በሚያስደንቅ ተነሳሽነት የከተሞቹን ፕላን መሰረት በማድሩግ ያለምንም ካሳ ክፍያ ንብረቶቹን በማንሳት ጭምር አዳዲስ መንገዶች ከፈታ ስራን ሰርቷል ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ እንደ ሀገር የተጀመረዉና በሐዋሳ ከተማ ተግባራዊ እየተደረገ ያለዉ የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ክልሉ ዋና ዋና ከተሞች በማስፋት እየተከናወነ ባለዉ ሥራ የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዉ ይህንኑ ሥራ በሌሎች ከተሞችም ለማስቀጠል ያለዉ የተደራጀ የህዝብ ጥያቄ እየጨመረ በመምጣቱ በአግባቡ በመምራት ዉጤቴማ ማድረግን ይጠይቃል ብለዋል።

ከተሞች በሰበሰቡት ገቢ ከሚያሰሯቸዉ የልማት ስራዎች በተጨማሪ የክልሉ መንግስት ባስቀመጠዉ አቅጣጫ ቢሮዉ በጀት በመመደብ እተከናወነ ያለዉ ፍትሐዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታና የአቅም ግንባታ ስራ ከትሞች ተወዳዳሪና ለነዋሪዎቻቸዉ ምቹ እንዲሆኑ ከማድረግ ባለፈ ለዘመናት የቆየዉን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ እየተመለሰ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

የገጠር ማዕከላትን ፕላን በማስከበር ከተሞች የዘመናዊነት ገጽታን ይዘዉ እንዲያድጉ ይረዳቸዋል ያሉት የቢሮ ኃላፊ ከተሞች የከተሜነት መልክ ይዘዉ በሚፈለገዉ ስታንዳርድ መሠረት እንዲገነቡ እየተደረገ ያለዉ ድጋፍም የአመራሩን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል።

በከተሞች ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎትን በማዘመን ቀልጣፋና እርካታን የሚያረጋግጥ ሥራ በመስራትና ዕድገታቸውን በዘላቂነት ለማስቀጠል እየተደረገ ያለዉን ጥረት ወደ ተጨባጭ ዉጤት ለመቀየር የቢሮዉ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ በአዲሱ በጅ ት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።

በአጠቃላይ በዚህ ዓመት የተጀመረዉን የታችኛዉ መዋቅር ተቋም ግንባታ ስራ ላይ የታዩ ጥንካሬዎችን ይበልጥ አጠናክሮ በማስቀጠልና ክፍተቶቹን ደግሞ አርሞና የቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ አካል አድርጎ ለመፈጸም ቀጣይነት ያለ ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች የየከተሞቹን ሪፖርት በየከተሞቹ ካደረጉት የመስክ ምልከታ ጋር በማያያዝ ሰፊ ግምገማ አካሂደዋል።

በመድረኩ የቢሮዉ አመራሮች፣ የተለያየ ዘርፍ ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተሮች እና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

በግምገማዉ በአንዳንድ ከተሞች የሚታየዉ የአመራር ብቃት ማነስ፣ የገቢ አማራጮችን በማስፋት ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ ለልማት ከማዋል ጋር የሚታዩ ጉድለቶች እና ሌሎች ችግሮች በቀጣይ በሚደረግ ድጋፍ በማረምና በማብቃት ሊሰራ እንደሚገባ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።

በመጨረሻም ተሣታፊዎቹ ቢሮዉ ለሥራ ምቹ በማድረግ አዲስ እያስገነባና የግንባ

19/07/2025

12/07/2025

Address

Awassa

Telephone

+251916367938

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tariku Donka posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tariku Donka:

Share