31/01/2026
ለአለታ ጩኮ ከተማ እየተዘጋጀ ያለ የአካባቢ ልማት ፕላን /NDP/ እና የከተማ ድዛይን /urban desiegn/ ለባለድርሻ አካላት ለዉይይት ቀረበ
አለታ ጩኮ፣ ጥር 23/2018 ዓ.ም፦ በሲዳማ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ የከተሞች ፕላን ኢንስትቲዩት በደቡባዊ ሲዳማ ዞን ለአለታ ጩኮ ከተማ እየተዘጋጀ ያለ የአካባቢ ልማት ፕላን /NDP/ እና የከተማ ድዛይን /urban desiegn/ ለባለድርሻ አካላት ለዉይይት ቀርቧል።
በመድረኩ የሲዳማ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ሰለሞንን ጨምሮ የቢሮዉ ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች፣ የአለታ ጩኮ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ነጋዴዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸዉ ታዋቂ ግለሰቦች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዉይይቱን ያስጀመሩት በቢሮዉ የከተሞች ፕላን ኢንስትቲዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታደሰ ታዎታ እንዳሉት በክልሉ መዋቅራዊ ፕላን ከተዘጋጀላቸዉ ከተሞች አንዱ ከተማ የአለታ ጩኮ ከተማ አንዱ መሆኑን አንስተዉ በከተማዉ ለሚሰሩ ሥራዎችን የሚመራ ፕላን እየተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።
በመሆኑም እየተዘጋጀ ያለዉ ይህ ፕላን በኢንስትቲዩቱ ባለሙያዎች የከተማ ነዋሪዉን ያሳተፈ ዝርዝር ጥናት መደረጉን ጠቅሰዉ ዝግጅቱን አጠናቅቆ ወደ ትግበራ ለመግባት ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ዉይይት በማድረግ ያልተካተቱ ጠቃሚ ግብአቶችን በመቀበል የፕላን ዝግጅቱ አካል እንዲሆን ስለሚደረግ አስተያየት እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
የአለታ ጩኮ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ቶርባ ቶሼ በበኩላቸዉ የአለታ ጩኮ ከተማ ከተቆረቆረ ረጅም ጊዜ ቢሆንም ዕድገቷን በሚመጥን ፕላን ለመምራት የፕላን ዝግጅት እያደረገ ያለዉን የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮን አመስግነዉ ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊዉን ስራ በመስራትና የቅርብ ክትትል ሲያከናዉን የቆየ በመሆኑ የዉይይቱ ተሳታፊዎችም ዉጤታማና ጠቃሚ ግብአቶችን በመስጠት እንዲሳተፉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በክልሉ እየተዘጋጀ ያለዉ ፕላን በኢንስትቲዩቱ ባለሙያዎች በዝርዝር ቀርቧል።
ፕላኑ ለዉይይት የቀረበበት ዋነኛዉ ምክንያት ዝግጅቱ ተጠናቅቆ ወደ ትግበራ ከመገባቱ በፊት ለባለድርጃ አካላት ቀርቦ ተጨማሪ እና ጠቃሚ ግብዓቶችን በመሰብሰብ ጠቃሚ የሆኑትን በፕላኑ አካቶ የተሟላ ፕላን ዝግጅት ለማድረግ እንደሆነ ተነግሯል።
በዉይይቱ ላይ የተገኙት የቢሮዉ ኃላፊ አቶ ብሩክ ሰለሞን እንደተናገሩት የመደመር መንግስታችን እሳቤ ከተሞች ዉብ፣ ጽዱ፣ አረንጓዴ እና ለኑሮ የሚመቹ እንዲሆኑ የክልላችን መንግስት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ከተሞቻችን በፕላን እንድመሩ ቢሮዉ እንደየከተሞቹ ዕድገት ደረጃ ፕላን እየተዘጋላቸዉ እንዲተገበሩና ከፕላን ጋር ተያይዞ የኮሪደር ልማት ሥራ ድዛይን በማዘጋጀት እየተሰራ በመሆነ ሥራዎቻችንን ለማቀላጠፍ የነዋሪዎችና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።
በአጠቃላይ በመድረኩ ሰፊ ዉይይት የተደረገ ሲሆን በዉይይቱ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በቢሮዉ ምክትል ኃላፊና የከተሞች ልማታዊ ሰፍትኔት እና አረንጓዴ ልማት ኃላፊ አቶ ታሪኩ ዶንቃን ጨምሮ በመድረኩ መሪዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ ግብአት የሆኑ ጠቃሚ አስተያየቶችን የፕላን አካል ለማድረግ በመስማማት ተጠናቋል።