Sidama Ejjeeto Tube

Sidama Ejjeeto Tube Media/Production hee'ne reenante, ree'ne hee'ra woyyitanno!!

በሲዳማ ክልል መስኖ ልማት ኤጀንሲ በኩል እየለማ የሚገኘው በክልሉ የመጀመሪያው የሃባብ Watermelon ምርት
28/04/2025

በሲዳማ ክልል መስኖ ልማት ኤጀንሲ በኩል እየለማ የሚገኘው በክልሉ የመጀመሪያው የሃባብ Watermelon ምርት

ጀግናው መሪያችንን ሺህ አመት ኑርልን እወድሃለን አብርሽ 🙏ጀግናው መሪ ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ ከመሠረቱ ጀምሮ በሚዛናዊ ፖለቲካን የሚያራምድ የብሔር ብሔረሰቦች መብት እንዲከበር ነፃነትና...
16/01/2025

ጀግናው መሪያችንን ሺህ አመት ኑርልን እወድሃለን አብርሽ 🙏

ጀግናው መሪ ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ ከመሠረቱ ጀምሮ በሚዛናዊ ፖለቲካን የሚያራምድ የብሔር ብሔረሰቦች መብት እንዲከበር ነፃነትና ወንድማማችነት እንዲጠናከር ሁሌም የሚተጋ ከወጣነትነት ዕድሜ ጀምሮ ለዚህ መስዋዕነትን እየከፈለ የኖረ ህልም የሰው ልጆች በሰላምና በእኩልነት በምድር እንዲፀና ብሎም ምድር ለሰው ልጆች እንድትመች የሚተጋ ታማኝ እና ትልቅ ሰው ነው።

ከወረዳ አመራርነት እስከ ዞን በተለያዩ ቦታዎች ላይ ሲሰራ ህዝብን የሚጎዱ አመለካከትና ተግባር ውስጥ ሳይሳተፍ ህሊናውን ጠብቆ እጁና ልቡን ንጽህ በመሆን በታማኝነት ህዝብን ያገለገለ በዚህም ተግባሩ በቀድሞ ደቡብ ክልል በተለያዩ የመሪነት ቦታዎች ሲያገለግል በታማኝነት በትህትና ማንንም ሳይለያይ ወደ ሁሉም ዞኖች፤ ወረዳዎች እስከ ቀበሌ ድረስ እየወረደ ለህዝባች ልማት አንድነትና ሰላም ባለመታከት የሰራ መሆኑን የቀድሞ የደቡብ ክልል አመራሮች፤ ሠራተኞች ሁሉም በአንድ ቃል ስለ ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ ይመሰክራሉ እስከ አሁንም በዚህ ተግባሩ ተመስጋኝ እንደሆነ እስካሁን ያወራሉ።

እጁና ልቡን ንጽሁ መሆኑን የሚታወቀው በተለያዩ ቢሮዎች እና በከፍተኛ ሃብት ባላቸው ተቋማት ውስጥ ሲመራ ህዝብን በድሎ፤ ለግሌ ጥቅም ልስራ ብሎ በብልሹ አሠራር ውስጥ የማይሳተፍ ፈሪሃ እግዚአብሔር ያለው መሪ መሆኑን አብሮ በሲዳማ ክልል፤ በቀድሞ ደቡብ ክልልን በተለያዩ ተቋማት አብሮት የሰሩ ሁሉ በአግራሞት ይመሰክራሉ።

ክቡር አቶ አብርሃም ማርሻሎ ሀገር ምድር የሚያውቃቸው ለሀገር አለኝታና ባለውለታ፥ ለሀገሩ ትልቅ መሰዋዕነት የከፈሉ፥ የሰላም አንባሳደር፥ የልማት ፊትአውራር፥ የለውጥ ሐዋሪያ፥ የተራማጅ አስተሳሰብ ባለቤት ከክልል አልፎ ለሀገር ልማት ትልቅ ዋጋ የከፈሉና እየከፈሉ ያሉ ባለምጡቅ አዕምሮ ባለቤት መሆናቸው ይታወቃል።

የህዝቦች አንድነትና ወንድማማችነት የሚያምን የህዝብ ልጅ ነው። ከሁሉም በላይ አብርሃም ማን እንደሆነ የኢትዮጽያ ህዝብ ብሎም የሲዳማ ህዝብ እና የወላይታ ህዝብ ጠንቅቆ ያውቀዋል።

ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ ላይ የተነሳውን ረብ የለሽ ወሬ ፍፁም ተቀባይነት የለውም።

እንኳን ለ2017 ዓ.ም ለኢሬቻ በዓል በሰላም አድረሳችሁ ፣  አደረሰን!Irreechi: Faajjii Tokkummaafi Obbolummaati! Irrecha: The symbol of Unity an...
05/10/2024

እንኳን ለ2017 ዓ.ም ለኢሬቻ በዓል በሰላም አድረሳችሁ ፣ አደረሰን!

Irreechi: Faajjii Tokkummaafi Obbolummaati!
Irrecha: The symbol of Unity and Fraternity!
ኢሬቻ የአንድነት ፣ የወንድማማችነትና የእህታማማችነት ምልክት ነው!

Sidaama Ejjeetto Tube

ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ሲዳማ ለነፃነቱ የመጨረሻውን የደም ዋጋ የፈለበት እለት 11/11/2011ዓ.ም።የመስዕዋትነት ገድላችንን ዛሬ 5 አመት የመታሰቢያ ቀኑ ነው።11/11/2016ዓ.ምን ግ...
18/07/2024

ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ሲዳማ ለነፃነቱ የመጨረሻውን የደም ዋጋ የፈለበት እለት 11/11/2011ዓ.ም።

የመስዕዋትነት ገድላችንን ዛሬ 5 አመት የመታሰቢያ ቀኑ ነው።

11/11/2016ዓ.ምን ግን አሸንፈን በጠላቶቻችን ፊት ማሸነፋችንን እንዘክራለን!!!

  የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ ፊቼ-ጨምበላላ በታላቅ ድምቀት በሀዋሳ ከተማ እየተከበረ ይገኛል። አባቶች በሶሬሳ ጉዱማሌ የቄጣላውን ዜማ እያሰሙ ይገኛሉ።የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ...
06/04/2024



የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ ፊቼ-ጨምበላላ በታላቅ ድምቀት በሀዋሳ ከተማ እየተከበረ ይገኛል። አባቶች በሶሬሳ ጉዱማሌ የቄጣላውን ዜማ እያሰሙ ይገኛሉ።

የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ አቶ ጃጎ አገኘሁ የሲዳማ ህዝብ በፊቼ-ጨምበላላ ከዘመናቶች በፊት ከአለም የቀደመበት ታሪካዊ ፍታህዊነትን ያሰፈነበት በመሆኑ ዛሬ ዓለም ያደረሰብ ፍትሃዊነት እና እኩልነት ሲዳማ ከዛሬ መቶ አመታቶች በፊት ሲያደርገው የነበረ ነው።

በመሆኑም በፊቼ ጨምበላላ አባቶች በትኬሻቸው ጋሻ/ወንቆ እና ጦር በመያዝ ቄጣላ የሚያደርጉበት ኩነት ያለው ሲሆን ቄጣላ ደግሞ የሲዳማ አባቶች ሃዘናቸውን እና ደስታቸውን ብሎም ስሜታቸውን የሚገልፁበት የዜማ ስልት ነው። ይህም ፊቼ ጨምበላላ በአለም ቅርፅነት በዩኔስኮ በPerformance ሂደት እንዲመዘገብ የቄጣላ ዜማ ስርዓት ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረገ መሆኑንም ገለፀዋል።

በተለይም በከሰሞኑ የተመረቀው የአፊኒ ፊልም የሲዳማ ህዝብ ግጭት አፈታት ሂደት ላይ ትኩረት ያደረግ ሲሆን አፊኒ ማለትም (አወቃችሁ) ማለት ሲሆንን የአፊኒ የግጭት አፈታት ባህልም የተወሰደው ከዚህው ከጨምበላላ በዓል ላይ መሆኑን የገለፁ ሲሆን በቂም በበቀል እና በግጭት ፊቼ ጨምበላላ መክበር በፍፁም እንደማይቻል አቶ ጃጎ ገለፀዋል።

አሁን የምናከብረው የጨምበላላ በዓል በጨምላላን እንኑር በሚል መሪ ቃል እንደመንግስት እየተከበረ መሆኑንም ገልፀዋል።

የሲዳማ ህዝብ ዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምበላላ በዓል በዛሬው እለት ዋዜማው እየተከበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ወደ 2017 መሸጋገሩን አብስሯል።አይዴ ጨምበላላ
05/04/2024

የሲዳማ ህዝብ ዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምበላላ በዓል በዛሬው እለት ዋዜማው እየተከበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ወደ 2017 መሸጋገሩን አብስሯል።

አይዴ ጨምበላላ

31/03/2024

በዮኔስኮ የተመዘገበው የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል በመጋቢት 27/28 እንደሚከበር የብሔሩ አባቶች/አያንቶች ቀኑን አብስረዋል።

ወደ ሲዳማ ይምጡ የአለም ቅርስ የሆነው ፊቼ-ጨምበላላን በህብረት በአንድነት በፍቅር እናክብር!!!

#ኤጄቶ

 💚💙❤🙏Fichee Cambalaallate ayyaanira Cimeeyye dikkote fulte Fixaari barri 27/07/2016 M.D ikkinota Cambalaallate barri kay...
29/03/2024

💚💙❤🙏

Fichee Cambalaallate ayyaanira Cimeeyye dikkote fulte Fixaari barri 27/07/2016 M.D ikkinota Cambalaallate barri kayinni 28/07/2016 M.D barra dikko Qawaado ikkinotta Ayyaantotenni Lallaanboonni:-

Cambalaallate Ayyaaninni:- Oosonna saada digannanni haqqa dimurranni.
Fichee Cambalaallate barra baalu itanninna aganni hagiidhanni hosanno barraati!

Dancha Ayyaana Baalaho💚💙❤🙏

#አዋጅ

የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ ፊቼ ጨምበላላ በአያንቶች ቀኑ ተበሰረ ቀኑም በ27/28 በመጋቢት ወር ላይ እንዲከበር አብስረዋል።

💚💜❤️ ሲዳማዎች እንኳን አደረሳችሁ🙌

የሰሞኑኛዉ በሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ በወንዶ ማዞሪያ አከባቢ በግለሰብ ቤት ተገኝቶ ለጊዜው የት እንደገባ ያልታወቀው ማዕድን ተብሎ የተጠረጠረዉ (ለጊዜዉ ምንነቱ ያልተረጋገጠዉ) እቃ ዙሪያ ...
25/02/2024

የሰሞኑኛዉ በሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ በወንዶ ማዞሪያ አከባቢ በግለሰብ ቤት ተገኝቶ ለጊዜው የት እንደገባ ያልታወቀው ማዕድን ተብሎ የተጠረጠረዉ (ለጊዜዉ ምንነቱ ያልተረጋገጠዉ) እቃ ዙሪያ ያሉ መረጃዎች።

ሰሞኑን በሀዋሳ ከተማ በወንዶ ማዞሪያ አከባቢ አቶ ስለሺ በተባለ ግለሰብ እጅ ማዕድን ተብሎ የተጠረጠረዉ እና ለጊዜዉ ምንነቱ ያልተረጋገጠ እቃ ተገኝቶ በሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ተዪዞ ወደ ሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ቅጥር ጊቢ ከመጣ በኋላ ለጊዜዉ ባልታወቀ ሁኔታ መሰወሩ ይታወቃል።

ይህንንም ተከትሎ የተለያዩ ግለሰቦች ዉሸት የሆኑ መረጃዎችን በማስሰራጨት የሀሰት በፕሮፖጋንዳ በመንዛት ከህግ ቁጥጥር ስር ለመዉጣት እና ህብረተሰቡ ለማደናገር ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

ለአብነትም በትላንትናው እለት የቀድሞዉ የSMN የፌስቡክ ገፅ በነበረ እና በአሁኑ ወቅት ከሚዲያው (ከተቋሙ) ቁጥጥር ዉጪ በመሆን በግለሰቦች እጅ በሚገኘዉ Sidama Media Network የFacebook ገፅ ላይ ይህ ጠፋ የተባለዉ ለጊዜዉ ምንነቱ ያልተረጋገጠዉ እቃ በሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ኮሚሽነር መኖሪያ ቤት እንደተገኘ በመግለፅ የሀሰት መረጃ ተሰራጭቷል።

እዉነታዉ የቱ ነዉ ?

እዉነታዉ ይህ ለጊዜዉ ምንነቱ ያልታወቀዉ እቃ በሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኖሪያ ቤት ተገኘ መባሉ ሙሉ ለሙሉ ዉሸት ሲሆን እስካሁን ድረስ ያለበት ያልታወቀ እና እቃዉም እንዲገኝ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሽመልስ ቶማስ ብርቱ አመራርነት እየሰጡ የሚገኝ ሲሆን በዚህም በጉዳዩ ዙሪያ እጃቸዉ አለባቸዉ ተብለዉ የተጠረጠሩ የፀጥታ አካላት እና ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንዲዉሉ የተደረገ ሲሆን በቁጥጥር ስር የዋሉት ላይም ብርቱ ምርመራ እየተደረገባቸዉ ይገኛል።

በአሁን ወቅት ተጠርጥረዉ በእስር ላይ የሚገኙ አንዳንድ ግለሰቦች የሀሰት መረጃዎችን በማስሰራጨት ከህግ ቁጥጥር ስር ለማምለጥ እና የምርመራዉን ሂደት ለማደናቀፍ የተለያዩ የሚዲያ አዉታሮችን በመያዝ አሰማርተዉ የሚገኙ ሲሆን ኮሚሽኑ ግን ለየትኛዉም የዉሸት አሉባልታ ትኩረት ሳይሰጥ ምርመራዉን በተጠናከረ ሁኔታ እያካሄደ የሚገኝ ሲሆን እዉነታዉ በቅርቡ ይፋ ይወጣል ተብሎ ይጠበቃል።

እንዲሁም የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሽመልስ ቶማስ በአሁኑ ወቅት በጋምቤላ ክልል ሀገራዊ የሰላም እና የፀጥታ ጉባኤ በመሳተፍ ላይ የሚገኙ ሲሆን ባሉበት ሆነዉ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተሉ ከተለያዩ የፀጥታ መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት በጉዳዩ ዙሪያ የተጠረጠሩ የፀጥታ አካላትን እና ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር እንዲዉሉ በማድረግ እቃዉ ያለበት እንዲታወቅ ብርቱ ትግል በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

እዉነታዉ ይሄ ሆኖ ሳለ የምርመራዉን ሂደት ለማደናቀፍ አንዳንድ አካላት የኮሚሽነሩንም ሆነ የፀጥታ አካላትን ስም በሀሰት በማጠልሸት ላይ የሚገኙ ሲሆን የክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከዚህ በፊት እያደረገ እንደመጣዉ ይሄንንም ዉስብስብ ወንጀል በቅርቡ በማጥራት (በመፍታት) ለህብረተሰቡ እዉነተኛዉን መረጃ ይፋ የሚያደርግ ይሆናል።

ማሳሰቢያ 1:- በግለሰቡ እጅ ተገኘ የተባለዉ እቃ ምንነቱ ገና ያልተረጋገጠ ሲሆን በተለያዩ የሚዲያ አዉታሮች የተለያዩ ማዕድናትን ስም በመስጠት እየተሰራጨ የሚገኘዉ መረጃ ገና ያልተረጋገጠ ዜና ነዉ።

ማሳሰቢያ 2:- በአሁን ወቅት በመሰራጨት ላይ የሚገኘዉ ፎቶ በግለሰቡ እጅ ተገኘ የተባለዉ እቃ በሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ተዪዞ ወደ ሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ቅጥር ጊቢ በመጣበት ወቅት በኮሚሽኑ የመረጃ ዲቪዢን ቢሮ በር ላይ የተነሳ ነዉ እንጂ በኮሚሽነሩ መኖሪያ ቤት ነዉ የሚባለዉ መረጃ ፍፁም ከእዉነት የራቀ ዜና ነዉ።

መረጃዉን በማድረግ ለሁሉም ያዳርሱ !

እንኳን ለጌዲዬ ብሄር ዘመን መለወጫ የደራሮ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!
10/02/2024

እንኳን ለጌዲዬ ብሄር ዘመን መለወጫ የደራሮ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!

ለክብር አቶ መኩሪያ መርሻዬ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በተደጋጋሚ ጊዜ እንደጠየቅነው ሲዳማ በ130 ኣመት ትግል ባገኘው ድል ላይ ብዙሃኑ ከንቲባዎች ሲያላግጡ ተስተውሏል። እርሶም የዚህ አይነት ስ...
17/01/2024

ለክብር አቶ መኩሪያ መርሻዬ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ

በተደጋጋሚ ጊዜ እንደጠየቅነው ሲዳማ በ130 ኣመት ትግል ባገኘው ድል ላይ ብዙሃኑ ከንቲባዎች ሲያላግጡ ተስተውሏል። እርሶም የዚህ አይነት ስህተት ከመስራት አሁን የተሰበውን ከተማዋን ልሙጣዊ ለማድረግ የተሰራው ሴራ ቢቆም መልካም ነው። በዚህ ባንዲራ ስም ሲዳማ ሲገረፍ ሲሰደድ ሲሰቃይ እንደነበር ለሁሉም ግልጽ ነው።

አሁንም ይህን ባንዲራና የባንዲራውን ትርጉም በተሸከሙ ሰዎች ሀዋሳ ላይ ሊደረግ የታሰበውን ቅኝ ገዢነትና ወረራ እንዲያስቆሙልን በትህትና እንጠይቃለን!!

ከሰሞኑ በከተማው የሚከረበውን የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ ይህ ባንዲራ በከተማው እንዳይሰቀል ለመጠየቅ ለማሳሰብ እንወዳለን።

የክልላችን የደማችንን ዋጋ ቀለም ይህ ብቻ ነው!!

💚💜❤

#ኤጄቶ

Address

EVERYWHERE
Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama Ejjeeto Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category