Witness Hospitality

Witness Hospitality Focus on Hospitality Industry.

  የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን መንገድ …..የሀገራችን ቱሪዝም ካለበት ማነቆ አንዱ የአሰራር አለመዘመንና ዘለግ ያለ ዘልመዳዊ የቢሮክራሲ መንገዶች ይበልጥ ዘርፉን እንደ ካሮት የቁልቁል ጉዞ ላይ...
10/12/2024

የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን መንገድ …..

የሀገራችን ቱሪዝም ካለበት ማነቆ አንዱ የአሰራር አለመዘመንና ዘለግ ያለ ዘልመዳዊ የቢሮክራሲ መንገዶች ይበልጥ ዘርፉን እንደ ካሮት የቁልቁል ጉዞ ላይ እንዲገኝ አድርጎታል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በዘርፉ ሌሎች ሀገራት ያደጉበትን መንገድ የመከተልና የመተግበር እሳቤዎች በጥቂቱም ቢሆን እየታየ ነው፡፡ በዚህም በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱ መንግስታዊ መዋቅሮች ውስጥ የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን አንዱ ነው፡፡

ኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን በመንግስት መዋቅር የሚገኝ ነገርግን ለአሰራር ያመች ዘንድ Autonomous ሆኖ የክልሉን የቱሪዝም ሀብት የመለየት፣ መዳረሻዎችን እንዲለሙ የማድረግ እንዲሁም በሀገር ውስጥና በውጪ ለሚገኙ ጎብኚዎች የማስተዋወቅና ገቢ እንዲገኝ የመሸጥ ስራዎችን ያስተባብራል፡፡ ለዚህም ይረዳው ዘንድ Visit Oromia (ኦሮሚያን ይጎብኙ) በተሰኘው ንቅናቄ የገበያ እና ማስተዋወቅ ስራዎችን በዋናነት ይሰራል፡፡

በአፍሪካ ውስጥ የዚህ ሞዴል ዋነኛ ተጠቃሽና ተጠቃሚ ሀገር ጎረቤት ሩዋንዳ ናት፡፡ Visit Rwanda

አሁን ላይ ያለውን የሩዋንዳ ከፍተኛ የኢንቨስትመንትና ቱሪዝም እንቅስቃሴ በተለይ በቢዝነስ ቱሪዝም ያላቸውን ተመራጭነት ላስተዋለ ያለጥርጥር በዚህ ሞዴል ለአመታት ሳይታክቱ መስራት መልካም ውጤትን ለማየት አይነተኛ መንገድ መሆኑን ይገነዘባል፡፡ ባለፉት 10 ዓመታት የፖል ካጋሜዋ ሀገር በቪሲት ሩዋንዳ ንቅናቄ እጅግ እመርታዊ ለውጥ ከማምጣት ባሻገር በአለም ታሪክ ከምትታወቅበት የእርስበእርስ ጦርነት በላይ በቱሪዝሙ እየታወቀችበት ትገኛለች፡፡ የዚህ ንቅናቄ አካል በሆነው ከታዋቂና ተፅዕኖ ፈጣሪ የአለማችን ድርጅቶችና ተቋማት ጋር በጋራ አብሮ ከመስራት እስከ አጋርነት ብሎም ዋነኛ የገበያ ምንጭ እስከመሆን ደርሳለች፡፡

አርሰናል፣ፒኤስጂ፣ባየርሙኒክ ሩዋንዳ በስፖርት ቱሪዝም ተመራጭ እንድትሆን ብቻ ሳይሆን ምርትና አገልግሎቷን በተለይም ቡና በእነዚህ ግዙፍ ስቴድየሞች በጨዋታው እንዲቀርብ አስችሏታል፡፡ የየቡድኑ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ደጋፊዎች ሩዋንዳን መጎብኘት የቤት ስራቸው ካደረጉ ሰነበቱ፡፡ በዚህም በአፍሪካ ውስጥ በስፖርት በተለይ ቅርጫት ኳስ፣እግርኳስ እንዲሁም አሁን አሁን አለም አቀፍ የመኪና ውድድር በሩዋንዳ መካሄድ ጀምሯል፡፡

ባለፉት 10 ዓመታት ከ800 በላይ አለም አቀፍ ኹነቶችን በሀገረ ሩዋንዳ እንዲካሄድ ከማስቻሉም በላይ በየአመቱ የትልልቅ ኹነቶች መዳረሻ በመሆን ከአፍሪካ በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንድትቀመጥ አስተዋፅዖ አድርጓል፡፡

ለዚህም የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው ፖል ካጋሜ የቱሪዝሙ እንቅስቃሴ በመንግስታዊ መዋቅር ሆኖ ነገር ግን ቢሮክራሲ ያልበዛበት በቀጥታ ራሳቸው ፕሬዝደንቱ የሚመሩትና አቅጣጫ የሚሰጡበት በፋይናንስ ምክንያት ስራዎች የማይስተጓጎልበት የሀገሪቱ ትልቁ አምድ ዘርፍ እንዲሆን በማድረጋቸው ነው፡፡ Rwanda Development Board

እንመለስና …

የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽንም(OTC) ልክ እንደ ሩዋንዳ በኦሮሚያ ፕሬዝደንት ፅ/ቤት የሚመራ በተለመደው የመንግስት መዋቅርና አሰራር ያልተተበተበ በዚህም የክልሉን የቱሪዝም እምቅ ሀብት በመለየትና በማልማት፣ በተለያዩ ሀገራት በማስተዋወቅ፣የገበያ እድሎችን በመፍጠርና በንግድና መሰል አውደርዕዮች ላይ አግሬሲቭሊ በመሳተፍ የኢትዮጵያን ቱሪዝም ለአለም እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር አጋርነት በመፍጠር ዘርፉ ይበልጥ ትኩረት እንዲያገኝ የሚደረገውን ጥረት በግሌ የማደንቀው ተግባር ነው፡፡

ከተለመደው የቱሪዝም እንቅስቃሴ ባሻገር አማራጭ የቱሪዝም አይነቶችን እንደ ቡና፣ወይን እንዲሁም ሀላል ቱሪዝም ላይ ንቁ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑ ይበል ያሰኛል፡፡

ከዚህ በኃላ ምን እንዲሰራ ይጠበቅበታል ?

✍️መዳረሻን በመለየት ማልማት እንዲሁም የለማውን የማስተዋወቅ ተግባር ላይ በተሰራው ልክ የአገልግሎት ጥራት(Service Quality) ላይ በትይዩ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ ጎብኚዎች(ገበያው) ሲመጣ በተዋወቀው ልክ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል አልያ የዘላቂነት(sustainability) ጥያቄ ብቻ ሳይሆን መልካም ያልሆነ ልምድ ይዘው ከሄዱ የገበያ ድግግሞሽ(Market Reputation) እንዳይኖር አሉታዊ ተፅዕኖ ይፈጥራል፡፡

🔎ቱሪዝምን ከ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ (ዲጂታል ቱሪዝም) ከማስተሳሰር ፣ የሰው ሀብት ልማት ላይ ከመስራት አንጻር እንደ ጅምር ለሌሎችም ተመስሌታዊ መንገድ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡

#እንደ መውጫ

✔️የሌሎች ክልል ተመሳሳይ ተቋማትም ይህን መንገድ ቢከተሉ ከራሳቸው ክልል ባለፈ እንደ ሀገር በብዙ የሚጠቅም ይሆናል፡፡ ቪዚት ኦሮሚያ በክልሉ የሚገኙ መዳረሻ ቦታዎችን የሚያስተዋውቁበት መንገድ፣ የሚጠቀሟቸው ተስማሚ ገለጻዎች ከማራኪ ምስሎች ጋር እጅግ የሚደነቅ ነው፡፡

🔜አዳማ እና ቢሾፍቱ እንደ ቀዳሚ ተምሳሌታዊ ፕሮጀክት(Pilot Project) ተወስደው ትልቅ የቱሪዝም ስራዎች በተለይ በቢዝነስ ቱሪዝም ምሳሌ ሊሆኑ የሚችሉበትን አቅም መጠቀም ግን ግድ ይላል፡፡

#መደምደሚያ

በኢትዮጵያ የቱሪዝም እንቅስቃሴ በ ልክ መዳረሻዎችን በተገቢው መንገድ ያስተዋወቀ(Destination Marketing Org.) የመንግስትም ሆነ የግል ዘርፍ ተቋም የለም፡፡ በዚሁ መጠን የቱሪስት/ጎብኚ ቁጥርም በተሰራው ልክ መምጣትና ገቢ ማስገኘትም ያለበት ወቅት መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡

👍👍Thumbs Up Team Oromia Tourism Commission
Lelise Dhugaa 👏👏
Nega Wedajo Werete👍👍
Visit Oromia

Ethiopian Event Industry Key Players!!በአለም አቀፍ ደረጃ የኹነት ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ገቢ ከማስገኘትም በላይ ሀገራት ምርትና አገልግሎታቸውን እንዲሁም የእድገት ደረጃቸው...
02/12/2024

Ethiopian Event Industry Key Players!!

በአለም አቀፍ ደረጃ የኹነት ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ገቢ ከማስገኘትም በላይ ሀገራት ምርትና አገልግሎታቸውን እንዲሁም የእድገት ደረጃቸውን የሚያሳዩበት ዋነኛው መንገድ ሆኗል፡፡

ኢትዮጵያም በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትልልቅ ዓለምአቀፍ፣አህጉር አቀፍና ሀገራዊ ኹነቶችን በማሰናዳት ላይ ትገኛለች፡፡ ምንም እንኳን ዘርፉ እምቅ የገቢ ምንጭ ያለው ቢሆንም በተለያየ ምክንያት መጠቀም አልተቻለም፡፡ በመንግስት በኩል ከሚመጡ ትልልቅ ስብሰባዎችና ጉባዔዎች ባሻገር አሁን አሁን የግሉ ዘርፍ ተዋንያን በአለም አቀፍ ተወዳደሪ በሆነ መልኩ እጅግ ዘመናዊና ፈጠራ የታከለበት የኹነት ዝግጅቶችን ከሀገር አልፈው በጎረቤት እንዲሁም በአለምአቀፍ መድረክ ላይ በሚገባ እየተገበሩ ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ የግሉ ዘርፍ አንቀሳቃሾች ውስጥ ጥቂቶቹንና በዘርፉ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች መሀከል ፡-

ኦዚ ሆስፒታሊቲ ቢዝነስ ግሩፕ ፡- OZZIE International - Hotel & Resort Project Consultancy

ይህ ዘርፍ አንዱ የቱሪዝም አንቀሳቃሽ ሞተር እንደመሆኑ በሀገራችን የሆስፒታሊቲና ቱሪዝም ኢንዱስትሪ ፈር ቀዳጅ በሚያስብል ሁኔታ ከሀገር አልፎ አፍሪካውያን እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት በናፍቆት ጠብቀው እንዲገናኙ ያስቻለ፣ የሀገር ውስጥ አገልግሎት ሰጪዎች በልዩነት የዘርፉን ነባራዊ ሁኔታ በሚገባ ለአለም እንዲያሳዩ መንገዱን የጠረገ፣ የዘርፍ ባለድርሻዎችንና ባለሙያዎችን በአንድነት እንዲገናኙ በማድረግ፣ በአለምና በአህጉረ አፍሪካ የዘርፉ እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግልሰቦችን፣ተቋማትን እንዲሁም ገዢዎችን በአንድነት እንዲሰበሰቡና የገበያ ትስስር እንዲፈጠር( በሀገራችን ይህ አይነቱ ትስስር በቱሪዝም ዘርፍ ብዙም አልተለመደም ነበር) በማድረግ፣ የተለያዩ አለምአቀፍ ስምና ብራንድ ያላቸው አግልግሎት ሰጪዎች በተለይ ሆቴሎች በሀገራችን እንዲመጡ በማድረግ፣ የአለም የቱሪዝም እንቅስቃሴን በተለይ የቢዝነስ ቱሪዝምን( ማይስ) በልዩነት በማስተዋወቅ ብሎም ከተለያዩ ሀገራት ዘርፉን ጠንቅቀው የሚያውቁ ባለሙያዎች ልምድና ምልከታቸውን በአካል ተገኝተው በመድረክ ንግግር እንዲያደርጉና ኔትወርክ እንዲፈጠር ፕላትፎርሞችን በመፍጠር ረገድ ኦዚ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡

ስለ ሆቴል ሾው አፍሪካ፣ስለ ምስራቅ አፍሪካ የማይስ (MICE)እንቅስቃሴ እንዲሁም ስለ አጠቃላይ የአፍሪካ ሆቴልና ቱሪዝም ነባራዊ ሁኔታ ሁሉም በአንድ ቃል እንዲያወራ ያደረገ ፕላትፎርም ነበር፡፡ በቅርቡም እንደተለመደው የ 2025 ሆቴል ሾው አውደርዕይ በድምቀት ለማከናወን ዝግጅቱን እያደረገ ይገኛል፡፡

በኢትዮጵያ የኹነት ኢንዱሰትሪ ዘርፍ ተኮር በሆነ ሁኔታ በልዩነት ከሚሰሩ አንቀሳቃሾች ውስጥ ኦዚ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ የማይስ ቱሪዝም እንቅስቃሴ ከምስራቅ አፍሪካ አልፎ የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት አጀንዳ እንዲሆን ያስቻለ በተደጋጋሚ የሀገራችን የዘርፉ ባለሞያዎች መድረክ እንዲያገኙ አይን የከፈተ እንቅስቃሴ አድርጓል፡፡ Kudos 🙏 Kumneger Teketel WG

Flawless Events-

እንደስሙ ልክ የሆነ የኢትዮጵያ የኹነት ኢንዱስትሪ ከፍ ባለ ሁኔታ እንዲሄድ ብሎም ሀገሪቱ ከሌሎች ተመራጭ እንድትሆን በፈጠራ፣ በኢኖቬሽን፣በፍጥነትና በጥራት የተለያዩ ኹነቶችን) የኮርፖሬት ስብሰባዎችን፣ትልልቅ ጉባዔዎችንና የማነቃቂያ ጉዞ ዝግጅቶችን ከንድፈ ሀሳብ -እስከ መጨረሻ (End to End) ያሉትን ኹነቶች እጅግ በሚያምርና በደመቀ ሁኔታ በማሰናዳት ይታወቃል፡፡

የከዚህ ቀደሙ እንዳለ ሆኖ እንኳን በቅርቡ በሀገራችን ከተካሄዱት ትልልቅ አህጉርና አለም አቀፍ ኹነቶች( 3rd Pan African AI Confrenece, World Without Hunger Adwa Museum,46th CAF Annual Ordinary Assembly, African Refines & Distribution Association, Heineken Leadership Summit, እንዲሁም ከሀገር ውጪ በኬንያ ናይሮቢ African Fintech Summit) ስብሰባዎችና ጉባዔዎች ጀርባ ከ ጅምር እስከፍጻሜ ይህ ኢትዮጵያዊው Women owned Even Company አለ፡፡

በትልልቅ ኹነቶች ላይ የመገኘት አጋጣሚ አለኝ እናም ሁሌም የሚገርመኝ ለስራው ያላቸው ተነሳሽነት፣ወቅቱን የዋጀ አዳዲስ ፈጠራዎች፣ ለሁሉም ዝግጅቶች አዘጋጁን የሚመስል Ambience የመፍጠር ጥረታቸው እንዲሁም ስራን ጥንቅቅ አድርጎ የመስራትና ሆኖ የመገኘት ዲሲፕሊናቸው በሌሎች ሀገራትም የኹነት ዝግጅቶች ላይ እንዲጋበዙ ምክንያት ነው ብዬ አስባለው፡፡

እናም የኢትዮጵያ የቢዝነስ ቱሪዝም እንዲያድግና በርከት ያሉ አለምአቀፍ ይዘት ያላቸው ኹነቶች ወደ ሀገራችን እንዲመጡ የፍሎወልስ አይነት Destination Marketing Companies በብዛትና በጥራት መኖር አለባቸው በሶስተኛ ወገን ዝግጅት ከማሰናዳት( BPO) ባሻገር በራሳቸው አለምአቀፍ የኹነት ገበያ ላይ እየተሳተፉ፣እየተወዳዳሩ ትልልቅ በተለይ የኮርፖሬት ስብሳባዎችን፣የማነቃቂያ ጉዞዎችን፣የማህበራት ኮንፍራንሶችንና አውደርዕይዎችን እያመጡ መስራት ይኖርባቸዋል፡፡ በአመት አምስት ትልልቅ አለም አቀፍ ኹነቶችን በፍሎወለስ በኩል ቢመጣ ከራስ አልፎ የሀገር ኢኮኖሚ ላይ ያለው በጎ ተፅዕኖ የጥምር ሀገራዊ ምርት (GDP) መጠን እስከመቀየር የሚደርስ ነው፡፡

🙏
Prana Events :-

ከላይ እንደተጠቀሱት ሁሉ በሀገራችን የኹነት ዘርፍ በተለይ በትልልቅ የንግድ፣ዘርፍ ተኮር ባዛር እንዲሁም የሙያና የተለየ አውደርዕይ በማዘጋጀት ስማቸው ከሚጠቀሱ አሰናጆች በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱ መሀከል ነው ፕራና ኢቬንትስ. በሀገራችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለመደው የአውደርዕይ ዝግጅት ዲጂታል የመግቢያና መውጫ ምዝገባ ስርዓት እንዲኖረው፣እጅግ የተዋቡ ቀላልና ዘመናዊ ስታንዶች እንዲሁም የተለያዩ ድርጅቶችን ኮርፖሬት ስብሰባዎችንና ጉባዔዎችን በማሰናዳት ይታወቃል፡፡ Nebeyu Lemma 🙏

በዚህም በዘርፉ ያለውን ልምድና ተሞክሮ ይበልጥ በማስፋት በአለምአቀፍ የዘርፉ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ በመሆን ተመሳሳይ ኹነቶችን በማምጣት የግሉ ዘርፍ እድል ከተሰጠው ዘርፉን መቀየር እንደሚችል ማሳየት ይኖርባቸዋል፡፡

በመዝናኛው ዘርፍ ጆርካ ኢቬንትስ የሚጠቀስ ነው ይሁንና ከኢኮኖሚዊያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ አንጻር ከሌሎች የሚወዳዳር ባይሆንም ወደፊት ለመዝናኛው ዘርፍ ኹነቶች የሚሆኑ መሰረተ ልማቶችና የዝግጅት ቦታዎች እየተሰሩ መሆናቸውን በማሰብ ኢትዮጵያ ከዚህ የኹነት ዘርፍ ከፍተኛ ገቢ የምታገኝበት ይሆናል፡፡

#መውጫ

የኹነት ዘርፍ(ቢዝነስ ቱሪዝም) በኢትጵያ አይደለም ገና በአፍሪካም ብዙ ያልተነካ በዓለም አቀፍ በየአመቱ ከሚካሄዱ ኹነቶች እጅግ በጣም ጥቂቶቹ ብቻ በአፍሪካ የሚሰናዱ መሆናቸውን ከግምት በማስገባት በሚገባ ከተሰራበት የአፍሪካ አውራ መዳረሻ የመሆን እድሎች አሉን፡፡ አሁን አሁን በሀገራችን እየተሰሩ ያሉት የስብሰባ ማዕከላት፣የተለያዩ መሰረተ ልማቶች፣ለማነቃቂያ ጉዞ የሚሆኑ የማረፊያና መዝናኛ ስፍራዎች እንዲሁም የአፍሪካ የነፃ ንግድ ቀጠና እንቅስቃሴ እውን ሲሆን አንዱና ዋናኛው የገበያ ምንጫችን መሆኑን እየታሰበ መንቀሳቀስ ማለፊያ ይሆናል፡፡

    MICE (Meetings, Incentives, Conferences, and Exhibitions) is an important sector of the tourism industry as it contr...
27/11/2024



MICE (Meetings, Incentives, Conferences, and Exhibitions) is an important sector of the tourism industry as it contributes significantly to generating tourism receipts for the country. I am optimistic about the future and the continued growth of Ethiopian business tourism.

One of the key factors driving the growth of the MICE industry today is the availability of event venues, state-of-the-art convention centers, well-equipped exhibition spaces, and luxury accommodation facilities. These resources play a pivotal role in catering to the diverse needs of MICE events. Currently, there are different main event venues in Addis Ababa, including:

*️⃣ The African Union Multi-Purpose Hall

*️⃣ The renewed UNECA Conference Center

*️⃣ The Adwa Museum Conference Hall

*️⃣ The Science Museum Multi-Purpose Center

*️⃣ The upcoming Addis-Africa Convention Center, one of the largest event venues in the region.

While a few luxury hotels (Sheraton Addis, Hilton Addis, Skylight and Hayat Regency) have hosted events, these dedicated venues provide Ethiopia with a competitive edge in attracting and accommodating large-scale events, alongside ongoing infrastructure developments.

the Fact that Gorgora Resort, Wenchi, Chebera Elephant Doh, Halala Kela, and Beynouna Village are designed to cater to luxury incentive-based travelers.

However, collaboration between the private sector and event organizers, particularly in Market seeking with bid development is crucial for securing and sustaining major international events. for events to succeed we must offer sufficient returns on investment and demonstrate financial viability.

Looking ahead, there is no doubt that the Ethiopian Events industry (MICE) will become a vital facet of Ethiopia's overall economic framework. With the capacity to attract large-scale and Mega international events, Ethiopia is poised to strengthen its position as a leading destination in this field.

In the near future, the MICE sector will undoubtedly emerge as one of the most significant contributors to Ethiopia's economy.

Let’s work together and strive on our immense potentials for sharing the lucrative Global Events Market.

any Comments and suggestion accept with Pleasure.



ካፒቴን መሐመድ!!የኢትዮጵያ አየር መንገድን እ.ኤ.አ ከ1980 እስከ 1991 ዓ.ም በዋና ስራ አስፈፃሚነት በማገልገል ለአየር መንገዳችን ዘመን ተሻጋሪ ዕድገት የበኩላቸውን የመሪነት አስተዋፅ...
26/11/2024

ካፒቴን መሐመድ!!

የኢትዮጵያ አየር መንገድን እ.ኤ.አ ከ1980 እስከ 1991 ዓ.ም በዋና ስራ አስፈፃሚነት በማገልገል ለአየር መንገዳችን ዘመን ተሻጋሪ ዕድገት የበኩላቸውን የመሪነት አስተዋፅዖ ያበረከቱት ካፒቴን መሐመድ አሕመድ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ካፒቴን መሐመድ አሕመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው ባገለገሉበት ወቅት አየር መንገዱ ዛሬ ለደረሰበት የስኬት ደረጃ እንዲበቃ መሰረት የጣሉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የማይተካ የመሪነት ሚናቸውን ተጫውተው አልፈዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካፒቴን መሐመድ አሕመድ በህይወት ዘመናቸው ለአየር መንገዱ ባበረከቱት የመሪነት አስተዋፅዖ ምንግዜም ያስታውሳቸዋል።

የካፒቴን መሐመድ አሕመድ ስርዐተ ቀብር ዛሬ ሕዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች ፣ የቀድሞ የስራ ባልደረቦቻቸው እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት በኮልፌ ሙስሊም መካነ መቃብር ተፈፅሟል።

ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

ለሀገር ስላበረከቱት አስተዋፅዖ ከልብ እናመሰግናለን ካፒቴን!!🙏🏻🙏🏻

መልካም እረፍት ይሁንሎት።

ምንጭ ፡ ~የኢትዮጵያ አየር መንገድ

 #የቢዝነስቱሪዝምየኢትዮጵያ ቱሪዝም እንቅስቃሴ በፊት ከነበረው እሳቤ እየተላቀቀ አለም እየሄደበት/እየተጠቀመበት ወዳለው የቢዝነስ/ኹነት/ ቱሪዝም እየተቀላቀለ ይገኛል፡፡ እንደ ጅምር ብዙ መል...
22/11/2024

#የቢዝነስቱሪዝም

የኢትዮጵያ ቱሪዝም እንቅስቃሴ በፊት ከነበረው እሳቤ እየተላቀቀ አለም እየሄደበት/እየተጠቀመበት ወዳለው የቢዝነስ/ኹነት/ ቱሪዝም እየተቀላቀለ ይገኛል፡፡ እንደ ጅምር ብዙ መልካም ነገሮች በተለይ ለዘርፉ ወሳኝ የሚባሉት የመዳረሻና መሰረተ ልማት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የሆነ የመሰብሰቢያ ማዕከላት(Convention Center) በመዲናዋ እየተበራከቱ መምጣት አንዱ ማሳያ ነው፡፡

ከሆቴሎች መሰብሰቢያ አዳራሾች ባሻገር የአፍሪካ ህብረት አዳራሽ፣ከእድሳት በኃላ በአዲስ መልክ የጀመረው ኢሲኤ፣ ሚሊኒየም አዳራሽ( በተለይ ለአውደ ርዕይና መሰል ኹነቶች)፣ የአድዋ ሙዚየም አዳራሽ፣የሳይንስ ሙዚየም እንዲሁም በቅርቡ ተመርቆ ስራ የሚጀምረው የአዲስ አፍሪካ ኮንቬንሽ ማዕከል ኢትዮጵያ በዘርፉ ተወዳዳሪ ብቻ ሳይሆን በመሪነት መቀመጥ የሚያስችላት አቅም የፈጠረላት ቢሆንም ይህን ስራ በሀላፊነት የሚመራ ተቋም ባለመኖሩ ማግኘት የሚኖርባትን ከፍተኛ ገቢ እንድታጣ አስተዋፅዖው ከፍተኛ ነው፡፡

በዚህ ዘርፍ በአፍሪካ ደቡብ አፍሪካ በተለይ ኬፕታውንና ጆበርግ፣ ሞሮኮ፣ግብፅ፣ኬንያ፣ ሞሪሺየስ፣ሲሸልስ አሁን አሁን ደግሞ ሩዋንዳ በከፍተኛ ጥረት እየሰሩ በመሆናቸው በአፍሪካ የቢዝነስ ቱሪዝም መሪዎች ለመሆን በቅተዋል፡፡

ከላይ የተጠቀሱት ሀገራት ይህን ስራ በሀላፊነት የሚመራ ኮንቬንሽ ማዕከል አላቸው የተለያዩ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የስብሰባዎች፣ ጉባዔዎች፣የማነቃቂያ ጉዞዎችንና አውደርዕይ በአለም ዙሪያ የተለያዩ ቦታዎች እየዞሩ ገበያ ያመጣሉ፣ የዘርፉ ተፅዕኖ ፈጣሪ ገዢዎች ይገኙበታል ተብሎ በሚታሰብ ቦታ ሁሉ እየተገኙ ገበያ ያመጣሉ::

World Travel Market Africa(WTM) በአህጉራችን በደ.አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ የሚዘጋጅ ትልቅ የኹነት ዘርፍ ኤክስፖ ነው፡፡ ከአፍሪካ ብቻ ሳይሆን ከአለም ዙሪያ ገዢዎች እንዲሁም የዘርፉ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሚገኙበት ሀገራት ያላቸውን ምርትና አግልግሎት የሚያስተዋውቁበት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ስብሰባዎችንና ጉባዔዎችን በጨረታና ያለ ጨረታ የሚያገኙበት ኹነት ነው፡፡

IBTM World Incentives, Business Travel & Meetings በአለማችን በተለያዩ ቦታዎች ከሚካሔዱ የዘርፉ ግዙፍ ኹነቶች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ሀገራትና ከተሞች አገልግሎታቸውን በሚገባ የሚያስተዋውቁበትና የሚሸጡበት ፣ገዚዎች በቀጣይ ኹነት የሚያዘጋጁበትን ቦታ የሚመርጡበት፣ ማህበራት አማራጭ የገበያ ሁኔታን የሚያዩበት፣ የመዳረሻ ግብይት ኩባንያዎች Destination Marketing Organization (DMO) በአጠቃላይ የኹነት ገበያ ካታሊስቶች በአንድ ቦታ የሚገኛኙበት ስፍራ ነው፡፡

ታዲያ በዚህ አይነቱ ኹነት ላይ ተሳትፎ ምርትና አገልግሎትን ማስተዋወቅ ብሎም ከገዢዎች ጋር ቁርኝት መፍጠር ትልልቅ ስብሳበዎችንና ጉባዔዎችን ለማስተናገድ ዋነኛው መንገድ ነው፡፡

ለምሳሌ የዘንድሮው IBTM World ሰሞኑን በስፔን ባርሴሎና ተካሂዶ ነበር፡፡ የአለም ሀገራት ተሳትፈውበታል በዘርፉ የእኛ ተፎካካሪ የምንላቸው ደ.አፍሪካ፣ሞሮኮ.ግብፅና ሩዋንዳ አፍሪካን ወክለው ተሳትፈዋል ከትልልቅ ገዚዎች ጋር ተገናኝተዋል በቀጣይ በርካታ ኹነቶችን ለማስተናገድ ከወዲሁ ውል ማሰራቸውን አይተናል፡፡

ከዚህ ምን እንማራለን?

ለኹነት የሚሆን መዳረሻ/መሰብሰቢያ መገንባት ብቻ ሳይሆን ገበያውን ያለበት ቦታ አነፍንፎ/ አማትሮ ትልልቅ ኹነቶችን ማምጣት ከመጡም በኃላ ተገቢውን እንክብካቤ አድርጎ ለቀጣይ ኹነቶች ተመልሰው እንዲመጡ ማድረግ ለነገ የማይባል ተግባር ነው፡፡ ለዙህ ደግሞ ራሱን የቻለ ዘርፉን በሚገባ ባወቁ በበቁ ባለሞያዎች የተዋቀረ በመንግስታዊ አሰራር ቢሮክራሲ ያልታጠረ Autonomous ተቋም ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ሩዋንዳ ናት የፖል ካጋሜዋ ሩዋነዳ ይህን ስራ የሚያሳልጥላት Rwanda Convention Bureau (RCB) ነው፡፡ መንግስታዊ ነገር ግን በመንግስት ቢሮክራሲ ያልታጠረ የበጀትና የስራ ነፃነት ያለው ተቋም ነው፡፡

በርካታ አለምአቀፍ ተቋማትና ኤምባሲዎች በሚገኙባት ብሎም የአፍሪካ መዲና በሆነችው ኢትዮጵያ (አዲስአበባ) በመሪዎች ጥረት ብቻ ከሚገኝ ኹነት ይልቅ በሚያመጣው የኹነት አይነትና ብዛት የሚገመገም ድንበር ዘለልና ዘርፍ ተኮር ተቋም ያስፈልገናል፡፡ ይህን ካለደረግን አይደልም ከአለም ከጎረቤቶታችችን እንኳን መወዳደር አንችልም፡፡

ከስፖርት ቱሪዝም መገለጫዎች አንዱ የሆነው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ!!!ብዙ ልንማርበት የሚገባ ተቋም!! ብዙ ልንሰራበት የሚገባ የቱሪዝም አንዱ መስህብ/መዳረሻ ፌስቲቫል።
17/11/2024

ከስፖርት ቱሪዝም መገለጫዎች አንዱ የሆነው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ!!!

ብዙ ልንማርበት የሚገባ ተቋም!! ብዙ ልንሰራበት የሚገባ የቱሪዝም አንዱ መስህብ/መዳረሻ ፌስቲቫል።



ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ(ዶ/ር) ትናንት  ካደሩጉት የፓርላማ ንግግር ውስጥ ''የቱሪዝም ሴክተርን በተመለከተ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ  20 የሚሆኑ አለምአቀፍ ይዘት ያላቸው ጉባዔዎች ...
01/11/2024

ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ(ዶ/ር) ትናንት ካደሩጉት የፓርላማ ንግግር ውስጥ

''የቱሪዝም ሴክተርን በተመለከተ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ 20 የሚሆኑ አለምአቀፍ ይዘት ያላቸው ጉባዔዎች በሀገራችን ተስተናግደዋል፡፡ በኮሪደር ልማትና ሌሎች ምጬ ሁኔታዎችን እያዩም አለምአቀፍ ድርጅቶችና ተቃማት ሁነቶችን በሀገራችን ለማድረግ ፍላጎት እያሳዩም ነው'' ብለዋል፡፡

ይህ ለሴክተሩም ሆነ ለሀገራችን በጎ ዜና ነው፡፡

ይሁንና ከዚህ የተሻለ እንዲመጣ ጠንካራ ስራ ይፈልጋል ቁርጠኝነት ይፈልጋል ራሱን የቻለ ይህን የሚያሳልጥ ተቋም ያስፈልጋል፡፡ ሌላውን ትትን ጎረቤቶቻችን ሩዋንዳና ኬንያ የእኛን ያህል እንኳን ሪሶርስ ሳይኖራቸው በአግባቡ ያላቸውን ሀብት እየተጠቀሙ በዘርፉ ተቀዳሚ ተመራጭ ሀገራት ሆነዋል፡፡

እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ያለ ግዙፍና በአለም ገበያ ተወዳዳሪ ብሎም በየዘርፉ ተሸላሚ የሆነ ተቋም ይዘን ሳለ፣ የአፍሪካ ህብረትና ኢሲኤ እንዲሁም ሌሎች የኹነት ዝግጅት የሚደረግባቸው ማዕከሎች ኖሮን፣ ከ10 በላይ አለምአቀፍ ስምና ብራንድ ያላቸው እንዲሁም ቅንጡ ሀገር በቀል ሆቴሎችን በድምሩ ከ20 ሺህ በላይ ለአለም አቀፍ ገበያ በሚሆን መልኩ የተሰናዱ የመኝታ ክፍሎች ባላት ሀገር፣ የአለም ሀገራት ኤምባሲዎችና ቆንስላ ፅ/ቤቶች እንዲሁም ከ200 በላይ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች መቀመጫ የሆነች ሀገር፣ ሌሎች ሀገራት የሌላቸው በርካታ የገበያ አማራጭ ያላት ሀገር በጣት የሚቆጠር ኹነቶችን ያውም በጥቂት የግል ዘርፉ ተዋንያኖች ጥረት የሚመጣ ስብሰባ፣ጉባዔና መሰል ኹነቶችን ማስተናገዷ አሁንም ዘርፉ ላይ ብዙ የቤት ስራ መስራት እንዳለብን የሚያመላክት ነው፡፡

በሌሎች ሀገራት እንደሚታየው ይህ አይነቱ የቢዝነስ ቱሪዝም (ማይስ)በአብዛኛው የሚከወነው በግሉ ዘርፍ ተዋንያኖች ሲሆን የመቆጣጠርና የገበያ አማራጭ በማስፋት እንዲሁም በማሳለጥ በኩል መንግስታዊ መዋቅሮች ትልቅ ድርሻ ይኖራቸዋል፡፡ የቱሪዝም ቦርድ፣ኮንቬንሽ ማዕከሎች፣ የቪዚተር ቢሮ እንዲሁም በመንግስት መዋቅር የሚገኙ ሌሎች ክፍሎች ዋነኛ ባለድርሻ ሲሆኑ እንደ Destination Marketing Companies (DMC) እና Professional Conference Organizers (PCO) የኹነት አዘጋጆች ማህበራት እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ሙያ ማህበራት ደግሞ ገበያን ፈልጎ ከማምጣት ኹነቶችን በሚገባ አሰናድቶ እስከ ማጠናቀቅ ያለውን ሂደት በማሳለጥና ኢምፕሬሽን በመፍጠር ከዘርፉ የሚገኝ ገቢን በአግባቡ መጠቀም ይቻላል፡፡

በእኛ ሀገር አውድ ይህን ተግባር የሚከውኑት እጅግ በጣም ጥቂት የግሉ ዘርፍ ሞተሮች ናቸው፡፡ ከትልልቅ ስብሰባዎች፣ጉባዔዎችና አውደ ርዕዮች ጀርባ ሁሌም የማናጣቸው እንደ ኦዚ ሆስፒታሊቴ ቢዝነስ ግሩፕ፣ Flawless Events and Prana Events አሁን ላይ በንቃት እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ የግልና ማህበራት ዘርፍ ተወካይ አሳላጮች ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ኮንቬንሽ ቢሮ በዚህ ረገድ ከበፊቱ በጥቂቱ እንቅስቃሴ እያሳየ ቢገኝም በሚጠበቅበት ልክ ግን እየሰራ አይደለም፡፡ እንዲሁም የአዲስአበባ ባህል፣ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮም ይህን ዘርፍ በሩቁ ያለ ይመስላል ትኩረቱ ሁሉ ለአንድ ሜትሮፖሊታን ከተማ በሚሆን መልኩ አይደለም፡፡

ኢትዮጵያ አሁን ባላት ወቅታዊ ለገበያው በሚያስፈልጉ ሪሶርስ ብቻ ቢያንስ በአማካይ በወር ከሀያ በላይ አለምአቀፍና አህጉር አቀፍ ትልልቅ ኹነቶችን ማስተናገድ ትችላለች ይጠበቅባታልም፡፡

የቢዝነስ ቱሪዝም ፅንስ ሀሳብ በሚገባው ልክ ትኩረት አላገኘም፡፡

27/09/2024



በአርባምንጭ ከተማ ባጃጅ ላይ አነስተኛ ካሜራ (Go pro) እና በርካታ የስራ ፋይሎች የተቀመጡበት ሃርድዲስክ የያዘ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ቅርጽ ያለው ጥቁር አነስተኛ ቦርሳ ጠፍቶብኛል።
ለስራ በጣም አስፈላጊ የሆነ ካሜራ እና የበርካታ የጉዞ ኢትዮጵያዊ ስራዎች ፋይል ያለበት ሃርድ ዲስክ በመሆኑ ቦርሳውን ያገኛችሁ አካላት ከዚህ በታች በሚገኙ ስልክ ቁጥሮች ደውላችሁ ብታሳውቁን ወረታ ከፋይ መሆናችንን እንገልፃለን ።
+251911144964
+251911258785
+25191250 4225

Henoke Seyuome Hagere

  …..The ‘’Game Changer’’ will be Back on the Stage.More Than just a trade shows it’s showcasing the latest global Brand...
24/09/2024

…..

The ‘’Game Changer’’ will be Back on the Stage.

More Than just a trade shows it’s showcasing the latest global Brands and the meeting place for our Hospitality and Tourism Industry for consecutive years.

The Ultimate Platform for Both Industry Professionals and stakeholders.

Visitors from across all over the place can discover the next big thing in Hospitality from global manufacturers and local suppliers, helping to foster collaboration and drive innovation in the industry.@ the Grand Millennium Hall.

The Vibrant Hub of Africa Ababa Will be shining Again with the Pioneer Platform of Hospitality Industry.



Salute for the Man who Behind on pioneer Platform
Kumneger Teketel WG 🙏🙏🙏

Address

Piassa
Awassa

Telephone

+251904424763

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Witness Hospitality posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Witness Hospitality:

Share