ስንክሳር

ስንክሳር Ethiopian Synaxarium

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"

"የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል"
(አባ ጊዮርጊስ) ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንድት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።

✍️ ጸሎት እንዴት ይጸለያል?       ( በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ )➺ጸሎት ሰው ከልዑል እግዚአብሔር ጋራ የሚነጋገራት ነገር ናት|ጸሎት ብሒል ተናግሮ ምስለ እግዚአብሔር እንዲል|፤➛አንድም የ...
11/10/2025

✍️ ጸሎት እንዴት ይጸለያል?
( በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ )

➺ጸሎት ሰው ከልዑል እግዚአብሔር ጋራ የሚነጋገራት ነገር ናት|ጸሎት ብሒል ተናግሮ ምስለ እግዚአብሔር እንዲል|፤

➛አንድም የተበደለ ድኃ ከንጉሥ እንዲጮህ ሰው ወደ ልዑል እግዚአብሔር የሚጮሃት ጩኸት ናት፤

➺ባለፈው እያመሰገነ፥ ለሚመጣው እየለመነ የሚኖርባት፤

➛እግዚአብሔርን አንድም ራሱን ደስ የሚያሰኝበትን ነገር ሽቶ ወደ እግዚአብሔር የሚጮሃት ጩኸት ናት፤

✍️ለሚጸልይ ሰው ብዙ ሥርዐታት አሉት።

፩. በእግሩ ቀጥ ብሎ መጸለይ ይገባዋል፤ "በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ፥ በማለዳ በፊትህ እቆማለሁ፥ እጠብቃለሁም።" መዝ.5፥3።

፪. ወገብ ልቡናን በንጽህና ዝናር መታጠቅ ነው፤ "ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን፤" ሉቃ.12፥35 እንዲል።

፫. ፊትን ወደ ምሥራቅ መመለስ ነው፤ "በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ የኃይል ቃል የሆነ ቃሉን፥ እነሆ፥ ይሰጣል።" መዝ. 67፥33።

➛ከዚኽ ኹሉ ጋራ ወዲያና ወዲህ ማየትን፤ አንድም ልቡና ማባከንን መተው ይገባናል።

፬. አቲብ በአፅባዕት በአምሳለ መስቀል |ፊትን በትእምርተ መስቀል ማማተብ ነው|፤

➬ከላይ ወደ ታች|ትእምርተ ርደት ነው፦ ይኽም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማይ ወደ ምድር የመውረዱ ምሳሌ|፥

➬ከግራ ወደ ቀኝ|እኛን ከኃሣር ወደ ክብር፥ ከሲኦል ወደ ገነት የማውጣቱ ምሳሌ|፤

➣በጣት ፊትን ማማተብ አጋንንት ለማራቅ ነው። "እኔ ግን በእግዚአብሔር ጣት አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ እንግዲህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ደርሳለች።" ሉቃ.11፥20።

➥በትእምርተ መስቀል ፊትን ማማተብ፦

ሀ/. ፈጣሪ በመስቀሉ ድኅነተ ምዕመናንን ፈጽሞበታልና፤

ለ/. ዳግመኛም ስለኛ የተሰቀለ የቸርነቱን ነገር እናስብ ዘንድ ነው፤

ሐ/. ቅዱሳን ሐዋርያትም ረስጣ ፵ወ፱ እንዲኹም ሐዋርያት በመጀመሪያው ቀሌምንጦስ 49ኛው አንቀጽ፦ "ሰይጣን ከኛ ይርቅ ዘንድ በተረዳች ሃይማኖት ኹል ጊዜ ፊታችንን በመስቀል አምሳል እናማትብ ዘንድ፤ አጋንንት ከሚያመጡት ጉዳት እንድን ዘንድ ይኽን ምልክት አደረጉልን።

➲በትእምርተ መስቀል የሚያማትቡባቸው ጊዜያት፦

➦ጸሎት ሲጀመር፥

➦መስቀል፥ መስቀልን የሚያነሳ አንቀጽ ሲደርስ ነው።

፭. በፍርሃት፥ በረዓድ ኹኖ ጸሎቱን መጸለይ ነው።

➬የሚጸልየውም ጸሎት ወደ እግዚአብሔር የሚሳብበት ይኹን፤ አፍ ንባብ ይነዳ፥ ልብ ጓዝ ያሰናዳ እንዲሉ።

፮. አስተብርኮ፥ ሰጊድ ነው። "... ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ፡ ተብሎ ተጽፎአልና፡ አለው።" ማቴ. 4፥10።

➛አንድም ወንጌል በምሴተ ሐሙስ እንደጸለየ፤ በጉልበቱ እንደተንበረከከ ይመሰክራል። "ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ ተንበርክኮም፡—..." ሉቃ. 22፥41እንዲል።

✍️የሚሰገድባቸው ጊዜያት፦ ቁጥሩ በኛ ጉባዔ ተጽፏል። ሐተታ፦ ጊዜያቱ ሰባት የጸሎት ሰዓታት አሉ። የአንዱ ሰዓት 36 ሰጊድ ሲኾን የሰባቱ፦ 36x7= 252 ጊዜ ይሰገዳል። እንደ ጽናቱ መጠን 100, 200, 1000 ጨምሮ የሚሰግድ አለ።

➛የሚጸልይ ሰው በሚጸልይበት ጊዜ ሰጊድን ከሚያነሳ አንቀጽ ሲደርስ ለልዑል እግዚአብሔር ይስገድ። በአንድ ሰጊድ ከጀመረ በዚያው አንድ እየሰገደ መጨረስ፥ ሦስት ጊዜ እየሰገደ ከጀመረ ሰጊድ በሚልበት ኹሉ ሦስት፥ ሦስት ጊዜ እየሰገደ መጨረስ አለበት።

➬ጸሎቱን በጨረሰ ጊዜ እንዲህ ያድርግ በአንድ ጀምሮ እንደኾነ በአንድ ይጨርስ፤ አንዱ የአንድነት፥ ሦስቱ የሦስትነት ምሳሌ ነው።

✍️ከስግደት የሚከለክሉባቸው ጊዜያት፦

➾ሠለስቱ ምዕት በኒቅያ በጻፉት መጽሐፍ በ20ኛው አንቀጽ እሑድ፥ እሑድ፤ በባለሃምሳ አትስገዱ አሉ።

➾ዘኒቅያ 32ኛው አንቀጽ፦

➦ በጌታ በዓል፥
➦በእመቤታችን በዓል፣
➦ሥጋውን ደሙን ከተቀበሉ በኋላ አትስገዱ አሉ።

✍️ ስለምን እሑድ፥ እሑድ፤ በባለሃምሳ ስግደት ከለከለ ቢሉ፦

➥አክብሩ ያለውን ትእዛዝ ማፍረስ ነውና፤
➥አንድም በዚኽ ቀን ዕረፍተ ሥጋ አርፋችሁ ዕረፍተ ነፍስ ዕረፉበት ብሏል።

✍️ ስለምን በጌታ በዓል፥ በእመቤታችን በዓል ስግደት ከለከለ ቢሉ፦

➥በእመቤታችን ቃል ኪዳን በጌታ ካሳ አልዳንም ያሰኛልና፤

➲አንድም በዓል የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው። በዚህ ቀን ሲሰግዱ መዋል መንግሥተ ሰማያት ከገቡ በኋላ ኃጢኣት ሰርቶ ንስሓ መግባት አለ ያሰኛልና።

✍️ ስለምን ሥጋውን ደሙን ከተቀበሉ በኋላ መስገድ አይገባም አለ፤

➥ወዙ ይንጠፈጠፋልና፤
➥አንድም በሥጋ ወደሙ አልዳንም በትሩፋታችን ዳን ያሰኛልና።

✍️በጸሎት ጊዜ የሚገባስ ጣታችንን ዘርግተን፥ እጃችንን ማንሳት ነው።

➱"በሌሊት በቤተ መቅደስ ውስጥ እጆቻችሁን አንሡ፥ እግዚአብሔርንም ባርኩ።" መዝ.133፥2።

➱"እጆቼን ወደ አንተ ዘረጋሁ፤ ነፍሴም እንደ ምድረ በዳ አንተን ተጠማች።" መዝ.142፥6

✍️ ዳግመኛም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልዓዛርን ባስነሣው ጊዜ ወደ ሰማይ እንዳየ ዓይናችንን ወደ ሰማይ ማቅናት ነው።

➥"ኢየሱስም ዓይኖቹን ወደ ላይ አንሥቶ፡— አባት ሆይ፥ ስለ ሰማኸኝ አመሰግንሃለሁ።" ዮሐ.11፥41።

➥"ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓይኖቹን አነሣና እንዲህ አለ፡— ..." ዮሐ.17፥1-2።

👏የነግሁንና የመንፈቀ ሌሊቱን ጸሎት እጃቸውን ከታጠቡ በኋላ ይጸልዩ አለ።

➺ሰው ከተኛ ዝንየት አይጠፋምና፤ ወለእመ ኢረከቡ ማየ በውእቱ ጊዜ ይንፍሑ እደዊሆሙ ወይዕተቡ በምራቅ ዘይወጽእ እምአፉሆሙ|ያን ጊዜ ውኃ ባያገኙ እፍ ብለው ከአፋቸው በሚወጣው ምራቅ እጃቸውን አሻሽተው ያማትቡ|።

➦እመሰ ማየ ዮርዳኖስ ይወጽእ እም አፉከ|የዮርዳኖስ ውኃ ከአፍህ ይወጣልና|እንዲል።

➬ሚስት ያለችው ሰው ቢሆን ኹለቱም አንድ ጊዜ ይጸልዩ። ባለጸጋ ቢኾን እሱ ከአዳራሽ እሷ ከእልፍኝ፤ ድኃ ቢኾን እሱ ከጉበኑ እሷ ከማጀት ኹነው ይጸልዩ።

➬ሚስቱ ያላመነች|ከተጋቡ በኋላ በእምነት ባትመስለው| ብትኾን ግን ተለይቶ ብቻውን ይጸልይ።

➲በሩካቤ አንድ የኾኑ|ሩካቤ ፈጽመው ያደሩ| ሰዎች ከመጸለይ ወደ ኋላ አይበሉ።

➥ከውሽባ ቤት|ሻወር ቤት| ገብተን እንታጠብ አይበሉ።

➥ዘእንበለ ተሐጽቦ እድ ባሕቲቱ|እጃቸውን(ኃፍረተ ሥጋቸውን) ብቻ ይታጠቡ| እንጂ።

➲ዘር የወጣበትን ዘር የነጠበበትን አካል ይታጠቡ እንጂ፤ እስመ ሰብሳቦሙ ንጹህ ውእቱ|ሩካቤያቸው ንጹህ ነውና|።

➲"መጋባት በሁሉ ዘንድ ክቡር መኝታውም ንጹሕ ይሁን፤ ሴሰኞችንና አመንዝሮችን ግን እግዚአብሔር ይፈርድባቸዋል።" ዕብ.13፥4 እንዲል።

✍️ባስልዮስ በጻፈው መጽሐፍ በ28ኛዋ አንቀጽ ሳይበላ አስቀድሞ መጸለይ የሚገባ እግዚአብሔር የሚበላውን ምግብ ያበረክት ዘንድ፤ ሥራይ ቢኖርበት ያጠፋ ዘንድ ነው።

➾ከተበላ በኋላ መጸለይ የሚገባም እግዚአብሔር ሥጋን ከኃጢኣት ለመጠበቅ፤ ጤና ለማግኘት ምግቡን ከሰውነቶ ያስማማ ዘንድ ነው።

➬ካህናት ከሕዝቡ ጋራ ይጸልዩታል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ አባቱ አመልክቶ አምስቱን እንጀራ በባረካት ጊዜ ተቀምጦ እንደጸለየ ተቀምጠው ይጸልዩዋታል።

✍️መንገድ ሊነሡ የሚጸልዩት ጸሎት አለ።

➾"ጊዜውንም በፈጸምን ጊዜ ወጥተን ሄድን፤ ሁላቸውም ከሚስቶቻቸውና ከልጆቻቸው ጋር እስከ ከተማው ውጭ ድረስ ሸኙን፥ በባሕሩም ዳር ተንበርክከን ጸለይን፤ እርስ በርሳችንም ተሰነባብተን ወደ መርከብ ወጣን፥ እነዚያም ወደ ቤታቸው ተመለሱ።" ሐዋ.21፥5-6።

✍️መነኮሳት አሳጥረው ለይተው የሠሯት ጸሎት ናት።

➦ከደጅ የሚመጣ ፊቱን አማትቦ አቡነ ዘበሰማያት ደግሞ ይግባ፤

➦ከውስጥ የሚወጣው ፊቱን አማትቦ አቡነ ዘበሰማያት ደግሞ ይውጣ ብለው ሥርዐት ሰርተዋል።

👌ለምእመናን ኹሉ የታዘዘው ጸሎት ሰባት ጊዜያት ነው።

፩. መጀመሪያ ፀሐይ ሳይወጣ ከእንቅልፋቸው በነቁ ጊዜ ከመኝታቸው ተነሥተው በነግህ የሚጸልዩት ጸሎት ነው።

➥ጽልመተ ሌሊትን አርቀህ ብርሃነ መዓልትን ያመጣልን ሲሉ፤

➥አንድም የኹሉ አባቱ አዳም የተፈጠረበት ነውና።

➥አንድም ጌታ በጲላጦስ ፊት ቁሞ የተመረመረበት ጊዜ ነውና።

👏 እጃቸውን ከታጠቡ በኋላ ከተግባረ ሥጋ አስቀድመው መጸለይ ይገባል።

፪. ሦስት ሰዓት የሚጸልዩት ጸሎት ነው።

➥የኹሉ እናት ሔዋን የተፈጠረችበት፤

➥አንድም ዳንኤል የጸለየበት፤ "ዳንኤልም ጽሕፈቱ እንደ ተጻፈ ባወቀ ጊዜ ወደ ቤቱ ገባ፤ የእልፍኙም መስኮቶች ወደ ኢየሩሳሌም አንጻር ተከፍተው ነበር፤ ቀድሞም ያደርግ እንደ ነበረ በየዕለቱ ሦስት ጊዜ በጕልበቱ ተንበርክኮ በአምላኩ ፊት ጸለየ አመሰገነም።" ዳንኤል 6፥10 እንዲል።

➥አንድም እመቤታችን ብስራተ መልአክን ሰምታ ጌታችን የጸነሰችበት፤

➥አንድም ጌታ በጲላጦስ ፊት የተገረፈበት፤

➥አንድም በጽርሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደበት ሰዓት ነውና።

፫. በ ፮ ሰዓት የሚጸለይ ጸሎት ነው።

➥በቀትር ጊዜ ዋዕየ ፀሐይ ይጸናል፥ ከናላ ላይ ይወድቃል፥ ሐሞት ይበተናል፥ ሰውነት ይዝላልና ያን ጊዜ አጋንንት ይሠለጥናሉና እንዳይሠለጥኑበት፤

➥አንድም አዳም የካደበት፤

➥ኄኖክ ቤተ መቅደስን ያጠነበት፤

➥ጌታ የተሰቀለበት ሰዓት ነውና።

፬. በ ፱ ሰዓት የሚጸልዩት ጸሎት ነው።

➥መላእክት የሰውን ምግባርና ጸሎት የሚያሳርጉበት ሰዓት ነውና፤

➥አንድም ጌታ ነፍሱን ከሥጋው የለየበት ሰዓት ነውና።

፭. በሠርክ የሚጸለይ ጸሎት ነው።

➥ሠርክ የምጽአት ምሳሌ፤
➥ሰው ሲሰራ ውሎ ዋጋውን የሚቀበል በሠርክ ነው። ምእመናንም ምግባር ትሩፋታቸው ሲሠሩት ኑረው ዋጋቸውን የሚያገኙ በምጽአት ነውና።
➥አንድም ጌታ ወደ መቃብር የወረደበት ሰዓት ነውና።

፮. በንዋም ጊዜ|ከምሽቱ ፫ ሰዓት| የሚጸለይ ጸሎት፦ ጸሎተ ንዋም ነው።

➥ሥራኃ መዓልትን አሳልፈህ ዕረፍተ ሌሊትን ያመጣህልን ሲሉ፤

➥አንድም ጌታ የጸለየበት ሰዓት ነው፤

፯. ጸሎተ መንፈቀ ሌሊት|ከሌሊቱ ፮ ሰዓት| የሚጸለይ ጸሎት ነው።

➤እጃቸውን በውሀ ከታጠቡ በኋላ በመንፈቀ ሌሊት የሚጸለይ ጸሎት ነው።

➦ጌታ የተወለደበት፥ የተጠመቀበት፥ የተነሣበት፥ ዳግመኛም የሚመጣበት ሰዓት ነውና።

➦አንድም ጳውሎስ ጊዜ መንፈቀ ሌሊት እንዲል። "በመንፈቀ ሌሊት ግን ጳውሎስና ሲላስ እየጸለዩ እግዚአብሔርን በዜማ ያመሰግኑ ነበር፥ እስረኞቹም ያደምጡአቸው ነበር።" ሐዋ.16፥25።

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።ጥቅምት 2 ታላቁ አባት አባ ሕርያቆስ ልደታቸውና ዕረፍታቸው ነው፡፡ ➛ የፈጠጋሩ አቡነ ማትያስ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ➛ የአንጾኪያ...
11/10/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።

ጥቅምት 2 ታላቁ አባት አባ ሕርያቆስ ልደታቸውና ዕረፍታቸው ነው፡፡
➛ የፈጠጋሩ አቡነ ማትያስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
➛ የአንጾኪያው ታላቁ አባት አቡነ ሳዊሮስ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው ነው፡፡

🔥 አቡነ ማትያስ ዘፈጠጋር

አቡነ ተክለ ሃይማኖት የበቁ፣ የነቁ፣ ምግባር ሃይማኖታቸው እንደፀሐይ ያበራ፣ ከተጋድሏቸውም ብዛት የተነሣ ከብቃት ደረጃ ላይ የደረሱ ቅዱሳን የሆኑ ደገኛ መምህራንን በማሰልጠን በአንብሮተ እድ ዓሥራ ሁለት ዓሥራ ሁለት አድርገው እየሾሙ ለስብከተ ወንጌል በመላ አገራችን ያሰራጯቸው ነበር፡፡ እነዚህም ንቡራነ እድ ከዋክብት በመላ አገራችን የወንጌልን ብርሃን ያበሩ ቅዱሳን ናቸው፡፡ በመጀመሪያ በተክለ ሃይማኖት በአንብሮተ እድ የሾሟቸው 12ቱ ከዋክብት የወረቡ አኖሬዎስ፣ የሞረቱ ዜና ማርቆስ፣ የጽላልሹ ታዴዎስ፣ የድምቤው ገብረ ክርስቶስ፣ የወገጉ ሳሙኤል፣ የእናርያው ዮሴፍ፣ የዳሞቱ አድኃኒ፣ የወጁ ኢሳይያስ፣ የመንዝ የመራቤቴውና የወለቃው መርቆሬዎስ፣ የመሐግሉ ቀውስጦስ፣ የፈጠጋሩ ማትያስ፣ የደዋሮው ተስፋ ሕፃን፣ የእንሳሮው ዳዊት፣ የዘልዓቱ ናታን ናቸው፡፡
የፈጠጋሩ ማትያስም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከሾሟቸው ከ12 ንቡራነ እድ ውስጥ አንዱ ሲሆኑ ቁጥራቸውም ሁለተኛ ናቸው፡፡ ደብረ ሊባኖስን ያጥኑ የነበረው በሰኔ ወር ሲሆን በገዳሙም 13ኛው አባት በመሆን በመምህርነት አገልግለዋል፡፡ በሀገራችን ተዘዋውረው በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ወንጌልን ሲሰብኩ ኖረው በሰላም ዐረፈዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን።

🔥 አቡነ ሳዊሮስ፡-

ዳግመኛም በዚህች ዕለት ታላቁ አባት አቡነ ሳዊሮስ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው ነው፡፡
እጅግ ክቡር የሆኑት የአንጾኪያው ታላቁ አባት የአቡነ ሳዊሮስ ትውልዳቸው ከሮሜ ሀገር ሲሆን አባታቸው ሳዊሮስ የሚባሉ ኤጲስ ቆጶስ ናቸው፡፡ አባታቸው ሳዊሮስ ስለ ንስጥሮስ የከፋ ክህደት በኤፌሶን ከተማ ጉባኤ በተደረገ ጊዜ ከሁለት መቶው እጅግ ከከበሩት ሊቃውንት ቅዱሳን አባቶች ጋር ተሰብስበው ሃይማኖትን አቅንተዋል፡፡ ንስጥሮስንም በቃላቸው ትምህርትና የተለያዩ ተአምራትን እያሳዩ አስተምረው ሊያሳምኑት ቢሞክሩ ሰይጣን በልቡ ስላደረ ከክህደቱ ሊመለስ አልቻለም ነበርና ቤተ ክርስቲያንን እንዳያውክ ምእመናንም በክህደት በመርዙ እንዳይበክል ብለው ቅዱሳኑ በኅብረት አውግዘው ለዩት፡፡
ታላቁ አቡነ ሳዊሮስም ለጉባኤው በኤፌሶን ከተማ እንደመጡ ‹‹ከአንተ የሚወለድ ልጅህ ስሙም እንደ ስምህ ሳዊሮስ ተብሎ የሚጠራ ልጅህ የቀናች ሃይማኖትን ያጸናታል›› የሚል ታላቅ ራእይን ተመለከቱ፡፡ ይህም ታላቁ አቡነ ሳዊሮስ ባረፉ ጊዜ ልጃቸውን ሳዊሮስ ብለው ጠሩት፡፡ እርሱም ከቤተ ክርስቲያን ውጭ የሆኑትን የጥበብና የፍልስፍና ትምህርቶቸን በሙሉ ጠንቅቆ ተማረ፡፡ በአንዲት ዕለትም ከመምህሩ ዘንድ ወጥቶ በመንገድ ሲጓዝ በዋሻ ውስጥ የሚኖርና ራሱን እስረኛ ያደረገ አንድ ታላቅ ጻድቅ ሰው አገኘ፡፡ ያም ጻድቅ ሰው ሳዊሮስን ‹‹የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ሃይማኖታቸው ለቀና ምእመናን መምህራቸው የሆንክ ሳዊሮስ ሆይ መምጣትህ መልካም ነው›› አለው፡፡ ያም ጻድቅ ሰው ሳዊሮስን ከነጭራሹ ሳያውቀው በስሙ ስለጠራውና የሚደረግለትንም ከመሆኑ አስቀድሞ ትንቢት በመናገሩ በጣም ተደነቀ፡፡
ከዚህም በኋላ ሳዊሮስ የትሩፋት ሥራዎችን መሥራት ጀመረ፡፡ ወደ አቡነ ሮማኖስ ገዳም ገብቶ መነኮሰና በጾም በጸሎት በእጅጉ ይተጋ ጀመር፡፡ በገዳሙም ጽኑ በሆነ በመንፈሳዊ ተጋድሎ እየበረታ ሲሄድ ዜናው በሁሉ ዘንድ መሰማት ጀመረ፡፡ የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳሳት በሞት ባረፉ ጊዜ የከበሩ ሊቃውንት ኤጲስቆጶሳት በአንድ ሀሳብ ሆነው ፈቃደ እግዚአብሔርን ጠይቀው አቡነ ሳዊሮስን የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ይሾሙት ዘንድ ወደዱ፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔርም ያለ ፈቃዱ በግድ ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት፡፡
በአቡነ ሳዊሮስ በሹመታቸው ዘመን እስከ ዓለም ዳርቻ ያለች ቤተ ክርስቲያን ብርሃን ሆኑላት፡፡ የመለኮት ነገር የሚናገሩት ድርሰቶቻው እጅግ ድንቅ ናቸው፡፡ በየሀገሩ ወዳሚገኙ መናፍቃን ከሃድያን ትምህርታቸው በሚደርስ ጊዜ ሁለት አፍ እንዳለው ስለታም ሰይፍ ሥራቸውን ይበጥሳልና፡፡ የአቡነ ሳዊሮስን ትምህርታቸውን የሰማ መ_ና_ፍ_ቅ በውስጡ ያደረበት የጥርጥር መንፈስ መድረሻ ያጣል፡፡ አቡነ ሳዊሮስ በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ቤተ ክርስቲያንን እንደፋና አብርተውላት በዓለም መድረክ አንድ አድርገዋታል፡፡
አቡነ ሳዊሮስ በቀናው ተጋድሎአቸው ቤተ ክርስቲያንንና ምእመናንን ከመ-ና-ፍ-ቃን ተኩላዎች በመጠበቅ ሲተጉ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደጉና አማኙ ንጉሥ ሞቶ በእርሱ ፈንታ ስሙ ዮስጥያኖስ የሚባል መ_ና-ፍ_ቅ ነገሠ፡፡ ይህም ከሃዲ ንጉሥ ዮስጥያኖስ ‹‹በውሾቸ ጉባኤ›› የተወሰነውን የኬልቄዶንን ሃይማኖት የሚያምን መ_ና_ፍ_ቅ ከሃዲ ነው፡፡ ንግሥቲቱ ሚስቱ ቴዎድራ ግን ሃይማኖቷ የቀና ምግባሯ ያማረ ነው፡፡ አቡነ ሳዊሮስ በጣም ትወዳቸውና ታከብራቸው ነበር፡፡ ይህም ከሃዲ ንጉሥ አቡነ ሳዊሮስን ወደ ረከሰች ሃይማኖቱ ያስገባቸው ዘንድ ግድ አላቸው፡፡ በብዙ ማስፋራራትና ቁጣ ሊያስገድዳቸው ቢሞክርም አቡነ ሳዊሮስ ግን ቁጣውንና ማስፈራራቱን አልፈሩም፡፡ ንጉሡም አስገድዶ ወደ ረከሰች ሃይማኖቱ ሊያስገባቸው እንዳልቻለ ባየ ጊዜ አቡነ ሳዊሮስን በስውር ሊገድላቸው ፈለገ፡፡ ንግሥቲቱም ከሃዲው ንጉሡ ባሏ አቡነ ሳዊሮስን በሥውር ሊገድላቸው እንደሆነ ስትሰማ አባን ከአንጾኪያ አገር ወጥተው በመሄድ ራሳቸውን እንዲያድኑ ነገረቻቸው፡፡ አቡነ ሳዊሮስ ግን መሸሽ አልፈለጉምና ‹‹ክብር ይግባውና ስለ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ለመሞት የተዘጋጀሁ ነኝ›› ብለው ለንግሥቲቱ መለሱላት፡፡ ነገር ግን ብዙ ምእመናንና ንግሥቲቱ አጥብቀው ስለለመኗቸው ጻደቁ ወጥተው ወደ ግብፅ አገር ተሰደዱ፡፡ ከምእመናንም አብረዋቸው የተሰደዱ አሉ፡፡
ከሃዲውም ንጉሥ አቡነ ሳዊሮስን በስውር ሊገድላቸው አስቦ ይዘው እንዲያመጧቸው ወታደሮቹን ላካቸው ነገር ግን አላገኟቸውም፡፡ አቡነ ሳዊሮስን ጌታችን ስለሰወራቸው የንጉሡ ጭፍሮች ሊያገኟቸው አልቻሉም፡፡ እሳቸው በጭፍሮቹ አጠገብ እየተጓዙ ጭፍሮቹ ግን አያዩአቸውም ነበር፡፡ ጭፍሮቹም በፍለጋ ሲጓዙ ከአቡነ ሳዊሮስ ጋር በአንድ ቦታ የሚያድሩበት ጊዜም አለ ነገር ፈጽሞ አላዩአቸውም፡፡ እግዚአብሔር አቡነ ሳዊሮስን ለምእመናን ጥቅም ሲል አሁን እንዲሞቱ አልፈቀደም ነበርና ጭፍሮቹም ፈልገው ባጧቸው ጊዜ ወደ ንጉሣቸው ተመልሰው ሄዱ፡፡
አቡነ ሳዊሮስም ግብፅ አገር ከደረሱ በኋላ ከአንደኛው ገዳም ወደ አንደኛው ገዳም አንድ ተራ መነኩሴ መስለው በስውር የሚዘዋወሩ ሆኑ፡፡ በየሄዱበትም በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ምእመናንን የሚያጠነክሩ ሆኑ፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ድንቅ ድንቅ የሆኑ ብዙ ተአምራትን አደረገ፡፡ በአንዲት ዕለት አባታችን ወደ አስቄጥስ ገዳም በደረሱ ጊዜ በመጻተኛ መነኩሴ አምሳል ወደ አቡነ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን ገቡ፡፡ በዚያም ቄሱ ዕጣንንና ቁርባንን ሊያሳርግ ጀመረና እንደ ሥርዓቱ እየዞረ አጠነ፡፡ ሐዋርያት የጻፏቸውን ቅዱሳት መጻሕፍትና መልዕክቶቻውን የከበረ ወንጌልንም ካነበቡ በኋላ ቄሱ እጆቹን ታጥቦ ማኅፈዱን በገለጠው ጊዜ በጻሕሉ ውስጥ የቁርባኑን ኅብስት አላገኘውም፡፡ ደንግጦም መሪር ልቅሶን አለቀሰ፡፡ ከዚያም ወደ ሕዝቡ ተመልሶ ‹‹ወንድሞቼ እነሆ የቁርባኑ ኅብስት ተሰውሮ በጻሕሉ ውስጥ አላገኘሁትምና ይህ የሆነው በእኔ ኃጢአት ወይም በእናንተ ኃጢአት እንደሆነ ዐላወቅሁም›› አላቸው፡፡ ያንጊዜም የእግዚአብሔር መልአክ ለቄሱ ተልጦለት ‹‹ይህ የሆነው በአንተ ኃጢአት ወይም በሕዝቡ ኃጢአት አይደለም ነገር ግን ሊቀ ጳጳሳት አባ ሳዊሮስ እያለ መሥዋዕትን ለማሳረግ በመድፈርህ ነው›› አለው፡፡
ቄሱም በጣም ደንግጦ መልአኩን ‹‹ጌታዬ ሆይ! ሊቀ ጳጳሳት መኖሩን ዐላወቅሁም›› አለው፡፡ መልአኩም ተራ የመነኩሴ ልብስ ለብሰው ወደቆሙት ወደ አባ ሳዊሮስ አመለከተው፡፡ ቄሱም ወደ አቡነ ሳዊሮስ ሄዶ ከእግራቸው በታች ሰገደና ቡራኬ ተቀበለ፡፡ አባታችንም የጀመረውን ቅዳሴውን እንዲፈጽም ቄሱን አዘዙት፡፡ እርሳቸውንም በታላቅ ክብር ወደ ቤተ መቅደሱ አስገቧቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ቄሱ ወደ መሠዊያው በወጣ ጊዜ ተሰውሮበት የነበረውን የቁርባኑን ኅብስት በጻሕሉ ውስጥ መልሶ አገኘው፡፡ በዚህም ካህናቱና ሕዝቡም ሁሉ ምስጉን የሆነ ልዑል እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡
የቁርባኑም ሥርዓት ከተፈጸመ በኋላ ካህናቱና ሕዝቡ ከአቡነ ሳዊሮስ ቡራኬ ተቀበሉ፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ አባታችን አቡነ ሳዊሮስ ከአንደኛው ገዳም ወደ አንደኛው ገዳም አንድ ተራ መነኩሴ መስለው በስውር እየተዘዋወሩ በየሄዱበትም ምእመናንን እያጠነከሩ በእጆቻቸውም ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ሲያገለግሉ ኖሩ፡፡ በመጨረሻም ስካ ወደሚባል አገር ሄደው ስሙ ዶራታዎስ ከሚባል ደግ ምእመን ባለጸጋ ሰው ዘንድ ተቀምጠው ሳለ ጌታችን በእጆቻቸው ብዙ አስገራሚ ተአምራትን አደረገ፡፡ በመጨረሻም በዚህች ስካ በምትባል አገር የካቲት 14 ቀን እስካረፉ ድረስ በቀናች ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ሁሉንም አስተማሯቸው፡፡ በኋላም ታኅሣሥ 10 ቀን ምእመናን ቅዱስ ሥጋቸውን ዝጋግ ወደምትባል ገዳም አፍልሰውታል፡፡ ጥቅምት 2 ቀን ደግሞ አባታችን ተሰደው ወደ ግብፅ አገር የመጡበት ዕለት ነው፡፡ ከእስክንድርያ ውጭ ወደሆነቸ ደብረ ዝጋግ ገዳም ቅዱስ ሥጋቸው በፈለሰበት ወቅት እንዲህ ሆነ፡- ቅዱስ ሳዊሮስ ስሓ በምትባል አገር አምላክም በሚወድ ደገኛ ክርስቲያን ባለጸጋ ስሙ ዱራታዎስ በሚባል ሰው ዘንድ ባረፉ ጊዜ ከምእመናን ሰዎች ጋር ወደ በመርከብ አሳፍሮ ላከው፡፡ ወደ ደቡባዊ ባሕረ ቅርጣስ በደረሱ ጊዜ ግን መርከባቸውን ማንቀሳስ ፈጽሞ አልተቻላቸውም፡፡
ከዚያም ወደ ደብረ ዝጋግ አድርሰው ያ ባለጸጋ ዱራታዎስ በሠራለት ቦታ ውስጥ አኖሩት፡፡ በግብጽ አገርም ታላቅ ደስታ ሆነ፡፡ እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራቶችን ከሥጋቸው ገለጠ፡፡ ቅዱሱ በሕይወት ሳሉ የወለቀች አንዲት ጥርሳቸውን አንዱ መነኮስ አግኝቶ በጨርቅ ጠቅልሎ በገዳሙ አስቀምጧት ነበርና እርሷም ለሕሙማን ሁሉ ፈውስን የምትሰጥ ሆነች፡፡ እነርሱም ወደ እስክንድርያ ያመጧትና በሕሙማን ላይ ሲያኖሯት ሕሙማኑ ፈጥነው ይድናሉ፡፡ እግዚአብሔርም ቅዱስ ሳዊሮስን በሕይወታቸው ካሉበት ጊዜ ይልቅ በሞት ካረፉ በኋላ እጅግ ከፍ ከፍ አድርጓቸዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን።
(የዕረፍታቸውን ዕለት የካቲት 14 ን ይመልከቱ )

🔥 አቡነ ሕርያቆስ

ሕርያቆስ ማለት ‹‹ኅሩይ-የተመረጠ›› ማለት ነው፡፡ እንዲሁም ደግሞ ምሥጢረ ሥላሴን ከሁሉ ይልቅ አራቆ ይናገራልና አባቶቻን ሕርያቆስ ማለት ‹‹ረቂቅ›› ማለት ነው ይሉታል፡፡ ‹‹አብ ፀሐይ ወልድ ፀሐይ መንፈስ ቅዱስ ፀሐይ›› ብሎ አመስግኗልና አሁንም ሕርያቆስ ማለት ‹‹ፀሐይ›› ማለት ነው ይሉታል፡፡ ደግሞም የምእመናንን ልቡና በትምህርቱ ብሩህ አድርጓልና ሕርያቆስ ማለት ‹‹ብርሃን›› ማለት ነው፡፡ አንድም ደግሞ ሕርያቆስ ማለት ‹‹ንብ›› ማለት ነው፡፡ ንብ የማትቀምሰው አበባ እንደሌለ ሁሉ ሕርያቆስም ያልቀሰመው ሰማያዊ ዕውቀት የለምና እርሱን የማይጠቅሰው ሊቅ የለም፡፡
አባ ሕርያቆስ ስለ ምሥጢረ ሥላሴ እና ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ የሚያመሰጥረውን እመቤታችንን በተለያዩ ምሳሌያት እየመሰለ የሚያመሰግንበትን ድንቅ የሆነውን ድርሰቱን ‹‹ቅዳሴ ማርያምን›› ሰማያዊ ምሥጢር ወለል ብሎ ተከፍቶለት ደርሶታል፡፡ የብሕንሳው ኤዺስቆዾስ ስላረፉ በእሳቸው ምትክ የሚሾሙትን ሲያፈላልጉ መንፈስ ቅዱስ አባ ሕርያቆስን መረጣቸው፡፡ የከበሩ ሐዋርያት ‹‹የተማረና ግብረ ገብ የሆነ ይሾም›› ብለው ሥርዓት ሠርተዋል፡፡ ደግሞም ‹‹ሁለቱን አስተባብሮ የያዘ ባይገኝ የተማረ ከሆነ ይሾም›› ብለዋል፡፡ ምክንያቱም በትምህርቱ መናፍቃንን ተከራክሮ ይመልሳልና ነው፡፡ ደግሞም ‹‹ግብረ ገብም ከሆነ ይሾም›› ብለዋል፡፡ ምክንያቱም በጸሎቱ ይጠብቃል በትሩፋቱ ያጸድቃልና ነው፡፡ በዚህም መሠረት አባ ሕርያቆስ ያልተማረ ነገር ግን ግብረ ገብ ነውና ‹‹ትምህርቱን ውሎ አድሮ ያደርገዋል›› ብለው ሾሙት፡፡ አባ ሕርያቆስም የተማረው ለጸሎት ለቅዳሴ ያህል ትንሽ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ይህ ቅዱስ አባት በብሕንሳ ገዳም በ10000 መነኮሳት እና በ10000 መነኮሳይያት ላይ ተሹሞ የገዳሙ አስተዳዳሪ ሆነ፡፡
አባ ሕርያቆስ እመቤታችንን እጅግ ከመውደዱ የተነሣ ስሟን እንኳን ሲጠራ በመስጦ ልቡናው ይሰወርበት ነበር፡፡ ዘወትር ፍቅሯ ከማሰብ በቀር ሌላም አያስብም ነበር፡፡ እርሱ የነበረበት ዘመን የሊቃውንት ዘመን ስለነበር ሁሉም ለትምህርት ሲተጉ አባ ሕርያቆስ ግን ለጸሎትና ለደግነት ብቻ ይተጋ ነበር፡፡ የአባ ሕርያቆስ የሌት ተቀን ሞኞቱ ‹‹እንደ ቅዱስ ኤፍሬም የእመቤታችን ምስጋና እንደ ባሕር አሸዋ እንደ ሰማይ ኮከብ በዝቶልኝ እንደልብስ ለብሼም እንደ ምግብ ተመግቤው›› የሚል ነበር፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮም እጅግ ስለሚወዳት እመቤታችንም ትጠብቀው ነበር፡፡ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባ ሕርያቆስ በበረኃ ብቻውን እየተጓዘ ሳለ የእመቤታችንን ፍቅር በልቡ ሲያመላልስ ስሟን እያነሣ ሲዘምር በተመሥጦ ውስጥ ሆኖ መንገድ ሳተና ከታላቅ ገደል ጫፍ ደርሶ ሳያስበው ወደቀ፡፡ ከገደሉም ጫፍ ደርሶ ከወደቀ በኋላ እጅግ ደንግጦ ራሱን ቢመለከት አካሉ ሳይጎድል ልብሱ ሳይቆሽሽ አገኘው፡፡ በዚህም ተገርሞ ያለበትን አካባቢውን ቢያማትር ራሱን ብርሃንን በተሞላ የልብስ ዘርፍ ላይ አገኘው፡፡ ያም ብርሃንን የተሞላ የልብስ ዘርፍ የእመቤታችን የቀሚሷ ዘርፍ ነው፡፡ በዚህም እጅግ ደንግጦ ‹‹እመ ብርሃን›› ብሎ ጮኸ፡፡ እመቤታችንም ከፊቱ ቁማ ተገለጠችለት፡፡ እርሱም የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክን በገሃድ በዐይኑ አጠገቡ ቆማ ቢያያት በደስታ ዘለለ፡፡ እመቤታችንም በቃሏ አነጋግራው ባርካው ተሰወረችው፡፡ እርሱም ፍቅሯ ጣዕሟ ቢመስጠው ከሰው ሳይገናኝ ምግብም ሳይበላ እዚያው እገደሉ ውስጥ አንድ ዓመት በምስጋና ብቻ በተመስጦ ኖሯል፡፡ በኋላም እመቤታችን ድጋሚ ተገልጣለት ከገደሉ አውጥታ ወደ ሀገሩ አድርሳዋለች፡፡
ከዚህም በኋላ አባ ሕርያቆስ እርሱ በተሾመባ በብሕንሳ ገዳም ሴትና ወንድ ያልተለየባት ገዳም ነበረችና በዚህች ገዳም የተሾመው አባ ሕርያቆስ ብዙም ትምህርት ስላልነበረው ይንቁት ነበር፡፡ ‹‹ከመጠምጠም መማር ይቅደም›› እንዲሉ ‹‹ከመሾም በፊት መማር አይቀድምም›› እያሉም ይዘብቱበት ነበር፡፡ እርሱ ግን እንደጠሉኝ ልጥላቸው ሳይል በፍቅር በትሕትና ይመክራቸው ነበር፡፡ እነርሱ ግን ‹‹በምን ምክንያት እንሻረው›› እያሉ ይመክሩ ነበር፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ‹‹ቀድሰህ አቁርበን እንበለውና አይሆንም ካለን በዚህ ምክንያት እንሻረው?›› ብለው መከሩ፡፡ እርሱም ሥርዓተ ቅዳሴውን ፈጽሞ ወደፍሬ ቅዳሴው ሲደርስ የትኛውን ከባድ ቅዳሴ ቀድስ እንበለው?›› እያሉ ይመካከሩ ጀመር፡፡ እርሱ ግን ከቅዳሴ ሐዋርያት በቀር የሚያውቀው አልነበረም፡፡ አባ ሕርያቆስ እያዘነ ወደ መንበሩ ሲዞር ዞሮ ‹‹እመቤቴ ሆይ! መናቄን መገፋቴን ተመልከች›› ሲል ወዲያው እመቤታችን ወርዳ ጠራችውና በዘርፋፋው ቀሚሷ ላይ ረቂቅ የሆነ ቅዳሴን አሳየችው፡፡ የለመኗትን የማትነሣ፣ የነገሯትን የማትረሣ የብርሃን እናቱ እመቤታችንም የልቡን መሻት ተመልክታ ‹‹ጎስዐ ልብየ ቃለ ሠናየ ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ›› በማለት ጀምሮ ‹‹ዛሬም አብን ወልድንና መንፈስ ቅዱስን እናመስግን›› እስከሚለው ድረስ ሰተት አድርጋ አስደርሳዋለች፡፡ እነርሱም ይህንን ግሩም የሆነውን ቅዳሴውን አደነቁ፡፡
የሚንቁትና የሚጠሉት ‹‹ይህ የነገሩትን ቀለም እንኳን አከናውኖ መናገር የማይችል ዛሬስ እንግዳ ድርሰት እደርሳለው ብሎ አገኝ አጣውን የቆጥ የባጡን ይቀባጥራል›› ብለው ተደነቁበት፡፡ የሚወዱትና የሚያከብሩት ግን ‹‹ከመንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እንዲህ ያለ ምሥጢር ከእሩቅ ብዕሲ ይገኛልን!›› ብለው አደነቁለት፡፡ ወዲያው የሚወዱት የሚያከብሩት ‹‹ጽፈን ደጉሰን አንይዘውምን!?›› አሉ፡፡ የሚንቁት የሚጠሉት ደግሞ ‹‹ማን ተናገረው ብለን እንይዘዋለን?›› አሉ፡፡ እንደ ልማዱ አድርገን አንይዘውም አሉ፡፡ ለሃገራቸው እንግዳ ድርሰት የተደረሰ እንደሆነ ጽፈው ደጉሰው ከእሳት ይጥሉታል፡፡ ከእሳት ደህና ሆኖ የወጣ እንደሆነ ከውሃ ይጥሉታል፡፡ ከውኃም ደህና ሆኖ የወጣ እንደሆነ ከድውይ ሰው ላይ ይጥሉታል፡፡ ከእሳት ገብቶ ባይቃጠል፣ ከውኃ ገብቶ ባይርስ በመጨረሻም ድውይ የፈወሰ እንደሆነ ‹‹ደገኛ ድርሰት ነው›› ብለው ይይዙታል፡፡ ይህንንም ቅዳሴ ማርያምን ጽፈው ደጉሰው ከእሳት ላይ ጣሉት፣ ከእሳት ደህና ወጣ፡፡ ከውኃ ላይ ጣሉት-ከውኃ ደህና ሆኖ ወጣ፡፡ ከደውያን ላይ ጣሉት-ድውይ ፈወሰ፡፡ ይልቁንም ሙት አስነሣ፡፡ ከዚህም በኋላ ‹‹ደገኛ ድርሰት ነው›› ብለው ጽፈው ደጉሰው ይዘውታል፡፡ በጥራዝም 14ኛ አድርገው ጠርዘውታል፡፡ ቅዳሴ ከዚያ በፊት 13 ነበርና አሁን ግን 14ኛ አድርገው ጽፈውታል፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ከ14ቱም ቅዳሴ ተአምራት ያልተደረገበት የለም፡፡
ይህም ቅዳሴ ማርያም ስለ እመቤታችን እጅግ በጠለቀ ሁኔታ የሚያመሰጥር በመሆኑ በሰሙነ ፍልሰታ ይተረጎማል፡፡ ዕለቱን የሚመለከቱ ምሥጢራትም በዕለቱ ይተረጎማሉ፡፡ ምሳሌ ነሐሴ ሦስት የበዓታና፣ ነሐሴ ሰባት የፅንሰታ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የበዓታ ‹‹ድንግል ሆይ! አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ልጆች በጨዋታ ያደግሽ አይደለሽም፡፡ በቅድስና፣ በንጽሕና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ…›› የሚለውን ይመለከቷል፡፡ ነሐሴ ሰባትም ‹‹ድንግል ሆይ! ኃጢአት በሆነ ሩካቤ የተፀነስሽ አይደለሽም….›› የሚለውን ይመለከቷል፡፡
አባ ሕርያቆስ የእመቤታችንን ቅዳሴ እጅግ ድንቅ አድርጎ ለመጀመሪያ ጊዜ የቀደሰው በልደቷ ቀን ነው፡፡ ይኸውስ እንዴት ታወቀ ቢሉ አንድ ምግባር ሃይማኖቱ የቀና በትሩፋት የበለጸገ ደገኛ ባሕታዊ ነበርና ከተጋድሎውና ለእመቤታችን ካለው ፍቅር የተነሣሳ እመቤታችን ተገለጠችለት፡፡ እርሱም ‹‹ከ33ቱ በዓላት ማንን ትወጃለሽ?›› ብሎ ጠየቃት፡፡ እመቤታችንም ‹‹ኪዳነ ምሕረትን፣ ልደታን፣ አስተርአዮን፣ ፍልሰታን›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ከእነዚ ከ4ቱስ ማንን ትወጃለሽ?›› ቢላት እመቤታችን ‹‹ከጠባብ ወደ ሰፊ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን የወጣሁበት ነውና ልደቴን እወዳለው›› አለችው፡፡ ‹‹ቀድሞ እኔ ሳልወለድ እናትና አባቴን መባችሁን አንቀበልም ብለው አዝነው ተክዘው ነበር፡፡ የእነርሱ ሃዘን ሃዘኔ ነውና እኔን ከወለዱ በኋላ መባቸውን ተቀብለዋቸው ደስ ብሎዋቸዋል፡፡ የእነርሱ ደስታ ደስታዬ ነውና›› ብላዋለች፡፡
ይህንን ድንቅ የሆነውን የአባ ሕርያቆስን ቅዳሴ እመቤታችን ለሌላኛው ወዳጇ ለኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ገልጣለታለች፡፡ እመቤታችን ቅዱስ ኤፍሬምን ከሶርያ፣ አባ ሕርያቆስን ከብሕንሳ በደመና ጠቅሳ ቅዱስ ያሬድ ካለበት አድርሳ ‹‹አንተ ውዳሴዬን፣ አንተ ቅዳሴዬን ነግራችሁት በዜማ ያድርስ›› ብላቸው እነርሱም ለቅዱስ ያሬድ ነግረውት በዜማ አድርሶታል፡፡ ከዚሁም ጋር አያይዞ 13ቱንም ቅዳሴ በዜማ ደርሷል፡፡
በእመቤታችን በዓሏ ዕለት ጌታችን ተገልጦላቸው ቅዳሴዋን እንዲቀድሱ ነግሯቸው ለዚህም የሚሆን ከሰማይ ኅብስትና ጽዋ አውርዶላቸዋል፡፡ በዕለቱም ቅዳሴዋን ሲቀድሱ የከበሩ ሐዋርያት በቀኝ በግራ እየተራዷቸው ሲቀድሱ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ ኅብስቱንና ጽዋውን ጋርዶታል፡፡ በሌላ ጊዜም አቡነ ሳሙኤል ጊዜአቸው ደርሶ ከማረፉ በፊት ቅዱስ ሚካኤል ነሐሴ 16 ቀን ወደ ገነት ነጥቆ ወስዶ ከእመቤታችን ፊት አቁሞ አስባርኳቸዋል፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን የእመቤታችንን ቅዳሴዋን ሲቀድሱ ከምድር ከፍ ብለው ይታዩ ነበር፡፡ የዋልድባው አቡነ ሳሙኤል ቅዳሴ ማርያምን እየደገሙ ሲሄዱ ክንድ ከስንዝር ከመሬት ከፍ ይሉ ብለው ይሄዱ ነበር፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ዕለት ውኃውን ቢባርኩት ውኃው ኅብስት ሆኖላቸው ተመግበው ምእመናንንም መግበዋቸዋል፡፡ እመቤታችንም የፍቅር ምልክት ሁለት ንዋያት ከጠቻቸው በኋላ ‹‹ውዳሴዬን ከቅዳሴዬ ጋራ አንድ አድርጎ የሚደግመውን ሰው አንተ ከገባህበት ውሳጤ መንጦላዕት አገባዋለው›› ብላ ተስፋቸውን ነግራዋለች፡፡ ይህንንም መሠረት ነማድረግ ልጆቻው ዛሬ በዋልድባ ያጠና በቃሉ፣ ያላጠና በመጽሃፍ ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን ሳይደግም የሚውል የለም፡፡ ይህም ተስፋ ውዳሴዋን ከቅዳሴዋ ጋር አንድ አድርጎ ለሚደግም ሰው ሁሉ ነው እንጂ ለእነርሱ ብቻ አይደለም፡፡ ዳግመኛም ሃይማኖት ምግባሩ የቀና ያ ደገኛ ባሕታዊ እመቤታችንን ‹‹ከምስጋናሽ ሁሉ ማንን ትወጃለሽ?›› ብሎ ቢጠይቃት እርሷም ‹‹ልጄ ዳዊትን፣ አቡነ ዘበሰማያትን ቢደግሙለት እንዲወድ እኔም ውዳሴዬን ቅዳሴዬን ቢደግሙልኝ ወዳለሁ›› ብላዋለች፡፡
አባ ሕርያቆስ የብርሃን እናቱ እመቤታችን ድንቅ ምሥጢርን ከገለጠችለትና ከባረከችው በኋላ በዘመኑ ቁጥር አንድ ሊቅ ሆኖ እጅግ ብዙ ድርሳናትን ደርሷል፡፡ ቁጥራቸው እጅግ የበዙ ተግሣጻትን ጽፏል፡፡ አጠቃላይ ድርሰቶቹ ከ10 ሺህ በላይ ናቸው፡፡ በእንዲህ ያለ ንጽሕናና ቅድስና ሲያገለግል ኖሮ ጥቅምት 2 በሰላም ዐርፏል፡፡ ልደቱም በዚሁ ዕለት ነው፡፡
የአባ ሕርያቆስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን።

ምንጭ፦ የጥቅምት ❷ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃 🍃🍃🍃 🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ -https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔹https://www.facebook.com/MeseleNigatuDek0

🔸https://www.facebook.com/Mesele.Nigatu.Deko

ᴍᴇsᴇʟᴇ ɴɪɢᴀᴛᴜ ᴅᴇᴋᴏ
ጥቅምት ❶ ቀን 2011 ዓ.ም

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።ጥቅምት 1 ሰማዕቷ ቅድስት አንስጣስያ በዓለ ዕረፍቷ ነው፡፡ ➛ ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓሏ ነው፡፡ 🔥...
10/10/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።

ጥቅምት 1 ሰማዕቷ ቅድስት አንስጣስያ በዓለ ዕረፍቷ ነው፡፡
➛ ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓሏ ነው፡፡

🔥 ሰማዕቷ ቅድስት አንስጣስያ

ሀገሯ ሮም ሲሆን ወላጆቿ ደጋግ ክርስቲያኖች ስለነበሩ በሃይማኖትና በምግባር አሳደጓት፡፡ ስታድግ ባል ሊያጋቧት ሲሉ እርሷ ግን ሀሳቧ በምንኩስና ኖራ እግዚአብሔርን ማገልገል ስለሆነ ጠፍታ በመሄድ ተነሥታ በስውር ሮሜ አገር ካሉ ገዳማት በአንዱ ገዳም ውስጥ ገባች፡፡ በታላቅ ተጋድሎ መኖር ስትጀምር ብዙ የሰይጣን ፈተናዎች መጡባት ነገር ግን በተጋድሎ ብዛትና በጌታችን ቸርነት ሁሉንም ተወጣችው፡፡

የምትጾምበትን ቀን በማርዘም በየሁለት ቀኑ ታከፍል ጀመር፡፡ በጌታችን ጾም ግን ያለ ሰንበታት ቀን ምንም የማትቀምስ ሆነች፡፡ በእሳት የበሰለ ምግብ አትመገብም ነበር፡፡ ሴቷ የገዳሙ እመ ምኔት ቅድስት አንስጣስያንና ሌሎቹንም ደናግል አስከትላ ለንግሥ ወደ ሌላ ገዳም ስትሄድ በመንገድ ላይ የንጉሡ ዳኬዎስ ወታደሮች ክርስቲያኖችን ሰያሠቃዩ አገኟቸው፡፡ ቅድስት አንስጣስያም በዚህ እጅግ ተናዳ ወታደሮቹን በቁጣ ዘለፈቻቸው፡፡ ወታደሮቹም ይዘው ለመኰንኑ አቀረቧት፡፡ መኰንኑም ‹‹አንቺም የተሰቀለውን ክርስቶስን የምታመልኪ ነሽን?›› በማለት ጠየቃት፡፡ እርሷም ‹‹አዎ ስለ እኛ ስለ ሁላችንም ብሎ የተሰቀለውን ክብር ይግባውና እርሱን አመልከዋለሁ›› አለችው፡፡ በዚህም ጊዜ እጅግ ጽኑ ሥቃይን አሠቃያት፡፡ እሳት አስነድዶ ሥጋዋን በእሳቱ ውስጥ ጨመረው፡፡ ከእሳቱም አውጥቶ ዘቅዝቆ ሰቀላትና ከሥር በሚለበልብ ነገር እያጠነ ገረፋት፡፡ በሥቃይም ብዛት ቅድስት አንስጣስያ ከሃይማኖቷ እንዳልተናወጸች ባየ ጊዜ በመጨረሻ አንገቷን በሰይፍ ቆረጠው፡፡ እርሷም ሰማዕትነቷን በድል ፈጽማ የክብር አክሊልን ተቀዳጀች፡፡ ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣ በጸሎቷ ይማረን።

🔥ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት

በዘመነ ሐዋርያት በተመሳሳይ 'እንተ ዕፍረት-ባለ ሽቱ' ተብለው የሚጠሩ ኹለት እናቶች ነበሩ:: ኹለቱም ስማቸው ማርያም ስለነበር ለመለየት እንዲያመች አንደኛዋን 'ማርያም ኀጥእት-ከኀጢአት የተመለሰች፤ 2ኛዋን ደግሞ 'ማርያም እኅተ አልዓዛር ተብለው የሚጠሩ ኹለት የተለያዩ በዚህ ስም የሚጠሩ ቅዱሳት አንስት መኖራቸውን ሊቀ ሊቃውንት ስሙር አላምረውና ዲ/ን ዮርዳኖስ ያስተምራሉ። (ሌላ ጊዜ በዝርዝር እንመለስበታለን።)

በሉቃስ ወንጌል ላይ የምትገኘው ከኀጢአት ሕይወት የተመለሰችው ስትሆን በዮሐንስ ወንጌል 12:1 ላይ ያለችው የአልዓዛር እኅት (ድንግሊቱ) ናት። በዚኽችም ዕለት የምናስባት ይኽቺን ቅድስት ነው። እርሷም በቢታንያ አካባቢ ትኖር የነበረች ድንግል ወጣት ናት።

ጌታችንን በቤታቸው ተገኝቶ ሳለ እኅቷ ማርታ ለአገልግሎት ስትደክም ማርያም ግን ከእግሩ ሥር ተቀምጣ ቅዱስ ቃሉን በመስማቷ ጌታችን ‹‹ማርያምስ የማይቀሟትን መልካም ዕድል መረጠች›› በማለት መስክሮላታል፡፡ ሉቃ 10፡38-42፡፡ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስትም ወገን ደምሯታል፡፡ ማቴ 26፡6፡፡ አልዓዛርን ከ72ቱ አርድእት፣ ማርያምና ማርታን ደግሞ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ቆጥሯቸዋል።

እኅቷ ማርታ ደግሞ የምትኖረው ከኢየሩሳሌም 3 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው በቢታንያ መንደር ነው፡፡ ጌታችንም ወደ ኢየሩሳሌም ሲወጣና ሲገባ በቤቷ ያርፍ ነበር፡፡ እርሷም በሚገባ ታስተናግደው ነበር፡፡ እንዴት የታደለች ናት!!! ጌታችን ከሞት ያስነሣው ወንድማቸው አልዓዛር ደግሞ ጌታችን ይወደው የነበረ የቢታንያ ሰው ነው፡፡ አልዓዛርና እኅቶቹ ጌታችን ካረገ በኋላ በቀድሞው መኖሪያቸው እንግዶችን እየተቀበሉ ቤታቸውንም የወንጌል መማሪያ አድርገው ተቀምጠው ነበር፡፡ ነገር ግን ክፉዎች አይሁድ በክርስቲያኖች ላይ ስደት በማስነሣታቸው በ35 ዓ.ም ላይ አልዓዛርንና ሁለቱን እኅቶቹን በቀዳዳ መርከብ ጭነው ወደ ባሕር ጣሏቸው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ሦስቱንም በተአምራት ሰጥመው ከመሞት አዳናቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ሲፕረስ ወደምትባል አገር ሄደው ኑሮአቸውን በዚያ ከመሠረቱ በኋላ አልዓዛር የመጀመሪያው የኪትዮን (ፈረንሳይ ውስጥ የምትገኝ ከተማ) ሊቀ ጳጳስ በመሆን እኅቶቹም እንደቀድሞው እያገለገሉ ክርስትናን ማስፋፋታቸውን ታሪካቸው ይናገራል፡፡

የቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣ በጸሎቷ ይማረን።

ምንጭ፦ የጥቅምት ➊ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃 🍃🍃🍃 🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።መስከረም 30 የደብረ ክሳሄው አቡነ አብሳዲ ዕረፍታቸው ነው። ➛ ራሱን እብድ አድርጎ በስውር ይኖር የነበረው አባ ሣሉሲ ዕረፍቱ...
09/10/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።
መስከረም 30 የደብረ ክሳሄው አቡነ አብሳዲ ዕረፍታቸው ነው።
➛ ራሱን እብድ አድርጎ በስውር ይኖር የነበረው አባ ሣሉሲ ዕረፍቱ ነው፡፡
➛ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ በአትናቴዎስ ላይ ታላቅ ተአምር ያደረገለት ዕለት ነው፡፡

🔥 አባ ሣሉሲ

ይኸውም ቅዱስ ራሱን እብድ አድርጎ በስውር ይኖር የነበረ ነው፡፡ አባ ሣሉሲ በሰው ፊት ምንም አይጸልይም፣ አይጾምም ይልቁንም በሰው ፊት የሚመገበውን ፍሬ ያላምጣል፡፡ ይህንንም የሚያደርገው ከከንቱ ውዳሴ ለመራቅ ሲል ነው፡፡ ነገር ግን አበ ምኔቱ አባ ይስሐቅም ሥውር ሥራውን እያዩ ያደንቁ ነበር፡፡ ይህንንም ልማዱን ሊያስተውት ይፈልጉ ነበር ነገር ግን ልቡን እንዳያሳዝኑት ያስባሉ፡፡

አንድ ቀን በዓል ነበርና አበ ምኔቱ መነኮሳቱን ጠርተው "ከቁርባን በፊት እህል እንዳይቀምስ አባ ሣሉሲን ጠብቁት" ብለው አዘዟቸው፡፡ እነርሱም እየጠበቁት ሳለ አባ ሣሉሲ ግን "እንዲመገብ እፈልጋለሁና ልቀቁኝ" አላቸው፡፡ መነኮሳቱም "አንለቅህም" ብለው ግድ ባሉት ጊዜ ቆቡን ከራሱ ላይ አውልቆ "እመቤቴ ሆይ ከእነዚህ መነኮሳት እጅ አድኚኝ" ብሎ የቤተ ክርስቲያኑን ግድግዳ በቆቡ መታው፡፡ ግድግዳውም በቆቡ እንደመታው ወዲያው ተሰንጥቆለት በዚያ ወጥቶ ሄደ፡፡ አባ ሣሉሲ ወጥቶ ከሄደ በኃላ ግን የግድግዳው ግንብ ተመልሶ እንደቀድሞው ሆነ፡፡ መነኮሳቱም ይህን ድንቅ ተአምር ባዩ ጊዜ 300 ጊዜ ኪርያላይሶን እያሉ ጮኹ፡፡ እግዚኦታቸውንም በጨረሱ ጊዜ ያቺ ቆብ ወድቃ በመካከላቸው አገኟት፡፡ በእርሷም ብዙ ተአምራት እያደረጉባት በቤተ ክርስቲያን አስቀመጧት፡፡ አባ ሣሉሲም ከብዙ ወራት በኋላ በገዳሙ ባረፈበት ቦታ ሥጋው ተገልጦ ተገኘና በክብር ገንዘው ቀበሩት፡፡ ዕረፍቱም መስከረም 30 ነው፡፡
የአባ ሣሉሲ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን።

🔥 ጌታችን ለቅዱስ አትናቴዎስ ያደረገለት ታላቅ ተአምር፡-

2ኛውና ከሃዲው ቆስጠንጢኖስ በነገሠ ጊዜ የአርዮስን እምነት ተቀብሎ ቅዱስ አትናቴዎስን ከማንበሩ አሳዶ በምትኩ ከሃዲውን ጊዮርጊስን በማርቆስ መንበር ላይ ሾመው፡፡ እርሱም የረከሰች የአርዮስን እምነት ያልተቀበሉትን ሁሉ እንዲገድላቸው አዘዘው፡፡ ጊዮርጊስም ቁጥር የሌላቸው እጅግ ብዙ ክርስቲያኖችን በግፍ ገደለ፡፡
ቅዱስ አትናቴዎስም 6 ዓመት በስደት በሥቃይ ከኖረ በኋላ ወደ ቁስጥንጥንያ ሄዶ ከሃዲውን ቆስጠንጢኖስን "ወደ መንበሬ የማትመልሰኝ ከሆነ ግደለኝና ሰማዕትነቴን ፈጽምልኝ" አለው፡፡ ንጉሡም የቀናች ሃይማኖቱን ስለመለወጡ እንዳይገስጸው ፈርቶ ከአጠገቡም እንዲርቅለት በማሰብ አትናቴዎስን በረኃብ ተሠቃይቶ እንዲሞት ፈረደበት፡፡ ስለዚህም ቀዛፊ በሌለው ትንሽ መርከብ አድርጎ ያለምግብና ያለ መጠጥ በሜድትራኒያን በባሕር ላይ ጣለው፡፡ ነገር ግን ቅዱሳን መላእክት መርከቧን እየቀዘፏት አትናትቴዎስንም ሰማያዊ ምግብ እየመገቡት በ3ኛው ቀን እስክንድርያ ወደብ አደረሱት፡፡ ቅዱስ አትናትቴዎስንም ቅዱሳን መላእክት እየተራዱት በ3ኛው ቀን እስክንድርያ ወደብ እንደደረሰ ምእመናን ቸር ጠባቂያቸውና እረኛቸው ከተማቸው እንደደረሰ በሰሙ ጊዜ መብራታቸውን አብርተው እየዘመሩ በታላቅ ክብር ተቀብለው ቤተ ክርስቲያን አስገቡት፡፡
ከሃዲው ጊዮርጊስም ደንግጦ ወገኖቹን ሰብስቦ ሀገሩን ጥሎ ጠፋ፡፡ የእስክንድያ ምእምናንም ዛሬ ድረስ ያችን ዕለት ያከብሯታል፡፡ የጌታችን ቸርነቱ የቅዱስ አትናቴዎስ በረከቱ ይደርብን።

🔥 አቡነ አብሳዲ ዘደብረ ክሳሄ

አቡነ አብሳዲ አጽፋቸውን እንደጀልባ ተጠቅመው የኢያሪኮን ባሕር የተሻገሩት የታላቁ ጻድቅ የአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር ደቀ መዝሙር ናቸው፡፡ የደብረ ክሳሄው አቡነ አብሳዲ ገድላቸውን የፈጸሙት ኤርትራ ውስጥ ነው፡፡ ጻድቁ ምን ያህል ክቡር እንደሆኑ ይታወቅ ዘንድ በመጀመሪያ ስለእርሳቸው በአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር ገድል ላይ የተጻፈውን መመልከቱ እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡

ክቡር ጌታው መልአከ ምሕረት ወላዴ አእላፍ የኔታ ጥበቡ የተረጎሙትና ምዕራፈ ቅዱሳን ቅድስት ጣራ አንድነት ገዳም በ2009 ዓ.ም ያሳተመው የአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ገድለ ከገጽ
98 ጀምሮ እንደሚናገረው አባታችን ኤዎስጣቴዎስን በሐማሴን ሳሉ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲሔዱ አዘዛቸው፡፡ ዳግመኛም አቡነ ኤዎስጣቴዎስን ጌታችን በቃሉ ጠርቶ ‹‹በላይህ ላይ ያለውን ቅዱስ መንፈስ በወዳጅህ በልጅህ አብሳዲ ላይ አሳድር፣ ሙሴ የራሱን መንፈስ በነዌ ልጅ በኢያሱ ላይ እንዳሳደረ፣ ኤልያስም በረድኡ በኤልሳዕ ላይ እንዳሳደረ›› አላቸው፡፡ ምክንያቱም ልጆቻቸውን ትተው ወደ ኢየሩሳሌም ከዚያም ወደ አርማንያ እንዲሔዱ ነግሯቸዋልና ነው፡፡ አባታችንም ልጃቸውን አቡነ አብሳዲን ሦስት ጊዜ ‹‹አብሳዲ አብሳዲ አብሳዲ›› ብለው ጠሩት፡፡ እርሱም አባቱን ‹‹አቤት ጌታዬ እነሆ ጠርተኸኛልና›› አለው፡፡ አባታችን ኤዎስጣቴዎስም ‹‹እነሆ በረከት ከሰማይ ለአንተ ተሰጠች፣ ይህችንም በረከት ብርንና ወርቅን የማይወዱ ራሳቸውንም ወደ ጠባብ በር ያስገቡ እንደ አንተ ካለ ጻድቃንና ከተመረጡት በቀር
መቀበል የሚችል የለም፤ እነርሱም ሥጋቸውን አሳልፈው ለጻዕር ለጭንቅ የሰጡ ናቸው፤ ከተወለዱም ጀምሮ ጣፋጭ የሆኑ የምድር ምግቦችን ያልወደዱ ናቸው፣ ራሳቸውንም
እንደምታልፍ ነፋስ ያደረጉ ናቸው፡፡›› አባታችን ኤዎስጣቴዎስም ይህንን ተናግረው በአብሳዲ ራስ ላይ እጃቸውን ጫኑ፡፡ ሙሴ በኢያሱ እንደጫነ፣ ያዕቆብም በይሁዳና በሌዊ ላይ እጁን ጭኖ ለመንግሥትና ለክህነት እንደባረካቸው ዮሴፍም ልጆቹን ኤፍሬምና ምናሴን ይባርካቸው ዘንድ ወደ አባቱ እስራኤል አምጥቷቸው እርሱም የተባረከና ቅዱስ ሕዝብ ያድርጋችሁ ብሎ እንደባረካቸው እንደዚሁም ሁሉ አባታችን ኤዎስጣቴዎስ ልጃቸውን አብሳዲን እንዲህ እያሉ ባረኩት፡- ‹‹የቀደሙ አባቶች በረከት፣ የነቢያትና የሐዋርያት በረከት፣ ድል የሚነሡ የሰማዕታት በረከትና በተጋድሎ የጸኑ የጻድቃን በረከት፣ የቅዱሳን መላእክት በረከት፣ ማኅበረ በኩር የተባሉ የሁሉም ቅዱሳን በረከት፣ አምላክን የወለደች የቅድስት ድንግል ማርያም በረከት፣ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ በረከት በአንተ ላይና በልጆችህ ላይ ይደር፤ መታሰቢያዬንና መታሰቢያህንም በሚያደርጉ ላይ ይደር ለዘለዓለሙ አሜን›› ብለው መባረክን ከባረኩት በኋላ አብሳዲን ግንባሩን ቀብተው አተሙት፡፡

አቡነ አብሳዲ ገዳማትንና ምንኵስናን ለማስፋፋት ብዙ የደከሙ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ቀንና ሌሊት ሳያርፉ ምእመናን በማስተማር አባታቸው ኤዎስጣቴዎስ እንዳስተማሯቸው
ገዳማትንና ምንኵስናን በኤርትራና በኢትዮጵያ በማስፋፋት ለገዳማዊ ምናኔ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረጉ ሐዋርያ ናችው፡፡ በመንፈስ የወለዷቸው በርካታ መነኵሳት ልጆቻቸው አማካኝነት በኢትዮጵያና በኤርትራ የተገደሙት ገዳማት ከ120 በላይ ናቸው፡፡

በልጆቻቸው አማካኝነት በኤርትራ ከተገደሙት ገዳማት ውስጥ፦ ደብረ ኮል አቡነ ብሩክ (መራጉዝ)፣ የአቡነ ዮናስ ገዳማት (ደብረ ድኹኻን ቆሓይን፣ ደብረ ጽጌ ትምዛእ፣ ደብረ
ሣህል ዛይዶኮሎም)፣ ደብረ አቡነ ሙሴ (ማይ ጎርዞ)፣ ደብረ ሲና አቡነ ድምያኖስ፣ ምድሪ ወዲ ሰበራ፣ ደብረ ሐዋርያት አቡነ ሴት (ዓዲ ቂታ)፣ ደብረ ማርያም (ዓይላ) እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ እነኚህን እንደ ምሳሌ ጠቀስን እንጂ በኢትዮጵያም የአቡነ አብሳዲ ልጆች የመሠረቷቸው በርካታ ገዳማት አሉ፡፡ ለዚኽም ነው ታላቁ ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በሰዓታት ድርሰታቸው እንዲህ ሲሉ ያወደሷቸው፦
ሰአል ለነ አብሳዲ አበ ብዙኃን
ወላዲ አእላፍ መምህራን
በደብረ ማርያም መካን፡፡

አባታችን የረጅም ዘመን ተጋድሏቸውን በፈጸሙ ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኹለተኛ ጊዜ ተገልጦላቸው ‹‹…በሰሜን ያለች ይኽችን ገዳም ባርኬልሃለውና ከልጆችህ ጋር በእርሷ
ኑር›› ካላቸው በኋላ ቃልኪዳን ገብቶላቸው ተሰወረ፡፡ ቀደም ብለን እንደጠቀስነው ይኽችም ለአባታችን የተሰጠቻቸው ገዳም ማርያም ደብረ ክሳሄ ናት፡፡

ከዚኸም በኋለ ቅዱስ አባታችን አብሳዲ ደከመኝ ልረፍ ሳይሉ መላ ዘመናቸውን ሐዋርያዊ ተልዕኳቸውን ፈጽመው ከእግዚአብሔርም ቃል ኪዳን ተቀብለው በ101 ዓመታቸው መስከረም 30 ቀን 1383 ዓ.ም ዐርፈው ቆሓይን በምትገኘው ገዳማቸው ደብረ ክሳሄ ደብረ ማርያም ገዳም ተቀበሩ፡፡ ከእርሳቸውም በኋላ አቡነ ዘካርያስ፣ አቡነ ሮማኖስ (ግብጻዊ) እና አቡነ ተወልደ መኅህን እንዲሁም ሌሎች ልጆቻቸው የገዳማቸውን ማኅበር በመምራት ሐዋርያዊ ተልዕኳቸውን ፈጽመዋል፡፡

የአቡነ አብሳዲ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡

ምንጭ፦ የመስከረም ❸⓪ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃 🍃🍃🍃 🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔹https://www.facebook.com/MeseleNigatuDek0
መስከረም ❷❾ ቀን 2011 ዓ.ም

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። "ከናፍረ ጻድቃን ያረትዓ ስምዐ፤ ወሰማዕት ጕጉእ ቦ ልሳን እኩይ፦ የጻድቃን ከንፈሮች ምስክርነትን ያቀናሉ፤ የሚቸኩል ምስክር ግን ክፉ...
08/10/2025

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

"ከናፍረ ጻድቃን ያረትዓ ስምዐ፤ ወሰማዕት ጕጉእ ቦ ልሳን እኩይ፦ የጻድቃን ከንፈሮች ምስክርነትን ያቀናሉ፤ የሚቸኩል ምስክር ግን ክፉ አንደበት አለው።"

ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ላለፉት ተከታታይ ዓመታት ወደ ሰሜን አሜሪካ በማምራት የሕክምና ክትትል ሲያደርጉ መቆየታቸው የሚታወቅ ሲሆን በቅርቡም ተመሳሳይ ጉዞ አድርገው ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓመተ ምሕረት ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ በታላቅ ክብር መመለሳቸው ይታወሳል።

ይህንንም ተከትሎ ርእሰ ዐውደ ዓመትን በማስመልከት ለመላው ኢትዮጵያውያን የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው አባታዊ ቃለ በረከትና ቡራኬ በመገናኛ ብዙኃን አስተላልፈዋል፤ የመስቀል ደመራ በዓልንም በመስቀል አደባባይ ተገኝተው በማክበር ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን አባታዊ ትምህርተ ወንጌል፣ ቃለ ምእዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል፤ ቤተ ክርስቲያናችን በየዕለቱ የምታከናውናቸው መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ እና ዓለም አቀፍ ተግባራትንም በጽሕፈት ቤታቸው ሆነው በአባትነት እየመሩ በተሟላ ጤንነት ላይ ይገኛሉ።

ይሁን እንጂ ድብቅ አጀንዳ ይዘው ሐሰተኛ መረጃን በማሰራጨት መደበኛውን የቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ ማደናቀፍ ዓላማቸው ያደረጉ አካላት በማኅበራዊ የትስስር ገጾቻቸው ባጋሩት ፍጹም ከእውነት የራቀ መረጃ ውሉደ ክህነት እና በጎ ሕሊና ያላቸው ምእመናን በእጅጉ መጨነቃቸውን ለመገንዘብ ችለናል።

ስለሆነም ቅዱስነታቸው ሐዋርያዊ ተግባራትን ለመምራትም ሆነ ለማከናወን የማያስችል ምንም ዓይነት የጤና እክል ያልገጠማቸው፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘም ያቀረቡት ጥያቄ የሌለ መሆኑን እንገልጻለን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
አሜን።
መስከረም 28 ቀን 2018 ዓመተ ምሕረት

"...ዘፈጸምኪ ስምዐ በእንተ ኢየሱስ ንጉሠ ኤፍራታ፤ ሰላም ለኪ አርሴማ ምስለ እምኪ አጋታ፤ ወለደናግል ሰላም ምስሌኪ ዘሞታ።"
08/10/2025

"...ዘፈጸምኪ ስምዐ በእንተ ኢየሱስ ንጉሠ ኤፍራታ፤
ሰላም ለኪ አርሴማ ምስለ እምኪ አጋታ፤
ወለደናግል ሰላም ምስሌኪ ዘሞታ።"

08/10/2025

ጽናት !!

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።➛ መስከረም 29 ሰማዕቷ ቅዱስት አርሴማ ዕረፍቷ ነው፡፡ ➛ ከእርሷም ጋር ያሉ 27 ሰማዕታት አብረው ተሰይፈዋል፡፡➛ በዚህችም ...
08/10/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።

➛ መስከረም 29 ሰማዕቷ ቅዱስት አርሴማ ዕረፍቷ ነው፡፡
➛ ከእርሷም ጋር ያሉ 27 ሰማዕታት አብረው ተሰይፈዋል፡፡
➛ በዚህችም ቀን የቅዱስ ዮሐንስ ነባቤ መለኮት (ወንጌላዊው) እንደ ንስር መጥቆ "ቀዳሚሁ ቃል.." (ዮሐ. ፩፥፩) ብሎ ወንጌሉን የጻፈበት ዕለት ነው።

🔥 ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ

የቅዱስት አርሴማ አባቷ ቴዎድሮስ ከሌዋውያንና ከኃያላን ነገሥታት ወገን ሲሆን እናቷ አትኖስያ ደግሞ ከጳጳሳት አለቆች ወገን ናት፡፡ ወላጆቿ በሃይማኖት በምግባር ያጌጡ በበጎ ትሩፋት የተመሰገኑ ደጋግ ቅዱሳን ናቸው፡፡ በጾም፣ በጾሎት፣ በምጽዋትና ዓሥራት በኩራትን በማውጣት በመንፈሳዊ ሥራ ሁሉ እየተጉ ቢኖሩም ነገር ግን እስክ እርጅናቸው ዘመን ድረስ ልጅ ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበር፡፡ እናቷ ቅድስት አትኖስያ እንደ ነቢዩ ሳሙኤል እናት ሐና ጠዋት ማታ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በእግዚአብሔር ፊት ታለቅስ ነበር፡፡ እግዚአብሔር የልቧን ፈቃድ ይፈጽምላት ዘንድ ወደደና የቂሣርያውን ሊቀ ጳጳሳት ልድዮስን ስለ እርሷ ይጸልይላት ዘንድ አዘዘው፡፡
ሊቀ ጳጳሳቱም ስለ ቅድስት አትኖስያ ጸለየላት፡፡ እግዚአብሔር አምላክም የሊቀ ጳጳሳቱንና የቅድስት አትኖስያን ጸሎት ሰምቶ መልኳ እጅግ ያማረችን ሴት ልጅ ቅድስት አርሴማን ሰጣት፡፡ እናቷም እየተንከባከበች አሳድጋት ዕድሜዋ ከፍ ሲል አምላክን በወለደች በእመቤታችን ስም ወደተሠራች ቤተ ክርስቲያን ታገለግል ዘንድ ሰጠቻት፡፡ ቅድስት አርሴማ ወጣት በሆነች ጊዜ ወላጆቿ ባል ያጋቧት ዘንድ ወደዱ ነገር እርሷ ይህንን ፈጽሞ አልወደደችምና ወላጆቿን ‹‹እኔ የሰማያዊው የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ እንጂ ምድራዊ ሙሽራ አይደለሁም›› አለቻቸው፡፡
ቅድስት አርሴማ ከእርሷ በፊትም ሆነ ከእርሷ በኋላ በመልክና በውበት የሚመስላት የለም፡፡ ይህን ዓለም እንደትቢያ በመቁጠርና ፍጹም በመናቅ ጌታችንን ከተከተሉት ቅዱሳት ደናግል አንስት ውስጥ በመልክና በውበት ቅድስት አርሴማን የሚመስል የለም፡፡ አምላክን ከወለደች ከእመቤታችን በቀር የሚበልጣት ማንም የለም፡፡ እርሷም በምግባር በሃይማኖት ያጌጠች በመንፈሳዊ ተጋድሎ የበረታች በትሩፋት የበለጸገች ናት፡፡ ብሉይን ከሐዲስ አጠናቃ ተማረች፡፡ የአገሮችንም (የሮምያን፣ የጽርዕን፣ የሶርያን፣ የኪልቅያን) ቋንቋዎች ታውቅ ስለነበር ቅዱሳት መጻሕፍትንም ወደ ተለያዩ አገራት ቋንቋዎች ትተረጉማለች፡፡
ቅድስት አርሴማ 15 ዓመት በሆናት ጊዜ ከሃዲውን ዲዮቅልጥያኖስን ሰይጣን አስነሥቶት ነገሠ፡፡ ይኸውም ከሃዲ ንጉሥ ሚስት ያባ ዘንድ በመልኳ ውብ የሆነች ሴት ልጅን ይመርጡለት ዘንድ በሀገሩ ሁሉ እንዲሄዱ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ያገኟትንም ውብ የሆነችን ሴት መልኳን ሥለው ያመጡለት ዘንድ ሠዓሊዎችንም አብሮ ላከ፡፡ የተላኩትም ሰዎች ወደ ሮሜ አገር በደረሱ ጊዜ ቅድስት አርሴማ ያለችበትን የደናግል ገዳም አገኙ፡፡ ወደ ገዳሙም ገብተው ቅድስት አርሴማን አይተዋት በመልኳ ማማር እጅግ ተደስተው ‹‹ለንጉሡ ሚስት የምትሆነው ይህች ናት›› ብለው መልኳን በሥዕል ቀርጸው ለንጉሡ ላኩለት፡፡ ንጉሡም ሥዕሏን በተመለከተ ጊዜ ፈጽሞ ተደሰተ፡፡ ስለ ሠርጉ ወደ እርሱ ይመጡ ዘንድ ሕዝቡን ይጠሩአቸው ዘንድ ወደ ነገሥታቱና ወደ መኳንንቱ ሁሉ ላከ፡፡
በገዳም ያሉ ደናግልም ይህን በሰሙ ጊዜ እጅግ አዝነው አለቀሱ፡፡ ድንግልናቸውን እንደጠበቁ ያገለግሉት ዘንድ እግዚአብሔርን እየለመኑት ከገዳሙ ወጥተው ወደ ንጉሥ ድርጣድስ የግዛት አገር ወደ አርማንያ ደረሱ፡፡ በዚያም በምድረ በዳ ዋሻ ውስጥ ተቀመጡ፡፡ ቁጥራቸውም 75 ወንዶችና 39 ደናግል ሴቶች ነበሩ፡፡ በዋሻም ውስጥ በረሃብና በጥም እየተቸገሩ ተቀመጡ፡፡ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ቅድስት አርሴማን ፈልጎ ባጣት ጊዜ እጅግ ቢያዝንም ነገር ግን ቆይቶ በአርማንያ እንዳለች ሰማ፡፡ እርሷንም ይዞ ይልክለት ዘንድ ወደ አርማንያው ንጉሥ ድርጣድስ መልእክት ላከ፡፡ ድርጣድስም ለጣዖት የሚሰግድ ፀሐይና ጨረቃን የሚያመልክ ነው፡፡ በሰው እጅ የተጠረቡ ዕንጨቶችንና ድንጋዮችንም በቤቱ አስቀምጦ ‹‹አማልክት›› እያለ በመጥራት እንደ አምላክ ያመልካቸው ነበር፡፡ በውስጡም ሰይጣን አድሮበታልና የእርሱን ጣዖታት ሕዝቡም እንዲያመለኩ ያስገድዳቸው ነበር፡፡ ክርስቲያኖችንም እያሰረ በመግረፍ ያሠቃይ ነበርና ቅድስት አርሴማ በዋሻ ውስጥ ሆና አንዱ መኮንን ክርስቲያኖችን በመግረፍ ሲያሠቃይ ታየዋለች፡፡ ስለ ሰማዕታቱም ወደ እግዚአብሔር ስትጸልይ የብርሃን አክሊል የያዙ ቅዱሳን መላእክት ሰማዕታቱ ሲሰጧቸው አየች፡፡ ይህንንም ታላቅ ምሥጢር ባየች ጊዜ ‹‹አቤቱ አምላኬ ሆይ ስለስምህ እኔም ሰማዕት እሆን ዘንድ እርዳኝ›› እያለች ለመነች፡፡
ከዚህም በኋላ ወደ ሰማዕታቱ ዘንድ ስትሄድ መኮንኑ አያት ከመልኳ ማማር የተነሣ ደነገጠና ‹‹እመቤቴ ሆይ እዛው ባለሽበት ሆነሽ ተዋቸው ብትይኝ ፈትቼ እለቃቸው ነበር አንቺ ከዚህ መምጣት አያስፈልግሽም›› አላት፡፡ ቅድስት አርሴማም ‹‹እኔም የእነዚህን ሰማዕታት መከራ እሸከም ዘንድ እወዳለሁ፣ የእነርሱንም የክብር አክሊል አገኝ ዘንድ እሻለሁ›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹እመቤቴ ሆይ አንቺስ ከመንግሥት አዳራሽ ውጭ መኖር አይገባሽምና ለምን ይህን ከንቱ ነገር (ሞትን) ትወጃለሽ?›› አላት፡፡ ቅድስት አርሴማም ‹‹የጎሰቆልክ ጤልሜዎስ ሆይ ለእኔስ ሰማያዊው ንጉሥ በመንገሥቱ አዳራሽ አዘጋጅቶልኛል›› አለችው፡፡ ከዚህም በኋላ መኮንኑ ሰማዕታቱን ከእሥር ቤት ጣላቸውና ቅድስት አርሴማን ግን ከአጃቢዎች ጋር በክብር አስቀምጦ ምግብ መጠጡን አዘጋጀላት፡፡ እርሷ ግን ለሰማዕታቱ ስለ ሰማያዊው ስጦታቸው ትነግራቸው ነበር እንጂ ምግቡን አልቀመሰችም፡፡ ከሃዲው መኮንኑም ቅድስት አርሴማን ‹‹እሽ ብለሽኝ አንቺን ካገባሁ በቤቴ ያሉትን ሚስቶቼን ሁሉ አባርሬ አንቺን ብቻ ሚስት አድርጌ እስከ ዕለተ ሞቴ ድረስ እኖራለሁ ለዚህም በትላልቅ አማልክቶቼ ስም እምምልሻለሁ›› ብሎ መልእክተኛ ላከባት፡፡ ቅድስት አርሴማም መልአክተኞቹን መጻሕፍትን እየጠቀሰች የዓለምን ከንቱነትና የክርስቶስን ፍቅር አስተማረቻቸው፡፡ እርሷም የእግዚአብሔርን ቃል ስትነግራቸው ልባቸው እየተቃጠለ ያለቅሱ ነበር፡፡ እነርሱም ‹‹በቃልሽ አምነናል ጸሎትሽ ኃይል ይሁነን›› አሏት፡፡
መኮንኑም የቅድስት አርሴማን መልስ በሰማ ጊዜ በታላቅ ቁጣ ሆኖ ሰማዕታቱን ይዞ በማሠቃየት የበላዩ ወደ ሆነው ወደ አርማንያው ንጉሥ ድርጣድስ ዘንድ እንዲወስዷቸው አዘዘ፡፡ የአገሩ ሰዎችም ቅድስት አርሴማ ሰማዕት ትሆን ዘንድ ፈቅዳ ወደ ንጉሡ ዘንድ እንደሄደች ለእናቷ ለአትኖስያ ነገሯት፡፡ እናቷም መጥታ ‹‹ልጄ ሆይ ወደሞት ለምን ትሄጃለሽ? ወደ ሞት መሄድሽን እያየሁ አሁን ልቤ እንዲህ በሀዘን ከሚሰበር መነው መጀሪያውኑ ባልወለድኩሽ ይሻለኝ ነበር›› አለቻት፡፡ ቅድስት አርሴማ ግን የክርስቶስን ፍቅር ለእናቷ አስረዳቻት፡፡ በኪልቂያ አጋታ ብለው የሚጠሯት ወላጅ እናቷ አትኖስያም ‹‹አስተማሪዬ ልጄ አርሴማ ሆይ! እባክሽ እሺ በይኝ…›› እያለች ብዙ ብትለምናትም ቅድስት አርሴማ ግን እናቷንና የአገሯን ሰዎች ተሰናብታ ስትሄድ ሁሉም እያለቀሱ ሸኟት፡፡ በመንገድም ሳለች ቅድስት አርሴማን ወደ ንጉሥ ድርጣድስ የሚወስዷት ጭፍሮች ከሰማዕታቱ ጋር ሄዳ ሰማዕት ከምትሆን ይልቅ ወደ እናቷ መመለስ ብትፈልግ እንደሚመልሷት ነገሯት፡፡ እርሷ ግን ‹‹ከሰው ፍቅር ይልቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይበልጣል›› አለቻቸው፡፡
ሰማዕታቱም አርማንያ አገር እንደደረሱ ጭፍሮቹ የሰማዕታቱን እግሮቻቸውንና እጆቻቸውን እንዳሠሯቸው ለንጉሥ ድርጣድስ አስረኩቧቸው፡፡ መኮንኑም ለንጉሡ ‹‹ጌታዬ ሆይ እነሆ አንተ የምታመልካቸውን ጣዖቶችህን የማያመልኩትን ብዙ ክርስቲያኖችን ሰቀልናቸው፣ ገደልናቸው፡፡ የቀሩትንም እየገረፍን ይኸው ከፊትህ አቁመናቸዋል የወደድከውን አድርግባቸው፡፡ አንዲትም ውብ ሆነች ሴት ልጅ አብራቸው መከራ መቀበልን መርጣ መጥታለች የመልኳንም ማማርና ደም ግባቷን ባየን ጊዜ ደንግጠን በእርሷ ላይ አንዳች ክፉ ማድረግ አልተቻለንም›› አለው፡፡ ንጉሡም ያመጧት ዘንድ ሲነግረው መኮንኑ ‹‹ነገር ግን ጌታዬ ሆይ እርሷ በመልክ የሚስተካከላት የሌለ እጅግ ውብ ብትሆንም ‹ከሕይወት ይልቅ መሞት ይሻለኛል› ይምትል ናት›› አለው፡፡ ከዚህም በኋላ ሰማዕታቱን ወደ እሥር ቤት በመውሰድ ቅድስት አርሴማን ግን ይዘው ወደ ንጉሡ ዘንድ አመጧት፡፡ እርሷም ወደ ንጉሡ አዳራሽ እያማተበች ስትገባ ንጉሡ ባየት ጊዜ ልቡ ታወከ፡፡ ሰማዕቷ ግን ‹‹ከሰማያትና ከምድር ንጉሥ ከእግዚአብሔር አምላኬ ትለየኝ ዘንድ የወደድክ ሰነፍ ንጉሥ ሆይ! የሰይጣን መልአክተኛና የጥፋት ልጅ የይሁዳ ወገን ከእኔ ምን ትሻለህ? ከወደድክስ በእጅህ ሰማዕት እሆን ዘንድ እወዳለሁ›› አለችው፡፡ ከዚህም በኋላ ሰማዕቷ በጸለየች ጊዜ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በታላቅ ግርማ ተገለጡላት ነገር ግን ቅድስት አርሴማ ‹‹ጌቶች ሆይ! ነፍሰ ገዳይ እንዳልባል በማንም ላይ ጥፋት አይድረስ›› ብላ ለመነቻቸው፡፡ ሊይዟት የመጡት ሰዎችም ግርማዋን አይተው ፈሩ፡፡ ሰውነቷንም ቀርበው እንዳይነኳት የመለኮት ኃይል ከለከላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹ይህች ሴት አስማተኛ ናት፣ ጥበብና ምትሃት አላት›› ብለው ለንጉሡ በነገሩት ጊዜ እርሱም ‹‹ዛሬ ያሸነፍሽኝ እንዳይመስልሽ ነገ ብርቱዎች በሆኑ አማልክቶቼ ኃይል ድል አደርግሻለሁ›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹ዛሬም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ይረዳኛል፣ በእኔ በኃጢአተኛይቱና በደካማይቱ ኃይል አይደለም፡፡ በእነዚህ ቅዱሳን ሰማዕታት የጸሎት ኃይል እንጂ›› በማለት መለሰችለት፡፡ ሰማዕታቱም ከቅድስት አርሴማ ጋር በእሥር ቤት ሳሉ ‹‹የእግዚብሔርን ኃይል በአንቺ ላይ አይተናልና በጸሎትሽ አስቢን›› አሏት፡፡ እርሷም ‹‹በገድላችሁ ብርታት ለእኔ ጸልዩልኝ›› አለቻቸው፡፡ ቅድስት አርሴማ ሌሊት ታላቅ ምሥጢርን አየች፡፡ እልፍ አእላፋት የብዙ ብዙ የሚሆኑ ቅዱሳን መላእክት የሥላሴን ዙፋን ከበው ‹‹የጌትነትህ ምስጋና ሰማይንና ምድርን መላ ፍጹም አሸናፊ እግዚአብሔር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያሉ ሲጮኹ ተመለከተች፡፡ ይህንንም የመላእጅትን ዜማ እንደሰማችና እንዳየች ለሰማዕታቱ ነገረቻቸው፡፡ ‹‹ከእነዚህም መላእክት ውስጥ አንዱ ወደ እኔ ተልኮ መጣና በቀኜ ቆሞ በጥላው ሸሽጎ የሕይወትን እንጀራ መግቦኝ የድኅነትን ጽዋ አጠጣኝ፡፡ ያንጊዜም ሥጋዬ ወደ ምድር ወረደ፣ በላዬም ነፍሴ ተመለሰቸ፡፡ ከእንቅልፍ እንደሚነቃና የወይን ጠጅ ጠጥቶ ስካሩ እንደተወው ሰው ነቃሁ›› አለቻው፡፡
በነጋም ጊዜ ንጉሡ በፍርዱ ዙፋን ተቀምጦ ሰማዕታቱን ከእሥር ቤቱ አውጥተው ወደ ፍርድ አደባባይ ያመጧቸው ዘንድ አዘዘ፡፡ በፊቱም አቁሞ ለጣዖታት አማልክቶቹ እንዲሰግዱና እንዲሠው አዘዛቸው፡፡ እነርሱም ‹‹እኛስ የምናመልከው እውነተኛ አምላክ አለን ለረከሱ ጣዖታት አንገዛም›› ባሉት ጊዜ ‹‹ትእዛዜን ካልፈጸማችሁ ሰውነታችሁን በትንሽ በትንሹ እየቆራረጥኩ እጥለዋለሁ›› አላቸው፡፡ ሰማዕታቱም ‹‹በሚያስፈራ ቃልህና በቅጣትህ የምንፈራና አምላካችንን ክርስቶስን የምክደው አይደለንም፡፡ ስለ አምላካችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነፍሳችንን እንሰጥ ዘንድ ወደ አንተ መጥተናል›› አሉት፡፡ ያን ጊዜም ንጉሡ ድርጣድስ እጅግ ተቆጥቶ ‹‹ይህችን ሴት በማስቀደም ጽኑ ቅጣት ቅጧቸው የምታስተምራቸው እርሷ ናትና›› ብሎ አዘዘ፡፡ ጭፍሮቹም ‹‹የሴት ልቧ ደካማ ነውና ቅድሚያ ወንዶችን አሠቃይተን ብንገድል ሴቶቹ ለጣዖቶችህ ይገዛሉ›› በማለት ወንዶቹን ለብቻ ወስደው ለተራቡ አንበሶችና ሌሎች አውሬዎች ሰጧቸው፡፡ ቅድስት አርሴማም አጽናናቻቸውና ተሰነባብተው ወደ ሰማዕትነት ገቡ፡፡ ነገር ግን የተራቡት አንበሶችና ሌሎችም አውሬዎች ወደ ሰማዕታቱ መቅረብ አልተቻላቸውም ይልቁንም በሰማዕታቱ ፊት ሰገዱላቸው፡፡ በጅራታቸውም እየዳሰሷቸው አጫወቷቸው፡፡ የቅድስት አርሴማንም የእግሯን ትቢያ ላሱ፡፡ እርሷም በእጆቿ ዳሰሰቻቸው፡፡ አውሬዎቹም ብረቱን እየበጠሱ ንጉሡ ከመንግሥቱ ዙፋን እስኪወድቅ ድረስ አባረሩት፡፡ ወታደሮቹንም ሲያባርሯቸው ከእነርሱ ውስጥ 300 ጭፍሮች ሞቱ፡፡ የተረፉትም ይህንን ተአምር ሲያዩ እጅግ እያደነቁ ሰማዕታቱ ምትሃተኞች መሆናቸውን ተናገሩ፡፡ ይልቁንም ቅድስት አርሴማን ‹‹እርሷ መመኪያቸውና መሪያቸው ናትና አስቀድመን እንግደላት›› አሉ፡፡

ከዚህም በኋላ ጥልቅ ጉድጓድ ቆፍረው በውስጡ እሳትን አንድደው ሰማዕታቱን ከዚያ ይጨምሯቸው ዘንድ ሲመክሩ ንጉሡ በዚህ ምክራቸው ደስ ተሰኘ፡፡ እንደምክራቸውም ጥልቅ ጉድጓድ ቆፍረው በውስጡ እሳት አንድደው የተለያዩ ሰውነትን ቆራርጠው የሚጥሉ እንደ ዲን፣ ሙጫ፣ ቅንጭብ ጨምረው የእሳቱ ነጎድጓድ እስኪሰማ ድረስ አንድደው ሰማዕታቱን ከዚያ እንዲጨምሯቸው ንጉሡ አዘዘ፡፡ ቅድስት አርሴማንም ‹‹አሁን ከዚህ ማን እንሚያድንሽ አያለሁ›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹እኛንስ አምላካችን እንደሚያድነን አሁን ታያለህ አንተ ግን ከዚህ ክፋትህ ካልተመልስክና ጣዖት ማምለክህን ትተው እውነተኛውን አምላክ ካላመለክህ በኋላ ከዘላለማዊው እሳት ወዴት ትሸሻለህ? በማስ ትማጸናለህ? በዕንጨት ነውን ወይስ በድንጋይ? …. ›› በማለት ስለ ዕለተ ምጽዓት ሌላም ብዙ ነገር አስተማረችው፡፡ በዚህም ጊዜ ከወታደሮቹ አንዱ ተነሥቶ በኃይል ሲመታት ከአፍንጫዎቿ ደም እንደ ውኃ ፈሰሰ፡፡ ንጉሡም ‹‹በዚህ የምተውሽ አይደለሽም ሥጋሽን በእሳት አቃጥለዋሁ›› በማለት ተናገራት፡፡ ያንጊዜም ምድር አፏን ከፍታ ያንን የመታትን ወታደር ዋጠችው፡፡ ይህንንም ያዩ ሁሉ በማድነቅ እጅግ ፈሩ፡፡ ንጉሡም ፈርቶ ከዙፋኑ ላይ ፈጥኖ ተነሣ፡፡ ቅድስት አርሴማም ፈገግ ብላ በእርሱ ይመጣ ዘንድ ያለውን ነገር ትንቢት ነገረችው፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ስለ እኛ ይበቀልሃል፣ የአጋንንትም ማደሪያ ያደርግሃል፣ እንደ ጅብ በራስህ ሥጋህን እስከምትበላ ድረስ ያሳብድሃል፡፡ መልክህና ምሳሌህ ይለወጣል፣ እንደ በረሃ እሪያም ትሆናለህ፣ የምትናገረውን አታውቅም፣ የእርኩሳን አጋንንት የእግራቸው መረገጫ ትሆናለህ፡፡ ያንጊዜም የሙታንን ትንሣኤ ተስፋ ትታመን ዘንድ አለህ ይህ እንደሚሆንብህ በእውነት እነግርሃለሁ›› አለችው፡፡ ንጉሡም ይህን ጊዜ ‹‹እናተን በክፉ ቅጣት አሠቃይቼ ከገደልኩ በኋላ ይህን አሁን ያልሽውን ብሆን አይሳዝነኝም›› አላት፡፡ ይህንንም ሲነጋገሩ ወታደሮቹ መጥተው የእሳቱ ነበልባል ከሩቅ እስኪታይ ድረስ እንደነደደ ነገሩት፡፡ እርሱም ሰማዕታቱን ከእሥር ቤት አውጥተው በማምጣት ከቅድስት አርሴማ ጋር በእቶኑ እሳት ውስጥ ይጥሏቸው ዘንደ አዘዘ፡፡ ቅድስት አርሴማም ሰማዕታቱን ካጽናናቻቸውና ከመከረቻቸው በኋላ በመስቀል ምልክት አማትባ ማንም ገፍቶ ሳይጨምራት ራሷን ወደ እሳቱ ውስጥ ወረወረች፡፡ ቀጥሎም ዲያቆን ጤሜልዮስ ወደ እሳቱ ተወርውሮ ገባ፡፡ ታላቃቸው ጌርሎስም እንዲሁ ራሱን ወርውሮ ወደ እሳቱ ውስጥ ገባ፡፡ ሁሉም እንዲሁ በየተራ ራሳቸውን እየወረወሩ ገቡ፡፡ በጎች ወደ ወንዝ ውኃ እየሮጡ እንደሚገቡ ሁሉም ሰማዕታት ራሳቸውን እየወረወሩ ወደ እቶኑ እሳት ገቡ፡፡ ይህንንም ሲያደርጉ ያዩአቸው ወታደሮች ሁሉ በሀዘኔታ አለቀሱላቸው፡፡ ነገር ግን ወዲያው ሰማዕታቱ ከእሳቱ ውስጥ ሆነው እግዚአብሔርን በሰላም ሲያመሰግኑ አዩአቸውና እጅግ ተደነቁ፡፡ ቅድስት አርሴማም በዚያ ላሉት ሁሉ ወደፊት በንጉሡ ላይ የሚሆነውን ነገር በትንቢት ነገረቻቸው፡፡

ከዚህም በኋላ ንጉሥ ድርጣድስ ቅድስት አርሴማን እንደበቀሉለትና እንዲያጠፉለት ወደ አማላከቶቹ ቤት ይወስዷት ዘንድ የሠራዊቱን አለቆች አዘዛቸው፡፡ ወደ አማልክቶቹም ቤት በወሰዷት ጊዜ በዚያ ሆና ስትጸልይ በወንዶች አምሳል የተሠሩ 77 እና በሴቶች አምሳል የተሠሩ 33 ጣዖታት ሁሉ ተሰባበሩ፡፡ ከአንገታቸው የተሰበሩ አሉ፣ እግሮቻቸውና እጆቻቸው የተሰበሩ አሉ፣ ወገባቸው የደቀቁ አሉ፣ እንደትቢያም የተነተኑ አሉ፡፡ በምድርም ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም እንደመብረቅ ባለ ድምጽ መጥቶ ምድሪቱን መላትና በዚያ ያሉ ጣዖታት በሙሉ እንደትቢያ ጠፉ፡፡ ቅድስት አርሴማም ይህንን ባየች ጊዜ ደስ ተሰኝታ የሆነውን መጥቶ ያይ ዘንድ ወደ ንጉሡ ላከችበት፡፡ ንጉሡም በመጣ ጊዜ ‹‹አምላኬ መልአኩን ልኮ አዳነኝ፣ ጣዖታቶችህንም እንዳልነበሩ አደረጋቸው እህግዲህስ እፈር›› አለችው፡፡ ንጉሡም ‹‹በምትሃትሽ ይህንን እንዳደረግሽ ዐውቀለሁ›› አላትና ወደ እስር ቤት ወስዶ ከሰማዕታቱ ጋር ጨመራት፡፡
ሰማዕታቱም በእስር ቤት ሆነው እህልና ውኃ ከቀመሱ ሰባት ቀን ሆኗቸዋልና ርሀቡና ጥሙ እጅግ ጠናባቸው፡፡ ያንጊዜም ቅድስት አርሴማ ተነሡ እንጸልይ አለቻቸውና ቢጸልዩ ብርናኤልና አቅናኤል በሚባሉ ሁለት ቅዱሳን መላእክት እጅ ሰማያዊ ኅብሥትባ የገነት ውኃ መጣላቸው፡፡ ከመካከላቸውም ካህኑ ኢያሴኖስ ባርኮ ለሌሎቹ ሰማዕታት ሰጣቸውና ተመግበው ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ፡፡ የተረፋቸውም ኅብሥት በመላአክቱ እጅ ወደ ሰማይ ወጣ፡፡
በማግሥቱም ንጉሡ ወደ ፍርድ አደባባይ ባወጣቸው ጊዜ ሰማዕታቱ ፊታቸው እንደፀሐይ ያበራ ነበር፡፡ የእሥር ቤት ጠባቂውንም ጠርቶ ‹‹እህል ያበላሃቸውና የነገሥታትን ልብስ ያለበስካቸው ለምንድነው?› ብሎ ተቆጣው፡፡ ጠባቂውም ‹‹ጌታዬ ሆይ እነርሱስ ሳይበሉ ሳይጠጡ ይረካሉ እንጂ የሰጠኃቸው ምንም ነገር የለም›› አለው፡፡ ቃሉንም በመሐላ ካጸናለት በኋላ ‹‹ነገር ግን ንጉሥ ሆይ በሌሊት እሥር ቤት በብርሃን ተጥለቅልቆ አይቼዋለሁ፡፡ ዳግመኛም ሃያ ሰባት የብርሃን አክሎችም ሲወርዱ አየሁ›› አለው፡፡ ቀጥሎም ይህ ጠባቂ ‹‹ንጉሥ ሆይ እኔም በእነዚህ ሰማዕታት አምኛለሁ›› አለው፡፡ ወደ ቅድስት አርሴማም ዞሮ ‹‹እመቤቴ ሆይ በጸሎትሽ አስቢኝ›› በማለት ሌሎቹንም ሰማዕታት ተመጸናቸው፡፡ ንገሡም በዚህ እጅግ ተቆጥቶ ራሱን በሰይፍ አስቆረጠው፡፡ እርሱም በጣዖት የሚያመልክ አረማዊ ቢሆንም አምኖ በደሙ ተጠምቋልና የሰማዕትነትን የክብር አክሊል ተቀዳጀ፡፡ ቅዱሳን የሆኑ ሰማዕታቱም ይህን አደነቁ ሰማዕትነትን በመፈጸም ቀድሟቸዋልና፡፡ በድኑንም በምድረ በዳ ጣሉት ነገር ግን አውሬዎችና አሞራዎች አልበሉትም ቅዱሳን መላእክት ይጠብቁታልና፡፡
ንጉሡም ሰማዕታን በጽኑ ዱላዎች ካስደበደባቸውና ለእያንዳንዳቸው ሌላ ሦስት ሦስት መቶ ግርፋት ካስገረቸው በኋላ ወደ እሥር ቤት መለሳቸው፡፡ በመግስቱም ቅድስት አርሴማን አስመጥቶ ከእርሱ ጋር ትሴስን ዘንድ አባበላት፡፡ ‹‹ንግሥት አድርጌሽ በወርቅ ዙፋኔ ላይ ትቀመጫለሽ፣ በአርማንያ ካሉ ሴቶች ሁሉ በላይ አደርግሻለሁ…›› እያለ አባበላት፡፡ ቅድስት አርሴማ ግን ‹‹ልብህ የደነደነ ሰነፍ ሆይ ኃጢአትህን ሁሉ ይቅር ይልህ ዘንድ ወደ አምላክህ እግዚአብሔር ትመለስ ዘንድ በተሻለህ ነበር …›› እያለች አስተማረችው፡፡ ስለ ጌታችንም መንገሥት ካስተማረችው በኋላ ‹‹እኛ ሰማዕታቱ ስለ አንተ እንጸልይልሃለን›› አለችው፡፡ ንጉሡ በዚህ ጊዜ ‹‹ማመኔን ብትወጂ ግን ከእኔ ጋር ተስማምተሽ እንጋባለን ለአምላክሽም እገዛለሁ›› ሲላት ወዲያው እርኩስ መንፈስ ፊቱን መታውና ‹‹ከእናትህ መኅፀን ጀምሮ ያሳደኩህና በሥራህ ሁሉ ልብ፣ አፍና ብርታት ሆኜ በኃይሌም ብርታት የክርስቲያን ልጆችን እንድታስጨንቃቸውና እንትገድላቸው ያደረኩህን እኔን ለምን ተውከኝ? ስለዚህች ሴት ብለህ እግዚአብሔር አምላክን ታመልክ ዘንድ ወደድክን! ...›› እያለ በቁጣ ሆኖ አፉን አጣመመውና ምድር ላይ ጣለው፡፡ ከዚህም በኋላ ለጣዖታቱ ይሰግዱ ዘንድ ሰማዕታቱን በቁጣ አዘዛቸው፡፡ ነገር ግን የጣዖታቱ ካህናት መጥተው ጣዖታቱን ቅድስት አርሴማ እንዳጠፋቻቸው ነገሩት፡፡ ዳግመኛም ‹‹እርሷን ካልገደልካት አገራችን ትጠፋለች፣ መንግሥትህ ተሻራላች›› አሉት፡፡
ከዚህም በኃላ ከቅድስት አርሴማ ጋር ያሉትን 27ቱን ሰማዕታት ስሙ ጋብጋቦ ወደሚባል ወንዝ ወስደዋቸው አንገታቸውን በሰይፍ ቆረጧቸውና የሰማዕትነት ፍጻሜአቸው ሆነ፡፡ ከእነርሱም አንደኛውን በቅድሚያ አንገቱን ሲቆርጡት ሥጋው ወደ ምድር ወደቀ፡፡ ራሱ ግን ለብቻ ለአንድ ሰዓት ያህል ቆመች፡፡ ቡርክት ቅድስት አርሴማም ሮጣ ሄዳ የሰማዕቱን በርቲኖስን ራስ ያዘቻትና ወደ አንገቱ መለሰቻት፡፡ እርሱም "ሰማዕት ለመሆን እኔን ስላስቀደመ አምላኬ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ" እያለ ሦሰት ጊዜ ተነፈሰ፡፡ ለቅድስት አርሴማም "እመቤቴ ሆይ መምጣትን እንዲያፋጥኑ ከፀሐይ ይልቅ የምታበራ አገርን እንዲያዩ ለወንድሞቻችን ለእኅቶቻችን ነገሪያቸው" አላት፡፡ እርሷም ወደ ሰማዕታቱ ዞራ "ወንድማችን በገነት ያየውን ይነግረንና ያሳየን ዘንድ በሕይወት ኖሯል እንጂ አልሞተም" አለቻቸው፡፡
ከዚህም በኃላ ሰማዕታቱ እግዚአብሔርን አመስግነው "እኔ አስቀድሙ እኔ አስቀድሙ..." እያሉ ወታደሮቹን ለመኗቸው፡፡ እየተሻሙ በየተራ እየተሰየፉ ሰማዕትነታቸውን ፈጽመው የክብር አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ የእነዚህም የ27ቱ ክቡራን ሰማዕታት ስማቸው ይህ ነው፡- ካህኑ ኢያሚኖስ፣ አፍጢኖስ፣ በርቲኖስ፣ ጢሞና፣ ጢሞዓና፣ ዘኬዎስ፣ እስጢፋኑ፣ አርሞና፣ ኪርያኮስ፣ አንጥያኮስ፣ ያዕቆብ፣ ቡራኬሌስ፣ አስቂርያቆስ፣ አስኪርያኖስ፣ ሚርያኖስ፣ ትትግርጦስ፣ ያስቲኖስ፣ ጥልያኖስ፣ ዑልያኖስ፣ ጴርቅላስ፣ ኬብያኖስ፣ ጴጥሮስ፣ ጳክንዮስ፣ ሐናንያ፣ ሐሊባኖስ፣ ኤስያኖስ እና ኤልያብ ናቸው፡፡
ቅድስት አርሴማም የሰማዕታቱን ራሶቻቸውን ትሰበስብ ነበር፡፡ ወደ ሥጋቸውም ታጋጥመው ነበር በዚያም ጊዜ እንደመጀመሪያው ይሆናል፡፡ እንዳልተቆረጠም ይሆናል፡፡ ልብሶቻቸውንም ታለብሳቸዋለች፡፡ ይህንንም ታላቅ ተአምር ያዩ 92 የንጉሡ ወታደሮች ወደ ንጉሡ ሄደው "እኛም በአምላካቸው አምነን ክርስቲያን ሆነናል" በማለት መሰከሩ፡፡ ንጉሡም በፈረስ ገመድ ላይ አስሮ ሥጋቸው ተቆራርሶ እስኪወድቅ ድረስ ካሠቃያቸው በኃላ አንገታቸውን ሰየፋቸውና የክብር አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ ዳግመኛም በእነርሱ ምክንያት ሌሎችም አመኑ፡፡ ከዚህም በኃላ ንጉሡ ቅድስት አርሴማን ውበቷን እያሰበ ልቡናውን ሳተ፡፡ ድንግልናዋንም ሊያረክስ ሽቶ እናቷን አጋታን እንድታባብልለት አዘዛት፡፡ እናቷም ሄዳ "ልጄ ሆይ ስሚ ይህ አረማዊ እንዳያረክስሽ ተጠንቀቂ" አለቻት፡፡ ንጉሡም ቅድስት አርሴማን "መንግሥቴንና ግዛቴን ሁሉ አወርስሻለሁ" እያለ በመሀላ ቢለምናትም እሺ እንደማትለው ሲያውቅ ይዞ በግድ ወደ እልፍኙ ሊያስገበት ሲል ቅድስት አርሴማ ይዛ መሬት ላይ ጣለችው፡፡ በእርሷ ላይ ያደረ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሞገስ ሆኗታልና፡፡
እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የበረታ ኃይለኛ ስለነበረ አሁን በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ አፈረ፡፡ በዚህም እጅግ ተናዶ ለሥጋዊ ፈቃዱም እንደተመኛት ሊያገኛት ስላልቻለ ተስፋ ቆርጦ በንዴት አንገቷን ይቆርጧት ዘንድ አዘዘ፡፡ የቅድስት አርሴማንም ራሷን ቆረጧትና የሰማትነት ፍጻሜዋ ሆነ፡፡ ከአንገቷም ደም፣ ውኃ፣ ወተትና ማር ወደ አራቱም አቅጣጫ ፈሰሰ፡፡ እርሷና ሌሎቹም 72 ሰማዕታት ከተሰየፉ በኃላ ሥጋቸው ቀምድር ላይ ተጥሎ ቀረ፡፡ ንጉሡም ጋኔን ተጭኖበት መልኩ ተለውጦ እንደ እሪያ ሆነ፡፡ ከዚያ በፊት የአርማንያውን ሊቀ ጳጳሳት አቡነ ጎርጎርዮስን ንጉሡ ድርጣድስ ዕጣን ሊያሳርግ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ አቡነ ጎርጎርዮስን ጠርቶ ለአማልክት ዕጣን አሳርጉ ቢላቸው እሳቸውም ትእዛዙን አልፈጽምም ባሉት ጊዜ እጅግ ጽኑ በሆኑ በተለያዩ ሥቃዮች ካሠቃያቸው በኃላ ጥልቅ ጉድጓድ አስቆፍሮ በዚያ ውስጥ ጣላቸው፡፡ አባታችንም በዚያ ጥልቅ ጉድጓድ እንደተጣሉ ለ15 ዓመታት ኖሩ፡፡ ስለምግባቸውም እግዚአብሔር አንዲት እናትን አዘዘላቸው፡፡ በንጉሡ አዳራሽ አቅራቢያም የምትኖረው ይህች ሴት በእግዚአብሔር ታዝዛ እንጀራን እየጋገረች ወደ ጉድጓዱ ትጥልላቸው ነበር፡፡ ከእርሷም በቀር አባታችን በሕይወት መኖራቸውን የሚያውቅ ሰው የለም፡፡ እንዲህም እያደረገች 15 ዓመት ኖራለች፡፡
ንጉሡ ድርጣድስም ቅድስት አርሴማን ማግባት ፈልጎ ሳለ ፈጽሞ እምቢ ብትለው በእርሷ ምክንያት ብዙ ደናግል ሴቶችን ገደለ፡፡ ሰይጣን በልቡ ያደረበት ይህ ንጉሥ ድርጣድስም ደናግሎቹን እና ቅድስት አርሴማን በብዙ ሥቃይ ከገደላቸው በኋላ ሥጋቸውን በተራራ ላይ ጥሎት ነበር፡፡ ነገር ግን ምንም ሳይሆን በጌታችን ጥበቃ ኖረ፡፡ የቅድስት አርሴማንም ውበቷን እያሰበ ስላስገደላት የሚጸጸት ሆነ፡፡ ወገኖቹም ‹‹ከሀዘንህ ታርፍ ዘንድ ወደ ጫካ ሄደን አውሬ አድን›› አሉት፡፡ ንጉሡም በፈረሱ ተቀምጦ ወደ ጫካ ወጣ፡፡ ነገር ግን ሰይጣን ተዋሃደውና በእነ ቅድስት አርሴማና በአቡነ ጎርጎርዮስ ላይ በሠራው ግፍ እግዚአብሔር የተፈጥሮ መልኩን ቀይሮት እንደ እሪያ አደረገው፡፡ ንጉሥ ናቡከደነጾር ከእግዚአብሔር ቁጣ የተነሣ አእምሮው ስቶ ልቡ ተሰውሮ ወደ እንስሳነት እንደተለወጠ ሁሉ (ዳን 4፡28-37) ንጉሥ ድርጣድስም እንዲሁ ከእግዚአብሔር ቁጣ የተነሣ ወደ እሪያነት ተለወጠ፡፡
ንጉሡ ድርጣድስ ወደ እሪያነት ከተለወጠ በኋላ ያገኘውን ሁሉ የሚናከስ ሆነ፡፡ በቤተ መንግሥቱም ባሉ ሰዎች ላይ ሰይጣን አደረባቸውና ታላቅ ጭንቅ ሆነ፡፡ የንጉሡም እኅት በሌሊት ‹‹ጎርጎርዮስን ከጉድጓድ ካላወጣችሁት በቀር አትድኑም›› የሚል ራእይ አየችና ለወገኖቿ ነግረቻቸው፡፡ የሞተ መስሏቸው ስለነበር ይህን ሲሰሙ እጅግ ደነገጡና ሄደው ቅዱስ ጎርጎርዮስን 15 ዓመት ተጥሎ ከኖረበት ጉድጓድ ውስጥ በገመድ ጎትተው አወጡትና አክብረው ወሰዱት፡፡
እርሱም የእነ ቅድስት አርሴማን ሥጋ ወዴት እንዳደረሱት ሲጠይቅ በተራራው ላይ እንዳለ ነግረውት ሄዶ ሲያየው ምንም ሳይነካው በደህና አገኘው፡፡ አንሥቶም ባማሩ ቦታዎች አኖራቸው፡፡ ሰይጣን ያደረባቸውን የቤተ መንግሥቱንም ሰዎች ፈወሳቸው፡፡ ስለ ንጉሡም ወደ አውሬነት መለወጥ ነግረውት እንዲፈውሰው ለመኑት፡፡ አቡነ ጎርጎርዮስም ወደ ንጉሡ ሄደው በእሪያነቱ ሳለ ‹‹ብፈውስህና ባድንህ ከክፉ ሥራህ ትመለሳለህ? በእውነተኛው አምላክ በኢየሱስ ክርስቶስ ታምናለህ?›› አሉት፡፡ እሪያ የነበረው ንጉሥም ‹‹አዎ›› ቢላቸው ጸሎት አድርገው ፈውሱት፡፡ አእምሮውና የቀድሞው መልኩም ተመለሰለት፡፡ ነገር ግን አቡነ ጎርጎርዮስ ንጉሡ ዳግመኛ እንዳይታበይ በማለት ከእግሩ ላይ የእሪያ ጥፍር አስቀሩለት፡፡
የቤተ መንግሥንም ሰዎች ሁሉ ከፈወሳቸው በኋላ 8 ቀን እንዲጾሙ አዘዛቸው፡፡ ሃይማኖትንም አስተምሮ ሥርዓት ሠራላቸው፡፡ እርሱም ክህነት አልነበረውምና ወደ ሮሜው ንጉሥ ወደ አኖሬዎስና ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ መልአክት ላኩና ጳጳስ ይላኩላችሁ አላቸው፡፡ የሮሙ ሊቀ ጳጳሳትም ጎርጎርዮስን ሾሞ ላከላቸው፡፡ ንጉሡ አኖሬዎስም በዚህ ተደሰተ፡፡ ጎርጎርዮስም ተሹሞ ከመጣ በኋላ ሁሉንም አጠመቃቸው፡፡ አርማንያም በቅዱስ ጎርጎርዮስ ትምህርት በክርስትና የምትታወቅ አገር ሆነች፡፡ እርሱም በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን ሠራላቸው፡፡ ምእመናንያንም የሰማዕታቱን ሥጋ ሰብስበው በመልካም ቦታ ካስቀመጡት በኃላ የመከራው ዘመን ሲያልፍ የተዋበች ቤተ ክርስቲያን ሠርተው የቅዱሳኑን በዚያ አኖሩ፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡
የቅድስት አርሴማ ዕረፍቷ መስከረም 29 ነው፡፡ የቤተክርስቲያኗም ቅዳሴ በአርማንያ አገር፣ በኪልቂያ፣ በሶርያ፣ በአንጾኪያና በግብፅ አውራጃዎች ሁሉ በታኅሣሥ ወር በ6ኛው ቀን ሆነ፡፡ ጌታችን ከገባላት ብዙ ቃልኪዳን ውስጥ አንደኛው "... ልጁን በአንቺ ስም የጠራውን በመንግሥተ ሰማያት የበለጠና የከበረ ስምን እኔ እሰጠዋለሁ" የሚል ነው፡፡
የቅድስት አርሴማ ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣ በጸሎቷ ይማ አሜን።

🔥 ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ነባቤ መለኮት

ዳግመኛም በዚህች ዕለት ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ እንደ ንስር መጥቆ "ቀዳሚሁ ቃል.." ( ዮሐ. ፩፥፩) ብሎ ወንጌሉን የጻፈበት ዕለት እንደሆነ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ፡- ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌልን ለመስበክ ዕጣ የደረሰው እስያ ስለነበር ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስን አስከትሎ ሄደ፡፡ ይኽችውም ኤፌሶን በጥንቱ በታናሽ እስያ በዛሬው የቱርክ ግዛት ውስጥ ከተማ ናት፡፡ ዛሬ ኢያዞሎክ ተብላ የጥንት ታሪኳ ጠፍቷል፡፡ አስቀድሞ ቅዱስ ጳውሎስ ወንጌልን ሰብኮባታል፡፡ ደቀ መዝሙሩን ቅዱስ ጢሞቴዎስንም በከተማዋ ላይ ኤጲስቆጶስ አድርጎ ሾሞት ነበር፡፡ እርሱም በግፍ እስከተገደለበት ጊዜ ድረስ ቅዱስ ዮሐንስን እየረዳው በከተማዋ ብዙ አገልግሏል፡፡ በኋላ ግን በግፍ ገድለውታል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ወደ ኤፌሶን ለመሄድ በመርከብ ሲሳፈር መርከቡ በማዕበል ተሰበረ፡፡ ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስን መዕበሉ ወደ አንዲት ደሴት አደረሰው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ግን በመርከቡ ስባሪ ተንጠልጥሎ በባሕሩ ማዕበል መካከል 40 ቀንና 40 ሌሊት ከኖረ በኋላ ማዕበሉ ተፍቶ አብሮኮሮስ ካለበት ደሴት አደረሰውና ተያይዘው ኤፌሶን ከተማ ገቡ፡፡ የከተማይቱም ሰዎች እጅግ ክፉዎች ስለነበሩ መጀመሪያ ላይ ቅዱስ ወንጌልን መስበክ አልቻሉም ነበር፡፡ እነርሱም እጅግ ክፉዎች መሆናቸውን ስላወቀ ቅዱስ ዮሐንስ ገና ዕጣው ሲደርሰው በሀዘን አልቅሶ ነበር፡፡ አሁንም ከተማው በገቡ ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ምክንያት በመፍጠር ሮምና ለምትባል ሴት የውሽባ ቤቷ እሳት አንዳጅ ሆኖ አብሮኮሮስም ዕቃ አጣቢ ሆነው ተቀጠሩ፡፡ የቀጠረቻቸው ሴትም እጅግ ታሠቃያቸው ጀመር፡፡ ባሮቿ እንደሆኑ ተስማምተው ስለጻፉላት ትደበድባቸውም ነበር፡፡

እነርሱም በታላቅ ጉስቁልና ውስጥ እየኖሩ እያለ በአንዲት ዕለት የአገረ ገዥው ልጅ ለመታጠብ ወደ ውሽባው ቤት ገባ፡፡ በውሽባ ቤቱም የሰይጣን ኃይል ስለነበረበት የመኰንኑን ልጅ አንቆ ገደለው፡፡ የአገሪቱም ሰዎች ሁሉ ለሞተው የመኰንን ልጅ ሊያለቅሱ ሲሰበሰቡ ቅዱስ ዮሐንስም አብሮ ቆሞ ሲመለከት ሮምና መጥታ "በጌታዬ ልጅ ሞት ልትደሰት መጣህን" እያለች ረገመችው፡፡ እርሱም "አይዞሽ አትዘኚ" አላትና ወደ ሞተው ልጅ ቀርቦ በመስቀል ምልክት ካማተበበት በኋላ በፊቱ እፍ አለበት፡፡ የሞተውም ልጅ ድኖ ተነሣ፡፡ የሀገሪቱም ሰዎች እጅግ ደነገጡ፡፡ ሮምናም ደንግጣ "እግዚአብሔር የሚሉት አምላክ አንተ ነህን" ብላ ጠየቀችው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም "በፍጹም እኔ አምላክ አይደለሁም፣ እኔ የእርሱ አገልጋዩና ሐዋርያው ነኝ እንጂ" አላት፡፡ ሮምናም ስለበደለቻቸው በደል ሁሉ መሪር ዕንባን እያለቀሰች ይቅር እንዲሏት ለመነቻቸው፡፡ እነርሱም አረጋጉዋት፡፡ ከሕዝቡም ውስጥ ብዙዎቹ በጌታችን አመኑ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም ሌሎች ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን እያደረገ ወንጌልን እየሰበከ ከጣዖት አገልጋዮች በቀር ሁሉንም አሳምኖ አጠመቃቸው፡፡ አገልጋዮችን ኤጲስቆጶሳትን፣ ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ከሾመላቸው በኋላ ወደ ሌሎች አቅራቢያ አገሮች ሄደ፡፡

በመጨረሻም በከሃዲውና በጨካኙ በድምጥያኖስ ዘመን በጣዖት አምላኪዎች ተከሶ ለፍርድ ቀረበ፡፡ በፈላ ውኃ ካሠቃዩት በኋለ በፍጥሞ ደሴት አጋዙት፡፡ በዚያም ሳለ ራእዩን ተመልክቶ ጻፈው፡፡ ድምጥያኖስም ከተገደለ በኋላ ከግዞቱ ተመልሶ ሦስቱን መልእክታቱንና ቅዱስ ወንጌሉን ጽፏል፡፡ ጌታችንም አስቀድሞ ሞትን እንደማይቀምስ ለዮሐንስ ቃል ገብቶለት ነበርና (ዮሐ 21፡22) ጥር 4 ቀን እንደ ኤልያስና ሄኖክ ሞትን እንዳያይ ወደ ብሔረ ሕያዋን ወስዶታል።

ጌታችን ለዮሐንስ ያልነገረው እርሱም ያላስተማረው ምሥጢር የለም፡፡ ወንጌሉን መጻፍ ሲጀምር "በመጀመሪያ ቃል ነበረ፣ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ…" ብሎ የጌታችን ነገር ተመራምሮ ለመድረስ ሲል በመሀል መልአኩን በዮርዳኖስ ባሕር ላይ ሲሄድ አገኘው፡፡ መልአኩም የዮርዳኖስን ባሕር በእንቁላል ቅርፊት እየጨለፈ ወደ ውጭ ሲያፈስ ተመለከተው፡፡ ዮሐንስም ተገርሞ "ምን ማድረግህ ነው" አለው፡፡ መልአኩም "የዮርዳኖስን ባሕር ቀድቼ እየደፋሁ ልጨርሰው ነው" ሲለው ዮሐንስም መልሶ "ታዲያ በእንቁላል ስባሪ ነውን?" አለው፡፡ መልአኩም "አዎን" አለው፡፡ ዮሐንስም "በከንቱ ደከምክ" አለው፡፡ ይህን ጊዜ መልአኩም መልሶ "አንተስ እንጂ ደግሞ የአምላክን መገኘት፣ አኗኗሩንም ተመራምረህ በጥበብ ለማግኘት ብለህ 'በመጀመሪያ ቃል ነበረ፣ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ..' ብለህ ጀምረህ የለምን? አንተ ጌታን ተመራምረህ ካገኘህና ከደረስክበት እኔም የዮርዳኖስን ወንዝ በዚህ እንቁላል ቅርፊት ቀድቼ እጨርሰዋለሁ" አለው፡፡ ዮሐንስም ይህን ጊዜ ደንግጦ ዝቅ ብሎ "ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ…" ብሎ ሀሳቡን ለወጠና ሌላ ታሪክ ቀጠለ፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ በመከተሉ ክርስቲያኖችን ሁሉ ወክሎ እመቤታችንን በአደራ የተቀበለ እርሱም ለመቤታችን በአደራ የተሰጠ ሲሆን እመቤታችንን ከወሰዳት በኋላ ለ16 ዓመት እየተንከባከበ ጠብቋታል፡፡ እናቱም በሕፃንነቱ ስለሞተች እመቤታችን ናት እየተንከባከበች ያሳደገችው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ በመልኩም ከጌታችን ጋር ይመሳል ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ሥዕል የመሳል ተሰጥኦም ነበረው፡፡ ጌታችን በተሰቀለበት ዘመን የነበረው ጢባርዮስ ቄሳር ልጁ በሽተኛ ነበር፡፡ የጌታችንን የማዳን ሥራ እየሰማ እነ ጲላጦስም ስለጌታችን የሚጽፉለትን ይሰማ ስለነበር ልጁን ከጌታችን መቃብር ላይ እንዲያኖሩለት ላከው፡፡ ልጁም ፈጥኖ ተፈወሰለት፡፡ ጢባርዮስ ቄሳርም በልጁ መዳን ምክንያት የጌታችንን ውለታ ማስቀመጥ ፈልጎ የጌታችንን ሥዕሉን የሚሥልለትን ሲያጠያይቅ ዮሐንስን አገናኙት፡፡ ዮሐንስም ጌታችንን ልክ በዕለተ ዓርብ እንደተሰቀለ አድርጎ በመሣል ለጢባርዮስ ቄሳር ሰጠው፡፡ ሲሥለውም በመጀመሪያ ጌታችንን ልክ እንደተሰቀለ አድርጎ ራቁቱን ነበር የሳለው፡፡ ዮሐንስ የሳለው የጌታችን ሥዕልም አፍ አውጥቶ "በመጀመሪያ አይሁድ በኢየሩሳሌም ራቁቴን ሰቀሉኝ፣ አሁን ደግሞ አንተ ድጋሚ በሮም ራቁቴን ትሰቅለኝን?" ብሎ ተናገረው፡፡ ዮሐንስም እጅግ ደንግጦ "እንዴት አድርጌ ልሳልህ?" ብሎ የሳለውን ሥዕል ቢጠይቀው ሥዕሉም "ከለሜዳ አልብሰህ ሳለኝ" አለው፡፡ ዮሐንስም እንዳለው ከለሜዳ አልብሶ ከሳለው በኋላ ሥዕሉን ትኩር ብሎ ተመልክቶ ቢስመው ከንፈሩ አንድ ቀን ተኩል ያህል ተጣብቆ ቆይቷል፡፡ ዛሬም ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የምትጠቀምባቸውን የጌታችንን ስነ ስቅለት የሚያሳዩ ሥዕሎች መገኛቸው ይህ ወንጌላዊው ዮሐንስ የሳለው ሥዕል ነው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ በተለያዩ ስሞች ይጠራል፦
➛በሕይወቱና በኑሮው ሁሉ ጌታችንን ለመምሰል ይጥር ነበርና ጌታችንም እጅግ ይወደው ስለነበር " " ተባለ፣
➛የታላቁ ያዕቆብ ታናሽ ወንድም ስለሆነና አባቱም ዘብድዮስ ስለሚባል " " ተባለ፣
➛ለጌታችን ባለው ቅናትና ከወንድሙ ጋር ሆነው ባሳዩት የኃይል ሥራ እንዲሁም የጌታችንን አምላክነት በመግለጡ " " ተብሏል፣
➛ነገረ መለኮትን ከሌሎቹ በበለጠ ሁኔታ አስፍቶና አምልቶ በማስተማሩ " ወይም #ታኦሎጎስ" ተብሏል፣
➛ ኃላፊውንና መጻዒውን ጊዜ በራእዩ ስለገለጠ " #አቡቀለምሲስ" ተባለ፣ ይህም በግሪክኛ #ባለራእይ ማለት ነው፣
➛ የጌታችንን መከራ መስቀሉን እያስታወሰ 70 ዘመን ሙሉ እያለቀሰ ስለኖረና ፊቱም በሀዘን ስለተቋጠረ " " ተብሏል፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ምንጭ፦ የመስከረም ❷➑ ስንክሳር

🍃🍃🍃 🍃🍃🍃 🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ -https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔹https://www.facebook.com/MeseleNigatuDek0

መስከረም ❷❽ ቀን 2011 ዓ.ም

Address

Awassa

Telephone

+251926265782

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ስንክሳር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ስንክሳር:

Share

Category