ስንክሳር

ስንክሳር Ethiopian Synaxarium

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"

"የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል"
(አባ ጊዮርጊስ) ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንድት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።መስከረም 4  ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በዓለ ልደቱ ነው፡፡🔥 ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌሉ...
13/09/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።

መስከረም 4 ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በዓለ ልደቱ ነው፡፡

🔥 ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ

አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌሉ እንደነገረን በመንግስተ ሰማያት ታላቁ ሰው ወንጌላዊው ዮሐንስ ነው።

ቅዱሱ ሐዋርያ ከዘብዴዎስና ከማርያም ባውፍልያ ተወልዶ በገሊላ አካባቢ አድጐ ገና በወጣትነቱ መድኃኔ ዓለምን ተከትሎታል። ቅዱስ ዮሐንስ ከሐዋርያት ቀድሞ ጌታን ከመከተሉ ባሻገር በምንም ምክንያት ከጐኑ አይጠፋም ነበር። ስለ ንጽሕናውና በጐ የፍቅር ሕሊናው ሕጻን ሳለ በወንድሞቹ ሐዋርያት ዘንድ ሞገሱ ከፍ ያለ ነው።

ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌልን ለመስበክ ዕጣ የደረሰው እስያ ስለነበር ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስን አስከትሎ ሄደ፡፡ ይኽችውም ኤፌሶን በጥንቱ በታናሽ እስያ በዛሬው የቱርክ ግዛት ውስጥ ከተማ ናት፡፡ ዛሬ ኢያዞሎክ ተብላ የጥንት ታሪኳ ጠፍቷል፡፡ አስቀድሞ ቅዱስ ጳውሎስ ወንጌልን ሰብኮባታል፡፡ ደቀ መዝሙሩን ቅዱስ ጢሞቴዎስንም በከተማዋ ላይ ኤጲስቆጶስ አድርጎ ሾሞት ነበር፡፡ እርሱም በግፍ እስከተገደለበት ጊዜ ድረስ ቅዱስ ዮሐንስን እየረዳው በከተማዋ ብዙ አገልግሏል፡፡ በኋላ ግን በግፍ ገድለውታል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ወደ ኤፌሶን ለመሄድ በመርከብ ሲሳፈር መርከቡ በማዕበል ተሰበረ፡፡ ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስን መዕበሉ ወደ አንዲት ደሴት አደረሰው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ግን በመርከቡ ስባሪ ተንጠልጥሎ በባሕሩ ማዕበል መካከል 40 ቀንና 40 ሌሊት ከኖረ በኋላ ማዕበሉ ተፍቶ አብሮኮሮስ ካለበት ደሴት አደረሰውና ተያይዘው ኤፌሶን ከተማ ገቡ፡፡ የከተማይቱም ሰዎች እጅግ ክፉዎች ስለነበሩ መጀመሪያ ላይ ቅዱስ ወንጌልን መስበክ አልቻሉም ነበር፡፡ እነርሱም እጅግ ክፉዎች መሆናቸውን ስላወቀ ቅዱስ ዮሐንስ ገና ዕጣው ሲደርሰው በሀዘን አልቅሶ ነበር፡፡ አሁንም ከተማው በገቡ ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ምክንያት በመፍጠር ሮምና ለምትባል ሴት የውሽባ ቤቷ እሳት አንዳጅ ሆኖ አብሮኮሮስም ዕቃ አጣቢ ሆነው ተቀጠሩ፡፡ የቀጠረቻቸው ሴትም እጅግ ታሠቃያቸው ጀመር፡፡ ባሮቿ እንደሆኑ ተስማምተው ስለጻፉላት ትደበድባቸውም ነበር፡፡

እነርሱም በታላቅ ጉስቁልና ውስጥ እየኖሩ እያለ በአንዲት ዕለት የአገረ ገዥው ልጅ ለመታጠብ ወደ ውሽባው ቤት ገባ፡፡ በውሽባ ቤቱም የሰይጣን ኃይል ስለነበረበት የመኰንኑን ልጅ አንቆ ገደለው፡፡ የአገሪቱም ሰዎች ሁሉ ለሞተው የመኰንን ልጅ ሊያለቅሱ ሲሰበሰቡ ቅዱስ ዮሐንስም አብሮ ቆሞ ሲመለከት ሮምና መጥታ ‹‹በጌታዬ ልጅ ሞት ልትደሰት መጣህን›› እያለች ረገመችው፡፡ እርሱም ‹‹አይዞሽ አትዘኚ›› አላትና ወደ ሞተው ልጅ ቀርቦ በመስቀል ምልክት ካማተበበት በኋላ በፊቱ እፍ አለበት፡፡ የሞተውም ልጅ ድኖ ተነሣ፡፡ የሀገሪቱም ሰዎች እጅግ ደነገጡ፡፡ ሮምናም ደንግጣ ‹‹እግዚአብሔር የሚሉት አምላክ አንተ ነህን›› ብላ ጠየቀችው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም ‹‹በፍጹም እኔ አምላክ አይደለሁም፣ እኔ የእርሱ አገልጋዩና ሐዋርያው ነኝ እንጂ›› አላት፡፡ ሮምናም ስለበደለቻቸው በደል ሁሉ መሪር ዕንባን እያለቀሰች ይቅር እንዲሏት ለመነቻቸው፡፡ እነርሱም አረጋጉዋት፡፡ ከሕዝቡም ውስጥ ብዙዎቹ በጌታችን አመኑ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም ሌሎች ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን እያደረገ ወንጌልን እየሰበከ ከጣዖት አገልጋዮች በቀር ሁሉንም አሳምኖ አጠመቃቸው፡፡ አገልጋዮችን ኤጲስቆጶሳትን፣ ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ከሾመላቸው በኋላ ወደ ሌሎች አቅራቢያ አገሮች ሄደ፡፡ በመጨረሻም በከሃዲውና በጨካኙ በድምጥያኖስ ዘመን በጣዖት አምላኪዎች ተከሶ ለፍርድ ቀረበ፡፡ በፈላ ውኃ ካሠቃዩት በኋለ በፍጥሞ ደሴት አጋዙት፡፡ በዚያም ሳለ ራእዩን ተመልክቶ ጻፈው፡፡ ድምጥያኖስም ከተገደለ በኋላ ከግዞቱ ተመልሶ ሦስቱን መልእክታቱንና ቅዱስ ወንጌሉን ጽፏል፡፡ ጌታችንም አስቀድሞ ሞትን እንደማይቀምስ ለዮሐንስ ቃል ገብቶለት ነበርና (ዮሐ 21፡22) ጥር 4 ቀን እንደ ኤልያስና ሄኖክ ሞትን እንዳያይ ወደ ብሔረ ሕያዋን ወስዶታል፡፡

ጌታችን ለዮሐንስ ያልነገረው እርሱም ያላስተማረው ምሥጢር የለም፡፡ ወንጌሉን መጻፍ ሲጀምር ‹‹በመጀመሪያ ቃል ነበረ፣ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ…›› ብሎ የጌታችን ነገር ተመራምሮ ለመድረስ ሲል በመሀል መልአኩን በዮርዳኖስ ባሕር ላይ ሲሄድ አገኘው፡፡ መልአኩም የዮርዳኖስን ባሕር በእንቁላል ቅርፊት እየጨለፈ ወደ ውጭ ሲያፈስ ተመለከተው፡፡ ዮሐንስም ተገርሞ ‹‹ምን ማድረግህ ነው›› አለው፡፡ መልአኩም ‹‹የዮርዳኖስን ባሕር ቀድቼ እየደፋሁ ልጨርሰው ነው›› ሲለው ዮሐንስም መልሶ ‹‹ታዲያ በእንቁላል ስባሪ ነውን?›› አለው፡፡ መልአኩም ‹‹አዎን›› አለው፡፡ ዮሐንስም ‹‹በከንቱ ደከምክ›› አለው፡፡ ይህን ጊዜ መልአኩም መልሶ ‹‹አንተስ እንጂ ደግሞ የአምላክን መገኘት፣ አኗኗሩንም ተመራምረህ በጥበብ ለማግኘት ብለህ ‹በመጀመሪያ ቃል ነበረ፣ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ..› ብለህ ጀምረህ የለምን? አንተ ጌታን ተመራምረህ ካገኘህና ከደረስክበት እኔም የዮርዳኖስን ወንዝ በዚህ እንቁላል ቅርፊት ቀድቼ እጨርሰዋለሁ›› አለው፡፡ ዮሐንስም ይህን ጊዜ ደንግጦ ዝቅ ብሎ ‹‹ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ…›› ብሎ ሀሳቡን ለወጠና ሌላ ታሪክ ቀጠለ፡፡

እናቱም በሕፃንነቱ ስለሞተች እመቤታችን ናት እየተንከባከበች ያሳደገችው፡፡
ጌታችንን እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ በመከተሉ ክርስቲያኖችን ሁሉ ወክሎ በአደራ ድንግል እመቤታችንን ተቀብሏል። ከእርሷ ጋር ለ15 ዓመታት እየተንከባከበ ቢቀመጥ መዝገበ ምሥጢር ሆነ። ስንኩዋን ከሰው ልጆች ይቅርና ከልዑላኑ መላዕክትም ማዕረጉ ከፍ አለ። ሰው ቢበቃ መላእክትን ሊያይ ይቻለዋል። ቅዱስ ዮሐንስን ግን መላእክት ሊያዩት ይከብዳቸዋል። ከፍጥረት ወገን ከእመ ብርሃን ቀጥሎ ክቡር እርሱ ነው።

ቅዱስ ዮሐንስ በመልኩም ከጌታችን ጋር ይመሳሰል ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ሥዕል የመሳል ተሰጥኦም ነበረው፡፡ ጌታችን በተሰቀለበት ዘመን የነበረው ጢባርዮስ ቄሳር ልጁ በሽተኛ ነበር፡፡ የጌታችንን የማዳን ሥራ እየሰማ እነ ጲላጦስም ስለጌታችን የሚጽፉለትን ይሰማ ስለነበር ልጁን ከጌታችን መቃብር ላይ እንዲያኖሩለት ላከው፡፡ ልጁም ፈጥኖ ተፈወሰለት፡፡ ጢባርዮስ ቄሳርም በልጁ መዳን ምክንያት የጌታችንን ውለታ ማስቀመጥ ፈልጎ የጌታችንን ሥዕሉን የሚሥልለትን ሲያጠያይቅ ዮሐንስን አገናኙት፡፡ ዮሐንስም ጌታችንን ልክ በዕለተ ዓርብ እንደተሰቀለ አድርጎ በመሣል ለጢባርዮስ ቄሳር ሰጠው፡፡ ሲሥለውም በመጀመሪያ ጌታችንን ልክ እንደተሰቀለ አድርጎ ራቁቱን ነበር የሳለው፡፡ ዮሐንስ የሳለው የጌታችን ሥዕልም አፍ አውጥቶ ‹‹በመጀመሪያ አይሁድ በኢየሩሳሌም ራቁቴን ሰቀሉኝ፣ አሁን ደግሞ አንተ ድጋሚ በሮም ራቁቴን ትሰቅለኝን?›› ብሎ ተናገረው፡፡ ዮሐንስም እጅግ ደንግጦ ‹‹እንዴት አድርጌ ልሳልህ?›› ብሎ የሳለውን ሥዕል ቢጠይቀው ሥዕሉም ‹‹ከለሜዳ አልብሰህ ሳለኝ›› አለው፡፡ ዮሐንስም እንዳለው ከለሜዳ አልብሶ ከሳለው በኋላ ሥዕሉን ትኩር ብሎ ተመልክቶ ቢስመው ከንፈሩ አንድ ቀን ተኩል ያህል ተጣብቆ ቆይቷል፡፡ ዛሬም ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የምትጠቀምባቸውን የጌታችንን ስነ ስቅለት የሚያሳዩ ሥዕሎች መገኛቸው ይህ ወንጌላዊው ዮሐንስ የሳለው ሥዕል ነው፡፡
ቅዱሱ ከጌታችን ዕርገት በሁዋላ ለ70 ዓመታት በዚህ ምድር ሲኖር አብዛኛውን ጊዜውን ያሳለፈው በኤፌሶን አካባቢ ነው። ሕዝቡን ወደ ክርስትና ለማምጣት በአፍም በመጽሐፍም ደክሟል።

ሶስት መልዕክታት ፣ ራዕዩንና ወንጌልን ጽፎላቸዋል። ሕይወትን ስለ ሰበከላቸው በፈንታው ብዙ አሰቃይተውታል። ከእሳት እስከ ስለት: እስከ መጋዝም በስተእርጅና ደርሶበታል። እርሱ ግን በትእግስቱ ገንዘብ አድርጉዋቸዋል።

ቅዱስ ዮሐንስ በእናት ቤተ ክርስቲያን በተለያዩ ስሞች ይጠራል፡፡
➛ ፍቁረ እግዚእ
በሕይወቱና በኑሮው ሁሉ ጌታችንን ለመምሰል ይጥር ነበርና ጌታችንም እጅግ ይወደው ስለነበር "ፍቁረ እግዚእ" ተብሎ ይጠራል።
➛ ዮሐንስ ወልደ ዘብድዮስ
የታላቁ ያዕቆብ ታናሽ ወንድም ስለሆነና አባቱም ዘብድዮስ ስለሚባል ዮሐንስ ወልደ ዘብድዮስ ይባላል።
➛ ወልደ ነጎድጓድ
ለጌታችን ባለው ቅናትና ከወንድሙ ጋር ሆነው ባሳዩት የኃይል ሥራ እንዲሁም የጌታችንን አምላክነት በመግለጡ "ወልደ ነጎድጓድ" ተብሏል።
➛ ታኦሎጐስ (ነባቤ መለኮት)
ነገረ መለኮትን ከሌሎቹ በበለጠ ሁኔታ አስፍቶና አምልቶ በማስተማሩ "ነባቤ መነኮት ወይም ታኦሎጎስ" ተብሏል
➛ አቡቀለምሲስ (ምሥጢራትን ያየ)
ኃላፊውንና መጻዒውን ጊዜ በራእዩ ስለገለጠ "አቡቀለምሲስ" ይባላል። ይህም በግሪክኛ ባለራእይ ማለት ነው።

➛ ቁጹረ ገጽ
የጌታችንን መከራ መስቀሉን እያስታወሰ 70 ዘመን ሙሉ እያለቀሰ ስለኖረና ፊቱም በሀዘን ስለተቋጠረ "ቁጹረ ገጽ" ተብሏል፡፡
➛ ወንጌላዊ
➛ ሐዋርያ
➛ ሰማዕት ዘእንበለ ደም
➛ ደቀ መለኮት ወምሥጢር
➛ ርዕሰ ደናግል (የደናግል አለቃ)
➛ ዘረፈቀ ውስተ ሕጽኑ ለኢየሱስ (ከጌታ ጎን የሚቀመጥ)
➛ ንስር ሠራሪ
➛ ልዑለ ስብከት
➛ ምድራዊው መልዐክ
➛ ዓምደ ብርሃን
➛ ሐዋርያ ትንቢት
➛ ቀርነ ቤተ ክርስቲያን
➛ ኮከበ ከዋክብት

በዚህች ዕለት ቅዱሱ ሐዋርያ ከእናቱ ማርያም ባውፍልያ ፤ ከአባቱ ዘብዴዎስ መወለዱን ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች።
በቅዱስ ዮሐንስ ላይ ያደረ የእመቤታችን ድንግል ማርያምና የአንድ ልጇ ፍቅር በእኛም ላይ ይደር። ቸሩ ጌታ ስም አጠራራቸው ካማረና ከከበረ ወዳጆቹ በረከትን ያሳትፈን::

➛ መስከረም 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ኢያሱ ወልደ ነዌ (ነቢይና መስፍን)
2.ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ (ልደቱ)
3.ቅዱሳን ዘብዴዎስና ማርያም ባውፍልያ
4.አባ መቃርስ ሊቀ ዻዻሳት
5.አባ ሙሴ ዻዻስ

➛ ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
2.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
3.ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ (ሰማዕት)

"አሁንም እግዚአብሔርን ፍሩ። በእውነተኛም ልብ አምልኩት . . . እግዚአብሔርን ማምለክ ክፉ መስሎ ቢታያችሁ . . . የአሞራውያንን አማልክት ታመልኩ እንደ ሆነ: የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ። እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።"
(ኢያሱ. 24:14)

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአማላጅነታቸው የምንታመን የተዋሕዶ ልጆች የሆንን ሁላችንን የድባውን የአቡነ ሙሴን፣ የወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስንና የነቢዩን የቅዱስ ኢያሱን ረድኤት በረከታቸውን ያሳድርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡

ምንጭ፦ የመስከረም ➍ እና የጥር ወር ስንክሳር ፣

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ጸሎት ይማረን። አሜን።
⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0

መስከረም ❸ 🀄️ን 2011 ዓ.ም

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።መስከረም 3 በአንበሳ ላይ ተጭነው ይጓዙ የነበሩት ኢትዮጵያው ጻድቅ አቡነ አንበስ ዘአዘሎ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ➛  በበረሃ ዝናብ...
13/09/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።
መስከረም 3 በአንበሳ ላይ ተጭነው ይጓዙ የነበሩት ኢትዮጵያው ጻድቅ አቡነ አንበስ ዘአዘሎ ዕረፍታቸው ነው፡፡
➛ በበረሃ ዝናብን ያዘነበ፣ አራዊት ሁሉ እየተገዙለት፣ 45 ዓመት በታላቅ ተጋድሎ የኖረ በኀላም ሰይጣን በፈተና ጥሎት የነበረና በኋላም ሰይጣንን ድል ያደረገው አቡነ ሙሴ ዘገዳመ ሲሐት ዕረፍቱ ነው፡፡
➛ አባ ዲዮናስዮስ ዕረፍቱ ነው።

🔥 አባ ዲዮናስዮስ

ይኸውም የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳት ሲሆን እርሱም የትንሣኤ ሙታንን ድርሳን የደረሰው ነው፡፡ ይኸውም ‹‹ነፍስ ከሥጋ ጋር ትሞታለች፣ በትንሣኤም ከሥጋ አብራ ትነሣለች›› የሚሉ መ-ናፍ‑ቃን ከዐረቢያ አገር በመነሳታቸው ቅዱስ ዲዮናስዮስ በግብጽ የአንድነት ገባዔ አድርጎ ቢያስተምራቸው እምቢ ቢሉት ዛሬ በቤተ ክርስቲያን ስለ ትንሣኤ ሙታን የሚነገረውንና የነፍስን ረቂቅነት፣ ዘላለማዊና ሕያዊት መሆኗን የሚናገር ድርሳን ደረሰ፡፡ እግዚአብሔርንም ሲያገለግል ኖሮ በሰላም ዐርፎ ወደሚወደው አምላክ ሄደ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡

🔥 አቡነ አንበስ ዘአዘሎ

ከቅድስናው የተነሣ ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀሰው በአንበሳ ላይ ተጭኖ ነው፡፡ ተአምራትን በማድረግና ወንጌልን በማስተማር በጾም ጸሎት አብዝቶ የደከመ ሲሆን ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ሌት ተቀን በጸሎት ይተጋ የነበረ ታላቅ አባት ነው፡፡ አቡነ አንበስ ትውልዱ ትግራይ አድዋ በእንጭጮ ወረዳ ነው፡፡ በስሙ ትግራይ አድዋ "እንጭጮ አቡነ አንበስ ገዳም" እና በትግራይ ሽሬ ሁለት ትላልቅ ገዳማት አሉት፡፡ ቅዱስ ያሬድ በድርሰቱ ደጋግሞ የጠቀሳቸው ሲሆን የያሬድንም የድርሰቱን የአቋቋም ሥርዓት ያመጡት አቡነ አንበስ ናቸው፡፡
አቡነ አንበስ በአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እና በአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ጊዜ የነበሩ ሲሆን እሳቸውንም አንበሶች ያገለግሏቸው ነበር፡፡ ጻድቁ አቡነ አንበስ ከአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጋር የተገናኘ ትልቅ ታሪክ አላቸው፡፡ የላዕላይ ግብጹ አባ ብንያም፣ በአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ እና የአዘሎው አቡነ አንበስ እነዚህ 3ቱ ቅዱሳን ከየአሉበት በአንበሳቸው ተጭነው ዝቋላ አቡዬ ዘንድ እንደደረሱ የአቡዬ አንበሶች የ3ቱንም ቅዱሳን አንበሶች ዋጡዋቸው፣ አቡዬም በዚህ አዝነው ከበዓታቸው ወጥተው አንበሶቻቸውን ‹ትፉ› ብለው የበሉአቸውን አንበሶቻቸውን አስተፍተዋቸው ለ3ቱም ቅዱሳን የተበሉባቸውን አንበሶቻቸውን መልሰውላቸዋል፡፡ ይኸውም የሆነው እኝዲህ ነው፡- አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዝቋላ 7ቱ ሊቃነ መላእክት እየረዷቸው ሰባ ሺህ እልፍ አጋንንትን በእሳት ሰይፍ ፈጅተው ካጠፏቸው በኃላ ወደ ምድረ ከብድ ተመለሱ፡፡ ከዚህም በኀላ መንፈስ ቅዱስ የጠራቸው ሦስቱ ቅዱሳን አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ አቡነ አንበስ ዘአዘሎ እና የላዕላይ ግብጹ አቡነ ብንያም በአንበሶቻቸው ሆነው ወደ ጻድቁ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘንድ ምድረ ከብድ ገዳም መጡ፡፡
አባታችን ግን ስለተሰወራቸው እስከ 7 ቀን ድረስ በምህላ ሰነበቱ፡፡ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንበሶችም መጥተው የ3ቱን ቅዱሳን አንበሶች በልተውባቸው ተሰወሩ፡፡ 3ቱም ቅዱሳን ፈጽመው ደነገጡ፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስም የቅዱሳኑን ሀዘንና ድንጋጤ ተመልክተው በታላቅና በሚያስፈራ ግርማ ሆነው ስልሳ ነብሮችንና ስልሳ አንበሶችን አስከትለው ተገለጡላቸው፡፡ ቅዱሳኑም ከአቡዬ ግርማ የተነሣ ስለደነገጡ እንዳይፈሩም አረጋጉአቸው፡፡
ከዚህም በኃላ አባታችን "በምን ምክንያት ወደዚህ ገዳም ወደ እኔ መጣችሁ?" አሏቸው፡፡ ሦስቱ ቅዱሳን እንዲህ አሉ፡- "ጸሎትህ ቅድስት እንደሆነች ባወቅን ጊዜ ወደ አንተ መጣን፤ አንተ በሁሉ ርእሰ ባሕታውያን ነህና የእግዚአብሔርን ሥራ ትነግረን ዘንድ መጣን፤ ባላገኘንህም ጊዜ እስከ 7ቀን አለቀስን" አሉት፡፡ ዳግመኛም "አንበሶችህ መጥተው አንበሶቻችንን ደማቸውን ጠጡ ቆዳቸውንም በጥፍራቸው በጣጠሱ" ብለው ነገሯቸው፡፡ አባታችንም ይህንን ሲሰሙ አንበሶቻቸውን "እስከ ዕለቴ ሞቴ ድረስ በእግሬ ከረገጥኩት ትቢያ በቀር ምንም እንዳትበሉ ታዛችሁ የለምን? እግዚአብሔር ያላዘዛችሁትን ለምን በላችሁ? በሉ አሁንም የበላችሁትን ትፉ" አላቸው፡፡ እነዚያም አንበሶች አፋቸውን ከፍተው አንዳች ሳያስቀሩ አጥንታቸውን ሥጋቸውን በሙሉ ተፉአቸው፡፡ ጻዲቁ አባታችንም ወደ ምሥራቅ ተሠልሰው እግዚአብሔርን ከለመኑ በኃላ በአንበሶቹ ሥጋ ላይ ባረኩና "በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ተነሡ" አሏቸው፡፡ አንበሶቹም እንደ ዐይን ፈጥነው ተነሥተው እንደ ቀድሞው ሆኑ፡፡
የአቡነ አንበስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡

🔥 አቡነ ሙሴ ዘገዳመ ሲሐት

በሲሐት ገዳም ውስጥ በታላቅ ተጋድሎ ይኖሩ የነበሩ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ የሚመገቡትም የዘንባባ እንጨትና የወደቁ የዘይቱን ፍሬ ነበር፡፡ እነዚህንም ቢሆን አንድ ወፍ ከሚበላው የበለጠ አይመገቡም ነበር፡፡ ልብሳቸውም ከዘንባባ ቅጠል የተሠራ ሰሌን ነው፡፡ የዱር አራዊት ሁሉ ይገዙለት የነበረ ሲሆን የጸሎት ጊዜው ሲደርስ ብቻ እንዲሄዱ ይነግራቸዋል፡፡ ድርቅ ሲሆንባቸውም መጥተው በፊቱ ይቆማሉ፡፡ አቡነ ሙሴም የልባቸውን ፍላጎት በመንፈስ ቅዱስ ስለሚያውቅ ዝናብ በጸሎቱ እንደዘንብላቸው ያደርጋል፡፡ እንዲህም እያደረገ ከአራዊቱ ጋር እየኖረ በጾም በጸሎት እየተጋ 45 ዓመት ተቀመጠ፡፡
ነገር ግን አቡነ ሙሴ መጻሕፍትን የሚውቁ አልነበሩም፡፡ ሰይጣንም በኑሮአቸው ቀናባቸውና በተለያየ ሁኔታ እየተገለጸ በፈተና ሊጥላቸው አሰበ፡፡ ከበዓታቸው ሆነው ሳለ ዘመኑ ያለፈበት እጅግ የደከመ ሽማግሌ መስሎ በመንገድ ሲያዘግም ታያቸው፡፡ አቡነ ሙሴም ገዳማዊ መናኝ መስሏቸው ሄደው አምጥተው ከገዳማቸው አስገቡት፡፡ የዱር አራዊቱ ግን ሰይጣን መሆኑን ዐውቀውት ሸሽተው ሄዱ፡፡ አቡነ ሙሴም ሀገሩን፣ ሃይማኖቱንና ኑሮው እንዴት እንደሆነ ጠየቁት፡፡ በሽማግሌ የተመሰለው ሰይጣንም ‹‹እኔ በዓለም ኃጢአት በመሥራት ብዙ ዘመን ኖርኩ፣ አንዲት ሴት ልጅንም ወለድኩ፡፡ ከዚያም የዓለምን ኃላፊነትና ጠፊነት አሰብኩ፡፡ ከዓለምም ወጥቼ በበረሃ ውስጥ 40 ዓመት ኖርኩ፡፡ ልጄን ያገባት እንደሌለ ባሰብኩ ጊዜ በዚህ ነገር ምክንያት ወደ አንተ መጣሁ፣ ከአንተ በቀር የሚያገባት የለምና በሞትኩ ጊዜ የምትቀብረኝ አንተ ነህ፣ ብዙ ሃብትና ብዙም የአትክልት ሥፍራዎች ስላሉኝ ሁሉንም አንተ ትወርሳለህ›› አላቸው፡፡ አቡነ ሙሴም ደንግጠው ‹‹እኔኮ መነኩሴ ነኝ፣ ይህን ማድረግ አይቻለኝም›› አለው፡፡ ሽማግሌውም ‹‹የተመረጡት ጻድቃን ሆነው ሳለ ሚስቶች የነበሯቸው እነ አብርሃምን፣ ሙሴን፣ ዳዊትን…›› ከብሉይ መጻሕፍት ምስክር ማስረጃ አድርጎ እየጠቀሰ አስረዳው፡፡ በዚህም የአቡነ ሙሴን ልብ ወደ ተንኮል አዘነበለው፡፡ ሽማግሌውም በውስጡ ያጌጠች ቆንጆ ልጅ ያለችበት የተሸለመ አዳራሽ በምትሐት አሳየውና ሕመም ያገኘው መስሎ እየደከመ መጣ፡፡ የሞተም መሰለ፡፡ አቡነ ሙሴም አልቅሶ ገንዞ ቀበረው፡፡ ልጅቷ ወዳለችበት ያማረ አዳራሽ ሊገባ ሲል በነፋስ ተመስሎ ወደ ኋላ አዙሮ ጣለውና ወደቀ፡፡ አባ ሙሴም ወደ ልባቸውም ሲመለሱ ልጅቷን፣ አዳራሹን፣ የአትክልቱንም ቦታ አጡት፡፡ ወደ በዓታቸውም ተመልሰው የወዳደቁ ፍራፍሬዎችን አንስተው ለመብላት ሲሉ ሌላ ጊዜ እንደማር እየጣፈጣቸው ይመገቡት የነበረው ፍሬ ዛሬ ግን እንደ እሬት እጅግ መራራ ሆነባቸው፡፡ የዱር አራዊቱም ፈጽመው ራቋቸው፡፡ በጣም እርቧቸው ሳለ ወደ በዓታቸው ተመለሱ፡፡

አሁንም ያ ሰይጣን ወደ እስክንድያ የሚሄድ ሽማግሌ ነጋዴ መስሎ በአህያ ላይ ተቀምጦ ታያቸው፡፡ መብልና መጠትም ይዞ ነበር፡፡ አቡነ ሙሴንም ከእርሱ ጋር ወስዶ ወደ አንድ አገር አድርሶ ከዚያ ተዋቸው፡፡ ለሦስተኛ ጊዜም ሰይጣን በገዳም በምናኔ በምትኖር ሴት መነኩሴ ተመስሎ ተገለጠላቸው፡፡ እርሷም ውኃ የምትቀዳ መነኩሴ መስላ ቀረበችው፡፡ አቡነ ሙሴንም ‹‹ሥራህ ምንድነው?›› አለችው፡፡ አቡነ ሙሴም መነኩሴ እንደሆነና አሁን ሰይጣን በፈተና እንደጣለው የደረሰበትን ሁሉ ነገራት፡፡ እርሷም በልቧ ሳቀችበትና ወደቤቷ ወስዳ አብልታ አጠጥታ አጠገበችው፡፡ ከዚያም በብዙ ሽንገላ የጋብቻን ነገር አሳሰበችው፡፡ እጅግ ብዙ ገንዘብ እንዳላት፣ የሟች የንጉሥ ልጅ እንደሆነችም ነገረችው፡፡ ልቡም እንዳዘነበለ አይታ አይሁዳዊት መሆኗን በመንገር ብዙ ተስፋ አስደረገችው፡፡ ‹‹ወደ በረሃ ሄደን ቀብሬ ያኖርኩትን ብዙ ወርቅና ገንዘብ አውጥተን እንጠቀምበት›› በማለት ወደ በረሃ ወሰደችው፡፡ ትልቅ ተራራ ላይ ይዛው ከወጣች በኋላም ተለወጠችበት፡፡ እንዲህም አለችው፡- ‹‹እኔ ብዙዎችን ያሳትኩ ሰይጣን ነኝ፣ አንተንም ከገዳምህ አውጥቼ ሃይማኖትህንም አስካድኩህ፣ እነሆ በዚህ በረሃ ሙተህ ነፍስህ ወደ ገሃነም ትወርዳለች›› ብላው ተሰወረች፡፡ አቡነ ሙሴም ወደ ልቡ በተመለሰ ጊዜ በግራኝም በቀኝም መመለሻ መንገድ አጣ፡፡ ምድር ጠበበችውና አዙሮት ወድቆ በፊቱ ላይ አፈር እየነሰነሰ ጮኸ፡፡ ነፍሱም ከሥጋው ለመለየት እስከደረሰች ድረስ በምድር ላይ እየተንከባለለ ፈጣሪውን ተማጸነ፡፡
መሐሪና ይቅር ባይ አምላከም የቀድሞ ዘመን ተጋድሎውን አስቦ በቸርነቱ ራርቶለት ያጽናናው ዘንድ መልአኩን ላከለት፡፡ መልአኩም ‹‹አይዞህ አትፍራ ኃጢአትህ ተሠረየችልህ፣ ከሰባት ቀንም በኋላ ታርፋለህ፣ የእግዚአብሔር አገልጋይ ሳሙኤልም መጥቶ ይቀብርሃል›› አላቸው፡፡ ሳሙኤልም መጥቶ ንጉሥ ኢጋቦም በበረሃ አንጾአት ወደነበረች ገዳም ወሰደው፡፡ እርሷም የተሰወሩ ቅዱሳን የሚሰበሰቡባት ከዓለማውያን ሰዎች ተሰውራ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ ሳሙኤልም መሥዋዕትን ሲያሳርጉ አድርሶት አቡነ ሙሴ ሥጋ ወደሙን ከተቀበለ በኋላ መስከረም 3 ቀን በሰላም ዐርፎ ሳሙኤል ቀብሮታል፡፡
የአቡነ ሙሴ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡

ምንጭ፦ የመስከረም ❸ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃 🍃🍃🍃 🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0

መስከረም ❷ 🀄️ን 2011 ዓ.ም

.             🔰 መስከረም 2   🔰በዚህች ቀን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አንገቱ የተቆረጠበት ቀን ነው።              የ 2 ዓመት ከመንፈቅ ሕጻን እያለ ከእናቱ ኤልሳቤጥ ...
12/09/2025

. 🔰 መስከረም 2 🔰
በዚህች ቀን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አንገቱ የተቆረጠበት ቀን ነው።

የ 2 ዓመት ከመንፈቅ ሕጻን እያለ ከእናቱ ኤልሳቤጥ ጋር ወደ ሲና በርሃ ተሰደደ፤ በ 7 ዓመቱ እናቱ በርሃ ላይ ሞተችበት በድኗን ታቅፎ አለቀሰ። ጌታችን ለእመቤታችን ዘመድሽ ኤልሳቤጥ አርፋለች አላት። አዘነች ደመና ጠቅሶ ወደዚያው እንሂድ አላት። ዮሴፍና ሶሎሜን ጨምረው ወደ ዮሐንስ መጡ ብቻውንም ሲያለቅስ አገኙት፤ ከሰማይ ዘካርያስና ስምዖን ወርደው ገንዘው ቀበሯት።

እመቤታችን ለጌታ ዮሐንስን ይዘነው እንሂድ አለችው፤ ጌታም የለም መንገዴን ጠራጊ ነውና የአባቴ ፈቃድ እዚሁ በረሃ እንዲኖር ነው አላት።

ቅዱስ ዮሐንስ ኤልሳቤጥ ያሰፋችለት የግመል ቆዳ ነበረች እርሷን ለብሶ አንቦጣ የሚባል ቅጠልና የበርሃ ማር እየበላ በብሕትውና ኖረ። 30 ዓመት ከመንፈቅ ሲሆነው ወደ ዮርዳኖስ ወጣ የጌታን መንገድ አቅኑ እያለ አዋጅ ተናገረ ጌታንም አጠመቀ፤

የወንድሙን ሚስት በማግባቱ ቢወቅሰው በዚህ ተናዶ እና በሚስቱ ጥያቄ ጳጉሜ 1 ሄሮድስ እስርቤት ከተተው። በዛሬዋ ቀንም አንገቱን ቆረጠው። የተቆረጠች አንገቱ ክንፍ አውጥታ 15 ዓመት በደቡብ አረቢያና አካባቢው ሰብካ ሚያዚያ 15 ቀን በክብር አረፈ፤

ከብዙ ዘመናት በኋላ ያ ቦታ የነጋድያን ማደሪያ ሆነ፡፡ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ሁለት አማንያን ነጋዴዎች ወደዚያ ቦታ ደርሰው አደሩ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በሕልም ገለጠላቸውና የከበረች ራሱን ያወጡ ዘንድ አዘዛቸው፡፡ እነርሱም አወጡአት፡፡ ከእርሳቸውም ጋር ወደ ቤታቸው ወስደው ታላቅ ክብርን አከበሩዋት። ደቀመዛሙርቱ ከቀሪው አካሉ ጋር አድርገው ቀበሩት።

" ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችኋለሁ፥ ከነቢይም የሚበልጠውን።

‘እነሆ፥ መንገድህን በፊትህ የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ፡’ ተብሎ የተጻፈለት ይህ ነውና።

እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም።"

(ማቴ 11 : 9- 11 )

ለእግዚአብሔር ምሥጋና ይሁን እኛንም መለኮትን በአጠመቀ በከበረ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን ልዩ የሆነች በረከቱም ከእኛ ጋር ትሁን፤ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ስንክሳር

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።መስከረም  2 መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት አረፈ፡፡ 🔥 መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስዮሐንስ ማለት ‹‹ፍሥሐ ወሐሴ...
11/09/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።

መስከረም 2 መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት አረፈ፡፡

🔥 መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ

ዮሐንስ ማለት ‹‹ፍሥሐ ወሐሴት፣ ርኅራኄ›› ማለት ነው፡፡ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ጠራጊ የሆነው ቅዱስ ዮሐንስ የብሉይ ኪዳን የመጨረሻው የሐዲስ ኪዳን ደግሞ የመጀመሪያው ነቢይ ነው፡፡ ስለ ወላጆቹ ስለ ካህኑ ዘካርያስና ስለ ቅድስት ኤልሳቤጥ በቅዱስ ወንጌል ላይ እንዲህ ተብሎ ተመስክሮላቸዋል፡፡ ‹‹በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስሟም ኤልሳቤጥ ነበረ። ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ።›› ሉቃ 1፡5-6፡፡

በዚህች ዕለት መስከረም 26 ቀን እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ የራማውን ልዑል ቅዱስ ገብርኤልን ወደ በራክዩ ልጅ ዘካርያስ ልኮት መጥምቁ ዮሐንስ ከእርሱ ስለመወለዱ አበሰረው፡፡ እግዚአብሔር ወደ በራክዩ ልጅ ወደ ዘካርያስ ልጅ እንደሚወልድ ይነግረው ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ላከው፡፡ እርሱም በመሠዊያው በስተቀኝ በኩል ተገልጦ ለዘካርያስ ታየው፡፡ ለሰይጣን ቀኝ የለውምና መልአክ ግን ብርሃናዊ የማናዊ ነውና መልአክ እንደሆነ ለማጠየቅ በቀኝ በኩል ተገልጦ ታየው፡፡ አንድም ሰው ሁሉ ወደ የማናዊ ግብር የሚመለስበት ዘመን ደረሰ ሲል በቀኝ በኩል ታየው፡፡ አንድም ሰውን ሁሉ መክሮ አስተምሮ ወደ ቀኝ ወደ መንፈስ ቅዱስ ሥራ የሚመልስ ልጅ ትወልዳለህ ሲለው በቀኝ በኩል ተገልጦ ታየው፡፡ ነገር ግን ዘካርያስ የእርሱም ሆነ የሚስቱ ዕድሜአቸው ስለገፋ የሚስቱን የመፀነሷን ነገር አላምን ቢል መልአኩ ድዳ አድርጎታል፡፡

የአገሯ ሰዎች ሁሉ መካን በመሆኗ አልሳቤጥን ‹‹ጡተ ደረቅ፣ ማኅፀንሽም የተዘጋ፣ በረከትን ያጣሽ፣ መርገምንም የተመላሽ፣ የበቅሎ ዘመድ፣ ቢወልዷት እንጂ አትወልድ…›› እያሉ ይሰድቧት ነበር፡፡ አልሳቤጥም ‹‹በዚህ ወራት መፀነሷን ባወቀች ጊዜ ስድቤን ሁሉ ከሰው ያርቅልኝ ዘንድ እግዚአብሔር በረድኤት በጎበኘኝ ጊዜ እንዲህ አደረገኝን!›› ብላ አምስት ወር ፅንሷን ሠወረች (ለማንም አልተናገረችም)፡፡ እነርሱም ‹ይህቺ ሴት የበላችው ቂጣ ቢነፋት ፀነስኩ ትላለች›› ብለው ቢሰድቧት እንጂ ሌላ ረብ (ጥቅም) ባልነበረው ነበር፡፡ ኤልሳቤጥም ስድስት ወር በሆናት ጊዜ መልአኩ ለቅድስት ድንግል ማርያም አምላክን እንደምትወልድ አበሰራት፡፡ ድንግል ማርያምም መልአኩ ስለ ኤልሳቤጥ መፀነስ የነገራትን ለማረጋገጥ ወደ እርሷ ሄደች፡፡ እመቤታችንም ‹‹እንዴት ነሽ?›› ስትላት ኤልሳቤጥ በሰማች ጊዜ በማኅፀኗ ያለው ፅንስ በደስታ ሰገደ፡፡

ኤልሳቤጥም ‹‹እንዴት ነሽ?›› ስትላት የእመቤታችንን ድምፅ በሰማች ጊዜ የፈጠረው አምላክ በማርያም ማኅፀን ውስጥ መኖሩን አወቀ፡፡ የዓለሙ መድኃኒት ፈጣሪው በድንግል ማርያም ማኅፀን ውስጥ መኖሩን ለማየት የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዐይኖች በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ በእናቱ ማኅፀን ውስጥ የተገለጡ ሆኑ፡፡ የሁለቱም የማኅፀን መጋረጃዎች ሳይገለጡ ፈጣሪውን ለማየት የዮሐንስ ዐይኖች በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ተገልጠው እንደ መስታዎት ሆኑለት፡፡ የሁለቱም የማኅፀን መጋረጃዎች ፈጣሪውን ለማየት የዮሐንስ ዐይኖች አልከለከሉትም፡፡ መልአኩ ለአባቱ ለዘካርያስ ‹‹ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስን የተመላ ይሆናልና›› ብሎ እንደነገረው በእናቱ ማኅፀን ሆኖ በማርያም ማኅፀን ውስጥ ያለውን ፈጣሪውን አየው፡፡ ፈጣሪውንም ለመቀበል ሰገደለት፣ እንደ እንቦሳ ጥጃም በደስታ ፈንድቆ ዘለለ፡፡ በእርሱ ላይም የመላው መንፈስ ቅዱስ በኤልሳቤጥም ላይ መላባትና እንዲህ ብላ ተናረች፡- ‹‹ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ፣ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፡፡ የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እኔ ምንድነኝ?›› አለቻት፡፡

ዮሐንስ ሲወለድ ‹‹ስሙን ማን እንበለው?›› ብለው ድዳ የነበረውን አባቱን ዘካርያስን ቢጠይቁት በጽሑፍ አድርጎ ‹‹ዮሐንስ በሉት›› አላቸው፤ ያንጊዜም አንደበቱ ተፈታለት፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ‹‹ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል›› (ሉቃ 1፡13) ባለው ሰዓት አላመነም ነበር፡፡ አሁን ግን የልጁን ስም ‹‹ዮሐንስ›› ብሎ ሲለው ተዘግቶ የነበረው አንደበቱ ተፈቶለታል፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ጌታችንን በዕድሜ በ6 ወር ይበልጠዋል፡፡ ርጉም የሆነ ሄሮድስ መሢሕ ሕፃን ክርስቶስ መወለዱን ሲሰማ መንግሥቴን ይቀማኛል ብሎ በመፍራት በቤቴልሔም ያሉ ሁለት ዓመትና ከዚያ በታች ያሉ 144,000 (መቶ ዐርባ አራት ሺህ) የቤቴልሔም ሕፃናትን በሰይፍ ሲያስገድል ድንግል ማርያም ከልጇ ጋር ወደ ግብፅ ስትሰደድ፣ ቅድስት ኤልሳቤጥ ደግሞ ወደ ሲና በረሃ ሄዳ ልጇን ዮሐንስን ከዚያ ደብቃዋለች፡፡

ቅዱስ ዮሐንስና እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ወደ በረሃ ከገቡ አምስት ዓመት በሆናቸው ጊዜ እርሱ ዕድሜው ሰባት ዓመት ከመንፈቅ ከሆነው በኋላ እናቱ ኤልሳቤጥ ሞተችበትና ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ተወችው፡፡ ዮሐንስም በሰፊዋ በረሃ ውስጥ በአራዊቶች መካክል ብቻውን ቀረ፡፡ ለዮሐንስ ግን በእርሱ ላይ ምንም መጥፎ ነገር ሳያደርጉ የቶራና የአንበሳ፣ የነብርም ልጆች እንደ ወንድምና እንደ እኅት ሆኑት፡፡ አራዊቶችም ሁሉ ወዳጅ ሆኑት እንጂ፡፡ ምግቡም የበረሃ ቅጠል ነው፤ መጠጡም ከተቀመጠባት ድንጋይ ሥር የምትፈልቀው ውኃ ነበረች፡፡ ዮሐንስ ሰውነትን አለምልመው፣ ሥጋን አለስልሰው፣ ገጽንና ፊትን የሚያሳምሩትን የበረሃ ቅጠሎችንም አልተመገበም፡፡ አንቦጣ ከተባለችው ከአንዲት የበረሃ ቅጠልና ከጣዝማ ማር በስተቀር ከሚበሉት ምግቦች ሁሉ ዮሐንስ ሕርምተኛ ሆኖ የተለየ ነበር፡፡ በጣም የሚገርመው ነገር ዮሐንስ እስከ 30 ዓመቱ ድረስ በእንደዚህ ዓይነት ኑሮ ብቻውን የኖረ መሆኑ ነው፡፡ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የጌታችንን መንገድ ለመጥረግ ለእስራኤል መምህር ሆኖ እስከተገለጠ እስከ 30 ዘመኑ ድረስ የሰውን ፊት እንኳን ከቶ ሳያይ በበረሃ ብቻውን ከአራዊት ጋር ኖረ፡፡
ጌታችንም 30 ዓመት በሆነው ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ለእስራኤል ተገልጦ በማስተማርና የንስሓን ጥምቀት በማጥመቅ የጌታን መንገድ ጠረገ፡፡ ክፉዎችን ከክፋታቸው እንዲመለሱ በግልጽ የሚገስጽ ሆነ፡፡ የሄሮድያዳ ልጅ ንጉሥ ሄሮድስን በዘፈኗ በጣም አድርጋ ስላስደሰተችው እርሱም በተራው ሊያስደስታት ፈለገ፡፡ ‹እስከ መንግሥቱ እኩሌታ ድረስም ቢሆን የለመነችውን ይሰጣት ዘንድ በሕዝቦቹና በመኳንንቱ ሁሉ ፊት እንዳይከዳት በፅኑ ቃልኪዳን ማለላት፡፡› እንዲህም እያለ ‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ፣ የመንግሥቴንም እኩሌታ ቢሆን እሰጥሻለሁ ምን ላድርግልሽ?› እያለ በመሐላ ባላት ጊዜ በእናቷ ምክር የዮሐንስን አንገት ቆርጦ ይሰጣት ዘንድ ለመነችው፡፡ ንጉሥ ሄሮድስም ይህን ልመና ከአፏ በሰማ ጊዜ ‹የፈለግሽውን እሰጥሻለሁ› ብሎ በሕዝቡ ፊት ስለማለ ለሰው ይምሰል አዘነ፣ ተከዘ፡፡ ኃዘኑም ስለ ዮሐንስ መሞት አይደለም፣ ዮሐንስን ሕዝቡ ይወደው ስለነበር እነርሱን ስለ መፍራቱና መሐላ ምሎ ከዳ እንዳይባል ነው እንጂ፡፡ ስለ ዮሐንስ አዝኖ ቢሆን ኖሮ ቀድሞውንም በግፍ እንዲታሰር ባላደረገው ነበር፡፡ ወንድሞቼ እኅቶቼ ሆይ! ከመሐላ የተነሣ መፍራት ይገባችኋል፡፡ ‹የለመንሽውን ሁሉ እሰጥሻለሁ› ብሎ ስለማለ ሄሮድስ የዮሐንስን አንገት እንድትቆረጥ አደረገ፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በቅዱስ ወንጌል ‹ፈጽማችሁ አትማሉ› ብሏል፡፡ ከዚህ በኋላ ወታደሮች ሠይፍ ይዘው የዮሐንስን አንገት ይቆርጡ ዘንድ ወደ መኅኒ ቤት ሄዱ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም የሄሮድስ ጭፍሮች ሊገድሉት እንደመጡ በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ስላወቀ ከጨለማው ቤት ውስጥ አንገቱን በመስኮት አውጥቶ እንደሚመቻቸው አድርጎ ጠበቃቸው፡፡ የሄሮድስን ቃል እንዳያቃልሉ ጭፍሮቹም የመጥምቀ መለኮት ዮሐንስን አንገት ስለ መሐላው ቆረጡት፡፡ በመሐላ ምክንያት ባይሆን ኖሮ ሄሮድስ መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን ባላስገደለው ነበር፡፡ ዳግመኛም አለልክ መብላና መጠጣት ካለበት ቦታ እግዚአብሔርን መበደል፣ ማስቀየምና ማስቆጣት ይገኝበታል፡፡ ስካር ከሚገኝበት ቦታ አጋንንትና ኃጢአት ከዚያ አሉ፡፡ ስካርና ዘፈን ከሚገኝበት ቦታ የእግዚአብሔር መቅሰፍት የፈጣሪያችን ቁጣና በቀል ይፈጸምበታልና፡፡ ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ ስለ ዮሐንስ ሲናገር ‹‹ዮሐንስ የሚያበራ መብራት ነበረ›› ነው ያለው፡፡ ዮሐ 5፡35፡፡ ዳግመኛም ክብሩን ሲገልጥለት "እውነት እላችኋለሁ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም" በማለት መስክሮለታል፡፡ ማቴ 11:11፣ ሉቃ 7:28፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡

🔥 ቅዱስ ዳስያ ሰማዕት

በዚችም ቀን በግብጽ ውስጥ ታዕዳ ከሚባል አገር ዳስያ ሰማዕት ሆነ። ይህንንም ቅዱስ የእንዴናው አገረ ገዥ አርያኖስ አሠቃየው ጽኑ ሥቃይንም ከአሠቃየው በኋላ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ።

🔥 ቅዱስ ዲዲሞስና የቅድስት መሪና ሰማዕት

በዚህችም ቀን የሰማዕት ዲዲሞስና የቅድስት መሪና መታሰቢያቸው ነው።

ምንጭ፦ የመስከረም ➋ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃 🍃🍃🍃 🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0

መስከረም ❶ 🀄️ን 2011 ዓ.ም

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።መስከረም 1 ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል የተሾመበት ዕለት ነው፡፡➛  ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ሐዋርያው ቅዱስ በርተሎሜዎስ ዕረፍ...
10/09/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።
መስከረም 1 ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል የተሾመበት ዕለት ነው፡፡
➛ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ሐዋርያው ቅዱስ በርተሎሜዎስ ዕረፍቱ ነው፡፡
➛ ታላቁ አባት ጻድቁ አባ ሚልኪ ዕረፍቱ ነው፡፡
➛ ጻዲቁ ኢዮብም ከበሽታው የዳነው በዚህች ዕለት ነው፡፡
➛ በዚህችም ቀን ዳግመኛ የታላቂቱ አገር የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሜልዮስ አረፈ።

🔥 ጻድቁ ኢየብ

ጻዲቁ ኢዮብ በፈሳሽ ውኃ ታጥቦ ከደዌው ሁሉ ስለተፈወሰ ለሰዎች ልማዳቸው ሆኖ ዓመቱ ዞሮ ሲመጣ ፈሳሹ ውኃም በመላ ጊዜ በአዲስ ውኃ ይጠመቃሉ፣ በእርሱም ይባረካሉ፡፡

🔥 አባ ሜልዮስ

በዚህችም ቀን ዳግመኛ የታላቂቱ አገር የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሜልዮስ አረፈ። እርሱም ለአባታችን ሐዋርያና ወንጌላዊ ለሆነ ማርቆስ ሦስተኛ ነው።

ይህም አባት የሮሜ ንጉሥ አስባስያኖስ በነገሠ በ15 ዓመት ተሾመ ይኸውም የክብር ባለቤት ጌታችን በዐረገ በ40 ዓመት ነው። ክብር ይግባውና የክርስቶስን መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው በሹመቱም 12 ዓመት ኖረ። እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም በፍቅር አንድነት አረፈ።

🔥 ሐዋርያው በርተሎሜዎስ

ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ዕጣ የደረሰው አልዋሕ በሚባል አገር ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ሊያደርሰው አብረው ወደ አልዋሕ ሄዱ፡፡ ወደ ከተማው ለመግባት ምክንያት ፈለጉና ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ በርተሎሜዎስን "አትክልተኛ ባለሙያ ነው" ብሎ የወይኑን ቦታ እንዲጠብቅለት ለአንድ ባለጸጋ መኰንን ባሪያ አድርጎ ሸጠው፡፡ ባለጸጋውም በርተሎሜዎስን በ30 እስቴታር ገዝቶት ሄደ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ገንዘቡን ደብቆ ለቅዱስ በርተሎሜዎስ በድብቅ ሰጥቶት እንዲመጸውተው ነግሮት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ፡፡ አልዋሕ ከገባ በኋላ ቅዱስ በርተሎሜዎስ የወይን ቦታው አለቃ ሆኖ 40 ቀን ተቀመጠ፡፡ ወንጌሉን ባለመስበኩ በሀዘን እያለቀሰ ጌታችንን በጸሎት ጠየቀው፡፡ በገንዘቡ ገዝቶት ባሪያው ያደረገው ባለጸጋውም የወይኑን ቦታ ያይ ዘንድ እንደመጣ መርዘኛ እባብ ነድፎት ሞተ፡፡ ሕዝቡም ተሰብስቦ ሲያለቅስ በርተሎሜዎስ ግን ወደ ጌታችን ከጸለየ በኋላ ሄዶ ባለጸጋውን ሰው ከሞት አስነሣው፡፡ በዚህም ሕዝቡ ሁሉ አምነው ተጠምቀዋል፡፡
በርተሎሜዎስም ወደ ሌሎች አገሮች ሄዶ አስተማረ፡፡ ጌታችን ወደ በርበሮች ዘንድ ሄዶ ወንጌልን እንዲሰብክ አዘዘው፡፡ ረዳት እንዲሆነውም እንድርያስን ከደቀ መዝሙሩ ጋር ላከለት፡፡ የሀገሪቱ ሰዎች ግን እጅግ ክፉዎች ነበሩ፡፡ በሐዋርያቱም ፊት በአስማት አስደናቂ ተአምራት እያሳዩ ትምህርታቸውን የማይቀበሏቸው ሁኑ፡፡ ይህን ጊዜ ጌታችን ሰውን ከሚበሉ አገር አንዱን ገጸ ከልብ ይታዘዝላቸው ዘንድ በሚያዙትም ነገር ሁሉ ከትእዛዛቸው እንዳይወጣ አዘዘው፡፡ ሐዋርያትም ወደ በርበሮች አገር ዳግመኛ በገቡ ሰዓት ይበሏቸው ዘንድ ኃይለኛ አራዊትን አውጥተው ለቀቁባቸው፡፡ ያ ገጸ ከልብም በአራዊቱ ላይ ተነሥቶ እየነጠቀ በላቸው፡፡ ይህንንም የተመለከቱት በርበሮች እጅግ ፈርተው በድንጋጤ ብቻ የሞቱ አሉ፡፡ በሐዋርያቱም እግር ሥር ወደቁ፡፡ ሐዋርያቱም አስተምረው ካሳመኗቸው በኋላ አጥምቀዋቸዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ቅዱስ በርተሎሜዎስ እግዚአብሔርን ወደማያውቁ አገሮች ሄዶ ብዙ ተአምራትን እያደረገ አስተምሮ አጠመቃቸው፡፡ የከሃዲው ንጉሡ የአግሪጳን ሚስትም ትምህርቱን ሰምታ በጌታችን አመነች፡፡ ንጉሡ አግሪጳም በዚህ እጅግ ተቆጥቶ ቅዱስ በርተሎሜዎስን ብዙ ካሠቃየው በኋላ አሸዋ በተሞላ ትልቅ ከረጢት ውስጥ ከቶ ከነሕይወቱ ባሕር ውስጥ እንዲጥሉት አደረገ፡፡ ምእመናንም ሥጋውን አውጥተው በክብር ቀብረውታል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡

🔥 አባ ሚልኪ ዘቁልዝም

በላይኛው ግብጽ የሚኖሩ ባለጸጋ ወላጆቻቸው በስዕለት ወለዷቸው፣ ብሉይን ከሐዲስ አጠናቀው ከተማሩ በኋላ የአባታቸውን ወርቅ ለድኆች ሰጥተው ገዳም ገብተው መነኩሰው በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ። የአገረ ገዥውልን ልጅ ዘንዶ ውጦት ሳለ አባ ሚልኪ ዘንዶውን ጠርቶት ልጁን ይተፋው ዘንድ አዘዘውና ልጁ ጤነኛ እንደሆነ ከዘንዶው ውስጥ ወጣ። በውስጡ ያደረ ከይሲም በኖ ጠፋ። ጻድቁ ቤተክርስቲያን ሲሠሩ የመሠረቱ ድንጋይ ራሱ በተአምራት እየተፈነቀለ ይተከል ነበር። ለ300 መነኮሳትም አባት ሆነው በተአምራታቸው የፋርስንና የሮም ሰዎችን አሳመኗቸው። ዋሻ ዘግተው ሊኖሩ በማሉ ጊዜ ሰይጣን መሀላቸውን ሊያፈርስ አስቦ በሮሙ ንጉሥ ልጅ አድሮ አሳመማትና በአባ ሚልኪ ካልሆነ በቀር አልወጣም አለ። ንጉሡም ልኮባቸው በደመና ተጭነው ሄደው ልጅቷን ፈውሰው አድሮባት የነበረውን ሰይጣን ገዝተው አሠሩትና ከንጉሡ ቤት 14 ሰው የማይሸከመውን ድንጋይ በአንገቱ ላይ አሳስረው አስሸክመውት ሰው ሁሉ እያየው ወደ ገዳማቸው አስመጡትና ድንጋዩን የበዓታቸው መዝጊያ አደረጉት። ጻድቁ በብርቱ ሲጋደሉ ኖረው የሚያርፉበት ቀን ከተነገራቸው በኋላ እነ እንጦንስ፣ መቃርስ፣ ሲኖዳ፣ ብሶይ፣ ጳኩሚስ ተገልጠውላቸው ወንድማችን ና ወደ እኛ ብለዋቸው በሰላም ዐርፈዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡

🔥 ራጉኤል ሊቀ መላእክት

ራጉኤል ማለት የብርሃናት አለቃ ማለት ነው። የብርሃናት አለቃ ሲባል ፀሐይን፣ ጨረቃን እና ከዋክብትን በማመላለስና ለሰው ልጆች፣ ለአዝርዕት፣ ለእንስሳት፣ ለአራዊት ሁሉ ብርሃንን የሚመግብ ነው ማለት ነው።
➛ አንድም ራጉኤል ማለት የሚበቀል ማለት ነው። የሚበቀል ነው ማለት በቀል የሚገባው ለጠላት ነው የሰው ልጅ ጠላት ደግሞ ዲያብሎስ ነው። ስለሆነም ቅዱስ ራጉኤል እግዚአብሔርን አምነው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው በፍርሐተ እግዚአብሔር አምልኮቱን ለሚፈጽሙ ሁሉ ጠላት ዲያብሎስን የሚያርቅላቸው ወደ እነርሱም ፈጥኖ በመድረስ የሚታደጋቸው ነው ማለት ነው። ሔኖክ 6:4፡፡
➛ አንድም ራጉኤል ማለት የኃያላን ኃያል እግዚአብሔር ማለት ነው። የኃያላን ኃያል ያለው የእግዚአብሔርን ኃያልነት ከምድር ፍጥረታት ዘንድ ኃያል ከሚባሉት ሁሉ ሊገለጽ የማይችል ኃያልነቱን ለመግለጽ ኃያልነቱም ከ እስከ የሌለው መሆኑን ለመግለጽ የተቀመጠ ነው። ስለዚህ እግዚአብሔር ኃያል የኃያላን ኃያል መሆኑን የሚገልጽ ትርጉም አለው።
➛ አንድም ራጉኤል ማለት ጽኑ እግዚአብሔር ማለት ነው። የእግዚአብሔር አምላክን ጽኑነት ለማጉላት ሲል ጽኑ አለው። እግዚአብሔር የማይወላውል የማይዋዥቅ የማይከዳ ነው ለማለትም ሲል ይህ ስያሜ ተሰጠው። የእግዚአብሔርን ጽናት የሚያሳይ ትርጉም ያለው ስያሜ ነው።

🔥 የሊቀ መላእክት የቅዱስ ራጉኤል አገልግሎት እና ስልጣን፡-

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከዚህ ዓለም በ64 ዓመቷ ካረፈች በኋላ ሥጋዋ ወደ ዕፀ ሕይወት ሲነጠቅ (ሲያርፍ) አብሮ ለሔደው እና ሥጋዋን በእጣን ሲያጥን ለነበረው ለፍቁረ እግዚ ለቅዱስ ዮሐንስ ኅብስትን የመገበ መልአክ ነው።
በብርሃናት ሁሉ ላይ የሰለጠነ መልአክ ነው። ከአዳም ሰባተኛ ትውልድ የሆነ በእግዚአብሔር ፊት ግሩም ያማረ ሥራው የሰመረ እስከዛሬ የሞት ወጥመድ ያልያዘው የሞት ጥላ ያላረፈበት ነብዩ ሔኖክ "ከቅዱሳን መላእክት አንዱ የሆነ ጸላዒ ዲያብሎስን የሚበቀለው ራጉኤል በብርሃናት ላይ የሰለጠነ ነው" ሲል ስለ እርሱ ተናግሯል፡፡
እግዚአብሔር ዓለምን ይቆጣጠር ዘንድ የሾመው ታላቅና ቅዱስ መልአክ ነው። (ድርሳነ ራጉኤል ዘጥቅምት ገጽ 23) አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር ለመተካት ዓለምን የመለወጥ ሥልጣን የተሰጠው ቅዱስ መልአክ ነው። ከእግዚአብሔር የጌትነቱ አዳራሽ ይገባና ይወጣ ዘንድ ስልጣን ያለው ከኪሩቤልና ከሱራፌል ጋር ከፈጣሪ የጌትነት ዙፋን ፊት የሚቆም ነው።
ሎጥን ሚስቱንና ልጆቹን ከእሳተ ጎመራ ያዳነ የበለአምን እርግማን ወደ በረከት የለወጠ እርሱ ነው።
በቅዱስ ራጉኤል ሥነ ሥዕል ላይ የምናየው ይህ ባለ አራት እራስ ንስር ከአርባእቱ ኪሩቤል አንዱ ገጸ ንስር ነው። የሥላሴን የጌትነት ዙፋን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳት ናቸው። የሚሸከሙት ሲባል ጫማ የሰውን ልጅ እንደሚሸከመው እንጂ ችለውትስ አይደለም። እነርሱም የሰው ገጽ፣ የእንስሳ ገጽ፣ የንስር ገጽ እና የአንበሳ ገጽ ያላቸው ናቸው። ይህንንም ነብዩ ሕዝቅኤል "ለእያንዳንዱ እንስሳትም የተለያዩ አራት ገጾች ነበሩት። ይህውም በስተቀኝ በኩል የእንስሳ መልክ፣ በስተ ግራ የላም ገጽ፣ በበስተ ኋላም የንስር ገጽ የሚመስሉ ነበሩ" ብሏል ሕዝ 1፡6-13፡፡ ከዚህ የምንገነዘበው ነገር ቢኖር አራት ገጽ ካላቸው ኪሩቤል መካከል አንዱ ንስር መሆኑን ነው። ቅዱስ ራጉኤል ደግሞ የእነዚህ ኪሩቤል አለቃቸው (የጌትነቱ ዙፋን ጠባቂ) በመሆኑ በዚህ ምክንያት ማለትም እነርሱ ዙፋኑን ተሸካሚ እርሱ ደግሞ አጠገባቸው መቆሙ መንበሩን ጠባቂ በመሆኑ በዚህ አይነት የአገልግሎት ድርሻ አብረው ሊሳሉ ችለዋል። ቅዱስ ያሬድም በድጓው "አርባእቱ እንስሳ አልቄንጥሩ እንደሚባለው ንስር ፊት ለፊት አይታዩም አንዱም በመራቸው ይሔዳሉ እነርሱም እያንዳንዳቸው አራት ገጽ ሲኖራቸው ሳያርፉና ሳይደክሙ የሚያመሰግኑ ናቸው" በማለት ጽፏል።
➛ አንድም መላእክት ነገደ ሱራፌል እና ነገደ ኪሩቤል በመባል ይከፈላሉ። በነገደ ሱራፌል እነ ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ ሩፋኤል ወዘተ ሲሆኑ በነገደ ኪሩቤል ደግሞ ቅዱስ ገብርኤል ቅዱስ ራጉኤል ወዘተ ያጠቃልላል። ስለዚህ ቅዱስ ራጉኤል ነገዱ ከነገደ ኪሩቤል ነው በዚህም ላይ የነገደ ኪሩቤል አልቄንጡራ (አራት እራስ ንስር) አለቃቸው ቅዱስ ራጉኤል ነው። በዚህም ምክንያት አብረው ሊሳሉ ችሏል።

➛ አንድም መላእክትን ሁሉ እንደ እየሥራቸው መለያ ሥነ ሥዕላቸውን መሳል ልማድ ነውና። ለምሳሌ ቅዱስ ሚካኤል ከቅድስት አፎምያ ጋር፣ ቅዱስ ገብርኤል ከሠለስቱ ደቂቅ ጋር፣ ቅዱስ ዑራኤል ከእዝራ ሱቱኤል ጋር እንደሚሳሉት ሁሉ ማለት ነው። በዚህም መሰረት ቅዱስ ራጉኤልም ዐቃቤ መንበር ነውና መንበሩን በሚሸከሙት ኪሩቤል ከሚመሰሉት ንስሮች ጋር አብረው ሊሳሉ ችለዋል፡፡
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል ከአምላክ የተሰጠው ቃል ኪዳን እግዚአብሔር አምላክ በስሙ ለታመኑት ቅዱሳን፣ ጻድቃን፣ ሰማእታት፣ ሐዋርያት፣ ዘወትር ያለማቋረጥ ስሙን ለሚጠሩት ቅዱሳን መላእክት ሁሉ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል። የሰጣቸውም ቃል ኪዳን ዘላለማዊ እና ሊሻር የማይችል ነው። ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ራጉኤልም ይህን ቃል ኪዳን ሰጥቶታል "የራጉኤል አምላክ ይቅር በለኝ በማለት አንዲት ቃልስ እንኳን ቢናገር እንደ ወዳጄ እንደ አብርሃም፣ እንደ ባለሟሌም እንደ ይስሐቅ፣ እንደ አከበርኩትም እንደ ያዕቆብ ክብርን ባለሟልነትን እሰጠዋለሁ በራሱ ላይም አክሊል አቀዳጀዋለሁ እረጅም ዘመናት ሰፊ ወራትም እሰጠዋለሁ" ሲል ቃሉን ሰጥቶታል፡፡
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል መስከረም 1 ቀን ከሊቃነ መላእክት በ4ተኛ ደረጃ የተሾመበት ዕለት ነው። ግንቦት 1 ቀን ለታላቁ አባት ለሄኖክ ምሥጢራትን የገለጸበት በዓሉ ነው፡፡ ጥበቃው አይለየን፣ በምልጃው ይማረን፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ምንጭ፦ የመስከረም ❶ ስንክሳር

🍃🍃🍃 🍃🍃🍃 🍃🍃🍃
ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0
ጳጉሜን ❺ ቀን 2011 ዓ.ም

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን። ጳጉሜን 5 ከልብስ ተራቁቶ የሚኖር ታላቁን አስፈሪ ዘንዶ ለማዳ እንስሳ ያደረገ አባ በርሱማ ዐረፈ፡፡ ➛ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት...
09/09/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።

ጳጉሜን 5 ከልብስ ተራቁቶ የሚኖር ታላቁን አስፈሪ ዘንዶ ለማዳ እንስሳ ያደረገ አባ በርሱማ ዐረፈ፡፡
➛ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የሆነው ነቢዩ ቅዱስ አሞጽ ዕረፍቱ ነው፡፡
➛ ንጹሕና ድንግል የሆነ አባ ያዕቆብ ዐረፈ፡፡ ይኸውም በአቡነ ዮሐንስ ሐጺር ገዳም ሊቀ ዲያቆናት የነበረና በኋላ በምስር አገር ኤጲስቆጶስነት የተሾመና ምእመናንን በመልካም አጠባበቅ የጠበቀ የበጎች እረኛ የነበረ ነው፡፡

🔥 ነቢዩ ቅዱስ አሞጽ

ይኸውም እውነተኛ ነቢይ በእስራኤል ነገሥታት በኢዮአስና በዖዝያ ዘመን የነበረ አስተማሪና መካሪ የሆነ ነው፡፡ በእግዚአብሔርም ትእዛዝ የእስራኤልንና የይሁዳ ነገሥታትንም ሁሉ ይገሥጻቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ብዙ ትንቢታትን ተናገረ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መከራ ስለመቀበሉ፣ በዚያችም በመከራ ቀኑ ስለ ፀሐይ መጨለም ትንቢትን ተናገረ፡፡ እስራኤልም ስለሚደርስባቸው መከራና ልቅሶ፣ ረድኤትም እንደሚያጡ፣ የእግዚአብሔርንም ቃል መስማትን ከማጣት የተነሣ እንደሚራቡና እንደሚጠሙ ተናገረ፡፡ ዳግመኛም እስራኤል በሀገሩ ሁሉ በአሕዛብም መካከል እንደሚበተኑ ትንቢትን ተናገረ፡፡ ነቢዩ አምጽም የተናገራቸው ትንቢቶች ሁሉ በእስራል ላይ ተፈጽሙባቸው፡፡ የትንቢቱም ዘመን ከጌታችን ሥጋዌ በፊት በ800 ዓመት ነው፡፡
ይህም ታላቅ ነቢይ ስለ ሀገራችን ኢትዮዽያም እንዲህ ብሏል:- "የእሥራኤል ልጆች ሆይ! እናንተ ለእኔ እንደ ኢትዮዽያ ልጆች አይደላችሁምን? ይላል እግዚአብሔር፡፡" ት.አሞጽ 9:7፡፡ ይህም እኛ ኢትዮዽያውያን ከጥንትም ቢሆን እግዚአብሔርን በማመንና ሕጉን በመፈጸም ለእስራኤለውያን ምሳሌዎች መሆናችንን ነው፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡

🔥 አባ በርሱማ

ወላጆቹ በምስር አገር እጅግ ባለጸጎች ነበሩ፡፡ እነርሱም እግዚአብሔርን በማምለክና በሕጉ ጸንቶ በመኖር ያሸበረቁ ናቸው፡፡ እጅግ በበዛው ሀብታቸውም መጻተኞችን በፍቅር በመቀበልና ለጦም አዳሪዎች በመመጽወት እግዚአብሔረን የሚያስደስቱ ናቸው፡፡ ይህንን ቡሩክ የሆነ በርሱማን በወለዱት ጊዜ እግዚአብሔርን በመፍራትና የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትን በማስተማር በሃይማኖት በምግባር ኮትኩተው አሳደጉት፡፡

ከዚህም በኋላ የበርሱማ ወላጆቹ በሞት ሲያርፉ የእናቱ ወንድም ወላጆቹ የተውለትን ንብረት ወሰደበት፡፡ በርሱማም ይህንን ጊዜ ዓለም እንደጠዋት ጤዛ ታይታ የምትጠፋ መሆኗን አሰበ፡፡ እንዲህም አለ፡- ‹‹መድኃኒታችን ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ይጣላት ስለእኔም ሰውነቱን የጣላት ያገኛታል ብሏልና›› ብሎ አሰበ፡፡ ዳግመኛም ‹‹ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢገዛ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጠፋ ምን ይጠቅመዋል? ወይስ ሰው ስለነፍሱ ቤዛ ምን በሰጠ ነበር?›› የሚለውን የቅዱስ ወንጌል ቃል አሰበ፡፡ ማቴ 16፡26፣ ሉቃ 9፡25፡፡ ቅዱስ በርሱማ ይህንን ብሎ ከዓለም ወጣ፡፡ በበጋ ቃጠሎ በክረምት ቅዝቃዜ ልብስ ሳይለብስ በ5 ኮረብታዎች ላይ በታላቅ ተጋድሎ ኖረ፡፡ ወገቡንም በማቅ መታጠቂያ ይታጠቃል፡፡ በልቡልም ለራሱ ‹‹በርሱማ ሆይ በሚያስፈራ እውነተኛ ፈራጅ ፊት ትቆም ዘንድ አለህ›› እያለ ሁልጊዜ በጾም በጸሎት በስግደት በቀንና በሌሊት ይተጋ ነበር፡፡ የሚመገበውም በቀን አንድ ጊዜ በውኃ የራሰ ደረቅ ቂጣ ነው፡፡ ሰውነቱንም ከመጉዳቱ የተነሣ ቆዳው ከአጥንቱ ጋር ተጣበቀ፡፡

ከዚህም በኋላ አባ በርሱማ ውዳሴ ከንቱን ሽሽት ካለበት ቦታ ወጥቶ በምስር አገር ወዳለች የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ሄደ፡፡ በዚያም እንደቀድሞው በታላቅ ተጋድሎ እየኖረ ለ25 ዓመታት ተቀመጠ፡፡ በዚያችም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ በዋሻ ውስጥ ታላቅ ዘንዶ አለ፡፡ ሰው ሁሉ ይህን ታላቅ ዘንዶ ከመፍራቱ የተነሣ መብራትም አያበራም ነበር፡፡ አባ በርሱማም ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! እባቡንና ጊንጡን እንረግጥ ዘንድ በጠላት ኃይል ላይ ሁሉ ሥልጣንን የሰጠኸን አንተ ነህ፡፡ አሁንም በዚህ ዋሻ ውስጥ በሚኖር ከይሲ ላይ ታሰለጥነኝ ዘንድ እለምንሃለሁ›› ብሎ ከጸለየ በኋላ በመስቀል ምልክት አማትቦ ‹‹በተኩላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፣ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ›› የሚለውን የዳዊት መዝሙር እየዘመረ (መዝ 91፡13) ያንን ኃይለኛ ታላቅ ዘንዶ በእጆቹ ያዘው፡፡ በእጆቹም ከያዘው በኋላ እንዲህ አለው፡- ‹‹ከእንግዲህ ወዲህ ገራም ሁን፣ ታጠፋ ዘንድ ሥልጣን አይኑርህ፣ የሚሉህን ሰምተህ የምትታዘዝ ሁን እንጂ በማንም ላይ ከሰው ወገን ክፉ አታድርግ›› አለው፡፡ በዚህም ጊዜ ያ ታላቅ ክፉ ዘንዶ ለአባ በርሱማ ተገዢው ሆነ፡፡ ሂድ ሲለው የሚሄድ ሲጠራውም የሚመጣ ሆነ፡፡

አባ በርሱማ ተጋድሎውን በመጨመር ብርሃን በላዩ እስኪወጣ ድረስ እስከ ሰባት ቀን የሚጾም ሆነ፡፡ የውኃ ጉድጓድ ውስጥ እየገባ ሌሊቱን ሙሉ ሲጸልይ ያድራል፡፡ ምግቡንም ደረቅ ቂጣና መጠጡን የሚሸት ውኃ አደረገ፡፡ አስቀደሞ ከቤቱ ከወጣ ጀምሮ ቀይ ግምጃ ጨርቅ በማገልደም ሥጋውን ይሸፍናል፣ በጎንና በጎኑም መካከል ምንጣፍ አድርጎ አያውቅም፡፡ መጻሕፍትን አዘውትሮ ያነባል፡፡ ሰዎችም ምክር በጠየቁት ጊዜ መልካሙን የሕይወትን ቃል ይመግባቸዋል፡፡ ሁልጊዜም ‹‹ያለ ልብ ንጽሕና በቀር ማንም የእግዚአብሔርን መንግሥት ማየት አይችልም›› ይል ነበር፡፡ የልብ ንጽሕናን ሲልም ንስሓን ማለቱ ነው፡፡ ኃጢአት ሁሉ ከንስሓ በኋላ ይሠረያል ልብም ንጹሕ ይሆናልና፡፡ የክርስቲያን ወገኖችንም ሁሉ እንዲህ ያስተምራቸዋል፡፡ አባ በርሱማ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት ነበርና ብዙ ድውያንን ፈወሰ፡፡ ከጠላት ሰይጣን ብርቱ ፈተና የገጠመው ሁሉ ወደ አባ በርሱማ እየመጣ ይጽናናል፣ ደዌ ያለበትም ከሕመሙ ይፈወሳል፡፡ አባ በርሱማም ጽኑ ተጋድሎውን በፈጸመ ጊዜ በጳጉሜን 5 ቀን በሰላም ዐረፈ፡፡ ከማረፉም አስቀድሞ ደቀ መዝሙሩ ቀሲስ ዮሐንስ በልቡ ‹‹ከአባ በርሱማ በኋላ እንግዲህ ሰዎችን ማን ያጽናናቸዋል?›› አለ፡፡ አባ በርሱማም ደቀ መዝሙሩ በልቡ ያሰበውን በመንፈስ ቅዱስ ዐውቆ ‹‹ልጄ ዮሐንስ ሆይ! ‹የቶባን ልጅ ማለትም 'የብርቱ (የእግዚአብሔር) ልጅ' አባ በርሱማ› ብሎ ስሜን የሚጠራኝን ሁሉ እኔ ከእርሱ አልርቅም፣ እኔ እነሆኝ ብዬ የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ የሚሻውን ሁሉ እፈጽምለታለሁ›› አለው፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ ግራው ተመልክቶ ‹‹እነሆ ተመራመሩብን ከክፉ ሥራ ምንም ምን በእኛ ላይ አላገኙም›› አለ፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ምንድነው›› የሚለውን መዝሙር እስከመጨረሻው ዘመረ፡፡ ደቀ መዝሙሩ አብርሃምን ጠርቶ ቢላዋ እንዲያመጣለት አዘዘው፡፡ ቢላዋንም ሲያመጣለት ተቀብሎ ምላሱን ቆርጦ ጣላት፡፡ ከዚህም በኋላ ፊቱን በመስቀል ምልክት አማትቦ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ቅድስት ነፍሱን ተቀብለው ተድላ ደስታ ወደሚገኝባት ገነት አሳረጓት፡፡

የአባ በርሱማ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን አሜን።

🔥 አባ ያዕቆብ ዘምስር (ግብፅ)

ዳግመኛም በዚህች ቀን ንጹሕ ድንግል አባት የምስር አገር ኤጲስቆጶስ አባ ያዕቆብ አረፈ። ይህም ተጋዳይ የሆነ አባት ገና በታናሽነቱ የምንኵስናን ልብስ ይለብስ ዘንድ ነፍሱ ወደደች። ከሀገሩም ወጥቶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደና በአባ ዮሐንስ ሐጺር በዓት ውስጥ ኖረ በዚያም ጽኑዕ በሆነ ገድል ብዙ ዘመናት ተጠምዶ ኖረ።

ከዚህም በኋላ በአባ ዮሐንስ ሐጺር ቤተ ክርስቲያን ላይ ሊቀ ዲያቆናት አድርገው ሾሙት የደግነቱ፣ የትሩፋቱና የቅድስናውም ዜና ተሰማ። በእግዚአብሔርም ፈቃድ በምስር አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት።

በሹመቱ ወንበርም በተቀመጠ ጊዜ ጾምን ጸሎትን ጨመረ ስለ ሹመቱም ተጋድሎውንና አገልግሎቱን ከቀድሞው አበዛ እንጂ ቸልል አላለም። ሕዝቡንም ሁልጊዜ ያስተምራቸዋል መጻሕፍትንም ያነብላቸዋል ከእነርሱ ሥውር የሆነውንም ይተረጒምላቸዋል።

ኃጢአትን በመሥራት የሚኖሩትን ይገሥጻቸዋል፤ በንስሐ እስከሚመለሱም ሥጋውንና ደሙን ከመቀበል ያርቃቸዋል ። በጎ ተጋድሎውንም በፈጸመ ጊዜ ጥቂት ታመመ መንጋዎቹንም ጠርቶ በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ አዘዛቸው ደግሞ ካህናቱን ጠርቶ በጸሎትና በቅዳሴ ጊዜ ቸለል እንዳይሉ አዘዛቸው። ሁለተኛም ሥጋውንና ደሙን ለማክበር በንጽሕና እግዚአብሔርን በመፍራት ሁናችሁ ካላገለገላቸሁ ከደማችሁ ንጹሕ ነኝ አላቸው።

ከዚህም በኋላ ፊቱንና ደረቱን በመስቀል ምልክት አማተበ እጆቹንም ዘረጋ ዐይኖቹንም ራሱ ከደነና በሰላም አረፈ በአማሩ ልብሶችም ገነዙት ታላቅ ልቅሶንም አልቅሰው በክብር በምስጋና በማወደስ ቀበሩት።

ምንጭ፦ የጳጉሜን ❺ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃 🍃🍃🍃 🍃🍃🍃
ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ
https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0
https://www.facebook.com/meselenigatudeko

ᴍᴇsᴇʟᴇ ɴɪɢᴀᴛᴜ ᴅᴇᴋᴏ
ጳጉሜን ❹ 🀄️ን 2011 ዓ.ም

Address

Awassa

Telephone

+251926265782

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ስንክሳር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ስንክሳር:

Share

Category