Zagu Media

Zagu Media እንኳን ወደ Zagu Media በሰላም መጣችሁ!
ወቅታዊ፣ አገራዊ፣መዝናኛ እና የተለያዩ መረጃዎችን በብርሃን ፍጥነት ወደ እናንተ እናደርሳችሁላን!

13/09/2025

እስራኤል ጋዛን በአውዳሚ ቦንብ እየደበደበች ነው።

ኢትዮጵያዊቷ  አትሌት አለሽኝ ባወቀ በዙሪክ ዳያመንድ ሊግ በ3 ሺህ ሜትር ፍጻሜ ውድድር አሸነፈችየ19 ዓመቷ አትሌት አለሽኝ ርቀቱን 8 ደቂቃ 40 ሰከንድ ከ56 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት ...
28/08/2025

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አለሽኝ ባወቀ በዙሪክ ዳያመንድ ሊግ በ3 ሺህ ሜትር ፍጻሜ ውድድር አሸነፈች

የ19 ዓመቷ አትሌት አለሽኝ ርቀቱን 8 ደቂቃ 40 ሰከንድ ከ56 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት ነው ያጠናቀቀችው፡፡

via: fidel

የአገልግሎት ክፍያ ጭማሪ‼️==========የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተወሰኑ አገልግሎቶች ላይ ከመስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የአገልግሎት ክፍያ ዋጋ ላይ ማሻሻያ ...
28/08/2025

የአገልግሎት ክፍያ ጭማሪ‼️
==========
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተወሰኑ አገልግሎቶች ላይ ከመስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የአገልግሎት ክፍያ ዋጋ ላይ ማሻሻያ ሊያደርግ መሆኑን አስታውቋል።
ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ ዛሬ ነሀሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 እስከ ነገ ነሀሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጠዋት 11፡30 ሰዓት ድረስ ሁሉም የባንካችን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች አገልግሎት በጊዜያዊነት ይቋረጣል።

26/08/2025

" ከዚህ በኋላ የትኛውም የትምህርት ተቋም ያሉትን ተማሪዎች ማን፤ መቼ እንደገባ የሚገልጽ የአይን አሻራን ጨምሮ ትክክለኛ መረጃዎችን የማያስገቡ ከሆነ በፍጽሙ tolarate አናደርግም " - ትምህርት ሚኒስቴር

የኢትዮጵያ ቅጥረኛ ወታደር ከዩክሬን ጎን ሆኖ ሩሲያን እየተዋጋ እንደሆነ ተገለጸሩሲያ ከዩክሬን ጎን የቆሙ ቅጥረኛ ወታደሮችን ማንነት ይፋ አድርጋለችኢትዮጵያን ጨምሮ ከ89 ሀገራት የተውጣጡ ከ...
15/03/2024

የኢትዮጵያ ቅጥረኛ ወታደር ከዩክሬን ጎን ሆኖ ሩሲያን እየተዋጋ እንደሆነ ተገለጸ

ሩሲያ ከዩክሬን ጎን የቆሙ ቅጥረኛ ወታደሮችን ማንነት ይፋ አድርጋለች
ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ89 ሀገራት የተውጣጡ ከ13 ሺህ በላይ ቅጥረኛ ወታደሮች ለዩክሬን እየተዋጉ ነው ተብሏል

ኢትዮጵያዊው ቅጥረኛ ወታደር ከዩክሬን ጎን ሆኖ ሩሲያን እየተዋጋ እንደሆነ ተገለጸ።

ለአንድ ሳምንት በሚል የተጀመረው የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ሁለት ዓመት ያለፈው ሲሆን ጦርነቱ አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል።

ሩሲያ ከዩክሬን ጎን ቆመው እየተዋጉ ያሉ ቅጥረኛ ወታደሮችን ማንነት ይፋ አድርጋለች።

እንደ ሩሲያ መከላከያ ሚንስቴር መረጃ ከሆነ አንድ ኢትዮጵያዊ ከዩክሬን ጎን ሆኖ ሩሲያን እየወጋ ይገኛል ተብሏል።

ይህ ኢትዮጵያዊ እስካሁን በህይወት እንዳለ የተገለጸ ሲሆን ወታደሩ ኢትዮጵያዊ ከመሆኑ ውጪ ማንነቱ ይፋ አልተደረገም።

በአጠቃላይ ይህ ጦርነት ከተጀመረበት የካቲት 2014 ዓ.ም ጀምሮ ከ89 ሀገራት የተውጣጡ 13 ሺህ 387 ቅጥረኛ ወታደሮች ከዩክሬን ጎን ተሰልፈዋል።

ከጠቅላላው ቅጥረኛ ወታደሮች ውስጥም 5 ሺህ 962 ያህሉ በሩሲያ ጦር መገደላቸው ተገልጿል።

ፖላንድ ቅጥረኛ ወታደሮችን በማዋጣት ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን 2 ሺህ 960 ዎቹ ተገድለዋል ተብሏል።

ከፖላንድ በመቀጠል አሜሪካ፣ ካናዳ፣ ጆርጂያ እና ብሪታንያ ብዙ ዜጎቻቸው ከዩክሬን ጎን የቆሙ በቅጥረኛ ወታደርነት የተመዘገቡ ሀገራት ናቸው።

ከአፍሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ 13 ሀገራት የተውጣጡ 249 ወታደሮች ከዩክሬን ጎን ሆነዋል የተባለ ሲሆን 103 ያህሉ መገደላቸው ተገልጿል።

ናይጀሪያ፣ አልጀሪያ እና ደቡብ አፍሪካ በአንጻራዊነት ብዙ ዜጎቻቸው ለዩክሬን በቅጥረኛ ወታደርነት የተመዘገቡባቸው ሀገራት ናቸው።

Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ

አስፋዉ መሸሻ አረፈጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ በአሜሪካ ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ትላንት ማታ ማረፉ ተስምቷል::ለዘመድ ወዳጅና ለአድናቂወቹ መፅናናትን እንመኛለን።
14/01/2024

አስፋዉ መሸሻ አረፈ

ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ በአሜሪካ ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ትላንት ማታ ማረፉ ተስምቷል::

ለዘመድ ወዳጅና ለአድናቂወቹ መፅናናትን እንመኛለን።

በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል...
29/12/2023

በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች በ2016 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያዉ ወሰነ-ትምህርት ተማሪዎቻቸውን ለመጥራትና መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸዉን ሙሉ ለሙሉ ለመጀመር አልቻሉም ነበር ብሏል ሚኒስቴሩ።

በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድፖስት፣ የጸጥታ አደረጃጀቶችና የሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ሲያካሂድ መቆየቱ ተገልጿል።

" የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ፣ የአስሩ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ጸጥታ አካላት ትናንት ታህሳስ 18/2016 ዓ.ም በጉዳዩ ዙሪያ የመከሩ ሲሆን አሁን በክልሉ አንጻራዊ ሰላም የተፈጠረ በመሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን መጥራትና ማስተማር እንደሚችሉ ውሳኔ ላይ ተደርሷል። " ሲል ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

በዚህም መሰረት ከጥር 1/2016 ጀምሮ ባሉ ሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን ጠርተው የመማር ማስተማር ስራቸውን ይጀምራሉ ተብሏል።

በመሆኑም በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች የተመደቡ ተማሪዎች ዩኒቨርስቲዎቹ የሚያደርጉትን ጥሪ እንዲከታተሉ ጥሪ ቀርቧል።

የቱሪዝም ሚኒስቴር በተጋነነ ዋጋ የሚያከናውነው ግዢ መታረም እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳስቧል፡፡ቋሚ ኮሚቴው የቱሪዝም ሚ...
28/12/2023

የቱሪዝም ሚኒስቴር በተጋነነ ዋጋ የሚያከናውነው ግዢ መታረም እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳስቧል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው የቱሪዝም ሚኒስቴርን የ2014 በጀት ዓመት ሂሳብ ኦዲት ሪፖርት መነሻ በማድረግ ይፋዊ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ወ/ሮ አራሬ ሞሲሳ ተቋሙ ለደንብ ልብስ ግዢ በሚል ያከናወነው ክፍያ የተጋነነ ስለመሆኑ ጠቁመው፤ በቀጣይ የቱሪዝም ሚኒስቴርም ሆነ ሌሎች ተቋማት የሚመሩበት ወጥ የሆነ መመሪያ በገንዘብ ሚንስቴር ሊዘጋጅ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ያሉት ክፍተቶች ተፈትሸው ተጠያቂነት እንዲሰፍን፣ ከተቋሙ የለቀቁ ሰራተኞች የተቋሙን ንብረት ተመላሽ እንዲያደርጉ እንዲሁም ያለአግባብ ለቤት እድሳት የወጣው ገንዘብ ተመላሽ እንዲደረግ ቋሚ ኮሚቴው ለሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ያስቀመጣቸው አቅጣጫዎች ናቸው፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሰረት ዳምጤ በበኩላቸው በተቋሙ በየቀኑ ነዳጅ የሚሞላላቸው ተሸከርካሪዎች እንዲሁም ያለአግባብ የተከፈሉ ወጪዎች መኖራቸው በኦዲት ግኝት እንደተረጋገጠ ገልጸው፤ ተቋሙ የእርምት እርምጃ አለመውሰዱን አስረድተዋል፡፡

የቱሪዝም ሚንስቴር ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ በበኩላቸው ተቋሙ የውስጥ ኦዲት፣ የስነምግባር፣ የፋይናንስ፣ የንብረትና የተለያዩ ክፍሎችን በአዲስ መልክ በማደራጀትና ለባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት ቀደም ሲል የነበሩት የኦዲት ግኝቶች እንዳይደገሙ ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ ስለመሆናቸው ለቋሚ ኮሚቴው አብራርተዋል፡፡

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የአየር ትራንስፖርት ክፍያ አገልግሎትን ጀመሩ።ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከክፍያ በፊት  እስከ ስድስት መቶ ሺህ ብር ቅድሚያ ...
28/12/2023

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የአየር ትራንስፖርት ክፍያ አገልግሎትን ጀመሩ።

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከክፍያ በፊት እስከ ስድስት መቶ ሺህ ብር ቅድሚያ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችል አዲስ የአየር ትራንስፖርት ክፍያ አሰራርን ይፋ አድርገዋል።

ይህ አገልግሎት ተጠቃሚዎች የአየር ትራንስፖርት አገልግሎትን ተጠቅመው ክፍያውን ቆይተው የሚከፍሉበትን አዲስ የክፍያ አማራጭ ነው።

''ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል'' የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ አገልግሎት በ6 ወር ወይም በ12 ወር በሚደርስ የብድር ክፍያ የሚሰጥ መሆኑን የዳሽን ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ ዋና መኮንን አቶ ዩሃንስ ሚሊዮን የአገልግሎቱ ይፉ መደረግን አስመልክተው ተናግረዋል።

ደንበኞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን በዳሸን ባንክ የሂሳብ ቁጥር መክፈት እንደሚገባቸው እና በተጨማሪም በባንኩ ቢያንስ ለሶስት ወራት አገልግሎት ያገኙ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

ስምምነቱን አስመልክቶ የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና የንግድ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ለማ ያዴቻ ከዳሽን ባንክ ጋር በመተባበር የቀረበው አዲስ የክፍያ አማራጭ ከአየር መንገዱ የሞባይል መተግበሪያ ጋር የተቀናጀ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል ።

ደንበኞች የተፈቀደላቸው የብድር መጠን ሲያልቅ ማደስ የሚችሉ ሲሆን በአንዴ የወሰዱትን ብድርም ለተለያዩ በረራዎች ከፍለው መጠቀም ይችላሉ ተብሏል።

በሁለቱ ተቋማት ስምምነት በቀረበው በዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈቀደው የብድር ገንዘብ መጠን እስከ ስድስት መቶ ሺህ (600,000) ብር የሚደርስ ነው።

የሚፈቀደው ብድር ወለድ የሚታሰብበት ሲሆን ይህም ደንበኛው በመረጠውና ብድሩን በወሰደበት የጊዜ ገደብ ከብድሩ ጋር አብሮ የሚከፈል ይሆናል ተብሏል።

ሰበር‼️ጦርነት ይቁም፣ ሰላም ይስፈን የሚል ሰላማዊ ሰልፍ በትግራይ መቀሌ ሊካሄድ ነውበታህሳስ 21/2016 መቀሌ ላይ በመላ ኢትዮጵያ ጦርነት ይቁም ሰላም ይስፈን የሚል የተቃዉሞ ሰልፍ ተጠር...
28/12/2023

ሰበር‼️

ጦርነት ይቁም፣ ሰላም ይስፈን የሚል ሰላማዊ ሰልፍ በትግራይ መቀሌ ሊካሄድ ነው

በታህሳስ 21/2016 መቀሌ ላይ በመላ ኢትዮጵያ ጦርነት ይቁም ሰላም ይስፈን የሚል የተቃዉሞ ሰልፍ ተጠርቷል። የትግራይ አስተዳደር ሰልፉን መፍቀዱ ተሰምቷል።

EMS ከሰልፉ አስተባባሪዎች አንዱ የሆኑትን የህግባለሞያና ጠበቃ አበራ ንጉስ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ይሁኑ እውነታ አስረድተዋል።

በሰልፉ በየትኛውም የሀገሪቱ አካባቢ ያሉ ጦርነቶች እንዲቆሙ፣
ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ፣
በማንነታቸው የታሰሩ ዜጎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣

መንግስት የፖለቲካ ጥያቄዎችን በሆደ ሰፊነት በመነጋገርና በድርድር እንዲፈታ፣

ሀገሪቱ ከገባችበት የሰላም እጦት ፋታ እንድታገኝ ጦርነት ቆሞ ሰላም እንዲሰፍን የሚጠይቅ ሰልፍ ለተሃሳስ 21 ተዘጋጅቶ የመቐለ ከንቲባ መፍቀዳቸውን አቶ አበራ ንጉስ ለ EMS ዛሬ ማምሻውን ገልፀዋል።

ተመሳሳይ የሰልፍ ጥሪ በአዲስ አበባ ተጠይቆ መከልከሉ ይታወሳል።

28/12/2023

የገንዘብ ሚንስቴር ዴኤታው ኢዮብ ተካልኝ፣ ኢትዮጵያ በመጪው ጥር ወር ከቦንድ አበዳሪዎቿ ጋር ውይይት እንደምትጀምር እና ውይይቱ እንዳለቀ ሳይከፈል የቀረውን የዕዳ ወለድ ወዲያው ለመክፈል የሚያስችል ብቃት አለን ማለታቸውን የአሜሪካ የአማርኛው ድምፅ ዘግቧል። ሚንስትር ዴኤታው፣ ገንዘቡ በውይይቱ ወቅት ለዩሮ ቦንድ አበዳሪዎቹ ለመተማመኛ የሚያስፈልግ ከሆነም በተለየ አካውንት አስቀምጠን ውይይቱን መቀጠል እንችላለን ማለታቸውም በዘገባው ተጠቅሷል። ኢዮብ፣ ወለዱን መክፈል የማንችለው በአቅም ማነስ ሳይሆን የመርኽ ጉዳይ በመሆኑ ነው ሲሉ መናገራቸውም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ ለተበደረችው የ1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮ ቦንድ፣ መክፈል ለነበረባት 33 ሚሊዮን ዶላር ወለድ የተሰጣት ተጨማሪ 14 ቀናት ባለፈው ሰኞ በመጠናቀቁ፣ ከጋና እና ዛምቢያ ቀጥሎ ብድር መክፈል ያልቻለች ሦስተኛዋ የአፍሪካ አገር መሆኗ ይታወሳል።

28/12/2023

ኢሰመጉ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ የተለያዩ ቀበሌዎች የታጠቁ ኃይሎች በተለያዩ ቀናት በንጹሃን ዜጎች ላይ በፈጸሙት ጥቃት 56 ሰዎች ዘግናኝ በሆነ ሁኔታ እንደተገደሉ አስታውቋል። ኢሰመጉ፣ በበርካታ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት እንዲኹም እገታ መፈጸሙንም ገልጧል። ከተገደሉት መካከል ስድስት የአንድ ቤተሰብ አባላት እንደሚገኙበት ኢሰመጉ ጠቅሷል።በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ ልዩ በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን አካባቢ በተመሳሳይ ኅዳር 14 የታጠቁ ቡድኖች በፈጸሙት ጥቃት በዘጠኝ የቤተክርስቲያኒቱ አባላት ላይ "የጅምላ ግድያ" መፈጸሙን መረዳቱንም ኢሰመጉ አመልክቷል። መንግሥት ወንጀሉን የፈጸሙ አካላትን ባስቸኳይ ለፍርድ እንዲያቀርብና የሕግ የበላይነትን እንዲያረጋግጥም ኢሰመጉ ጠይቋል።

Address

Bahir Dar
6000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zagu Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Zagu Media:

Share