Selus Studio

Selus Studio Your Complete Photo, Design, & Printing Solution

የቀድሞው የወልድያ ከተማ ከንቲባ የነበሩት መሐመድ ያሲን ስለ  #ግዕዝ ይሄን ብለዋልአዎ ቋንቋ ይወለዳል፤ ያድጋል፤ ይሞታል። ግእዝ ግን እንዲሞት ተፈረደበት እንጂ ራሱን አልገደለም‼️ #መቅድ...
18/09/2025

የቀድሞው የወልድያ ከተማ ከንቲባ የነበሩት መሐመድ ያሲን ስለ #ግዕዝ ይሄን ብለዋል
አዎ ቋንቋ ይወለዳል፤ ያድጋል፤ ይሞታል። ግእዝ ግን እንዲሞት ተፈረደበት እንጂ ራሱን አልገደለም‼️

#መቅድም

የግእዝ ትምህርትን በተመለከተ በ3 ተከታታይ ክፍሎች ያለኝን የግል አመለካከት መሰረት በማድረግ ባጋራሁት ፅሁፍ መነሻነት በውስጥ መስመር በርካታ አስተያየቶችና ጥያቄዎች እየደረሱኝ ይገኛል።

ይህ ከሆነ ዘንዳ ከዚህ በታች ካሰፈርኩት አመለካከት የተለየ አቋም ያለው ግለሰብ የፈለገውን ስያሜ ወይም ትችት ሊሰጥ ይችል ይሆናል። ይህንን ግን በራሱ ገፅ እንዲያደርገው ከወዲሁ እመክራለሁ።

#ማሳሰቢያ

📝 ይህንን አተያይ በጨዋ ደንብ በሐሳብ ለሚሞግቱ ትልቅ ክብር አለኝ። የሚሰጡት አመክኒዮም አሳማኝ ከሆነ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ።

🙈 ነገር ግን ለስድድብ፣ ለብሽሽቅ፣ ለዘለፋ ተብለው የሚሰጡ ትችቶችን መልስ ለመስጠት በሚል የማጠፋው ጊዜ አይኖረኝም።



❶ ያኔ በኢትዮጵያ በጥንት ዘመን ለ200 ዓመታት ገደማ የመንግስት የስራ ቋንቋ እና የህብረተሰቡ መግባቢያ ቋንቋ የነበረው ግእዝ፤

❷ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ታሪክ ስነ ሃውልቶች የተሸከመው ግእዝ፤

❸ አያሌ ድርሳናት (ስለ ህክምና፣ ስለ ፍልስፍና፣ ስለ ማዕድናት፣ ስለ ፈዋሽ እፅዋት፣ ስለ ከዋክብት፣ ስለ አርኪዮሎጂ፣ ስለ ድንቅ ሐገራዊ ታሪኮች፣ ስለ ቀን ቆጠራ ወዘተ…) የተከተቡበት ግእዝ፤

❹ ለትግርኛና አማርኛ ቋንቋዎች መወለድ ስር ሁኖ ያገለገለው ግእዝ፤

❺ ሥርወ ቃላትን ለመመርመር ሰዋሰውን ለመለየት በእጅጉ የሚጠቅመው ግእዝ፤

❻ ሐገራችን ኢትዮጵያ የዘመናት ዑደት ስፍር ቀምራ የራሷን አሃዝ ያደላደለችበት ግእዝ፤

❼ ሐገር እንጂ ብሄር የሌለው ብቸኛ ቋንቋ ግእዝ፤

❽ ኢትዮጵያ አንድነቷን ጠብቃ እንድትኖር የቀድሞ ነገስታት ይመሩበት የነበረው የአስተዳደር ዘይቤ የተከተበበት ግእዝ፤

➒ ነጮች ጥቅሙን በቅጡ ተገንዝበው ኢትዮጵያውያንን በአስተማሪነት በመቅጠር በየዩኒቨርስቲዎቻቸው ዜጎቻቸውን የሚያስተምሩት ግእዝ ወዘተ…

እንዴትና ስለ ምን በጊዜ ሂደት የተናጋሪው ሰው ቁጥር ቀንሶ ከብሄራዊ ቋንቋነቱ ሊወርድ ቻለ❓ለግእዝ ቋንቋ መዳከም አቢይ ምክኒያት የአማርኛ መተካት ብቻ ሳይሆን ለቋንቋው የሚሰጠውና የተሰጠው ትኩረት መላላቱ የማያወላውል ምክኒያት መሆኑ ነው። በዚህም ተተኪው ትውልድ የትላንቱን ለዛሬ ማበርከት ያልቻ ሆኖ ይገኛል። በመሆኑም ትላንት የኢትዮጵያ የከፍታ መሰረት የነበረው ግእዝ ከነበረበት የብሔራዊና የውል ቋንቋነት ይቅርና ዛሬ ዛሬ ለእውቀት እንማረው መባል ሲጀመር የልዩነት ማዕከል እየተደረገ ይገኛል።

ግእዝ ከአሁኑ ዘመን ጋር እኩል ለመጓዝ የማይጠቅም ጊዜ ያለፈበት ያረጀ ቋንቋ ነውን❓አንዳንድ ሰዎች ከግእዝ ይልቅ እንግሊዝኛ፣ ቻይንኛ፣ ፈረንሳይኛ ወዘተ… ቢማሩ በእጅጉ የሚያተርፉ መሆኑን በመከራከሪያነት ሲያነሱ ይስተዋላል። እነዚህን መማር ጥቅሙ የላቀ መሆኑ አይካድም። ነገር ግን “አባቱን አያውቅ አያቱን ይናፍቅ” ያሰኛል።

በአሁኑ ዘመንስ ከሙታንነት ተቀስቅሶ በትውልዱ ላይ ሊጫን የተፈለገ የሃይማኖት መስበኪያስ ነውን❓በኔ ምልከታ ዛሬ ግእዝን ያወቀና የተማረ ሁሉ ነገረ ሀይማኖት ተረዳ ማለት አይደለም። ምክኒያቱም ቋንቋን ማወቅና መማር እምነትን የሚያስቀይር ቢሆን ኖሮ በእርግጥም ዛሬ ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የግብጽ ኦርቶዶክስ አማኞች እስልምናን በተቀበሉ ነበር። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በግእዝ የተጻፉ ብዙ የእስልምና እምነት መፀሀፎች ሲኖሩ በአረብኛም የተከተቡ ብዙ የኦርቶዶክስ ድርሳናት ይገኛሉ። ስለሆነም ግእዝ ሃይማኖታዊ ቋንቋ አይደለም። It’s Part of Our LIVING History.

ዛሬስ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ መሰጠቱን ደግፎ ነገር ግን በ1ኛ እና 2ተኛ ደረጃ ትም/ት ቤቶች እንዲሰጥ መወሰኑን በይፋ መቃወም የቋንቋውን ጠቃሚነት ካለመረዳት በሚመነጭ አመለካከት ይሆን❓ይህንን ጥያቄ የሚያነሱ አካላት ሊገነዘቡት ያልቻሉት ነገር ቢኖር ጥያቄው በራሱ የግእዝን መማር አስፈላጊነት የሚጠቁም መሆኑን ነው። በተጨማሪም አሁን እየተጠቀምንበት ያለው አማርኛ ቋንቋ ሆሄያቱ የግእዝ ፊደላት ሁነው ሳለና በዚሁ ቃላት እየፃፉ ግእዝን ማስተማር አያስፈልግም ሲሉ እንደመስማት የሚያሳዝን ነገር ከወዴት ይገኝ ይሆን።

እንደ ጥቅል እነዚህንና ተያያዥ ተጠየቆችን ስንመለከት ኢትዮጵያዊያን በአለም ፊት አንገታቸውን ቀና አድርገው በኩራት የሚናገሩለትን ማለትም ጥንታዊ የስርዓተ መንግስትና የስልጣኔ መነሻ፣ የራሷ ቋንቋና ፊደል፣ የቀን አቆጣጠር ወዘተ… ያላት ብርቅየ ሐገር ለመሆኗ መነሻ የሆነው ግእዝ በእርግጥም እንዲሞት ተፈረደበት እንጂ ራሱን አልገደለም የሚል ድምዳሜ እንዲያዝ ያደርጋል።

ዛሬም ዳግም እንዳይነሳ መቃብሩን አርቀው እየቆፈሩና በላዩ ላይ የልዩነት ቋጥኝና አለት እየጫኑበት ያሉት እሱ (ግእዝ) ባስገኘው የሚኮሩ ነገር ግን እሱን (ግእዝን) መማር በሚረግሙ አካላት ከሆነ ሰንበትበት ብሏል። እነሆ ይፋዊ ጥቃትም ውግዘትም በግእዝ ላይ ተከፍቶበት ይገኛል። ለዚህም ነው በድጋሚ ግእዝ እንዲገደል ተወሰነበት እንጂ ራሱን አላጠፋም የምንለው።

#መደምደሚያ

ግእዝ ከአማርኛና ሌሎች ኢትዮ-ሴማዊ ቋንቋዎች ጋር ሲወዳደር ንጹህ ሴማዊ ቋንቋ ነው። በተጨማሪም ግእዝ በመላው የአፍሪካ ሐገራት ውስጥ የመጀመሪያውና ብቸኛ አፍሪካዊ የራሱን ፊደላት የያዘ ቋንቋ ሲሆን በዓለምም ላይ ዋናና የስልጣኔ አራማጅ ከሚባሉት ቋንቋዎች አንዱ ሁኖ ይገኛል።

ስለሆነም ኢትዮጵያ የቀደምት ስልጣኔ ባለቤት መሆኗን በእርግጥም የምንኮራበት ከሆነ ለኩራታችን ምንጭ የነበረውን ግእዝ ከታች ጀምሮ ለማስተማር በትግበራ ላይ ስለሚገኝ በቀጣይ ስርዓተ ትምህርቱ እየዳበረ እንዲሄድ ለማሻሻያነት ግብዓት የሚሆኑ ጉዳዩችን በተደራጀ መንገድ ለሚመለከተው ተቋም በማቅረብ የዜግነት ግዴታዎን ሊወጡ ይገባል።

በመጨረሻም ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሐገር፣ የታሪክ እና የቅርስ ባለአደራ ነው‼️

አነታራኪው የግዕዝ ቋንቋ (ይስማዕከ ወርቁ)(፩) የግዕዝን ቋንቋ ከሰኩላሪዝም (Secularism) አንጻር ስናዬው...የግዕዝ ቋንቋ የሦስተኛ ክፍል የተማሪዎች መጽሐፍ ደርሶኝ እያገላበጥኩ ሁሉ...
18/09/2025

አነታራኪው የግዕዝ ቋንቋ

(ይስማዕከ ወርቁ)

(፩) የግዕዝን ቋንቋ ከሰኩላሪዝም (Secularism) አንጻር ስናዬው...

የግዕዝ ቋንቋ የሦስተኛ ክፍል የተማሪዎች መጽሐፍ ደርሶኝ እያገላበጥኩ ሁሉንም አየሁት። የሶስተኛ ክፍል የተማሪዎች መጽሐፍ 83 ገጽ አለው። ሲያጠናቅቅ ከግዕዝ ቋንቋ ወደ አማርኛ ቋንቋ የሚፈታ የሙዳዬ ቃላት ይዟል።

መጽሐፉን ሳዬው በትክክል የተዘጋጀ መሆኑን አይቻለሁ። የንግግሩ ቃላት ሁሉ እምነትን እንዳይነካ ሆኖ በጥንቃቄ የተዘጋጀ መሆኑን አረጋግጫለሁ። የግዕዝ ቋንቋን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት አስጠግታው እንደኖረች እሙን ነው። ይህን ሁሉም ያምናል። ሙስሊሙም ክርስቲያኑም። ግን ወደ ልጆቹ ሲመጣ አስጠግታ ያቆየችው ሃይማኖት አለችና የእነርሱን እምነት እንዳይሰብክ ልጆቻቸውን መከላከሉ ከእናትና ከአባት የሚጠበቅ ነው። ግን እነርሱ ሳይሆኑ የሚከራከሩት መጽሐፉን ያላዩት የፖለቲካ ጥገኞች የሆኑ ሰዎች መሆናቸውን መጽሐፉን እኔም ካየሁት በኋላ አረጋግጫለሁ። እንዲያውም ከተዋህዶ ሃይማኖት ጋር የግዕዝ ቋንቋ ተጠግቶ ስለኖረ አስጠግታው የኖረችውን ሃይማኖት ጥቅሶች እንዳያመጣ ስግቼ ነበር። እንደዛ ያለ ነገር ግን መጽሐፉን በማነብበት ወቅት አላገኘሁም። የግዕዝ ቋንቋ እና ሃይማኖት የተለያዩ እንደሆኑ ይህን መጽሐፍ ያዘጋጁት ሰዎች፣ ብልህ እንደሆኑ መጽሐፉን ሳነብ አረጋግጫለሁ። የመጽሐፉ "ኮፒ ራይት" ይዞኝ እንጂ ሙሉውን ለእናንተ እለጥፈው ነበር። የአዘጋጁት ሰዎች እና የተረከበው አካል መፍቀድ አለበት።

በአማርኛም የትኛውንም እምነት መስበክ ይቻላል። የእስልምናንም ሆነ የትኛውንም የክርስቲያን እምነት በማንኛውም ቋንቋ መስበክ ይቻላል። የግዕዝን ትምህርት በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ ለማስገባት ያሰቡ ሰዎች ሴኪውላር ማድረግ ያስፈልጋቸዋል። በፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም ሰኩውላሪዝምን (Secularism) ስናዬው፣ ሃይማኖትና መንግሥት የተለያዩ ናቸው። እኔ ግን እንደ ሀሳብ የምሰጠው፣ ኢትዮጵያ ከፖለቲካ የፀዳ ትልቅ የቋንቋ ተቋም ያስፈልጋታል። በዛ ተቋም ተገምግሞ አልፎ ቢሄድ ኖሮ እስከ አሁን የግዕዝ ቋንቋ ባላነታረከን ነበር። ማንም መንገደኛ አያደናግረንም ነበር። ከቋንቋዎች ሁሉ ደግሞ የመጀመሪያውና ኢትዮጵያን የምናስጠራበት ቋንቋ አንዱና ዋነኛው ግዕዝ ነው። የኢትዮጵያ ቀርቶ የአፍሪካ ሁሉ ኩራት ነው።

ግዕዝ ቋንቋውን ግን የኦርቶዶክስ ሃይማኖት አስጠግታው ስለኖረች፣ ከዛ አንዳንድ ጥቅሶች እንዳይገቡ መጠንቀቅ ያሻል ብዬ ነበር ግን መጽሐፉን ሳነበው ምንም የሚያጨቃጭቅ ነገር አላዬሁበትም። በጥራዝ ነጠቅ ያወሩ ሰዎች ነበር የሚያደናግሩን። በተለይም ከዚህ በፊት የተለጠፉ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ያላቸውን ሰዎች መጽሐፍ ከጎግል ላይ እያወጡ በትምህርት ስርዐቱ ውስጥ የገባ መስሎን እኔም ብዙ ሰዎችን በስልክ መከራቸውን ሳበላ ነበር። ግን በፍፁም እንደዛ እንዳልሆነ መጽሐፉን ሳነብ አረጋገጥኩ። ወደ ፊት በስርአተ ትምህርቱ ውስጥ የግዕዝ ትምህርት እየሰፋ ሲሄድ፣ መጽሐፍ የሚያሰናዱ ሰዎች እንደዚህ መጽሐፍ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። የማንኛውንም እምነት እንዳይነካ፣ የትኛውንም ሃይማኖት እንዳይጎሽም አድርገው የማስተላለፍ ግዴታ አለባቸው። ይህ ግዴታ ነው።

(፪) የግዕዝ ቋንቋ አስተማሪዎች እነማን ይሁኑ?

የግዕዝን ቋንቋ የሚያስተምሩት ዲያቆናትና ቄሶች ናቸው ይባላል። ሃይማኖቱ አስጠግቶት ስለኖረ፣ እምነትን እንዳነካ አድርገው የተማሩት እንዲያስተምሩ መሆን አለበት። ያውም ከዩኒቨርስቲ የተመረቁ ቢሆን ይመረጣል። የግዕዝ ቋንቋ ሰኩላር (Secular) እየሆነ ሲመጣ ግን ሙስሊሞቹ ሰኩላር (Secular) ሆነው ማስተማር አለባቸው። አንድን ቋንቋ እየተጸየፍክ ግን እንኳን ለማስተማር ለመማርም አትበቃም። አንዳንድ የወሎ ሙስሊሞች ግዕዝ ያውቃሉ። እኔ ዛምራ የተባለው ልቦለዴን በምጽፍበት ወቅት ያገኘኋቸው አንድ ሙስሊም ሰው በግዕዝ ቋንቋ አውርተውኛል። እንዴውም የመጀመሪያውን ምዕራፍ የሰጠሁት አንድ ሙስሊም ልጅ ወደ ቅኔ ቤት ሲገባ የሚያሳዬውን ጠባይ በመንተራስ የተፃፈ ነው።

(፫) የግዕዝ ቋንቋ የጠንቋዮች እና የደብተራዎች እውቀት ነው ለሚሉ...

ጠንቋይ ማለት አደናጋሪ ማለት ነው። አምታቺ ነው። የማታውቀውን ቃል ያነበልብልሃል። የማታውቀውን ቃል ከግዕዝ ቃል እያወጣ መተት ደገምኩልህ ሊልህ ይችላል። እንዲያውም ከድግምት ቃላት ውስጥ አረብኛም በብዛት አለበት። ትናንት አንዱ የለጠፈውን የመተት ቃል አይቼ በሳቅ ፈረስኩ። የለጠፈውም ሰው እርሱ ሙስሊም ነኝ ይላል። ግን ቃላቱን አይቼ ስመረምረው ባብዛኛው የአረብኛ ቃላት አሉበት። ጫጫጫጫ ጃጃጃጃጃ ከሚለው ውስጥ አንዳንድ በተን በተን ያሉ የግዕዝ ቃላት አሉበት። ጳጳጳጳ ፓፓፓፓፓፓ ከሚለው ውስጥ ደግሞ ብዙ የአረብኛ ቃላት አሉበት። አስማተኞች መተተኞች እንዳይበሉን እንወቅ። ካላወቅክ ደግሞ ይበሉሃል። ይሸጡሃል። እንዳትሸጥ እወቅ። በሁሉም ቋንቋ መተት አለ። ድግምት አለ። በእንግሊዝኛም፣ በጀርመንኛም፣ በፈረንሳይኛም ድግምት አለ። እንዲያውም በአፍሪካ ቋንቋዎች አይብስም? በናይጀሪያማ አስማቱን የግላቸው ያደረጉት ይመስላል። ከዛ ውጪ ወደ አስማቱ ስንወርድ የተለያዩ የሚያምታቱ እና ብዙሃኑ የማያውቃቸውን ቃላት አሰማተኞች ይደርታሉ። ካላወቅህ ተበላህ ነው የምልህ። ይሸጡሃል። ይለውጡሃል። ገንዘብህን ንብረትህን ትበላለህ።

የግዕዝ ትምህርትን አትማሩ ማለት ግን የጠንቋዮች ስብከት ሊሆን ይችላል። ምክንያቱም አስማቱን ካወቅክባቸው በምን ሊደግሙት ይችላሉ? ይህ ይሰመርበት።

(፬)ከህክሞና አንፃር...

የግዕዝ መጻሕፍት የህክምና፣ የስነፈለግ፣ የኬሚስትሪ የእፅዋት ሳይንስን፣ የፊዚክስ ሁሉ አጭቀው ነው የያዙት። ይህን ፍለጋ ነው ነጮች የግዕዝን ቋንቋ ለማዎቅ የሚፈልጉት። ከዚህ አንጻር ሌላ ጊዜ መመለስ አለብኝ። አሁን ተዘርዝሮ አያልቅም።

እኔ በልጅነቴ ነው ሰባተኛ ክፍል ሆኜ ወደ ሀዋሳ የሄድኩት። ሀዋሳ ማለት የብዙ ቋንቋ ተናጋሪ ያለበት ከተማ ናት። ተማሪቹ አፋቸውን የፈቱበት የየራሳቸው ቋንቋ አላቸው። በተጨማሪም አማርኛ፣ እንግሊዝኛ እና ሲዳምኛ ትምህርት ቤት እንማራለን። ብዙዎቹ ተማሪዎች ባለ ብዙ ቋንቋ (Multilingual) ናቸው። እኔ ግን በልጅነቴ የግዕዝ ቋንቋ በመማሬ በእርሱ እንኳን ተጽናናሁ እንጂ ከአማርኛ በቀር በምንም አልግባባቸውም ነበር። አማርኞዬም ለእነርሱ ይከብዳቸው ይመስለኛል። ብቼኝነቴ ከመጽሐፍ ጋር አቆራኘኝ። ብቼኝነቴ እንድጽፍ ገፋፋኝ። ስለዚህ ሰናጠቃልለው የግዕዝ ቋንቋንተማሪዎች መማራቸው ሊበረታታ ነው የሚገባው። በሌላ ክፍለ ሀገር ያሉት ባለ ብዙ ቋንቋ ተናጋሪዎች ናቸው። ቢያንስ አንድ ቋንቋ በተጨማሪ ቢማሩ ጥሩ ነው ብዬ አስባለሁ። ጥሩ ጊዜ ከመጣ ደግሞ በሁሉም ክፍለሀገር ቢሰጥ ጥሩ ነው። ግዕዝ ማለት የሁላችንሞ ቋንቋ ነው። ከመጽሀፉ ላይ አልፎ አልፎ ለምስክርነት እንዲረዳ ተጠቅሜአለሁ። ሰናይ ጊዜ።


+ ቅዳሴ የማይችሉት ካህን + ታሪኩ የኾነው በግብጽ ሀገር ነው። የተወሰኑ ምዕመናን ተሰብስበው ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና የተሰኙትን ካህን ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ከሰሷቸው። የክሱ ጭብጥ "ካህኑ...
13/09/2025

+ ቅዳሴ የማይችሉት ካህን +

ታሪኩ የኾነው በግብጽ ሀገር ነው። የተወሰኑ ምዕመናን ተሰብስበው ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና የተሰኙትን ካህን ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ከሰሷቸው። የክሱ ጭብጥ "ካህኑ የቅዳሴውን ጸሎት በቅብጥ ቋንቋ ለማለት ተቸግረዋል፤ በአግባቡ በቃላቸው ማድረስ አይችሉበትም" የሚል ነበር። መቼም "ቅዳሴ መቀደስ አይችልም" የሚል ክስ በካህን ላይ ሲመጣ ከባድ ነውና፤ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ቶማስ ጉዳዩን እንደሰሙ ካህኑ በአስቸኳይ እንዲመጡ መልእክት ላኩባቸው። ቀሲስ ዳንኤል ዮሐናም ጥሪው በደረሳቸው በማግስቱ ለጉዞው መዘጋጀት ጀመሩ። አህያቸውን እየጫኑ እያለም ባለቤታቸው በመንገድ ላይ ረሃብ ከጸናባቸው እንዲበሉት በሚል የጋገረችላቸውን ኅብስት በመሀረብ ጠቅልላ ሰጠቻቸው። ካህኑ ቀሲስ ዮሐናም ኅብስቱን ተቀብለው የሀገረ ስብከቱ መቀመጫ ወደ ሆነው አል-ሚኒያ ጉዞ ጀመሩ።

በመንገድ ላይ እየሄዱ ሳለም ሊቀ ጳጳሱ ሊጠይቁኝ ይችላሉ ብለው ያሰቧቸውን የቅዳሴ ክፍሎች በቅብጥ ቋንቋ እያዜሙ መለማመድ ጀመሩ። በዚህ ሁኔታ ተጉዘውም ወደ አል-ሚኒያ ደረሱ።

ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና ወደ ሊቀ-ጳጳሱ ብጹዕ አቡነ ቶማስ ቢሮ ሲገቡ ግን ሊቀ-ጳጳሱ ባዩት ሁኔታ ተደናገጡ። ቀሲስ ዳንኤል በእጃቸው በመሃረብ የተጠቀለለ እና በደም የራሰ ኅብስት ይዘዋል። ሊቀ ጳጳሱም በመንገዳቸው ምን እንዳጋጠማቸው ቀሲስ ዳንኤልን ጠየቁ። ቀሲስ ዳንኤልም በትህትና መንፈስ ኾነው "በዚህ መሀረብ የተጠቀለለው ኅብስት ነው። በመንገድ እየመጣሁ እያለሁ ቅዳሴውን በቅብጥ ቋንቋ እየተለማመድኩ ነበር" ብለው መለሱ። ብጹዕ አቡነ ቶማስ በሁኔታው ተደነቁ። ለካስ በካህኑ ጸሎት ኅብስቱ የጌታችንን አማናዊ ቅዱስ ሥጋ ሆኖ ነበር።

ሊቀ ጳጳሱ የጌታችንን አማናዊ ቅዱስ ሥጋ በቦታው ለነበሩት ሰዎች ካቀበሉ በኋላ ወደ ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና በመዞር "በሉ ወደመጡበት ቤተክርስቲያን ይመለሱ፤ ከዚህ ቀደም ሲያደርጉ እንደነበረው አገልግሎትዎን ይቀጥሉ" ብለው አሰናበቷቸው። እርሳቸውን ለመፈተን ተሰብስቦ የነበረውም ጉባዔ ተበተነ።

ምንጭ፦ “Mallawy’s Blessed Priest: The Late Hegumen Daniel Youhanna Maqa" by Fr. Youannis Kamal

ከዱባይ ስውሯ ማርያም በዌልቸር ሄዤ በእግሬ ወጣሁየዛሬው ታሪካችን የብዙዎቻችንን ልብ የሚነካ ነው። ዱባይ የምትኖረው አንዲት እህታችን በድንገት ባልታወቀ ህመም ከአልጋ ላይ ዋለች። ለስድስት ...
25/08/2025

ከዱባይ ስውሯ ማርያም በዌልቸር ሄዤ በእግሬ ወጣሁ

የዛሬው ታሪካችን የብዙዎቻችንን ልብ የሚነካ ነው። ዱባይ የምትኖረው አንዲት እህታችን በድንገት ባልታወቀ ህመም ከአልጋ ላይ ዋለች። ለስድስት ወራት ሙሉ መቆም፣ መራመድ፣ መመገብ እና መልበስ ሁሉ ተሳናት።

በዱባይ ያሉ ብዙ ዶክተሮችን ብትጎበኝም መፍትሄ ማግኘት ስላልቻለች፣ ተስፋ ቆርጣ “ከሞትኩም በአገሬ ልሙት” ብላ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰች።

ቤተሰቦቿም “ልትሞት ነው” በሚል ፍርሃት ሶስት ቀን ሙሉ ሲያለቅሱና ሲጠብቋት ቆዩ። ነገር ግን በልቧ ያለው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅር ትንፋሽ ሊሰጣት ቻለ። ድካሟንና ህመሟን ሁሉ ችላ “እባካችሁ ወደ እመቤቴ ውሰዱኝ፣ እግርጌዋ ላይ ልሙት” ብላ በእንባ ለመነቻቸው።

በአምስት ሰዎች ታዝላ ወደ ስውሯ ማርያም ፀበል ሄደች። የደረሰችው የድካም ጫፍ ላይ ሆና ነበር።። ገና ፀበል መጠመቅ ከጀመረች በሶስተኛው ቀን ቀስ እያለች እግሮቿን ማዘዝ ጀመረች።

በሰባተኛው ቀን ደግሞ ተአምር ተፈጸመ። ሙሉ በሙሉ ድና በሁለት እግሮቿ እየተራመደች ከቤተመቅደሱ ወጣች።

ዛሬም ወደ ስራዋ ተመልሳ ዱባይ ትገኛለች። “ለኔ የደረሰች ድንግል ማርያም ለእናንተም ትድረስላችሁ” ትላለች።

ስርክ አዲሥ 🙌

🙏🙏🙏

ከ30ሺህ በላይ ምዕመናን ተገኝቷል።13ኛው ማዕዶት ለኢትዮጵያ የኪነጥበብ መርሐግብር እጅግ በደመቀ መልኩ ከ30 ሺህ በላይ ምዕመናን በተገኙበት በዛሬዉ እለት መካሄዱን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።በፎቶ...
17/08/2025

ከ30ሺህ በላይ ምዕመናን ተገኝቷል።

13ኛው ማዕዶት ለኢትዮጵያ የኪነጥበብ መርሐግብር እጅግ በደመቀ መልኩ ከ30 ሺህ በላይ ምዕመናን በተገኙበት በዛሬዉ እለት መካሄዱን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።

በፎቶ ይመልከቱ!

📸 Selus Studio
Your Complete Photo & Print Solution

🎉 Photography Services
• Wedding 📷
• Birthday 🎈
• Graduation 🎓
• Studio Portraits
• ID & Passport Photos
• Family & Baby Photography

📸 Selus Studio – Where Every Moment Becomes a Memory!
✨ Your go-to place for professional photography, printing & creative design.
📍 Located in Bahir Dar Depo to noc 30 meter
📞 Contact us via telegram:

📌 Follow us for updates and sample

Selus Studio

  ?" ልጆች ስልክ ከያዙ ጥናታቸውን እስከጭራሹ እየረሱት ተቸገርን። ምን ብናደርግ ይሻላል ? " - ወላጆች➡️ " ወላጆች አልገባቸውም ገና ለልጆቻቸው ቦምብ ነው እያሳቀፉ ያሉት " - የሥነ...
09/08/2025

?

" ልጆች ስልክ ከያዙ ጥናታቸውን እስከጭራሹ እየረሱት ተቸገርን። ምን ብናደርግ ይሻላል ? " - ወላጆች

➡️ " ወላጆች አልገባቸውም ገና ለልጆቻቸው ቦምብ ነው እያሳቀፉ ያሉት " - የሥነ ልቦና ባለሙያ

በተለይ በአስራዎቹ የእድሜ ክልል ያሉ ልጆች ከማጥናት፣ ከመታዘዝ ይልቅ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ላይ በመቸከል በከፋ ሱስ እየተዘፈቁ፣ አልባሌ ነገር እየተለማመዱ መሆኑን ወላጆች ገልጸዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የልጃቸውን ሁኔታ ያስረዱ አንዲት እናት፣ " አዝዠው የነበረውን ሥራ ለመስራት ‘እሺ’ ካለኝ በኋላ ስልክ ሲጠይቀኝ አይሆንም ስለው ሁሌም ትዕዛዝ አይፈጽምም " ሲሉ ስለ 12 ዓመት ልጃቸው ድርጊት ተናግረዋል።

" የጥናት ጊዜውን ራሱ ስልክ ከያዘ ስለሚረሳው ከአባቱ ጋር ሁሌ ግጭት ነው። ሁሌም ይቀጣል ግን ሊስተካከል አልቻለም " ያሉት እኝሁ እናት፣ " በትምህርቱ አንደኛ ደረጃ ለቆ አያውቅም አሁን ሰንፏል። ምን ባደርገው ይሻላል? " ሲሉ ጠይቀዋል።

ሌላኛው ወላጅ፣ " ልጄ ስልክ ላይ ከተጣደ አይንቀሳቀስም። መመገብንም ይዘነጋዋል። ዝም ዝዬ ስከታተለው ጌም ብቻ ሳይሆን ሌሎች አስነዋሪ ነገሮችንም ነው የሚመለከተው " ሲሉ ተናግረዋል።

" በተለይ የአዲሱ መፅሐፍ ህትመት በወቅቱ ባለመድረሱ ለሶፍት ኮፒ ማንበቢያ ስልክ ከገዛሁ በኋላ ነው እንዲህ የሆነው " ሲሉ ምንክንያቱን አስረድተዋል።

እኛም የህፃናት የስልክ አጠቃቀማቸው ላይ ምን መደረግ አለበት ? ስንል የሥነ ልቦና ባለሙያ የሆኑትን ቴዎድሮስ ድልነሳውን (ከእርቅ ማዕድ የሥነ ልቦና ማዕከል) አስተያዬት ጠይቀናል።

ባለሙያው አቶ ቴዎድሮስ ድልነሳው ምን አሉ ?

" እኛ አንድ የስልጠና ሴንተር አለን ከባጀት ዩዝና አዲክሽን ጋር የተያያዘ። ክላስ ላይ ራንደም አሰስመንቶች እሰራለሁና ከፍተኛ ነው ቁጥሩ አላግባብ የሆነ ሱስ የማስያዝ ደረጃ የሚደርስ አጠቃቀም ያላቸው።

አብዝተው የሚጠቀሙ፣ ሲቀር ቅር የሚላቸው፣ ክላስ ቁጭ ብለው ስለሱ የሚያስቡ፣ ከሰዎች ጋ ኮኔክት የማያደርጉ፣ ሲታዘዙ በጣም የሚነጫነጩ፣ ብቸኝነት የሚሰማቸው፣ ማቆም የሚከብዳቸው ብዙ ልጆች ናቸው።

ወላጆች ብዙ ፈተና ነው ያለባቸው። ግን ሳይቃጠል በቅጠል ነው መሆን ያለበት። ስልክ፣ ታብሌት አለመስጠት ነው።

ቴሌቪዥንም ህፃናት በአሁኑ ወቅት እቤት እንዲመለከቱ ሪኮመንድ አላርግም በእውነቱ። በሳምትንት አንዴ ወይም ሁለቴ የሚከፈት ካልሆነ በስተቀር። ምክንያቱም ቲቪ ላይ ራሱ ዩቱብ አለው " ብለዋል።

መፍትሄውን በተመለከተ ባለሙያው ምን አሉ ?

" ስልክን ጨምሮ ሌሎች ዲቫይሶች በሌለበት ቤት ልጆችን ማሳደግ በጣም ጥሩ ነው። ወላጆች ደግሞ ስልካቸው ላይ ስለሚጣዱ ልጆችም ስልክ ላይ ይጣዳሉ።

ልጆች ስልክ፣ ታብሌት መጠቀም የሚማሩት ከወላጆቻቸው ነው። ወላጅ ሥራ ሰርቶ ሲያበቃ ስልክ እነጎረጎረ መቀመጥን እንደ ኖርማል ካየው ከዚያ ይጀምራል ችግሩ።

ለልጆች ሰዓት መገደብን፣ ዲሲፕሊንድ መሆንን ማስተማር ያስፈልጋል። ሚዲያ ሊትረሲ እንደሚባለው የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ሊትረሲም አለና የቴክኖልጂ ሊትረሲ ያስፈልጋል።

መጀመሪያ ወላጅ መማር፣ መሰልጠን አለበት። ወላጆች አልገባቸውም ገና ለልጆቻቸው ቦምብ ነው እያሳቀፉ ያሉት። ቢላ ሽንኩርት ይቆርጣል ግን ደግሞ እጅም ይቆርጣልና እንኳን ልጆች ወላጆች እተቆራረጠ ነው እጃቸው " ሲሉ አስገንዝበዋል።

ወላጆች ለልጆቻቸው ስልክም ሆነ ታብሌት የሚሰጧቸው የልጆቻቸውን ፍላጎት ያሟሉ ስለሚመስላቸው ጨምር ነውና በዚህ ረገድ ምን ማስተዋል አለባቸው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ባለሙያው ተከታዩን ምክር ለግሰዋል።

ምን አሉ ?

“ ወላጆች ማስተዋል አለባቸው። የግንዛቤ ችግር አለ። ግንዛቤ ሰፊ ሥራ ነው የሚፈልገው። ልጅ የሚያስፈልገው ምንድን ነው ? የሚለው ነው ግንዛቤው።

ልጅ የሚልገው ሌላ ነው የሚያስፈልገው ደግሞ ልላ ነው። ልጆች ጓደኞቻቸው ታብሌት ይዘው ካዩ ይገዛ ሊሉ ይችላሉ ግን የሚያስፈልጋቸውን የሚያውቀው ወላጅ ነው።

ስለዚህ ወላጅ መሪ እንጂ ተመሪ አይደለም። ልጅ የፈገውን ነገር ሁሉ ማሟላት አይደለም ሥራው። ይህን መረዳትና ማወቅ በጣም ወሳኝ ነው።

ወላጅ ለመሆን ማነው ያስተማረን ? ከየት ነው እውቀታችን የመጣው ? ብለን መጠየቅ መቻል አለብን ካለዛ በመላ ነው ልጆች የምንመራው ማለት ነው።

በመላ የሆነ ነገር ደግሞ እንደ እድል ነውና ጥሩም መጥፎም ይወጣዋል። ስለዚህ በጥበብ፣ ዘመኑን በዋጀ፣ መንፈሳዊ ህይወትን፣ ባህልን፣ ኑሯችንን ባማከለ መልኩ መኖር ነው ነጥቡ " ብለዋል።

Via ቲክቫህ

ይሄ የተቀደሰ ሐሳብ እንዲሳካ የምትፈልጉ  #ሼር አድርጉትበስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን🙏አቤቱ ደውይ ነኝና ፈውሰኝ  (መዝ ፮፥፪)እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ በር...
06/08/2025

ይሄ የተቀደሰ ሐሳብ እንዲሳካ የምትፈልጉ #ሼር አድርጉት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን🙏

አቤቱ ደውይ ነኝና ፈውሰኝ (መዝ ፮፥፪)
እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ በርዕሰ ገዳማት ወ አድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የእናቶችና የአባቶች አንድነት ገዳም የ፬ ቱ ጉባያተ መጻህፍት ምስክር ጉባኤ ቤት በባህር ዳር ከተማ በአይነቱ ልዩ የሆነ ሆስፒታል ለመገንባት ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡

ለዚህም ይረዳ ዘንድ 400 ሚሊዮን ብር በመጀመሪያ ዙር ለመሰብሰብ ታቅዶ የገቢ ማሰባሰብ ስራው ተጀምሯል ፡፡ እርሰዎም ለሆስፒታል ግንባታ ፕሮጀክት እውን መሆን በሚከተሉት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የበኩልዎን ድጋፍ እንዲያደርጉ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡

በሒሳብ ስም ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የአራቱ ጉባኤያት መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት

የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ፡ 1000680619488

ዳሽን ባንክ፡5020827358011

አቢሲኒያ ባንክ፡ 219553568

ዓባይ ባንክ፡ 2011111181981013

አሐዱ ባንክ፡ 0068829811701

የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን፤ (መጽሐፈ ነህምያ 2:20)

ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር
+251 982 333 444
+251 983 333 444
+251 984 333 444

በመደወል ያግኙን!

መርዶን እንደ ብስራት (በእውቀቱ ስዩም) ሌሊቱ ተሽሮ፣ ጀንበር ዳግም ነግሳ የአንሶላ መግነዜን፣ በጥሼ ስነሳ አንዲት የንጋት ወፍ፣ መስኮቴ ላይ ቆማ እንዲህ ትለኛለች፣ በሚያስገርም ዜማ “እን...
05/08/2025

መርዶን እንደ ብስራት
(በእውቀቱ ስዩም)

ሌሊቱ ተሽሮ፣ ጀንበር ዳግም ነግሳ
የአንሶላ መግነዜን፣ በጥሼ ስነሳ
አንዲት የንጋት ወፍ፣ መስኮቴ ላይ ቆማ
እንዲህ ትለኛለች፣ በሚያስገርም ዜማ
“እንባህን ቆጥበው፣ በየጥጉ አትዝራው
መከረኛው እንጂ አያልቅም መከራው”
የደነደነ ልብ፣
በብዙ ጥገና በብዙ ስብራት,
ሲቀበል ይኖራል፣ መርዶን እንደ ብሥራት::

23/07/2025

ድንቅ ሴት!
ታተርፉበታላችሁ!

23/07/2025

ድንቅ ምክር
ታገሱ ታተርፊበታላችሁ!

21/04/2025

👉“አንተ የእስራኤልን ልጆች ቍጥር ተቀብለህ፥ በቈጠርሃቸው ጊዜ መቅሰፍት እንዳይሆንባቸው፥ በቈጠርሃቸው ጊዜ ከእነርሱ ሰው ሁሉ እንደ ቍጥራቸው መጠን ።” (ዘጸ. 30፥12)
👉“የማስተስረያውንም #ገንዘብ ከእስራኤል ልጆች ወስደህ ለመገናኛው ድንኳን ማገልገያ ታደርገዋለህ፤ በእግዚአብሔርም ፊት ለእስራኤል ልጆች መታሰቢያ ይሁን።” (ዘጸ. 30፥16)
👉“ #ኀጥእ የጻድቅ #ቤዛ ነው፤ #በደለኛም የቅን ሰው #ቤዛ ነው።” (ምሳሌ 21፥18)
👉“እኔ የእስራኤል ቅዱስ አምላክህ እግዚአብሔር መድኃኒትህ ነኝ፤ አድርጌ፥ ኢትዮጵያንና ሳባንም ለአንተ ፋንታ ሰጥቻለሁ።” (ኢሳ. 43፥3)
👉“ሹምና ፈራጅ እንድትሆን የሾመህ ማን ነው? ብለው የካዱትን፥ ይህን ሙሴን በቍጥቋጦው በታየው በመልአኩ እጅ እግዚአብሔር ።” (ሐዋ. 7፥35)

 #ሰበር! : የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን " በቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ በወንጀል የሚያስጠይቅ ድርጊት ፈጽመዋል " ያለቻቸው አቶ ጽጌ ስጦታው እና አቶ ምስጢረ መዝገቡ የተባ...
11/04/2025

#ሰበር!
: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን " በቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ በወንጀል የሚያስጠይቅ ድርጊት ፈጽመዋል " ያለቻቸው አቶ ጽጌ ስጦታው እና አቶ ምስጢረ መዝገቡ የተባሉ ግለሰቦች ተጠርጥረው በሕግ ቁጥጥርስ ስር መዋላቸውን አሳውቀች።

የቤተክርስቲያኗ የሕግ ባለሙያዎች ዐቢይ ኮሚቴ ፥ " እራሳቸውን ' መሪጌታ ' ጽጌ ስጦታው እና ' መሪጌታ ' ምስጢረ መዝገቡ ብለው የሚጠሩ ግለሰቦች በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሥርዓተ እምነት ላይ በወንጀል የሚያስጠይቅ ድርጊት ፈጽመዋል በሚል ተጠርጥረው የወንጀል አቤቱታ ቀርቦባቸዋል " ሲል አሳውቋል።

በዚህም የፌደራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ በዛሬው ቀን ተጠርጣሪዎችን በሕግ ቁጥጥር ሥር በማዋል የወንጀል ምርመራውን በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።

" ከግለሰቦቹ በተጨማሪ እንዳልካቸው ዘነበ የተባለ ግለሰብ በተመሳሳይ ከዚህ ቀደም በቤተክርስቲያኗ ላይ ፈጽሞታል ተብሎ በተጠረጠረበት ስም ማጥፋት በቅርቡ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውሎ ቃሉን ሰጥቶ በዋስትና መለቀቁንና በአቃቤ ሕግ በኩልም የወንጀል አቤቱታ ክስ ቀርቦ በሒደት ላይ ይገኛል " ሲል አሳውቋል።

መረጃው የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኅን አገልግሎት ነው።

Address

Bahir Dar
6000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Selus Studio posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category