Gojjam press

Gojjam press አብ ቀባዒ ወልድ ተቀባዒ መንፈስ ቅዱስ ቅብዕ ትክክለኛው ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ነው፡፡
ተዋህዶ የሚያሰኝም ይህ ነው!

03/09/2025

አባ አብርሀም

26/08/2025
20/08/2025

በዓለ ደብረ ታቦር እና ቡሄ
++++++++++++++++++++
ጌታችን ምሥጢረ መለኮቱን ለገለጠበት ለበዓለ ደብረ ታቦር እንኳን በሰላም አደረሰን!

ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን፣ ክብረ መንግሥቱን መግለጡን በማሰብ በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ ቀን በዓሉ በድምቀት ይከበራል፡፡ ይህ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ዘንድ ‹ቡሄ› በመባል ይታወቃል፡፡ ቡሄ ማለት ‹መላጣ፣ ገላጣ› ማለት ነው፡፡ በአገራችን ክረምቱ፣ ጭጋጉ፣ ደመናው ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታይበት በዚሁ በዓል አካባቢ ስለ ኾነ በዓሉ ‹ቡሄ› ተብሎ ይጠራል፡፡ በዓለ ደብረ ታቦር ጌታችን ምሥጢረ መለኮቱን የገለጠበት፤ ብርሃን የታየበትና ድምፀ መለኮቱ የተሰማበ ዕለት ስለ ኾነ ‹የብርሃን› ወይም ‹የቡሄ› በዓል ይባላል፡፡

ቡሄ ሲመጣ የክረምቱ ጨለማነት አልፎ ወደ ብርሃን፣ ወደ ጥቢ የሚያመራበት፤ ወደ መፀው የሚገባበት፤ ወገግታ የሚታይበት፤ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚሸጋገርበት ወቅት በመኾኑ ከቡሄ በኋላ የጠነከረ ክረምት አይኖርም፡፡ ‹‹ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት›› እንዲሉ፡፡ በአንዳንድ የአገራችን አካባቢዎች የቡሄ ዕለት ማታ ምእመናን ችቦ ያበራሉ፡፡ ይህም በደብረ ታቦር ለታየው ብርሃነ መለኮት ምሳሌ ነው፡፡ ሕፃናቱ ይህ በዓል ከመድረሱ በፊት ቀደም ብለው ጅራፍ ሲገምዱና ሲያጮኹ (ሲያኖጉ) ይሰነብታሉ፡፡ እናቶችም ለዚህ በዓል የሚኾን ዳቦ ለመጋገር ስንዴያቸውን ሲያጥቡ፣ ሲፈትጉ ይሰነብታሉ፡፡ በበዓሉ ዋዜማ (ነሐሴ ፲፪ ቀን) ሕፃናት በየቤቱ እየዞሩ ‹‹ቡሄ ና በሉ፤ ቡሄ በሉ፡፡ ቡሄ መጣ፤ ያ መላጣ፤ ቅቤ ቀቡት እንዳይነጣ …›› እያሉ ይጫወታሉ፡፡ በዚህ ጊዜ እናቶች ካዘጋጁት ዳቦ እያነሡ ይሰጧቸዋል፡፡ ሕፃናቱ ‹ቡሄ› የሚሉትም ዳቦውን ነው፡፡

ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን በገለጠበት ዕለት እረኞች ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች ችቦ አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጥተዋል፡፡ ‹ቡሄ› ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ የሚሰጠውና በበዓሉ ችቦ የሚበራውም ከዚህ ታሪክ በመነሣት ነው፡፡ ለክርስትና ልጅ፣ ለአማች፣ ለምራት፣ ለዘመድ አዝማድ ዅሉ የቡሄ ዳቦ ይሰጣል፡፡ ልጆችም ዳቧቸውን እየገመጡ ጅራፍ ሲገርፉ ይውላሉ፡፡ የጅራፉ መጮኽ የድምፀ መለኮት ምሳሌ ሲኾን፣ ጅራፉ ሲጮኽ ማስደንገጡም ነቢያትና ሐዋርያት በድምፀ መለኮት መደንገጣቸውንና መውደቃቸውን ያስታውሳል፡፡

መምህረ ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስቱን ተማሪዎቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ በደብረ ታቦር ምሥጢር መግለጡን በማስታዎስ የአብነት ተማሪዎች ከመምህራቸው ጋር በመኾን በዓለ ደብረ ታቦርን (ቡሄን) ያከብራሉ፤ ስሙን ይጠራሉ፡፡ የአብነት ተማሪዎች ‹‹ስለ ደብረ ታቦር›› እያሉ እኽል ከምእመናን በመለመንና ገንዘብ በማዋጣት ጠላውን ጠምቀው፣ ዳቦውን ጋግረው፣ ቆሎውን ቆልተው ለደብረ ታቦር ዕለት ሊያስቀድሱ የመጡትን ምእመናን በመጋበዝና እርስበርስ በመገባበዝ፣ እንደዚሁም ቅኔ በማበርከት በዓለ ደብረ ታቦርን በታላቅ ድምቀት ያከብራሉ፡፡ ይህም እስከ አሁን ድረስ በአብነት ትምህርት ቤቶች የሚሠራበት ነባር ትውፊት ነው፡፡

ነገር ግን በአንድ አካባቢዎች በተለይ በከተማ ዙሪያ በዓለ ደብረ ታቦር (ቡሄ) ሃይማኖታዊ ትውፊቱን የለቀቀ ይመስላል፡፡ ለዚህም ልጆች የሚጫወቱበት መዝሙር ግጥሙና ዜማው ዓለማዊ መልእክት የሚበዛበት መኾኑ፤ በወቅቱ ችቦ ከማብራት ይልቅ ርችት መተኮሱና በየመጠጥ ቤቱ እየሰከሩ መጮኹ፤ ወዘተ. የበዓሉን መንፈሳዊ ትውፊት ከሚያደበዝ

18/08/2025

ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት የሚጠይቀው የደመወዝ ማሻሻያ፦
*****************************

ከመስከረም 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡ በዚሁ ማሻሻያ መሠረት፦

1. ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4,760 ወደ ብር 6,ዐዐዐ እንዲያድግ
ይደረጋል፡፡
2. የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6,940 ወደ ብር 11,500 ይሻሻላል።
3. ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም
ማሻሻያ ይደረግበታል፡፡
4. ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21,492 ወደ ብር 39,000
እንዲያድግ ይደረጋል፡፡

በዚህ ጉዳይ ላይ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሰጠውን መግለጫ በኮሜንት መስጫው ውስጥ ያገኙታል፦

14/08/2025
14/08/2025

አለም ሁሉ ኦርቶዶክስ ይሆናል። በመጨረሻው ሰዓት እውነት ትገለጻለች እውነትም ኦርቶዶክስ ላይ ትገኛለች። እውነትን መፈለግ ብልህነት ነው ።

መልካም ፆመ ፍልሰታ
11/08/2025

መልካም ፆመ ፍልሰታ

11/08/2025

"በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ክስ ተመስርቶበት ከሀገር እንዳይወጣ እግድ ተጥሎበታል" ተብሎ ሲነገር የነበረው ፓስተር ትዝታው ሳሙኤል፣ ወደ አሜሪካ መመለሱን ወዳጆቹ ገለጸዋል። ይህ ክስተት፣ "ፖሊስ ፈልጌ አጣሁት" ያለው ግለሰብ እንዴት ከሀገር ሊወጣ ቻለ? የሚል ጥያቄን በማስነሳት፣ የህግ የበላይነትን ጉዳይ በድጋሚ አነጋጋሪ አድርጎታል።

ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም.፣ ፓስተር ትዝታው ሳሙኤል በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ "ለኢየሱስ" የተሰኘ ታላቅ የመዝሙር ድግስ ካዘጋጀበት ዕለት ሁለት ቀን ቀደም ብሎ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የህግ ክፍል ኃላፊ መግለጫ መስጠታቸው ይታወሳል።

በመግለጫውም፣ ቤተክርስቲያኗ በፓስተሩ ላይ ክስ እንደመሰረተችና በዚህም መሰረት የፍርድ ቤት የማሰር ትዕዛዝና ከሀገር የመውጣት እግድ እንደተላለፈበት አስታውቀው ነበር። የሚገርመው ግን፣ የፌደራል ፖሊስ፣ በሺዎች ፊት መድረክ ላይ የነበረውን ፓስተር "ፈልጌ አጣሁት" ማለቱ፣ በወቅቱ ከፍተኛ መነጋገሪያን ፈጥሮ ነበር።

ከዚህ ሁሉ ውዝግብ ከአንድ ሳምንት በኋላ፣ ፓስተር ትዝታው ሳሙኤል አሜሪካ ተመልሷል መባሉ፣ የብዙዎችን ግምት ወደ ሌላ አቅጣጫ ቀይሮታል።

አንድ ግለሰብ ላይ የፖሊስ የጉዞ እግድ አለ እየተባለ፣ እንዴት የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን የኢሚግሬሽን ቁጥጥር አልፎ ሊወጣ ቻለ? የሚለው ጥያቄ በስፋት እየተነሳ ነው።

የህግ ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ ይህ ክስተት በኢሚግሬሽንና በጸጥታ አካላት በኩል ከባድ የሆነ የኃላፊነት ጉድለት ወይም ሆን ተብሎ የተደረገ ማላላጥ መኖሩን ያሳያል።

"የፓስተሩ ከሀገር መውጣት፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጀመረችው የህግ ሂደት ላይ ትልቅ እንቅፋት ከመፍጠሩም በላይ፣ በሀገሪቱ የፍትህ ስርዓት ተአማኒነት ላይ ጥቁር ጥላን አጥልቷል" ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።

በጉዳዩ ላይ ከሚመለከታቸው የመንግስት የጸጥታ አካላት በኩል የተሰጠ ምንም አይነት ይፋዊ ማብራሪያ የለም።

10/08/2025

ድልድዩ በጎርፍ ተወሰደ‼️
በአማራ ክልል ከአዲስ አበባ-ደብረማርቆስ-ባህርዳር
በሚወስደዉ መንገድ በጊደብ ወንዝ ላይ የተሰራዉ ድልድይ በጎርፍ ተወሰደ‼️

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የደብረማርቆስ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ተገጣጣሚ ድልድይ በፍጥነት በመንገንባት ለአገልግሎት ለማብቃት እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

ድልድዩ በጎርፍ የተወሰደዉ ነሐሴ 3/2017 ሌሊት ጮቄ አካባቢ በጣለዉ ከባድ ዝናብ በተፈጠረ ጎርፍ ነዉ። ድልድዩ ጥዋት አካባቢ እንደተወሰደ የአካባቢዉ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የደብረማርቆስ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ስለጉዳዩ ጠይቀናቸዉ ችግሩ መከሰቱን ገልጸዉ ተገጣጣሚ ድልድይ ለመስራት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በዛሬዉ እለት ከአዲስ አበባ መጫን መጀመራቸዉን ገልጸዉልናል።

የጌደብ ወንዝ በአማኑኤል ከተማ አስተዳደር የዉላ ቀበሌ አካባቢ የሚገኝ ወንዝ ነዉ።

በተመሳሳይ በዚሁ ወንዝ ላይ የአንጎት በለምና ቀበሌ ነዋሪዎችን ከአማኑኤል ከተማ ጋር የሚያገናኝ የብረት ድልድይ በጎርፍ ተወስዷል።

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gojjam press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share