አሚኮ ስፖርት AMECO Sport

አሚኮ ስፖርት AMECO Sport Ameco Sport Provides Real-time Sport updates.

ስፖርት ዜና፡ ሐምሌ 01/2017 ዓ.ም
08/07/2025

ስፖርት ዜና፡ ሐምሌ 01/2017 ዓ.ም

#አሚኮ #ዜና

ቼልሲ ከፍሉሚኔንሴ ለፍጻሜ ለመድረስ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል።ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 01/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ የእንግሊዙን ቼልሲ ከብራዚሉ ፍሉሚኔ...
08/07/2025

ቼልሲ ከፍሉሚኔንሴ ለፍጻሜ ለመድረስ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል።

ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 01/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ የእንግሊዙን ቼልሲ ከብራዚሉ ፍሉሚኔንሴ በሜትላይፍ ስታዲየም የሚያደርጉት የዛሬው ጨዋታ ተጠባቂ ነው።

ፍሉሚኔንሴ እና ቼልሲ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው የሚገናኙት። ሁለቱም ቡድኖች ግማሽ ፍጻሜው ላይ ለመድረስ ጠንካራ ፉክክር አድርገዋል። ፍሉሚኔንሴ በእስካኹን የክለቦች የዓለም ዋንጫ ጉዞው ሽንፈት አልገጠመውም።

በጥሎ ማለፉ ኢንተር ሚላንን 2ለ0 በማሸነፍ እና በሩብ ፍፃሜው ደግሞ አል ሂላልን 2ለ1 በማሸነፍ ነው ለግማሽ ፍፃሜው መድረስ የቻለው። የቀድሞው የቼልሲ አምበል ትያጎ ሲልቫ የድሮ ክለቡ ቼልሲን ይገጥማል።

የኮንፈረንስ ሊግ አሸናፊው ቼልሲ በዚህ ውድድር ከጊዜ ወደ ጊዜ ጥንካሬውን እያሳየ ነው።

ከምድቡ ሁለተኛ ኾኖ 16ቱ ውስጥ የገባው ቼልሲ ቤንፊካን 4ለ1 በማሸነፍ እና ከዚያም ፓልሜራስን 2ለ1 አሸንፎ ለግማሽ ፍጻሜው በቅቷል።

የዛሬው ጨዋታ አሸናፊ ከሪያል ማድሪድ እና ፒኤስጂ አሸናፊ ጋር ለዋንጫ ይፋለማል።

ጨዋታ ምሽት አራት ሰዓት ይደረጋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

ስፖርት ዜና፡ ሰኔ 30/2017 ዓ.ም
07/07/2025

ስፖርት ዜና፡ ሰኔ 30/2017 ዓ.ም

#አሚኮ #ዜና

ሪያል ማድሪድ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል።ባሕር ዳር፡ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ሪያል ማድሪድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ያደረጉት የክለቦች የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ በማድሪድ አሸ...
06/07/2025

ሪያል ማድሪድ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል።

ባሕር ዳር፡ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ሪያል ማድሪድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ያደረጉት የክለቦች የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ በማድሪድ አሸናፊነት ተጠናቅቋል። ጨዋታው አምስት ግቦች ሲቆጠሩበት ነጮቹ 3ለ2 በመርታት ግማሽ ፍጻሜ ደርሷል።

ጎንዛሎ ጋርሺያ እና ፍራን ጋርሺያ ለሪያል ማድሪድ አስቀድመው ግብ አስቆጥረዋል። ዶርትሙንድ በማክስሚሊያን ቤየር ጎል ቢያስቆጥርም፣ ኪሊያን ምባፔ ለሪያል ማድሪድ ሦስተኛውን ጎል አስመዝግቦ መሪነቱን አጠናክሯል።

አዲሱ ፈራሚ ዲን ሁጅሰን በማድሪድ በኩል ቀይ ካርድ በቀይ ካርድ ከሜዳ መውጣቱን ተከትሎ ዶርትሙንድ ውጤቱን ለመቀየር ተጭኖ ተጫውቷል።

በዚህም ሰርሁ ጉይራሲ በፍፁም ቅጣት ምት አስቆጥሮ ለዶርትሙንድ ሁለተኛዋን ጎል አስመዝግቧል። ተጨማሪ ግብ ለማግኘት ያደረገው ጥረተሰ ግን ሳይሳካ ጨዋታው ተጠናቅቋል።

የማድሪዱ አጥቂ ጎንዛሎ ጋርሺያ በእስካኹን የውድድሩ ሂደት አራት ግቦችን በማስቆጠር የውድድሩን ከፍተኛ ግብ አግቢነት እየመራ ኘው።

ሪያል ማድሪድ በግማሽ ፍጻሜው ከፓሪስ ሴንት ዠርሜይን ጋር ይገናኛል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

የፈረንሳዩ ፒኤስጂ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀለ። ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ)በክለቦች ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ፒኤስጂ ከባየር ሙኒክ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 0 በኾነ ውጤት ...
05/07/2025

የፈረንሳዩ ፒኤስጂ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀለ።

ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ)በክለቦች ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ፒኤስጂ ከባየር ሙኒክ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 0 በኾነ ውጤት አሸንፏል።

የፒኤስጂን የማሸነፊያ ግቦች ወጣቱ ተጨዋች ዲዚሬ ዱዌ እና ኦስማን ዴምቤሌ ማስቆጠር ችለዋል።

በጨዋታው የባየር ሙኒክ ወሳኝ አማካይ ጀማል ሙሲያላ ምናልባት ለረጅም ጊዜ ከሜዳ የሚያርቀው ከባድ ጉዳት አጋጥሞታል።

ፒኤስጂ ማሸነፉን ተከትሎ ግማሽ ጻሜውን የተቀላቀለ ሦስተኛው ክለብ ኾኗል።

በግማሽ ፍፃሜው ፒኤስጂ የሪያል ማድሪድ እና ቦርስያ ዶርትመንድን አሸናፊ የሚገጥሙ ይኾናል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

4ኛው የኽምራ ሊግ የእግር ኳስ ውድድር ተጀመረ። ሰቆጣ ፡ ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) 4ኛው የኽምራ ሊግ የእግር ኳስ ውድድር በሰቆጣ ከተማ አስተናጋጅነት መካሄድ ጀምሯል። በውድድሩ 8 ...
05/07/2025

4ኛው የኽምራ ሊግ የእግር ኳስ ውድድር ተጀመረ።

ሰቆጣ ፡ ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) 4ኛው የኽምራ ሊግ የእግር ኳስ ውድድር በሰቆጣ ከተማ አስተናጋጅነት መካሄድ ጀምሯል።

በውድድሩ 8 ክለቦች በሁለት ምድብ ተደልድለው ውድድራቸውን ያደርጋሉ። ከእግር ውድድሩ በተጨማሪ ለመጀመሪያ ጊዜ አራት ክለቦች በመረብ ኳስ የሚወዳደሩ ይኾናል።

በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ መልዕክት ያስተላለፉት የሰቆጣ ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጌትነት እሸቱ ስፖርት የሰላም መድረክ፤ የአንድነት መስበኪያ ዓደባባይ ነው ብለዋል።

በዋግ ኽምራ አካባቢ እየተነቃቃ ያለውን ስፖርታዊ ውድድር የበለጠ ለማሳደግ ከተማ አሥተዳደሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መኾኑን ጠቁመዋል። ውድድሩ በፍጹም ወንድማማችነት እንዲካሄድ ስፖርተኞች የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አሳስበዋል።

የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ኀላፊ አብድራህማን መኮንን በመላው አማራ የስፖርታዊ ውድድር የዋግ ኽምራ እግር ኳስ ቡድን ያሳየው ብቃት የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ያለበትን ደረጃ የሚያሳይ ነው ብለዋል።

ተስፋ የተጣለባቸው ስፖርተኞችን እያፈሩ እንደኾነ የተናገሩት ኀላፊው በቀጣይም የዋግን ስፖርት የበለጠ ለማሳደግ ማዘውተሪያ ቦታዎችን ለማስገንባት በጋራ መሥራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

በኽምራ ሊግ ለሚወዳደሩ የስፖርት ክለቦች በስፖርታዊ ጨዋነት ተወዳድረው ውጤታማ እንዲኾኑ አሳስበዋል።

በምድብ አንድ የመጀመሪያ መርሐ ግብር አንድ ጨዋታ ተካሂዷል። ካስትል እግር ኳስ ክለብ እና ሌተናል ጄኔራል ኃይሉ ከበደ እግር ኳስ ክለብ ተገናኝተው አንድ አቻ ተለያይተዋል።

ባለፈው ዓመት በተካሄደው የዋግ ኽምራ ሊግ ውድድር አስክሽ ከነማ የዋንጫ ባለቤት መኾኑ የሚታወስ ነው።

ዘጋቢ:- ደጀን ታምሩ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

ስፖርት ዜና፡ ሰኔ 28/2017 ዓ.ም
05/07/2025

ስፖርት ዜና፡ ሰኔ 28/2017 ዓ.ም

ስፖርት ዜና፡ ሰኔ 28/2017 ዓ.ም

የዓለም ክለቦች ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬም ቀጥሎ ይካሄዳል፡፡ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የዓለም ክለቦች ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬም ሲቀጥል ፒኤስጂ ከባየር ሙኒክ በኢት...
05/07/2025

የዓለም ክለቦች ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬም ቀጥሎ ይካሄዳል፡፡

ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የዓለም ክለቦች ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬም ሲቀጥል ፒኤስጂ ከባየር ሙኒክ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ምሽት 1 ሰዓት ያገናኛል፡፡

የዛሬውን የሁለቱ ታላላቅ ክለቦች ጨዋታ ምሽት የመርሴዲስ ቤንዝ ስታዲየም ያስተናግዳል፡፡ ታላላቆቹ ክለቦች ፒኤስጂ እና ባየር ሙኒክ በዓለም ክለቦች ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ላይ የሚያደርጉት ጨዋታ በእግር ኳሱ አፍቃሪያን በጉጉት ነው የሚጠበቀው፡፡

ፓሪስ ሴንት ጀርመን አሁን ላይ ጥሩ አቋም ላይ ነው የሚገኘው። በተለይም ኢንተር ማያሚን 4ለ0፣ ሲያትል ሳውንድርስን 2ለ0፣ እና አትሌቲኮ ማድሪድን 4ለ0 ያሸነፈበት ጨዋታ ክለቡ ያለበትን ጥሩ አቋም ያሳየ ነበር።

ባየር ሙኒክ በበኩሉ እዚህ ደረጃ ሲደረስ ጠንካራ አቋሙን እያሳየ ነው፡፡ ክለብ ፍላሜንጎን 4ለ2፣ ቦካ ጁኒየርስን 2ለ1 እና ኦክላንድ ሲቲን 10ለ0 ያሸመፈበት ጨዋታ ያለውን ወቅታዊ አቋም በግልጽ ያሳየበት ጨዋታ ኾኖ አልፏል።

ሌላው በዓለም ክለቦች ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ የዛሬ የምሽት የ5 ሰዓቱ ጨዋታ ሪያል ማድሪድን ከቦሩሲያ ዶርትሙንድ የሚያገናኘው ነው፡፡ የሪያል ማድሪድ እና የቦሩሲያ ዶርትሙንድ ጨዋታ ሜትላይፍ ስታዲየም ያስተናግዳል።

ሁለቱ ግዙፍ ክለቦች በጥሩ አቋም ላይ መገኘታቸው ጨዋታውን ተጠባቂ እንዲኾን አድርጎታል፡፡

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

"ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች አለመኖር ስፖርቱን እየጎዳው ነው" ኢንስትራክተር አብርሃም መብርሃቱ ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር ዓለም አቀፋ ስ...
05/07/2025

"ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች አለመኖር ስፖርቱን እየጎዳው ነው" ኢንስትራክተር አብርሃም መብርሃቱ

ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር ዓለም አቀፋ ስታዲየም በኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት አማካኝነት "ስፖርት ለአሸናፊ ሀገር" በሚል መሪ መልዕክት ውይይት እየተካሄደ ነው።

በውይይቱ ላይ ኢንስትራክተር አብርሃም መብርሃቱ በሀገራችን ስፓርት ሕዝብን ከሕዝብ በማቀራረብ፣ መልካም ገጽታን በማስተዋወቅ፣ ሕዝቦች ለአንድ ዓላማ እንዲቆሙ በማድረግ፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ የስፖርት ሰዎችን በማፍራት እና ንቁ ዜጋን በመፍጠር እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ አውስተዋል።

ይሁን እንጂ በስፖርቱ ዘርፍ የሚታየው የመልካም አሥተዳደር እጦት ሙያተኞች ሥራቸውን በተረጋጋ ሁኔታ ለመሥራት አመቺ አለመኾኑ በዘርፉ ከዚህም በላይ ተጠቃሚ እንዳንኾን አድርጓል ብለዋል ኢንስትራክተር አብርሃም መብርሃቱ።

በየስፖርት ዓይነቱ ከዜጎች ፍላጎት ጋር የሚመጣጠኑ ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች አለመኖር ሌላኛው ማነቆ መኾኑንም ተናግረዋል። የምልመላ ሂደት እና የቁጥጥር ሥርዓት በተጨማሪም የሥልጠና ሂደታችን ዓለም አቀፋዊ እና ሳይንሳዊ አለመኾን አሁንም ዘርፉን የጎዳው ኾኗል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ስፖርቱን ለማሳደግ የፖሊሲ ችግር የለባትም ያሉት ኢንስትራክተር አብርሃም መብርሃቱ ከሌሎች ሀገራት ጋር ሲነጻጸርም ጥሩ መኾናቸውን በምልከታቸው ማረጋገጣቸውን አንስተዋል። ኾኖም ተግባራዊ ለማደረግ የሚኬድበት ርቀት ውስንነት አለበት ብለዋል።

የዘርፉን ውስንነት ለመቅረፍ ከታዳጊ ሕጻናት ጀምሮ በእውቀት ላይ የተመረኮዘ የሥልጠና መስመር በሁሉም የስፖርት ዓይነቶች መዘርጋት እና መስጠት እንዳለበት አሳስበዋል።

በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጪ ያለን አቅም በትክክል መጠቀም እና በፖሊሲዎች ውስጥ ማካተት እንዲሁም የሴቶች ልማት ላይ መሥራት እንደመፍትሄ አስቀምጠዋል።

ዘጋቢ:- ሐናማርያም መስፍን

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

21ኛው ስለኢትዮጵያ መድረክ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) 21ኛው ስለኢትዮጵያ መድረክ "ስፖርት ለአሸናፊ ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር...
05/07/2025

21ኛው ስለኢትዮጵያ መድረክ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።

ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) 21ኛው ስለኢትዮጵያ መድረክ "ስፖርት ለአሸናፊ ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።

በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አዘጋጅነት ሁለተኛ ምዕራፍ ስለኢትዮጵያ መድረክ ዛሬ ትኩረቱን ስፖርት ላይ አድርጎ "ስፖርት ለአሸናፊ ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ነው።

በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተጀመረው መድረክ የባሕል እና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፣ የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ድኤታ መክዩ መሐመድን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የስፖርት ባለሙያዎች፣ የተቋማት ኀላፊዎች እና የሚዲያ ባለሙያዎች ተሳታፊ ናቸው።

በመድረኩ መክፈቻም የኢትዮጵያን የስፖርት ታሪካዊ ሂደቶች የሚያስቃኝ የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ ለዕይታ ቀርቧል።

በመቀጠልም የፓናል ውይይት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል። ውይይቱን የሚመሩት ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ ሲኾኑ የመወያያ ሃሳብ የሚያቀርቡት ደግሞ የካፍ ኤሊት ኢንስትራክተር አብርሐም መብራቱ፣ የባሕል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ መኪዩ መሐመድ፣ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ድኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ እንዲሁም በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የጥናትና ምርምር ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አመንሲሳ ከበደ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ስፖርት ለአሸናፊ ሀገር" በሚል ያዘጋጀው ይህ መድረክ ሁለተኛው ምዕራፍ 7ኛ መድረክ ነው። የዛሬውን መድረክ ጨምሮ እስካሁን በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ 21 መድረኮችን ማዘጋጀቱን ከኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ዘጋቢ፦ ሐናማርያም መስፍን

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

ቼልሲ ለግማሽ ፍጻሜ ደረሰ።ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በክለቦች የዓለም ዋንጫ ቼልሲ የብራዚሉ ፓልሜራስን በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜ ደርሷል። ጨዋታው 2ለ1 ሲጠናቀቅ ለእንግሊዙ ...
05/07/2025

ቼልሲ ለግማሽ ፍጻሜ ደረሰ።

ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በክለቦች የዓለም ዋንጫ ቼልሲ የብራዚሉ ፓልሜራስን በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜ ደርሷል።

ጨዋታው 2ለ1 ሲጠናቀቅ ለእንግሊዙ ክለብ ኮል ፓልመር እና ማሎ ጉስቶ ግቦችን አስቆጥረዋል። ኢስታቩ ዊሊያን ደግሞ የፓልሜራስን ግብ ከመረብ አሳርፏል።

ቼልሲ በግማሽ ፍጻሜው ከሌላኛው የብራዚል ክለብ ፍሉሚንሴ ጋር ይጫወታል።

የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬም ሲቀጥሉ በተለይ ፒኤስጂ እና ባየርሙኒክ የሚገናኙበት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ጨዋታው ምሽት 4:00ሰዓት ላይ ይደረጋል።

አነጋግ ላይ ደግሞ ሪያል ማድሪድ ከቦሩሲያ ዶርትሙንድ ጋር ይጫወታል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

በክለቦች የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ፍሉሚኔንስ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቀለ። ባሕር ዳር: ሰኔ 27/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በክለቦች ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ፍሉሚኔንስ ከአል ሂላል ጋር ያደረጉት...
04/07/2025

በክለቦች የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ፍሉሚኔንስ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቀለ።

ባሕር ዳር: ሰኔ 27/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በክለቦች ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ፍሉሚኔንስ ከአል ሂላል ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 1 በኾነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የፍሉሚኔንስን የማሸነፊያ ግቦች ማርቲኔሊ እና ሄርኩለስ ሲያስቆጥሩ ለአል ሂላል ሊዮናርዶ ከመረብ አሳርፏል።

የብራዚሉ ክለብ ፍሉሚኔንስ ማሸነፉን ተከትሎ ግማሽ ፍጻሜውን የተቀላቀለ የመጀመሪያው ክለብ ኾኗል።

የፍሉሚኔንሱ ተከላካይ ሁዋን ፍሬይቴስ የማስጠንቀቂያ ካርድ መመልከቱን ተከትሎ በቅጣት የግማሽ ፍጻሜው ጨዋታ ያመልጠዋል።

በግማሽ ፍፃሜው ፍሉሚኔንስ የቼልሲ እና ፓልሜራስን አሸናፊ የሚገጥም ይኾናል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Address

Bahirdar
Bahir Dar
6000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አሚኮ ስፖርት AMECO Sport posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to አሚኮ ስፖርት AMECO Sport:

Share