አሚኮ ስፖርት AMECO Sport

አሚኮ ስፖርት AMECO Sport Ameco Sport Provides Real-time Sport updates.

30/08/2025

ስፖርት ዜና፡ ነሐሴ 24/2017 ዓ ም #አሚኮ #ዜና

30/08/2025

የአሚኮ ካፕ ውድድር ፍጻሜ

30/08/2025

የአሚኮ ስፖርት ዘገባዎች አርአያነት በሚዲያ ባለሙያዎች እይታ

"ስፖርት ለዓባይ" ውድድር በደሴ ከተማ ተጀመረ። ደሴ: ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ "ስፖርት ለዓባይ" በሚል መሪ መልዕክት የተለያዩ ስ...
30/08/2025

"ስፖርት ለዓባይ" ውድድር በደሴ ከተማ ተጀመረ።

ደሴ: ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ "ስፖርት ለዓባይ" በሚል መሪ መልዕክት የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች በደሴ ከተማ መካሄድ ጀምረዋል።

የደሴ ከተማ አሥተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ተወካይ ኀላፊ ይህይስ ኃይሉ በደሴ ከተማ አሥተዳደር ስፖርት ምክር ቤት አዘጋጅነት የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከዚህ መድረስን አስመልክቶ "ስፖርት ለዓባይ" በሚል መሪ መልዕክት የስፖርት ፌስቲቫል ተጀምሯል ብለዋል።

ዛሬ የስፖርት ቤተሰቦች በተገኙበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በጎዳና ላይ ተካሂዷል ብለዋል። በመተባበር የጀመርነው የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከዚህ በመድረሱ ተደስተናል ነው ያሉት ተሳታፊዎች።

በሳምንት ሦስት ቀን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንሠራለን ያሉት ተሳታፊዎቹ የዛሬውን ለየት የሚያደርገው የሕዳሴ ግድብ አፈጻጸምን አስመልክቶ የተሠማንን ደስታ ለመግለጽ በመኾኑ ነው ብለዋል።

በቀጣይ ቀናት መርሐ ግብሩ የሚቀጥል ሲኾን የብስክሌት እና የእግር ኳስ ጨዋታ ውድድሮችም እንደሚደረጉ ተመላክቷል።

ዘጋቢ፦ ደምስ አረጋ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

ማንቸስተር ዩናይትድ ከበርንሌይ ዛሬ ጨዋታውን ያደርጋል። ባሕር ዳር: ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 2025/2026 የውድድር ዘመን ሦስተኛ ሳምንት ዛሬ ሲቀጥል ...
30/08/2025

ማንቸስተር ዩናይትድ ከበርንሌይ ዛሬ ጨዋታውን ያደርጋል።

ባሕር ዳር: ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 2025/2026 የውድድር ዘመን ሦስተኛ ሳምንት ዛሬ ሲቀጥል ስድስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ።

ዛሬ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በሊጉ ባደረገው ጨዋታ ከድል ጋር መገናኘት ያልቻለው ማንቸስተር ዩናይትድ የመጀመሪያ ድሉን ለማስመዝገብ የሚጫወት ይኾናል።

ማንቸስተር ዩናይትድ በኦልድ ትራፎርድ ጨዋታውን ሲያደርግ ይህን ጨዋታ ማሸነፉ የውድድር ዘመኑን ለማስተካከል የሚያግዘው በመኾኑ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶታል።

ምንም እንኳን ዩናይትድ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከድል ጋር መገናኘት ያልቻለ ቢኾንም ከአዲስ ቡድኖች ጋር ሲገናኝ ጥሩ ታሪክ ያለው ክለብ በመኾኑ ይህን ጨዋታ ለማሸነፍ እንደማይቸገር ነው እየተገለጸ ያለው። ክለቡ ከአዲስ ቡድኖች ጋር በተገናኘበት የመጨረሻዎቹ 23 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች በአንዱም አልተሸነፈም።

በሌላ በኩል በርንሌይ ከሰንደርላንድ ጋር ባደረገው ጨዋታ ድልን መቀዳጀቱ ለዛሬው ጨዋታ በጥሩ የሥነ ልቦና ግንባታ ላይ ኾኖ ነው ወደ ሜዳ የሚገባው።

ክለቡ ምንም እንኳን በሰው ሜዳ ላይ የሚጫዎት ቢኾንም ዩናይትድ ላይ ያለው ከፍተኛ ጫና ሊያግዘው እንደሚችል ነው የሚገመተው።

ሁለቱ ክለቦች ከዚህ በፊት ለመጨረሻ ጊዜ በኦልድ ትራፎርድ የተገናኙበት ጨዋታ በአቻ ውጤት 1ለ1 ነበር መጠናቀቅ የቻለው ዛሬስ የሚለው የሚጠበቅ ነው።

ዩናይትድ ወደ መልካም አቋሙ ይመለሳል ወይስ የበርንሌይ አሠልጣኝ ስኮት ፓርከር በኦልድ ትራፎርድ ላይ በቅርብ ጊዜ የነበራቸውን ስኬት ይቀጥላሉ የሚለው ይጠበቃል። ጨዋታውም ቀን
11፡00 ሰዓት ላይ ይካሄዳል።

ሌሎች ጨዋታዎችም ሲቀጥሉ፦
👉ቸልሲ ከፉልሀም 8፡00 ሰዓት ላይ

👉ሰንደርላንድ ከብሬንትፎርድ 11፡00 ሰዓት ላይ

👉ቶተነሃም ከቦርንማውዝ 11፡00 ሰዓት ላይ

👉ወልቨስ ከኤቨርተን 11፡00 ሰዓት ላይ

👉ሊድስ ከኒውካስትል ደግሞ ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

አጫጭር የዝውውር ዜናዎች ከአሚኮ፦ባሕር ዳር: ነሐሴ 23/2017 ዓ.ም (አሚኮ) 👉ኮቢ ማይኑ በውሰት ዩናይትድን ለመልቀቅ ጥያቄ አቅርቧል። ነገር ግን ዩናይትድ የተጫዋቹን ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ...
29/08/2025

አጫጭር የዝውውር ዜናዎች ከአሚኮ፦

ባሕር ዳር: ነሐሴ 23/2017 ዓ.ም (አሚኮ) 👉ኮቢ ማይኑ በውሰት ዩናይትድን ለመልቀቅ ጥያቄ አቅርቧል። ነገር ግን ዩናይትድ የተጫዋቹን ጥያቄ ውድቅ ማድረጉን ጎል ጽፏል። አሠልጣኝ አሞሪም ማይኑን እንፈልገዋለን ብለዋል።

👉በቢቢሲ መረጃ መሠረት ዣቪ ሲሞንስ ወደ ቶትንሃም የሚያደርገውን ዝውውር ለማጠናቀቅ የሕክምና ምርመራውን አጠናቅቋል።

👉ሊቨርፑል ለኢሳክ ዝውውር 130ሚሊዮን ፓውንድ ለማቅረብ መዘጋጀቱን ቴሌግራፍ አስነብቧል። የተጫዋቹ ዝውውር በቀጣዮቹ 48 ሰዓታት መልክ እንደሚይዝም ዘገባው ጨምሯል።

👉አሠልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ከፌነርባቼ አሠልጣኝነት ተሰናብተዋል። ፌነርባቼ ለሻምፒዮንስ ሊግ ማለፍ አለመቻሉ በአሠልጣኙ ስንብት ምክንያት መኾኑን ቢቢሲ በስፖርት ገጹ አስነብቧል።

👉ቼልሲ ጋርናቾን ለማስፈረም ተስማምቷል። ተጫዋቹ በቀጣዮቹ ሰባት ዓመታት ለቼልሲ ለመጫወት ፊርማውን እንደሚያሰፍር ሜትሮ አስነብቧል።

👉ኒውካስትል ዩናይትድ ከጀርመኑ ስቱትጋርት አጥቂ ለማስፈረም ጫፍ ደርሷል። ኒክ ዋልቲሜድ የተሰኘው ይህ ተጫዋች በባየር ሙኒክ ሲፈለግ ነበር ብሏል ስካይ ስፖርት።

👉አርሰናል የፒሮ ሂንካፒን ዝውውር ለማጠናቀቅ ተቃርቧል። አርሰናል ተጫዋቹን በውስት ለማስፈረም እና በቀጣይ ተጫዋቹን በቋሚነት ከፈለገ 60 ሚሊዮን ዩሮ ለመክፈል ከሊቨርኩሰን ጋር ተስማምቷል።

👉ጎል አርሰናል እና ፖርቶ በኪዌር ዝውውር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስነብቧል። ተከላካዩ በአርቴታ ተመራጭ ባለመኾኑ ነው አርሰናልን የሚለቀው።

👉ሪያል ማድሪድ ኦፕሚካኖን በቅርበት እየተከታታለ ነው ሲል የዘገበው ደግሞ ስፖርት ቢልድ ነው። ተጫዋቹ የባየር ሙኒክ ውሉ በቀጣይ ዓመት የሚጠናቀቅ ይኾናል። ለተጨማሪ ጊዜ ለመቆየት እስካሁን ስምምነት ላይ አልደረሰም።

👉የቱርኩ ቢሽክታሽ ኦሊጎኖ ሾልሻየርን ከአሠልጣኝነት አንስቷል። ቢሽክታሽ በኮንፈረንስ ሊግ በቀድመ ጨዋታ በመሸነፉ ነው የቀድሞው የዩናይትድ ተጫዋች እና አሠልጣኝ ለስንብት የተዳረገው።

ዘጋቢ፦አስማማው አማረ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

ጆዜ ሞሪንሆ ከፌነርባቼ አሠልጣኝነት ተሰናበቱ።ፖርቱጋላዊ አሠልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ከፌነርባቼ አሠልጣኝነታው ተነስተዋል። ለአሠልጣኙ መሰናበት ምክኒያት የተባለው ክለቡን ወደ አውሮፖ ሻምፒዮንስ ሊ...
29/08/2025

ጆዜ ሞሪንሆ ከፌነርባቼ አሠልጣኝነት ተሰናበቱ።

ፖርቱጋላዊ አሠልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ከፌነርባቼ አሠልጣኝነታው ተነስተዋል። ለአሠልጣኙ መሰናበት ምክኒያት የተባለው ክለቡን ወደ አውሮፖ ሻምፒዮንስ ሊግ ማሳለፍ አለመቻላቸው ነው።

ፌነርባቼ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ በቤኔፊካ መሸነፉ ይታወሳል።

በዙሪክ ዳይመንድ ሊግ በሴቶች 3ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት ፋንታዬ በላይነህ አሸነፈች።ባሕር ዳር: ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ማምሻውን በዙሪክ በተካሄደው የመጨረሻ የዳይመንድ ሊግ ውድ...
28/08/2025

በዙሪክ ዳይመንድ ሊግ በሴቶች 3ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት ፋንታዬ በላይነህ አሸነፈች።

ባሕር ዳር: ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ማምሻውን በዙሪክ በተካሄደው የመጨረሻ የዳይመንድ ሊግ ውድድር በሴቶች 3ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት ፋንታዬ በላይነህ አሸንፋለች።

ከውድድሩ መጠናቀቅ በኋላ አሸናፊውን ለመለየት አገባባቸው የተቀራረበ ስለነበር ዳኞች ረጅም ጊዜ ወስደው ከመረመሩ በኋላ አትሌት ፋንታዬ ማሸነፏን አረጋግጠዋል።

አትሌት ፋንታዬ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 8:40.56 ፈጅቶባታል።

አትሌት ልቅና አምባው በ8:41.06 በመግባት አሜሪካዊቷን አትሌት ተከትላ ሦሥተኛ በመኾን አጠናቅቃለች ሲል የዘገበው አትሌቲክስ አፍሪካን
ነው።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ድልድል ይፋ ሆነ ባሕር ዳር: ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የሊግ ዙር እጣ ድልድል ምሽቱን በሞናኮ ይፋ ኾኗል። የውድድር ዓመቱ የአውሮ...
28/08/2025

የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ድልድል ይፋ ሆነ

ባሕር ዳር: ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የሊግ ዙር እጣ ድልድል ምሽቱን በሞናኮ ይፋ ኾኗል።

የውድድር ዓመቱ የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ በሃንጋሪ ቡዳፔስት ፑሽካሽ አሬና ይከናወናል።

በእጣ ማውጣት ሥነ ስርዓቱ ላይ የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር የሚያዘጋጃቸውን ሁሉንም የክለብ ውድድር ዋንጫዎችን ያሸነፈው ብቸኛ ክለብ ቼልሲ የማስታወሺያ ሽልማት ተበርክቶለታል።

ዝላታን ኢብራሂሞቪች ደግሞ የ2025 የዩ ኤ ፋ የፕሬዝዳንት ሽልማት አሸናፊ ኾኗል።

በብራዚላዊው ካካ እና ስዊድናዊው ታሪካዊ ተጫዋች ዝላታን ኢብራሂሞቪች መሪነት በወጣው ድልድል 36 ክለቦች ተሳታፊ ይኾናሉ።

በእጣ ድልድሉ መሠረት በጉጉት የሚጠበቁ ጨዋታዎች በርክተው ታይተዋል።

አርሰናል ከባየርን ሙኒክ፣ ኢንተር ሚላን እና አትሌቲኮ ማድሪድ ጋር የሚያደርጋቸው ጨዋታዎች አጓጊ ኾኗል።

ቼልሲ በበኩሉ ከባርሰሎና እና ባየርን ሙኒክ ጋር የመጫወት ግዴታ ተጥሎበታል። በዚህ ዙር እያንዳንዱ ክለብ ስምንት ጨዋታዎችን ያከናውናል።

ባለፈው ዓመት የተጀመረው አዲሱ ፎርማት ክለቦች በሚሰበስቡት ነጥብ መሰረት ከ1 እስከ 8 የሚጨርሱት ቀጥታ ወደ ጥሎ ማለፍ ያልፋሉ።

ከ9 እስከ 24 የሚጨርሱ ደግሞ እርስ በእርስ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ አድርገው አሸናፊዎቹ ቀጣዩን ዙር ይቀላቀላሉ።

ከ25 እስከ 36 የሚጨርሱ ክለቦች ከውድድሩ ይሰናበታሉ። በዘንድሮው ውድድር እንግሊዝ ስድስት ክለቦችን በማሳተፍ ቀዳሚውን ስፍራ ይዛለች።

በታዘብ አራጋው

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

አጫጭር የዝውውር ዜናዎች ከአሚኮ፦ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ሊቨርፑል የአሌክሳንደር ኢሳክን ዝውውር እውን ለማድረግ አሁንም ጥረት ላይ ነው። ኒውካስትል እና ኢሳክ ባለመግ...
28/08/2025

አጫጭር የዝውውር ዜናዎች ከአሚኮ፦

ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ሊቨርፑል የአሌክሳንደር ኢሳክን ዝውውር እውን ለማድረግ አሁንም ጥረት ላይ ነው። ኒውካስትል እና ኢሳክ ባለመግባባታቸው እንደቀጠሉ ናቸው። ቢቢሲ በስፖርት ገጹ ሊቨርፑል አሁንም ስዊድናዊን አጥቂ ለማስፈረም እየሠራ መኾኑን ዘግቧል።

👉ክርስቶፎር ኑኩኩ ኤሲሚላንን ለመቀላቀል መስማማቱን ጎል አስነብቧል። ኑኩኩ ብዙ ተስፋ ተደርጎበት ለቼልሲ መፈረሙ ይታወሳል። ነገር ግን ፈረንሳዊ አጥቂ በሰማያዊዮቹ ቤት በልኩ ሳይገኝ አሁን መውጫ በር ላይ ተገኝቷል።

👉አሊሀንድሮ ጋርናቾ የቼልሲ ንብረት ሊኾን ስለመቃረቡ የጻፈው ደግሞ ደይሊ ሜል ነው። ተጫዋቹ በግል ቼልሲን ለመቀላቀል ዝግጁ ሲኾን ዩናይትድ እና ቼልሲ በዝውውር ገንዘቡ ገና አልተሰማሙም።

👉የክርስቲያል ፓላሱ ዋርተን በሪያል ማድሪድ እየተፈለገ ነው። እንደ አስ መረጃ ከኾነ የአሎንሶው ቡድን ዳኒ ሲባዮስ ክለቡን ለመልቀቅ በመፈለጉ ተተኪው እንዲኾን ነው ዋርተንን የሚፈልገው።

👉አርሰናል በሂንካፔ ዝውውር ዙሪያ ከባየር ሊቨርኩሰን ጋር በቀጥታ ንግግር እያደረገ ነው። ኢኳዶሯዊ ተከላካይ የዝውውሩ ወቅት ከመጠናቀቁ በፊት አርሰናልን የመቀላቀል እድሉ ሰፊ ነው ብሏል ጎል በዘገባው።

👉ጁቬንቱስ ኮሎ ሞዋኒን ለማስፈረም ተስማምቷል። በጎል መረጃ መሠረት ጁቬ ለፒኤስጂ 51 ሚሊዮን ፓውንድ ለመክፈል ተስማምቷል።

👉አድሬ ኦናና ከማንቸስተር ዩናይትድ የመውጣት ፍላጎት እንደሌለው ፋብሪዚዮ ጽፏል። ኦናና በዩናይትድ በሚሠራቸው ስህተቶች ተደጋጋሚ ትችት እያስተናገደ ነው። ይህን ተከትሎ ተጫዋቹ በውሰት ወደሌላ ክለብ ሊያመራ እንደሚችል እየተወራ ነው። ኦናና ግን ዩናይትድን እንደማይለቅ አሳውቋል።

👉ዣቪ ሲሞንስ ዝውውሩን ለማጠናቀቅ ለንደን ይገኛል። ቼልሲ እና ቶትንሃም የሲሞንስ ፈላጊዎች ናቸው። ከሁለቱ የለንደን ክለቦች ለየትኛው ይፈርማል የሚለውም እየተጠበቀ ነው።

👉ሪያል ማድሪድ ኮቢ ማይኑን ለማስፈረም ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ፉክክር ውስጥ ገብቷል። ማይኑ በአሠልጣኝ አሞሪም ተመረጭ ባለመኾኑ ክለቡን ሊለቅ እንደሚችል የሜትሮ መረጃ ያሳያል።

👉ጆዜ ሞሪንሆ ወደ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ለመመለስ እያሰቡ መኾኑን ጎል አስነብቧል። አወዛጋቢው አሠልጣኝ ፌነርባቼን እየመሩ ነው። ነገር ግን ኖቲንግሃም ፎረስት ጆዜን አሠልጣኝ የማድረግ ሃሳብ አለው።

👉ማንቸስተር ዩናይትድ የሀሪ ማጉየርን ውል ለማራዘም ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው ደግሞ ደይሊ ሜል አስነብቧል።

በአስማማው አማረ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

 #አሚኮስፖርት
28/08/2025

#አሚኮስፖርት

ስፖርት ዜና፡ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም #አሚኮ #ዜና

Address

Bahirdar
Bahir Dar
6000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አሚኮ ስፖርት AMECO Sport posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to አሚኮ ስፖርት AMECO Sport:

Share