
24/04/2025
ምንም ዓይነት የነፃ ትምህርት ዕድል እየሰጠ አለመኾኑን የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።
ባሕር ዳር:ሚያዝያ 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ምንም ዓይነት የነፃ ትምህርት ዕድል እየሰጠ አለመኾኑን የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል።
ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ባወጣው መረጃ በባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ነፃ የትምህርት ዕድል እንሰጣለን በማለት በሀሰተኛ መረጃ ገንዘብ የሚሰበስቡ እንዳሉ ማወቁን ገልጿል።
በአሁኑ ወቅት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠው ምንም ዓይነት የነፃ ትምህርት ዕድል እንደሌለ አውቃችሁ በተሳሳተ መረጃ ገንዘባችሁን ያለአገባብ እንዳታባክኑ በጥብቅ እናሳውቃለን ነው ያለው በማሳሰቢያ መልዕክቱ።
ከሀሰተኛ መረጃ መጠንቀቅ እንደሚገባ ዩኒቨርሲቲው አሳሳስቧል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን