አሚኮ እውነታ ማጣሪያ AMECO Fact Check

አሚኮ እውነታ ማጣሪያ  AMECO Fact Check Ameco Fact check your ubiquitous platform to check facts.

30/07/2025

የትጋት ምልክት!

የጥንቃቄ መልዕክት፦ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በሀሰተኛ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ማስታወቂያዎች።ካናዳን ጨምሮ ሕጋዊ የሥራ ስምሪት የሁለትዮሽ ስምምነት ወዳልተገባባቸው የ...
27/07/2025

የጥንቃቄ መልዕክት፦

ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በሀሰተኛ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ማስታወቂያዎች።

ካናዳን ጨምሮ ሕጋዊ የሥራ ስምሪት የሁለትዮሽ ስምምነት ወዳልተገባባቸው የተለያዩ ሀገራት ለሥራ እንልካለን የሚሉ ሀሰተኛ ማስታወቂያዎች በማኅበራዊ ትስስር ገጾች በስፋት እየተዘዋወሩ ይገኛል፡፡

ይህም ገንዘብ ከማጭበርበር ባለፈ ለሕገወጥ የሰዎች ዝውውር፣ የጉልበት ብዝበዛ፣ ፆታዊ ጥቃትና መሰል የከፋ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ የሚዳርግ ነው። በመኾኑም ሁሉም ጥንቃቄ እንዲያደረግ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አሳስቧል።

በዚህ መሠረት፦

👉ኢትዮጵያ ካናዳን ጨምሮ ከየትኛውም የአውሮፓ ሀገር ጋር የሁለትዮሽ የሥራ ስምሪት ስምምነት የላትም።

👉የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለየትኛውም የጉዞ ወኪል ወይም ኤጀንሲ የሁለትዮሽ ስምምነት ወዳልተገባባቸው ሀገራት ዜጎችን ለሥራ እንዲያሰማራ የሰጠው ውክልናም ኾነ ፍቃድ የለም፤

ሕጋዊ ሥራ ስምሪት የሚሰጥባቸው ሀገራት የትኞቹ ናቸው?

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሕጋዊና ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ለመዘርጋት ባደረገው ጥረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ሀገራት ጋር ሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡

እነዚህም 👇

👉ሳዑዲ አረቢያ
👉የተባበሩት አረብ ኤሚሬት
👉ዮርዳኖስ
👉ሊባኖስ
👉ኳታር እና
👉ኩዌት መኾናቸው ተጠቅሷል።

ሀሰተኛና አጭበርባሪ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ማስታወቂያዎች ዋነኛ መለያቸው ምንድን ነወ?

👉የቅድሚያ ክፍያዎችን እንዲከፍሉ ይጠይቃሉ (ለቪዛ፣ ለሥራ ማስኬጃ፣ ለህክምና እና ሌሎች በሚል።

👉ለቀላል ሥራዎች አማላይ ጥቅማ ጥቅም እና በከፍተኛ የደመወዝ መጠን እንደሚያስቀጥሩ ቃል ይገባሉ።

👉ፈጣን ውሳኔዎችን እንዲያደርጉ ግፊት ያደርጋሉ።

👉ሀሰተኛ የሆነና ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተሰጠ ፈቃድ ወይም ውክልና አለን በሚል ሰነዶችን ያሳያሉ።

👉በተለያዩ የውጭ ሀገር ቁጥሮች እየደወሉ አጭበርባሪነታቸው እንዳይታወቅ ጥረት ያደርጋሉ።

👉ወጥመዳቸው ውስጥ ያስገቧቸውን ዜጎች በአካውንት ብር እንዲያስገቡ ካደረጉ በኋላ አድራሻቸውን ይሰውራሉ።

ሕጋዊና ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት እንዴት ማግኘት ይቻላል?

👉በየትኛውም ሀገር ሕጋዊ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ለመኾን በመጀመሪያ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት lmis.gov.et መመዝገብ።

👉የሚሰጠውን ሥልጠና መውሰድና ብቃትዎን በምዘና ማረጋገጥ ያስፈልጋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

ለጥንቃቄ፦ በድምጽ ጥሪ አማካኝነት የሚፈጸም የሳይበር ጥቃት፦ባሕር ዳር: ሐምሌ09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የቪሺንግ(Vshing) መረጃ በማጥመድ ከሚፈጸሙ የጥቃት አይነቶች አንዱ ነው። በድምጽ...
16/07/2025

ለጥንቃቄ፦

በድምጽ ጥሪ አማካኝነት የሚፈጸም የሳይበር ጥቃት፦

ባሕር ዳር: ሐምሌ09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የቪሺንግ(Vshing) መረጃ በማጥመድ ከሚፈጸሙ የጥቃት አይነቶች አንዱ ነው። በድምጽ ጥሪ አማካኝነት የሚፈጸም የጥቃት ዓይነት ነው።

አጭበርባሪዎች ሕጋዊ አካል መስለው ስልክ በመደወል የግለሰቦችን የግል መረጃዎች፣ የይለፍ ቃሎች፣ የክሬዲት ካርድ ቁጥሮችን እና ሌሎች መሰል ሚስጥራዊ መረጃዎችን ለመመንተፍ ይህን የጥቃት አይነት ይጠቀማሉ።

የዚህ አይነት ማጭበርበር በእውነተኛ ሰዎች ወይም አስቀድሞ በተቀዳ ሮቦ-ኮሎች (robocalls) የሚፈጸም ነው።

በመኾኑ ከማያውቁት አካል ለሚደረግ የስልክ ጥሪ የትኛውንም መረጃ ከመስጠት መቀጠብ እንደሚገባ ከኢንሳ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

እየተስፋፋ ያለዉ የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ የመረጃ ስርጭት የዜጎችን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው። ባሕር ዳር: ሰኔ 12/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኅን ባለሥልጣን የሀ...
19/06/2025

እየተስፋፋ ያለዉ የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ የመረጃ ስርጭት የዜጎችን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው።

ባሕር ዳር: ሰኔ 12/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኅን ባለሥልጣን የሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን አስመልክቶ ለሦስተኛ ጊዜ በተቋሙ በወጣዉ ጥናታዊ ሪፖርት ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አማካሪ ታምራት ደጀኔ በሀገሪቷ እየተስፋፋ ያለዉ የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ የመረጃ ስርጭት የዜጎችን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው ብለዋል።

በመኾኑም የአገልግሎት ሰጪ ኩባንያዎች የአቅም ግንባታ ሥራዎች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ጥሪ አድርገዋል።

ኩባንያዎች የሚሰጧቸዉን አገልግሎቶች የሀገሪቷን ብሔራዊ ጥቅም ባማከለ መልኩ ሊኾን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

ማኅበራዊ ሚድያ ማንኛውንም ይዘት በአነስተኛ ዋጋ፣ በፍጥነት እና በቀላሉ አዘጋጅቶ፣ ማንነትን ሳያሳውቅ ለማሰራጨት ዕድል የሚፈጥር በመኾኑ የጥላቻ ንግግር እና የሀሰተኛ መረጃ አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን ጥናቱ አመላክቷል፡፡

በመግለጫዉ ላይ በሕግ አውጭው ክፍል የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል የሚረዳ የፖሊሲ እና ማኅበራዊ ሚዲያን የሚመራ የሕግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት አስፈላጊ መኾኑ ተነስቷል።

የማኅበራዊ ሚዲያ አቅራቢ ኩባያዋች በሀገሪቱ ለሚሰጡት አገልግሎት ለተጠቃሚዎች የአቅም ግንባታ ሥራ መሥራት እንዳለባቸው እንዲኹም በሀገሪቱ ቅርንጫፎቻቸውን መክፈት እንዳለባቸው ተነስቷል።

የሀሰተኛ መረጃዎች እና የጥላቻ ንግግሮች ዋነኛ ምንጮች ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፤ የመገናኛ ብዙኅን እና ግለሰቦች፤ የሃይማኖት ተከታዮች እና ፖለቲከኞች መኾናቸው ጥናቱ ማረጋገጡም ተነስቷል።

ጥናቱ አምስት የማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ መሰረት በማድረግ የተጠና መኾኑን የገለጹት አማካሪዉ በጥናቱ ከ2000 በላይ የጥላቻ ንግግር እና የሀሰተኛ ይዘቶች ላይ የናሙና ግምገማ ተደርጓል።

ከነዚህ ውስጥ 1995 መረጃዎች ተተንትነዋል፤ በቀጣይ ሁሉንም የመገናኛ ብዙኅን አዉታሮችን ተደራሽ የሚያደርግ ጥናት እንደሚጠና ተናግረዋል፡፡

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

ምንም ዓይነት የነፃ ትምህርት ዕድል እየሰጠ አለመኾኑን የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ። ባሕር ዳር:ሚያዝያ 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ምንም ዓይነት የነፃ ትምህርት ዕድል እየሰጠ አለመኾኑን...
24/04/2025

ምንም ዓይነት የነፃ ትምህርት ዕድል እየሰጠ አለመኾኑን የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።

ባሕር ዳር:ሚያዝያ 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ምንም ዓይነት የነፃ ትምህርት ዕድል እየሰጠ አለመኾኑን የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል።

ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ባወጣው መረጃ በባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ነፃ የትምህርት ዕድል እንሰጣለን በማለት በሀሰተኛ መረጃ ገንዘብ የሚሰበስቡ እንዳሉ ማወቁን ገልጿል።

በአሁኑ ወቅት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠው ምንም ዓይነት የነፃ ትምህርት ዕድል እንደሌለ አውቃችሁ በተሳሳተ መረጃ ገንዘባችሁን ያለአገባብ እንዳታባክኑ በጥብቅ እናሳውቃለን ነው ያለው በማሳሰቢያ መልዕክቱ።

ከሀሰተኛ መረጃ መጠንቀቅ እንደሚገባ ዩኒቨርሲቲው አሳሳስቧል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

ከውስጥ አዋቂዎች ጋር የተያያዙ ዋና ዋና  የሳይበር የጥቃት ስጋቶች:- ባሕር ዳር: ሚያዝያ 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር ከውስጥ አዋቂዎች ጋር የተያያ...
24/04/2025

ከውስጥ አዋቂዎች ጋር የተያያዙ ዋና ዋና የሳይበር የጥቃት ስጋቶች:-

ባሕር ዳር: ሚያዝያ 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር ከውስጥ አዋቂዎች ጋር የተያያዙ ዋና ዋና የሳይበር ጥቃት ስጋቶች ያላቸውን ጉዳዮች አጋርቷል።

ተቋማት ብዙውን ጊዜ ጠቃሚ ሀብቶችን ከጥቃት ለመጠበቅና በአግባቡ ለማሥተዳደር ለተወሰኑ አካላት ሚስጥራዊ መረጃዎችን የማግኘት እድል ለውስን ሠራተኞች ይሰጣሉ።

ይህን መብት ያገኘ አንድ ሠራተኛ ግልጽ ባልሆነ የሥራ ምክንያት ከተሰጠዉን መብት በላይ ለመጠቀም ከሞከረ፣ ይህ አይነቱ ሁኔታ ምናልባት የውስጥ አዋቂ ስጋት ምልክት ተደርጎ ይወሰዳል። የውስጥ አዋቂዎች ጋር የተያያዙ የጥቃት ስጋቶች ያላቸውንም የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር አሳውቋል።

👉የመረጃ ምዝበራና ጥሰት

👉የአዕምሮአዊ ንብረት ስርቆት

👉የተቋምን መረጃና የመረጃ ሥርአትን ማበላሸት

👉የገንዘብና ተያያዥ ጉዳዮች ማጭበርበር

በውስጥ አዋቂዎች እንዲህ አይነት ችግሮች እንዳይፈጠሩ ጥንቃቄ ማድረግ እና መከታተል ይመከራል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

ለጥንቃቄ፦ በድምጽ ጥሪ አማካኝነት የሚፈጸም የሳይበር ጥቃት፦ባሕር ዳር: ሚያዝያ/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የቪሺንግ(Vshing) መረጃ በማጥመድ ከሚፈጸሙ የጥቃት አይነቶች አንዱ ነው። በድምጽ ...
22/04/2025

ለጥንቃቄ፦ በድምጽ ጥሪ አማካኝነት የሚፈጸም የሳይበር ጥቃት፦

ባሕር ዳር: ሚያዝያ/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የቪሺንግ(Vshing) መረጃ በማጥመድ ከሚፈጸሙ የጥቃት አይነቶች አንዱ ነው። በድምጽ ጥሪ አማካኝነት የሚፈጸም የጥቃት ዓይነት ነዉ።

አጭበርባሪዎች ሕጋዊ አካል መስለዉ ስልክ በመደወል የግለሰቦችን የግል መረጃዎች፣ የይለፍ ቃሎች፣ የክሬዲት ካርድ ቁጥሮችን እና ሌሎች መሰል ሚስጥራዊ መረጃዎችን ለመመንተፍ ይህን የጥቃት አይነት ይጠቀማሉ።

የዚህ አይነት ማጭበርበር በእውነተኛ ሰዎች ወይም አስቀድሞ በተቀዳ ሮቦ-ኮሎች (robocalls) የሚፈጸም ነው።

በመኾኑ ከማያዉቁት አካል ለሚደረግ የስልክ ጥሪ የትኛዉንም መረጃ ከመስጠት መቀጠብ እንደሚገባ ከኢንሳ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

የዲጂታል ክፍያ ጥንቃቄ !
19/04/2025

የዲጂታል ክፍያ ጥንቃቄ !

በበዓላት ወቅት ሐሰተኛ የብር ኖቶች በስፋት የመሰራጨት ዕድል ሰፊ ነው። ባሕር ዳር:ሚያዝያ 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በበዓላት መዳረሻ ወቅት በገበያ ላይ የሐሰተኛ የብር ኖቶች ዝውውር በስ...
18/04/2025

በበዓላት ወቅት ሐሰተኛ የብር ኖቶች በስፋት የመሰራጨት ዕድል ሰፊ ነው።

ባሕር ዳር:ሚያዝያ 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በበዓላት መዳረሻ ወቅት በገበያ ላይ የሐሰተኛ የብር ኖቶች ዝውውር በስፋት እንደሚታይ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባሕር ዳር ዲስትሪክት አስታውቋል።

በተለያዩ ከተሞች በዓልን ምክንያት በማድረግ በሐሰተኛ ገንዘብ የሚገበያዩ ግለሰቦች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ መጨመሩንም ባንኩ ገልጿል።

የባንኩ የባሕር ዳር ዲስትሪክት ሥራ አሥኪያጅ ጋሹ አላዩ በተለይም በበዓላት ወቅት በገበያ ቦታዎች መጨናነቅ ስለሚኖር ሐሰተኛ የብር ኖቶች በስፋት የመሰራጨት ዕድል እንዳላቸው ነው የተናገሩት።

ባንኩ ደንበኞቹን ከመጭበርበር እና ከዝርፊያ ለመከላከል አስፈላጊውን ጥንቃቄ እያደረገ እንደኾነ የገለጹት ሥራ አሥኪያጁ የሐሰተኛ የብር ኖት ዝውውርን ለመከላከል ግብይቶችን በባንክ በኩል ማድረግ የመጀመሪያው አማራጭ መኾኑን አሳስበዋል።

በተለይም አርሶ አደሮች የእንስሳት ግብይት እና ሌሎች ምርቶችን ሲሸጡ ገዥው ገንዘቡን በቀጥታ ወደ ባንክ አካውንታቸው እንዲያስገባ በማድረግ ከሐሰተኛ ገንዘብ እና ከዝርፊያ ራሳቸውን መጠበቅ እንደሚችሉ አሳስበዋል።

በተጨማሪም ማንኛውም ሰው ብዙ ገንዘብ ይዞ ከመንቀሳቀስ ይልቅ የዲጂታል ክፍያ አማራጮችን እንዲጠቀም ነው ያስገነዘቡት።

ይህ የማይመች ከኾነ ደግሞ ገንዘቡን በባንክ አካውንቱ ገቢ እንዲደረግለት ማድረግ እንደሚችል ጠቁመዋል።

የኅብረተሰቡ ግንዛቤ ከበፊቱ የተሻሻለ በመኾኑ የሐሰተኛ የብር ኖት ማጭበርበር እየቀነሰ መምጣቱንም አመልክተዋል።

የእጅ በእጅ ግብይት በሚደረግበት ጊዜ ሐሰተኛውን ከትክክለኛው የብር ኖት በጥንቃቄ መለየት እንደሚቻል የገለጹት ሥራ አሥኪያጁ የሐሰተኛው ኖት ወረቀት ከመደበኛው ብር ጋር ሲነጻጸር መሠረታዊ የሚባሉ በገንዘቡ ላይ የታተሙ መለያዎች ከመኖራቸውም በተጨማሪ በመዳሰስ ሊለይ የሚችል እንደኾነም ተናግረዋል።

በመኾኑም ኅብረተሰቡ ገንዘብ ሲቀበል በጥንቃቄ እንዲመረምር አሳስበዋል።

በሌላ በኩል የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሚዲያ ክፍል ዋና ኀላፊ ምክትል ኮማንደር መሳፍንት እሸቴ የሐሰተኛ ገንዘብ ዝውውር በተደጋጋሚ የሚፈጸም ወንጀል መኾኑን ገልጸዋል።

ምክትል ኮማንደር መሳፍንት በተለይም በበዓላት ወቅት የገበያ እንቅስቃሴ ሲጨምር የሐሰተኛ የብር ኖቶች ወደ ገበያ የመሰራጨት ዕድሉ ሰፊ እንደኾነ ተናግረዋል።

በገበያ ላይ በብዛት የሚዘዋወሩት የሐሰተኛ የብር ኖቶች የመቶ እና የሁለት መቶ ብር ኖቶች ሲኾኑ በተለይም በቁም እንስሳት ግብይት ወቅት በአርሶ አደሩ አካባቢ በስፋት እንደሚሰራጩ ምክትል ኮማንደሩ አስረድተዋል።

የሐሰተኛ የብር ኖትን ለመለየት የባንኮች የራሳቸው መለያ ዘዴዎች እንዳሏቸው ገልጸው ኅብረተሰቡ መለያዎችን በጥንቃቄ እየለየ እንዲጠቀም አሳስበዋል።

የፖሊስ ተቋሙ በበዓላት ወቅት በገበያ ቦታዎች ላይ ልዩ የጥበቃ ስምሪት እንደሚሰጥ የገለጹት ምክትል ኮማንደሩ፣ ማንኛውም የኅብረተሰብ ክፍል የሐሰተኛ የብር ኖት ዝውውር መኖሩን ካወቀ ወዲያውኑ ለፖሊስ በመጠቆም ወንጀሉን ለመከላከል የበኩሉን እንዲወጣ አሳስበዋል።

በተጨማሪም ኅብረተሰቡ የሐሰተኛ የብር ኖቶችን መለያ ባሕሪያት በትክክል ማወቅ እና ግብይቶችን በባንክ በመፈጸም ከመጭበርበር ራሱን መጠበቅ ይኖርበታል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የተሰጠ መግለጫ፦
08/04/2025

ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የተሰጠ መግለጫ፦

"መንግሥት ከንግድ ባንክ የተበደረው አንድ ትሪሊዮን ዕዳ አለበት በሚል የተሠራጨው ዜና ሀሰት ነው"የኢትዮጵያ ንግድ ባንክባሕር ዳር: መጋቢት 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮዽያ ንግድ ባን...
07/04/2025

"መንግሥት ከንግድ ባንክ የተበደረው አንድ ትሪሊዮን ዕዳ አለበት በሚል የተሠራጨው ዜና ሀሰት ነው"የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

ባሕር ዳር: መጋቢት 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ በዚህ በጀት ዓመትም ኾነ ከዚያ በፊት አንድም ብር ለመንግሥት በቀጥታ አበድሮ እንደማያውቅ መግለጫ ሰጥቷል።

መንግሥት ከሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች (በብሔራዊ ባንክ በኩል ለሽያጭ ከሚቀርበው የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ውጪ) በቀጥታ የመበደር አሠራርም ሆነ ልምድ የለውም ብሏል በመግለጫው።

ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ በዚህ በተገባደደው ሳምንት ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የስምንት ወራት የሥራ አፈጻጸም ማቅረባችንን ተንተርሶ በሪፓርተር ጋዜጣ የዕሁድ ዕትም ቅጽ 30 ቁጥር 2602 መጋቢት 28 ቀን 2017 ዓ.ም ታትሞ የተሰራጨው ዜና ከርዕሱ ጀምሮ ለቋሚ ኮሚቴው ከቀረበው ሪፖርትም ኾነ ከእውነታው የተለየ እና የተዛባ መረጃ ሆኖ አግኝተነዋል ማለቱን ከባንኩ የትስስር ገጽ ላይ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

ለምሳሌ በጋዜጣው ዕትም ርዕስ ላይ የተገለጸው እና "መንግሥት ከኢትዮዽያ ንግድ ባንክ የተበደረው አንድ ትሪሊዮን ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ” የተባለው ዜና ከእውነት የራቀ ከመኾኑም በላይ በሪፖርቱም ፈጽሞ እንደዚህ አይነት ሀሳብ አልቀረበም ነው ያለው ባንኩ።

“ባለፉት 15 ዓመታት 92 በመቶ ብድር የተሰጠው ለመንግሥት ተቋማት ነው ተብሏል” የሚለው ሀሳብም ስህተት ነው ብሏል።

የቀረበው ሪፖርት በግልጽ እንደሚያሳየው ከለውጡ በፊት የባንካችን የብድር ትኩረት ለመንግስት ተቋማት እንደነበር እና ይህ ብድር አድጎ በመጨረሻም ከአምስት ዓመት በፊት እስከ 92 በመቶ እንደደረሰ እና ከአምስት ዓመት ወዲህ ግን ያ አሠራር የተቀየረ እና ቅድሚያ ለግል ተበዳሪዎች እየተሰጠ በመሆኑ፤ ለምሳሌ ያህል በዚህ ስምንት ወራት ከተሰጠው ጠቅላላ ብር 264 ነጥብ 65 ቢሊዮን ብድር ውስጥ ከ88 በመቶ በላይ ብድር የተሰጠው ለግሉ ዘርፍ በመኾኑ አሁን ያለው የመንግሥት ተቋማት የብድር ክምችት ድርሻ ወደ 72 በመቶ ዝቅ ማለቱን ተመላክቷል።

በመሰረቱ ይህ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ዕዳ መንግሥት በቀጥታ ራሱ የተበደረው የመንግሥት ዕዳ ሳይኾን የተለያዩ እንደ ባንካችን ያሉ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች የተበደሩት ዕዳ ነው ብሏል።

መንግሥት በእነዚህ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ውስጥ የባለቤትነት ድርሻ ቢኖረውም እነዚህ ተቋማት ከአሥፈጻሚው መንግሥት የተለዩ እና የራሳቸው ካፒታል ያላቸው፣ እንደ ማንኛውም ድርጅት ንግድ ፈቃድ አውጥተው የሚነግዱ፣ በድርጅታቸው ስም ገንዘብ የሚበደሩ፣ ሊያተርፉም ኾነ ሊከስሩ የሚችሉ፣ ለትርፍ የተቋቋሙ የልማት ድርጅቶች ሲኾኑ ብድሮቹንም የወሰዱት ለራሳቸው ፕሮጀክቶች በመሆኑ ለእነዚህ ተቋማት የተሰጠውን ብድር የመንግሥት ብድር ተደርጎ መወሰዱ ስህተት እንደኾነ ገልጻል።

በሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ አሥተዳደር መሠረት መንግሥት ማንኛውም ዓይነት የአጭርም ሆነ የረጅም ጊዜ የገንዘብ ፍላጎቱን በሕግ በተቀመጠው አሠራር እና ምንጭ ያሟላል እንጂ ከሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች በቀጥታ ብድር የሚወስድበት አግባብ የለም ነው ያለው ባንኩ በመግለጫው።

ትክክለኛው እውነታ ይህ ሆኖ እያለ አንዳንድ የመገናኛ ብዙኃን ዕዳውን መንግሥት በቀጥታ የተበደረው ዕዳ እንደሆነ አድርገው በሪፖርተር ጋዜጣም ሆነ ጋዜጣውን ተከትለው በወጡ አንዳንድ የሚዲያ አካላትም መረጃውን በተዛባ እና በተሳሳተ መልኩ መዘገባቸው ከባንካችን መግለጫ አውድ ውጭ የቀረበ ከመኾኑም በላይ የጋዜጣው ርዕስ በውስጡ ከተጻፉት ሀሳቦች ጋርም ያልተጣጣመ መኾኑ አንባቢያንን ግራ ሊያጋባ እንደሚችል ስለሰጋን እውነታውን ለማሳወቅ ተገደናል ነው ያለው።

በጋዜጣው በጉልህ ከተገለጸው በተቃራኒ መንግሥት የልማት ድርጅቶች ከባንካችን የተበደሩትን እና ለበርካታ ዓመታት ሳይከፍሉ የቆዩትን ከፍተኛ የብድር ገንዘብ በባንካችን ላይ የደቀነውን አደጋ በመገንዘብ የሚከተሉትን እርምጃዎች በመውስድ ባንካችንን ከውድቀት ታድጎታል ብሏል።

1ኛ. የልማት ድርጅቶቹ ከባንካችን ብድሩን የሚወስዱበት አሠራር አመላለሱን የሚያረጋግጥ ስላልነበረ ይህ አሠራር ሙሉ በሙሉ እንዲቀር እና ባንካችን የውሳኔ ነጻነት እንዲኖረው ለመንግሥት ተቋማትም ቢሆን አዋጭ የንግድ ሀሳብ ለሚያቀርቡ እና ባንካችን ስለአመላለሱ እርግጠኛ ለኾነባቸው ብቻ ብድር እንዲሰጥ አቅጣጫ የተቀመጠው ከአምስት ዓመት በፊት ነው።

ይህ ብቻ ሳይኾን ቅድሚያ ለግል ተበዳሪዎች እንዲሰጥ እና የመንግስት የልማት ድርጅቶችም ቀድመው የጀመሩትን ፕሮጀክቶች ሳይጨርሱ ሌላ እንዳይጀምሩ ስለተደረገ ከአምስት ዓመት በፊት 92 በመቶ ደርሶ የነበረው የመንግሥት ተቋማት አጠቃላይ የብድር ድርሻ ወደ 72 በመቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝቅ ማለቱ እና የግሉ ተበዳሪዎች ድርሻ ደግሞ ከ8 በመቶ ወደ 28 በመቶ በፍጥነት ማደጉ ከፍተኛ ስኬት ሆኖ የቀረበና አንባቢያን ሊያውቁት የሚገባው ጥሬ ሀቅ ነው።

2ኛ.የልማት ድርጅቶቹ በወቅቱ መመለስ ያልቻሉትን ዕዳ በተመለከተ ደግሞ፡-
ሀ. መጀመሪያ የመንግስት ዕዳ እና ሀብት አሥተዳዳሪ ድርጅት በማቋቋም እዳዎቹን እንዲከፍል ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል። በዚህ ጥረትም ከብር 42 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ እንዲከፈል ተደርጓል።

ለ. ችግሩ በዕዳ እና ሀብት አሥተዳደር ድርጅት ጥረትም ሊፈታ እንደማይችል በመረጋገጡ በዚህ የበጀት ዓመት መጀመሪያ ላይ አጠቃላይ የአከፋፈል ችግር የገጠመው የመንግሥት የልማት ድርጅቶች የብር 845 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዕዳ ተሰባስቦ ወደ ገንዘብ ሚኒስቴር እንዲዞር እና በየዓመቱ በጀት ተይዞለት እና በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲከፈል ለዚህም ተመጣጣኝ የመንግሥት ቦንድ ለባንካችን እንዲሰጥ በፓርላማ ጭምር በማጽደቅ ኀላፊነት የሚሰማው እና ቆራጥ መንግሥት ብቻ የሚፈጽመው ታሪክ በመሥራት ባንካችንን ከውድቀት ኢኮኖሚያችንንም ከትልቅ አደጋ ያዳነ እርምጃ በመውሰዱ መንግሥታችንን እጅግ በጣም አመስግነናል ብሏል።

ከዚሁ ከተዛወረው ዕዳ ላይ ደግሞ በስምምነቱ መሰረት የመጀመሪያ የግማሽ ዓመት ወለድ በጥር ወር መጀመሪያ ላይ በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ብር 38 ቢሊዮን ለባንካችን ተከፍሏል። ስለዚህ መንግስት ባንካችንን ለማዳን ሲል ከልማት ድርጅቶች ተቀብሎ መክፈል ከጀመረው ዕዳ ውጪ የተበደረው ምንም ገንዘብ እንደሌለ ለሕዝባችን ማሳወቅ እንፈልጋለን።

3ኛ. መንግሥት ከልማት ድርጅቶች ከተረከበው ከፍተኛ ዕዳ በተጨማሪ ባንካችንን ለማጠናከር የብር 54 ነጥብ 7 ቢሊዮን የካፒታል ጭማሪ በማድረግ ከላይ ከተገለጸው የድርጅቶች ዕዳ ጋር ተደምሮ ብር 900 ቢሊዮን የመንግስት ቦንድ እንዲሰጠን በማድረጉም ባንካችንን ሊገጥሙት የሚችሉትን የፋይናንሻል ስጋቶችን መቋቋም ብቻ ሳይሆን ጠንካራ እና ተወዳዳሪ ባንክ እንዲሆን ረድቶታል።

4ኛ. መንግሥት ባንካችንን የበለጠ ለማጠናከር ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር ላለፉት አምስት ዓመታት ጥልቅ ሪፎርም እንድናደርግ ከፍተኛ ድጋፍ እና አመራር የሰጠን ሲሆን የባንካችን ካፒታል የበለጠ እንዲጠናከርና የውጪ ምንዛሬ ፍላጎታችንን ለማሟላት ያለመ 650 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የካፒታል ማሳደጊያ ድጋፍ እንድናገኝ በማድረጉ ባንካችንን የበለጠ የሚያገዝፈው እና የማይበገር ጠንካራ ተወዳዳሪ የሚያደርገው የመንግሥታችን ልዩ ድጋፍ በመሆኑ ባንካችን አሁንም አብዝቶ ያመሰግናል።

እንግዲህ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ በስብሰባው ላይ የቀረቡትና ሕዝባችን ሊያውቃቸው የሚገቡ ብዙ መልካም ዜናዎች እያሉ ያለመታደል ሆኖ አሉታዊ ዜና የመናፈቅ ችግር ጎልቶ በታየበት አኳኋን ሪፖርተርም ሆነ ሌሎች ጥቂት ሚዲያዎች የባንካችንን እጅግ በጣም አንጸባራቂ የስምንት ወራት አፈጻጸም ላይ ጥላሸት ለመቀባት መሞከራቸው አሳዛኝ ተግባር ሆኖ አግኝተነዋል።

ይልቁንም ሕዝባችን ቢያውቀው የሚጠቅመው ባንካችን በስምንቱ ወራት አፈጻጸም በሁሉም ቁልፍ መለኪያዎች እጅግ በጣም የላቀና ከምንግዜውም እጅግ በጣም ከፍ ያለ ውጤት ማስመዝገቡን ነበር። ለምሳሌ ያህል፦

1. በቁጠባ (Deposit)
√ በ8 ወራት ብቻ ብር 367 ቢሊዮን ማሰባሰብ መቻሉ፤ የዚህም ውጤት ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ሲነጻጸር 344 በመቶ በላይ ዕድገት መሆኑ፣
√ የባንካችን አጠቃላይ ተቀማጭ ብር 1 ነጥብ 54 ትሪሊዮን በላይ መድረሱ፤ በዚህም የባንካችን የገበያ ድርሻ የመቀነስ ጉዞውን ቀይሮ በ2 ነጥብ 2 በመቶ በማደግ ወደ 49 ነጥብ 3 በመቶ ከፍ ማለቱ፣

2. ብድር
√ በ8 ወራት ብቻ ብር 149 ነጥብ 2 ቢሊዮን መሰብሰቡ፤ ይህም ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲወዳደር የ66 ነጥብ 8 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡ ፣
√ በዚሁ ጊዜ ውስጥ አዲስ የተለቀቀ ብድር ብር 264 ነጥብ 7 ቢሊዮን መሆኑ፤ ይኸውም ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ82 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ መሆኑ፤ ከተለቀቀው አዲስ ብድር ውስጥ ከ88 ነጥብ 2 በመቶ በላይ ለግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ የተሰጠ መሆኑ፣

√ የባንካችን አጠቃላይ ብድር ከፍተኛ ዕድገት ያስመዘገበ በመሆኑ የባንካችን የብድር የገበያ ድርሻ የመቀነስ አቅጣጫውን ቀይሮ እ.ኤ.አ. ጁን 2024 ከነበረው 42 ነጥብ 8 በመቶ ከፍተኛ ዕድገት በማሳየት 51 ነጥቅ 7 በመቶ ከፍ ማለቱ፣
√ የባንካችን የተበላሹ ብድሮች ምጣኔ አምና በተመሳሳይ ጊዜ ከነበረው የ2 ነጥብ 7 በመቶ ወደ 2 ነጥብ 3 በመቶ ዝቅ ማለቱ፤

3. በውጪ ምንዛሪ
- ባንካችን በ8 ወራት አፈጻጸሙ 2 ነጥብ 45 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ማሰባሰቡ፤ ይህም ግኝት ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ16 ነጥብ 7 በመቶ እድገት የነበረው መሆኑ፣
- በተለይም ከግል ኃዋላ እና ከሸቀጥ ወጪ ንግድ የተገኘው የውጪ ምንዛሪ እንደቅደም ተከተሉ የ52 ነጥብ 2 በመቶ እና የ58 በመቶ ከፍተኛ እድገት ማስመዝገብ መቻላቸው፣
- ባንካችን በ8 ወራት ውስጥ አጠቃላይ ለገቢ ንግዱ የከፈለው የውጪ ምንዛሪ መጠን 5 ነጥብ 14 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱ እና ከዚህም ውስጥ ለግሉ ሴክተር የተከፈለው 1 ነጥብ 22 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ከአምና ተመሳሳይ ወቅቶች ጋር ሲነፃፀር የ58 በመቶ ከፍተኛ እድገት ማስመዝገቡ መልካም ስኬት ነው፡፡

4. ካፒታል
የባንካችን አጠቃላይ ካፒታል ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ሲወዳደር የ105 በመቶ ዕድገት በማሳየት ብር 132 ቢሊዮን መድረሱ፤

5. አጠቃላይ ሀብት
የባንካችን አጠቃላይ ሀብት በስምንት ወራት በብር 641 ነጥብ 7 ቢሊዮን በማደግ ብር 2 ነጥብ 07 ትሪሊዮን መድረሱ፤ በዚህ የ44 ነጥብ 8 በመቶ ከፍተኛ ዕድገት ማስመዝገብ በመቻሉ በሀብት የነበረን የገበያ ድርሻ እ.ኤ.አ. በጁን 2024 ከነበረው 43 ነጥብ 7 በመቶ ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ 50 ነጥብ 4 በመቶ መድረስ መቻሉ፤

6. አጠቃላይ ገቢና ወጪ
√ በ8 ወራት ባንካችን በሁሉም ዘርፍ ከፍተኛ የገቢ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን አጠቃላይ ገቢውም ብር 109 ቢሊዮን መድረሱ፤ ይኸውም ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲወዳደር የ26 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡ ፣
√ ባንካችን ጥብቅ የወጪ ቅነሳ ፕሮግራም ሲከተል የነበረና ከፍተኛ የተበላሹ ብድሮች ቅነሳ በማድረጉ ምንም እንኳን በማክሮ ኢኮኖሚው ደረጃ ብዙ ወጪ ጨማሪ ምክንያቶች ቢኖሩም ባንካችን ከመደበኛ የስራ እንቅስቃሴው ያስመዘገበው የወጪ ዕድገት የ2 ነጥብ 6 በመቶ ብቻ በመሆኑ አጠቃላይ የመደበኛ ኦፕሬሽን ወጪ ብር 76 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብቻ መሆኑ፤

7. መደበኛ ያልተጣራ ትርፍ
√ ባንካችን በ8 ወራት ብር 32 ነጥብ 6 ቢሊዮን ያልተጣራ ትርፍ ከመደበኛ ኦፕሬሽን ማግኘት መቻሉ እና ይኸም አፈጻጸም ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ170 ነጥብ 5 በመቶ ዕድገት ያሳየ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት ዓመቱን በሙሉ ተመዝግቦ ከሚያውቀው ትልቁ ትርፍም ከፍተኛ ብልጫ ያሳየ መሆኑ፣

8. የዲጂታል ግብይት
√ ባንካችን በ8 ወራት በዲጂታል ቻናሎቹ ብቻ ከብር 7 ነጥብ 7 ትሪሊዮን በላይ ማንቀሳቀሱ፤ አጠቃላይ የግብይት ብዛትም የ1 ነጥብ 27 ቢሊዮን የበለጠ መሆኑ የተንቀሳቀሰው ገንዘብ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ92 በመቶ ዕድገት ያሳየ ሲሆን የግብይት ብዛት ዕድገትም ከ84 በመቶ በላይ ዕድገት የነበረው መሆኑ፤
√ ከባንካችን አጠቃላይ የደንበኞች ግብይት በስምንቱ ወራት አማካይ ግብይት 79 በመቶ በዲጂታል የተስተናገዱ ሲሆን 21 በመቶው ብቻ ወደ ቅርንጫፎቻችን ጎራ ብለው የተስተናገዱ መሆኑ ለደንበኞቻችን ምቾት እና ለባንካችን በወጪ ቁጠባም ያገዘና እጅግ በጣም ከፍተኛ ስኬት ማስመዝገቡ የሚጠቀሱ ከፍተኛ ቁልፍ ስኬቶች ናቸው፡፡

በሌሎች በተቀሩትም ዘርፎች ተመሳሳይ ስኬት የተመዘገበበት በመሆኑ እጅግ በጣም ደስ ይለናል፤ ሁላችሁም የተከበራችሁ የባንካችን ደንበኞችም ሆናችሁ ሀገር ወዳዶች በሙሉ በባንካችን መልካም አፈጻጸም ደስ እንደምትሰኙ እና ከባንካችን ጋር አብሮነታችሁን እንደምታጠናክሩ እናምናለን።

በመጨረሻም ባንካችን ለመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴው በግልጽ ካቀረበው እውነታ ባፈነገጠና በተዛባ መልኩ የሪፖርተር ጋዜጣ በዜና አርዕስቱ “መንግስት ከኢትዮዽያ ንግድ ባንክ የተበደረው አንድ ትሪሊዮን ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ” በሚል እንዲሁም በሌሎች ጥቂት ሚዲያዎችም የመንግስት ዕዳ ብር 1 ነጥብ 3 ትሪሊዮን እንደተሻገረና አሁናዊ የመንግስት የብድር ዕዳ ዕድገትን የሚያሳይ በሚመስል መልኩ ተቀናብሮ የቀረበው ዘገባ ሀሰተኛ ከመሆኑም ባሻገር ከላይ በዝርዝር በተመላከቱት እውነተኛ መረጃዎች ላይ ተመስርቶ በባንካችን በኩል የቀረበውን ትክክለኛ ሪፖርት የማያንጸባርቅ እና እነዚህን ለመንግስት የልማት ድርጅቶች የተሰጡትን ብድር ለባንካችን ለመክፈል መንግስት እያደረገ ያለውን ቁርጠኝነት ታሳቢ ያላደረገ በመሆኑ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ሚዲያዎች የተላለፈው የተዛባና የተሳሳተ ዘገባ እንዲታረም እናሳስባለን ሲል በመግለጫው አትቷል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በኢ ቢ ኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈውን   "አዲስ ምዕራፍ” የቴሌቪዥን ፕሮግራም አገደ። ባሕር ዳር: መጋቢት 23/2017 ዓ.ም (አሚኮ)  የኢትዮጵያ መገና...
01/04/2025

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በኢ ቢ ኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈውን "አዲስ ምዕራፍ” የቴሌቪዥን ፕሮግራም አገደ።

ባሕር ዳር: መጋቢት 23/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን “አዲስ ምዕራፍ” የቴሌቪዥን ፕሮግራም ላይ አሥተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል።

ባለሥልጣኑ ባወጣው መረጃ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በኢ ቢ ኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ አዲስ ምዕራፍ በተሰኘ ፕሮግራሙ እሑድ መጋቢት 14/2017 ዓ.ም ያሰራጨውን ፕሮግራም ከመገናኛ ብዙኃን አዋጅ እና ከዘርፉ ሕጎች አንጻር በመገምገም አሥተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል፡ ብሏል።

በዚሁ መሠረት በቴሌቪዥን ጣቢያው የቀረበው ፕሮግራም በሐሰተኛ መረጃ ላይ የተመሠረተ፣ ሕዝብን የሚያሳስት እና ጥርጣሬን የሚፈጥር፣ የመገናኛ ብዘኃን አዋጅ 1238/2013 የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣው አዋጅ 1185/2012 እንዲሁም የጋዜጠኝነት ሙያ ስነ ምግባርን የሚጥስ የፓራጆርናሊዝም አሠራርን የተከተለ ሆኖ ተገኝቷል ነው ያለው።

ጣቢያውም በፕሮግራሙ ዙሪያ ተጠይቆ ለባለሥልጣኑ በሰጠው ምላሽ ያሰራጨው ፕሮግራም ሐሰተኛ መሆኑን እና ስህተት መፈጸሙን ገልጿል ብሏል።

ባለሥልጣኑ ጉዳዩን መርምሮ በጣቢያው የሚሰራጨው “አዲስ ምዕራፍ” የተሰኘ ፕሮግራም በኤዲቶሪያል አሠራሩ ላይ አስፈላጊውን እርምት ወስዶ ለባለሥልጣኑ እስኪያሳውቅና ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ የአዲስ ምዕራፍ ፕሮግራም በመገናኛ ብዙኃን አዋጁ መሠረት ከስርጭት ታግዶ እንዲቆይ የተወሰነ መኾኑን አሳውቋል። የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው መኾኑንም ባለሥልጣኑ አሳውቋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Address

Bahir Dar
6000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አሚኮ እውነታ ማጣሪያ AMECO Fact Check posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to አሚኮ እውነታ ማጣሪያ AMECO Fact Check:

Share