Visit Gojjam

Visit Gojjam gojam

በቀድሞዉ ጎጃም ክፍለ ሀገር ባሕር ዳር አዉራጃ የባህርዳር ኤርፖርት1976 ዓምBlue nile press Visit Gojjam Gojjam
17/02/2026

በቀድሞዉ ጎጃም ክፍለ ሀገር ባሕር ዳር አዉራጃ የባህርዳር ኤርፖርት1976 ዓም

Blue nile press Visit Gojjam Gojjam

12/12/2025
 #ጎጃም ነጭ ለባሽ ነጭ  አምራች  ነው!ጎጃም አዘነን የጎጃም ማህበረሰብ መገለጫ ባህላዊ  ልብስ አድርጎ መወሰድ አግባብ  አይደለም! # # # # # #  የጐጃም ማህበረሰብ እጅግ ጥንታዊ ከ...
02/11/2025

#ጎጃም ነጭ ለባሽ ነጭ አምራች ነው!

ጎጃም አዘነን የጎጃም ማህበረሰብ መገለጫ ባህላዊ ልብስ አድርጎ መወሰድ አግባብ አይደለም!
# # # # # #
የጐጃም ማህበረሰብ እጅግ ጥንታዊ ከሚባሉት የአገራችን ክፍሎች አንዱ የሆነና ተነግሮ የማያልቅ የተፈጥሮ ጸጋ፣ የታሪካዊና የጥንታዊ ቅርሶች መገኛ እንዲሁም ካለፉት የማህበረሰቡ አባላቶች የወረሳቸው የራሱ መገለጫ የሆኑ ባህል፣ ወግና ልማድ እንዲሁም እምነትና ፍልስፍና ባለቤት የሆነ ታላቅ ህዝብ ነው፡፡

የጎጃም ማህበረሰብ የራሡ መገለጫ የሆኑ ድንቅ ባህላዊ ሀብቶች ባለቤት ሲሆን ከባህላዊ መገለጫዎች መካከልም ከጥንት የማህበረሰቡ አባላት ሲወርድ ሲዋረድ የመጡ፣የራሡ የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ፣ማንነቱን፣ ጀግንነቱን ፣ ፍልስፍናውን የሚገልፅባቸው ድንቅ ሀገረ ሰባዊ ባህላዊ አልባሳት ባለቤት ነዉ ።

ነገር ግን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ባለማወቅም ይሁን ሆን ተብሎ የማህበረሰቡን ባህል ለማጥፋት የጎጃምን ማህበረሰብ ባህል የማይወክሉ አልባሳትን የመጠቀም እንቅስቃሴዎች እየተበራከቱ መጥተዋል።

የማህበረሰቡን ባህል በመወከል በተለያዩ ባህላዊ ሙዚቃዎች፣ በሚዲያዎች ፣በታዋቂ ሰዎች፣ የተለያዩ ዝግጅቶች ላይ እየቀረቡ ያሉ የአልባሳት አይነቶች መካከል አንዱ ጎጃም አዘነ ነዉ ።

ጐጃም አዘነ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የጐጃምን ማህበረሰብ ባህላዊ አልባሳት ተደርጐ እየተወሰደ ያለ የአልባሳት አይነት ነው፡፡ይህ የአልባሳት አይነት ምንም እንኳን የጐጃም ማህበረሰብ እንደሌሎች የአገራችን ህዝቦች ሁሉ ቴክኖሎች አምርቶት በአካባቢው በርካሽ ዋጋ ከመገኘቱና አልባሳቱ ከሚሰጠው ከፍተኛ አገልግሎት የተነሳ በአሁኑ ስዓት የማህበረሰቡ አባላት በስራ ጊዜያት አልባሳቱን እየተጠቀሙበት የሚገኙ ቢሆንም እንደማህበረሰቡ አባላት ወይም የባህሉ አዋቂዎች ገለፃ ጐጃም አዘነ የጐጃምን ማህበረሰብ ባህል መወከል ወይም መግለፅ አይችልም ።

ጐጃም አዘነ የተባለበትን ምክንያት ስንመለከት ፡፡

በአብዛኛው የማህበረሰቡ አባላት የሚገልፀው ጐጃም አዘነ በመባል የሚጠራው የአልባሳት አይነት ስያሜውን ያገኘበትን ምክንያት ሲያስቀምጡ የጐጃም ማህበረሰብ በቀደሙት ጊዜያት ይጠቀምበት የነበረው የአልባሳት አይነት በአካባቢው ይመረት ከነበረው የጥጥ ምርት ነዉ ። ከጥጥ የሚሰራው ያልባሳት አይነትም ነጭ ሲሆን በማህበረሰቡ ባህል መሰረት ነጭ አልባሳት የደስታ፣ የሰላም፣ የጥጋብ ወዘተ… መገለጫ እንደሆነና ይለበስም የነበረው የአልባሳት አይነት ነጭ መሆኑን ይገልፃሉ ፡፡

ከዚህም ጋር በተያያዘ ነጭ በመልበስ ይታወቅ የነበረው የጐጃም ማህበረሰብ በአንድ ወቅት በአብዛኛው ማህበረሰብ ዘንድ ጠቆር ባለ ከለር የተሰራ የአልባሳት አይነት ለብሰው በማታየታቸው ምነው ጐጃም ነጩን ትቶ ጥቁሩን የለበሰ ? ምን ነክቶት ነው ጐጃም የአዘን ልብስ የለበሰ ? እተባለ እንደተወራና ከዚህ ጋር ተያይዞም አልባሳቱ #ጐጃም አዘነ እየተባለ መጠራትእንደጀመረ ገልፅውልናል ፡፡

በማህበረሰቡ ባህል መሰረት ጥቁር ልብስ የሀዘን መግለጫ ሲሆን አንድ ሰው ጠቆር ያለ ያልባሳት አይነት ከለበሰ የአዘነ ወይም አዘንተኛ መሆኑን ለማመላከት ተብሎ የሚደረግ ሲሆን የጐጃም ማህበረሰብ ነጩን አልባሳት በመተው ጠቆር ያለውን ያልባሳት አይነት ከመጠቀማቸው ጋር በተያያዘ የአልባሳቱ መጠሪያ ጐጃም አዘነ ሊባል ችሏል ፡፡ይህ የስያሜ አሰጣጥ በአብዛኛው የማህበረሰቡ አባላት የሚነገር አፈ ታሪክ ነዉ ።

በቀደሙት የማህበረሰቡ አባላት የሚለበሰው ያልባሳት አይነት ነጭ መሆንና ማህበረሰቡም ይህንን ያልባሳት አይነት በመልበሱ ጐጃም አዘነ፣ ተቸገረ፣ተከፋ፣ወዘተ…. ከተሰኘ አመለካክት የተሰጠው ስያሜ ሲሆን

#የጐጃም አዘነ ታሪካዊ አመጣጥ ስንመለከት
ጐጃም አዘነ በመባል የሚጠራው የአልባሳት አይነት ምንም እንኳን በአሁኑ ሰዓት የጐጃም ማህበረሰብ ባህል ተደርጐ ይወሰድ እንጅ አልባሳቱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

እንደ ማህበረሰቡ አባላት አገላልፅ ከሆነ ጐጃም አዘነ ተብሎ የሚጠራው የአልባሳት አይነት ወደ ጐጃም ማህበረሰብ ከመጣ ከሁለት አስርት አመታት የዘለለ ታሪክ እንደሌለውና ከ1970ቹ መጨረሻ እና ከ1980ቹ መጀመሪያ አካባቢ በአሉት ጊዜት ወደ እዚህ አካባቢ እንደመጣ የማህበረሰቡ አባላት ይናገራሉ ፡፡ እንደ መረጃ ሰጭዎቻችን ገለፃ ከሆነ የጐጃም አዘነ ታሪካዊ አመጣጥ በተመለከተ የተለያዩ መላ ምቶች የሚሰነዘሩ ሲሆን አመጣጡ በተመለከተ ከሚነገሩት መላ ምቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ ቀጥለን እንመለከታለን ፡፡

፨የጐጃም አዘነን ታሪካዊ አመጣጥ ከሚጠቁሙ መላ ምቶች መካከል አንዱ ሲሆን የአብዛኛው የማህበረሰቡ አመለካክት እንደሚያመለክተው ጐጃም አዘነ በመባል የሚታወቀው የአልባሳት አይነት በጐጃም ማህበረሰብ አባላት ዕውቀት፣ፍልስፍና፣ ባህል ወግና ልማድ መሰረት በማድረግ የተሰራ ወይም የተፈጠረ ሳይሆን ከደቡብና ከኦሮሞያ ክልል በመጡና በሙያው በሰለጠኑ የህግ ታራሚዎች አማካኝነት ሙያውን በጐጃም ላሉ የህግ ታራሚዎች ስልጠና በመስጠትና ሙያውን በማስተማር ሙያውን እንዳስተላለፉትና የህግ ታራሚዎች በስር ቤት ቆይታቸው ሙያውን እየተማሩ የስር ጊዜቸውን ጨርሰው ሲወጡ ይለብሱት የነበርና የስረኞች መለያ በመሆን ያገለግል የነበር የአልባሳት አይነት መሆኑን በመግለፅ እስረኞች እና በስርቆት ሙያ ላይ የተሰማሩ እራሳቸውን ለመደበቅ ይጠቀሙበት የነበረ የኋላ ኋላ ከአገልግሎትና ከሚሰጠው ጥቅም ጋር በተያያዘ ብዙሀኑ የማህበረሰብ አባል ዕውቀቱን እንደተማረና በአካባቢው ማምረት መቻሉን እንዲሁም አልባሳቱን መጠቀም እንደተጀመረ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፤

፨ሁለተኛው የመላ ምት አይነት የሚያመለክተው/የሚያሰረዳው/ ጐጃም አዘነ በመባል የሚታወቀው ያልባሳት አይነት ወደ ጐጃም ማህበረሰብ የመጣው ከቀደሙት የማህበረሰብ አባላት ሲወርድ ሲዋረድ በመጣ ሀገረ ስብአዊ ልማድ ሳይሆን በደርግ መንግስት ጐ/ማ/ጣ /ጐልማሶች ማሰልጠኛ ጣቢያ/ ይባል በነበረው እና መንግስት ጐልማሶችን እያደራጀ የተለያዩ የሙያ አይነቶች ያሰተምርበት በነበርበት ወቅት በስልጠና አማካኝነት በአካባቢው ለአሉ የእደ ጥበብ ባለሙያዎችና ለሌሎች ግለሰቦች ከአዲስ አበባ /ከሽዋ/ በመጡ የእደ ጥበብ ሙያ ባላቸው ባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት ዕውቀቱን እንዳስተላለፉትና አልባሳቱን በአካባቢ ማምረት እንደተቻለ እና አልባሳቱን በስራ እንዲሁም በልዩ ልዩ ጊዚያት እየተጠቀመበት መምጣቱን የተገኘው መረጃ ያመለክታል ፡፡

፨ሦስተኛው የመላ ምት አይነት የሚያመለክተው ጐጃም አዘነ በመባል የሚጠራው የአልባሳት አይነት ከሌላ አካባቢ የመጣ የማህበረሰቡን ባህል መሰረት ያላደረገ የማህበረሰቡን ማንነት መግለፅና መጠቆም ማይችል የአልባሳት አይነት መሆኑን የሚያሰረዱ ሲሆን፣ ይህም አልባሳት መጣ ተብሎ የሚታመነው ከ1980-1983 ዓ.ም በተካሄደው በኢህዴግና በደርግ የጦርነት ዘመን ሲሆን አልባሳቱንም ያመጡት የደርግ ወታደሮች እንደነበሩ ከመረጃ ሰጭዎቻችን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ እንደ መረጃ ሰጭዎቻችን አገላልፅ ከሆነ የደርግ ወታደሮች ይህን ያልባሳት አይነት የእግርና የእጅ ቁስል እንዲሁም ሌሎች የሰውነት ክፍሎቻቸውን በሚመቱ ጊዜ ቁስሉን ለመጠምጠም የሚጠቀሙበት እንደነበርና ከኢህአዴግ ወታደሮች በገጠማቸው ከፍተኛ ጥቃት የተነሳ ከማህል አገር ወደ ጐጃም በሚያፈገፍጉበት ወቅት በኢህአዴግ ወታደሮች ላለመማረክና
ወታደር መሆናቸውን ላለማሳወቅ ይለብሱት እንደነበርና ወደዚህ አካባቢ ለብሰውት እንደመጡ በመግለፅ የማህበረሰቡ አባላት አልባሳቱን ከሚሰጠው ጠቀሜታና አገልግሎት የተነሳ ሊጠቀምበት እንደቻለ ከመረጃ ምንጮቻችን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

፨የጐጃም አዘነ ታሪካዊ አመጣጥ በተመለከተና ወደ ጐጃም ማህበረሰብ እንዴት ሊመጣ እንደቻለ ከሚጠቁሙ መላ ምቶች መካከል የመጨረሻው መላ ምት ሲሆን፣ በዚህም መላ ምት የምንረዳው ከመጀመሪያዎች ሌሎች መላ ምቶች ጋር ተመሳሳይ ሲሆን፣ አልባሳቱ ወደ ጐጃም ማህበረሰብ የመጣውና በማህበረሰቡ እየተዋወቀበት የሄደበት ምክንያት ከጐጃም ማህበረሰብ ወደ ሌላ አካባቢ ማለትም ሽዋ፣ ደቡብ፣ ኦሮሚያ በመሳሰሉት አካባቢዎች በንግድ ይሄዱ የነበሩ ነጋዴዎች ለብሰውት ይመጡ የነበረ መሆኑን ገልፅው የማህበረሰቡ አባላትም
አልባሳቱ ከሚሰጠው ጥቅምና አገልግሎት የተነሳ አልባሳቱን በማስመጣትና በመግዛት መጠቀም እንደጀመረ ገልፅው የኃላ ኃላ ግን ባካባቢው እያመረተ መጠቀም መቻሉን ከተገኛ መረጃ ለመረዳት ተችሎል ፡፡

በአጠቃላይ እስከ አሁን የተመለከትናቸው አፈ ታሪኮች እንደሚያሰረዱት /እንደሚያመለክቱት/ ጐጃም አዘነ በመባል የሚጠራው የአልባሳት አይነት ምንም እኳን በአሁኑ ስዓት የጐጃም ማህበረሰብ ባህል ተደርጐ እየተወሰደና በተለያዩ መድረኮች የማህበረሰቡን ማንነት እየወከለ በመቅረብ ላይ ያለ ያልባሳት አይነት ቢሆንም የአልባሳቱ አሰያየምና ታሪካዊ አመጣጥ የሚያመለክተው የጐጃም ማህበረሰብ ቁሳዊ ባህል /አገረሰባዊ አልባሳት/ አለመሆኑን ነው፡፡

ስለዚህ ጎጃም አዘነ የጎጃምን ማህበረሰብ ባህል መወከልና መገለጫ ተደርጐ መወሰድ እንደሌለበት የማህበረሰቡ አባላት ይገልፃሉ ፡፡ ምክንያቱን ሲያሰቀምጡ የጐጃም ህዝብ የራሱ መገለጫ የሆኑ በፆታ፣ በዕድሜ፣በሌሎች መለያዎች ተለይተው ማህበረሰቡ የሚጠቀምባቸው ባህላዊ አልባሳት ያለው ሲሆን፣ እነዚህ የአልባሳት አይነቶችም ከአለፉት የማህበረሰቡ አባላት ሲወርድ ሲዋረድ በመጣ ልማድ የተወረሱ ናቸው፡፡

ነገር ግን በቅርብ ጊዜት የመጣው ጎጃም አዘነ በአሁኑ ሰዓት የጎጃምን ባህል በመወከል እየቀረበ ያለ የአለባበስ ዓይነት መሆኑ ትክክል ያልሆነ እና መስተካከል ያለበት እንደሆነ ማህበረሰቡ አባላት ይገልፃሉ ።

ጎጃም አዘነ የጐጃም ማህበረሰብ በመወከል በአሁኑ ስዓት እየቀረበ ያለ ያልባሳትና የአለባብስ ስርዓት ሲሆን፣ ይህ የአልባሳትና የአለባብስ ስርዓት የጐጃምን ማህበረሰብ ትክክለኛውን ባህል መግለፅ የማይችልና የማህበረሰቡ መገለጫ ተደርጐ መወሰድ የሌለበት የአልባሳት አይነት ነው፡፡

ምክንያቱም የጐጃም ማህበረሰብ ከሌላው ማህበረሰብ የሚለየው የራሱ የሆነ ማንነት ያለው ሲሆን፣ በማህበረሰቡ ባህል ፣ወግ ፣ ልማድ ፣ ዕውቀትና ጥበብ መሰረት በማድረግ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የበርካታ ቁሳዊና መንፈሳዊ ሀብት ባለቤት ነዉ ።

የማህበረሰቡ ቁሳዊና መንፈሳዊ ሀብት የሆነው ባንድ ቀን ጀንበር የተፈጠረ ሳይሆን በረጅም ዘመን የታሪክ ሂደት ተፈጠረና የማህበረሰቡን የትናት አሻራ የሚያንፀባርቁ እንዲሁም የዛሬን ማንነት የሚጠቁሙ ሲሆን፣ የማናቸውም ማህበረሰብ ባህል ሆነ ልማድ በአንድ ቀን ጀንበር ተፈጥሮ ያደረ ሳይሆን ከአለፉት የማህበረሰቡ አባላት የተወረሰ ነው፡፡

በዚህም መሰረት ጎጃም አዘነ በመባል የሚጠራው ያልባሳት አይነት በማህበረሰቡ ዘንድ ከሁለት አስርት አመታት የዘለለ ታሪክ የለውም፡፡ ይሁንና የጐጃም ማህበረሰብ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ1500 ዓመተ አለም ገደማ ጀምሮ እንደነበረና እንዲሁም በአራተኛው /4/ መቶ ክፈለ ዘመን ገደማ የዛሬ ስያሜውን /መጠሪያውን/ ያገኘ ማህበረሰብ ሲሆን፣ ይህ ማህበረሰብ እጀግ ጥንታዊ የሆነውን የማህበረሰቡን ባህል ከሁለት አስርት አመታት ባለው የአልባሳት አይነት የማህበረሰብ መገለጫ /ባህል/ ተደርጐ መወሰዱ ከማህበረሰቡ ጥንታዊነት ጋር ሲነፃፀር ተገቢ አይደለም፡፡

ጎጃም አዘነ የጐጃምን ማህበረሰብ ከማይወክልባቸው ምክንያቶች አንዱ በአሁኑ ስዓት አልባሳቱ በአገራችን ኢትዮጵያ በሚገኙ ደጋማው ክፍል በስፋት አገልግሎት የሚሰጥ በመሆኑና የጐጃም ማህበረሰብ ብቻ የሚጠቀምበት ባለመሆኑ የጐጃምን ማህበረሰብ ብቻ ሊወክል አይችልም ፡፡

አልባሳቱ የሚለበሰው ለተለያዩ ስራዎችና ለለሊት ልብስነት ከመሆኑም በተጨማሪ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ከበራዎችና ክብረ ባህሎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ማህበራዊ ክስተቶች አገልግሎት አለመሰጠቱና የማህበረሰቡ አባላት እንደ ባህል መግለጫና መገለጫነት አድረገው አለመጠቀማቸው ፡፡

የአልባሳቱ ተስተላልፎ በተመለከተ ከአያት ቅድመ አያቶቻቸው ወይም ከቀደሙት የማህበረሰቡ አባላት የተወረሰ ሳይሆን መደበኛ በሆነ መንገድ በትምህርት፣ በስልጠና በመሳሰሉት ዕውቀቱ /የአሰራር ጥበብ/ የተላለፈ ከመሆኑም ጋር በተያያዘ ምንም አይነት የማህበረሰቡን የፈጠራ ጥበብ፣ እውቀት፣ ፍልስፍናና ዕርዕዮተ አለምን ወዘተ… የማህበረሰቡን ልማድ የማሳየት አቅም የለውም፡፡

አልባሳቱ ከማህበረሰቡ ባህላዊ አልባሳት የማይመደብ መሆኑና ከአለፉት የማህበረሰቡ አባላት ያልተወረሰ እንዲሁም በቀደሙት ጊዜት አገልግሎት ላይ ያልዋለ ማህበረሰቡ በአካባቢው በሚያገኘው ጥሬ እቃና መስሪያ ቁስ በመጠቀም በባህሉ መሰረት ያልተሰራ በመሆኑ አልባሳቱን የጐጃምን ማህበረሰብ ባህል መወከል እንደማይችል ማሳያ በመሆን የቀረበ ሲሆን፣ በተለያዩ መድረኮች የምናያቸው የጐጃምን ማህበረሰብ ሀገረስባዊ ሙዚቃ የሚጫወቱ ዘፋኞችና ተወዛዋዦች እየለበሱት ያለው የአልባሳት አይነትና የአለባብስ ስርዓት ትክክል ባለመሆኑ መስተካከል መቻል አለበት፡፡

#ቆየት ባሉት ጊዜያት የጐጃምን ባህል በመወከል ይቀርብ በነበሩ ባህላዊ ሙዚቃዎች ላይ የቀድሞውን የአለባበስ ስርዓትና የአልባሳት አይነት የምናየው ሲሆን ለአብነትም የግሽ አባይ የኪነት ቡድን ሙዚቃዎችን ብንመለበከት ከ1980ቹ ዘመን በፊት የጐጃምን ማህበረሰብ አለባብስ ምን እንደሚመስልና እና ምን አይነት አልባሳቶችን ይጠቀም እንደነበር ለማሳየት ያስችላል፡፡

በእነዚህ የኪነት ባለሙያዎች የሚታየው የአልባሳት አይነትና የአለባብስ ሰርዓት ትክክለኛውን የማህበረሰቡን ባህል በመወከል የቀረበ ሲሆን ከዚህም መረዳት የምንችለው በዚህ ዘመን ጐጃም አዘነ በመባል የሚታወቀው የአልባሳት አይነት በማበረሰቡ ዘንድ የማይታወቅ በመሆኑና ካለፉት የማህበረሰቡ አባላት ያልተወረሰ መሆኑን ለመገንዘብ ያስችላል ።

ነገር ግን ይህ ያልባሳት አይነት የጐጃምን ማህበረሰብ ባህል ሊወክል የሚችለው ከቀደሙት የማህበረሰብ አባላት የተወረሰ፣ በማህበረሰቡ ባህል ፣ ወግ፣ ልማድ፣ እምነትና ፍልስፍና መሠረት የተሰራ ቢሆን ኑሮ የማህበረሰቡን ባህል መገለጫ በማድረግ መወሰድ ይቻል ነበር፡፡

ይህም ሲባል አንድ የማህበረሰብ አባል አንድ አልባሳትን በሚለብስበት ጊዜ የራሱ የሆነ ትርጉምና ትዕምርት ይሰጠዋል ፡፡ ነገር ግን ጐጃም አዘነ ምንም አይነት የሚያስተላልፈው ትእምርት የሌለ ሲሆን፣ አልባሳቱን የሚጠቀሙበት ዋነኛ ምክንያት አልባሳቱ የሚሰጠውን ጥቅምና አገልግሎት መሰረት በማድረግ መሆኑን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ስለዚህ የጎጃም ማህበረሰብ ጐጃም አዘነ በመባል የሚጠራውን የአልባሳት አይነት ልክ እንደሌሎች የአገራችን ህዝቦች ሁሉ በስራ ወቅት የሚጠቀምበት የስራ አልባሳት እንጅ የማህበረሰቡን ባህል፣ ማንነት መወከል የሚችል አልባሳት አለመሆኑን ለመግለፅና መስተካከል እንዳለበት ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

ከዚህ አኳያም ዩኒቨርስቲዎች ፣የባህል አዋቂዎች ፣ምሁራንና የባህል ተቆርቋሪዎች ትክክለኛውን የጎጃምን ህዝብ ባህላዊ አለባበስ በማጥናት ፣በማሳየትና በማስተዋወቅ የድርሻችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን ።

የጎጃም ተወላጆች ፣የጎጃም ባህላዊ ዘፈን አዘጋጆች እና ሙዚቀኞች ፣ታዋቂ ግለሰቦች የጎጃምን ማህበረሰብ በጎጃም አዘነ መወከላችሁን ወይም መግለፃችሁን እንድታቆሙ በጥብቅ እያሳሰብን ትክክለኛውን የጎጃም ማህበረሰብ ባህላዊ አልባሳት እንድትጠቀሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን ።

"ጎጃም ነጭ ለባሽ ነጭ አምራች ነዉ !"

የምስራቅ ጎጃም ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ

ከጎጃም ባህላዊ አልባሳት ጥናት
የተወሰደ

22/09/2025

ጎጃም ፈለገ ግዮን

ጎጃም የራሱ የሆነ የረዥም ጊዜ ታሪክ ያለው ሲሆን ስሙም በብዙ መንገድ ይተረጎማል። “ጎጃም” የሚለው ስም “ጎጇም”፣ “ቤታም”፣ “ቤተኛ” እና “የሥልጣኔ ምንጭ” ተብሎ ይተረጎማል።

ይህ ትርጉም የጎጃምን የጥንት ሥልጣኔ እና የበለፀገ ባህላዊ አኗኗር ያመለክታል። በጥንት ዘመን የጎጃም ስም ፈለገ-ግዮን እንደነበር የሚታመን ሲሆን ይህም ከጣና ሐይቅ ጋር ያለውን ቅርበት እና ጎጃም መነሻውን ካደረገው በቀጠናው ከሚገኙት ታላላቅ ወንዞች መካከል አንዱ የሆነውን ዓባይ ወንዝን ያመለክታል።

የዓባይን ወንዝ ተከትለው በኢትዮጵያ የስልጣኔ መነሻ ከሆኑት ግዮናዊያው ታሪክ ተመራማሪ የሆነው የግሪክ ታሪክ ፀሐፊው ሄሮዱተስ ደግሞ ጎጃምን “የአምላክ ምድር” እና “የደጎች እና የበቁ ቅዱሳን መኖሪያ” በማለት ገልጾታል። ይህ አባባል ጎጃም ለሃይማኖታዊ እና መንፈሳዊ ህይወት ከፍተኛ ቦታ የሚሰጥ ምድር መሆኑን ያሳያል።

ጎጃም እንደሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ሁሉ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ከፍተኛ ቦታ ይሰጣሉል። በብዙ ገዳማትና አድባራት የታወቀ ሲሆን ከነዚህም መካከል ከዓለም ቅርስነት አንዱ የሆነው እና ታቦተ ጽዮን ለረዥም ጊዜ ተቀምጣበታለች የሚባለው ጣና ቂርቆስ፣ ደብረ ወርቅ፣ መርጡለማርያም፣ ዳጋ እስጢፋኖስ እና ሌሎችም ገዳማት ይገኙበታል። እነዚህ ቦታዎች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ዋና ማዕከሎች ናቸው።

ከሃይማኖታዊ ህይወት በተጨማሪ የጎጃም ባህል በራሱ ለየት ያለ ቦታ አለው። የጎጃም ህዝብ ለባህላዊ ጭፈራ፣ ለባህል አልባሳት፣ ለሙዚቃ እና ለሥነ-ጽሁፍ ትልቅ ቦታ ይሰጣል። የጎጃም ባህላዊ ጭፈራዎች እንደ እስክስታ እና ትዝታ ልዩ በሆኑ እንቅስቃሴዎችና ውበት ይታወቃሉ። ባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያዎች እንደ ክራር፣ መሰንቆ እና ዋሽንት የጎጃም የባህል ህይወት ዋና አካል ናቸው። የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትናዊ አለባበስ፣ አጊያጊያጥ፣ አመጋገብና የምግብ ዝግጅት፣ የሀዘንና ደስታ ረገላለጽ፣ የሰረሰግና የጋብቻ ባሕል፣ ነባርና ጥንታዊ የእርሻ ባሕል ያለው አምራች፣ አራሽ፣ ቀዳሽና አርበኛ እንዲሁም የራሱ ስርወመንግስትና መናገሻ ያለው የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት ህዝብ ነው።

ጎጃም በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የራሱ የፖለቲካዊ ሚና የነበረው ነገድ ነው። ከጥንት ነገስታት አንስቶ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በብዙ መልኩ አብይ ሚና ተጫውቷል። ለምሳሌ ያህል በታላቁ አድዋ ጦርነት ላይ ጉልህ ሚና የተጫወቱት አርበኞችና መሪዎች ከጎጃም እንደነበሩ ይነገራል። ይህም የጎጃም ህዝብ ለአገሩ ነጻነት እና ለሀገር ፍቅር ያለው ትልቅ ቦታ ያመለክታል።

በጎጃም የሥነ-ጽሁፍ ታሪክ ለሃይማኖታዊ መጻህፍት፣ ቅኔ፣ ግጥሞች እና ምሳሌያዊ አነጋገሮች ትልቅ ቦታ ተሰጥቷል። በብዙ የኢትዮጵያ ታሪክ ፀሐፊዎች መሠረት የጎጃም የሊቃውንት ትምህርት ቤት በሰፊው የሚታወቅ ነው። በዚህም ብዙ ታላላቅ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት እንደ አለቃ አያሌው ታምሩ፣ ደብተራ ፍቅረሥላሴ ወርቅነህ እና ሌሎችም ተምረዋል። እነዚህም የጎጃም ባህላዊ እና መንፈሳዊ ህይወት ለኢትዮጵያ ታሪክ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ያሳያሉ።

ጎጃም የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ቀጠና ሆኖ የራሱ ባህል፣ ሃይማኖትና ታሪክ ያለው ህዝብ ነው። ይህ ታሪካዊ ቀጠና ለኢትዮጵያ የፖለቲካ እና የባህል ታሪክ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን ለወደፊትም በዘርፉ ትልቅ ቦታ ይዞ ይቀጥላል።
አሁን ላይ ከውስጥም ይሁን ከውጭ የዓባይን ወንዝ የፖለቲካ ሃይል አስቀድመው የሚፈሩ ወገኖች ለዘመናት በእድገቱ እና ስልጣኔው እንዲሁም የመልማትና የማደግ ፍላጎት ከፍተኛ ጫና እየተደረገበት የሚገኝ ነው።

ለም መሬት፣ ማራኪ ተራራና ሸንተረር፣ በርካታ ወንዞች፣ ሰፊ ውሃማ አካል፣ የሚለማ መሬትና መስኖ ያለው ቀጠና ነው። ከበጌምድር ተዋስኖ እስከ ኢሊባቡር ወለጋ/ቢዛሞ፣ ከሱዳን መተከልና ሽናሻን ማንነቶች የቀፈ ሰፊ የግዛት ወሰን አለው።

Bahirdar City Communications
Hello Gojjam,Bahir Dar
Henoke T Yeshetlla
Tkt Eth

አደይ አበባ
15/09/2025

አደይ አበባ

08/09/2025

ቋግሜ፣ ጳጉሜ!

ከሴ ጥሩ መዓዛ ያለው የተክል ዓይነት ነው፡፡ ተክሉ ወይንጠጅ ቀለም ያለው አበባ ያብባል፡፡ በጎጃም በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች የከሴ ማበብ እና ለአጨዳ መድረስ እንደ አዲስ ዘመን ብስራት ይታ...
03/09/2025

ከሴ ጥሩ መዓዛ ያለው የተክል ዓይነት ነው፡፡ ተክሉ ወይንጠጅ ቀለም ያለው አበባ ያብባል፡፡ በጎጃም በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች የከሴ ማበብ እና ለአጨዳ መድረስ እንደ አዲስ ዘመን ብስራት ይታያል፡፡ ልጆች እና እናቶች በፍልሰታ ፆም ወቅት ከሴን መሬት ላይ በመጎዝጎዝ ይተኙበታል፡፡ ይሄም ከመንፈሳዊ ትርጓሜው ባሻገር ተፈጥሯዊ የጤና መጠበቂያ መንገድ እንደሆነ ይታመናል፡፡

በእነማይ፣ እናርጅ እናውጋ እና ሸበል በረንታ ወረዳዎች ደግሞ ከነሐሴ 16 ጀምሮ ይሄን ተክል የማጨድ እና ለወዳጅ ዘመድ ስጦታ የማበርከት በዓል ይከበራል፡፡ በዓሉ የከሴ አጨዳ በዓል የሚባል ሲሆን ቀደም ብሎ ከሚከበረው የአሸንድዬ በዓል እና ቀጥሎ ከሚመጣው የእንግጫ ነቀላ በዓል ጋር ተቀላቅሎ የሚከበር ነው፡፡

ከሴ በእናንተ አካባቢ ምን ተብሎ ይጠራል?


©
Visit Amhara

በአረንጓዴው የጎጃም ምድር ነጭ የለበሱ ልጃገረዶች እና ታዳጊዎች ድንቅ ዝማሬ እያሰሙ የሚታበት የእንግጫ ነቀላ በዓል እየደረሰ ነው፡፡ የአዲስ ዓመት መምጣት ብስራት ከሆኑ የድንቅ ምድር ድንቅ...
27/08/2025

በአረንጓዴው የጎጃም ምድር ነጭ የለበሱ ልጃገረዶች እና ታዳጊዎች ድንቅ ዝማሬ እያሰሙ የሚታበት የእንግጫ ነቀላ በዓል እየደረሰ ነው፡፡ የአዲስ ዓመት መምጣት ብስራት ከሆኑ የድንቅ ምድር ድንቅ ክብረ በዓላት አንዱ የሆነው እንግጫ ነቀላ በጎጃም በሚገኙ በርካታ ወረዳዎች በልጃገረዶችና ታዳጊዎች በናፍቆት እየተጠበቀ የሚከበር ተወዳጅ በዓል ነው፡፡

የእንግጫ ነቀላ በዓል መከበር የሚጀምረው ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት በአንዳንድ የጎጃም ወረዳዎች በዓሉ ከአሸንድዬ እና ከከሴ አጨዳ በዓላት ጋር በጥምረት ሲከበር ይቆያል፡፡ ነሐሴ አልፎ ጳጉሜን እና መስከረም ሲደርሱ ደግሞ የእንግጫ ነቀላ በዓል ድባብ እና ድምቀት ምልዑ ሆኖ በምድሪቱ ላይ ይታያል፡፡

የእንግጫ ነቀላ በዓል መነሻ ምክንያት እንደሆኑ ከሚታመኑ መላምቶች አንዱ ሀይማኖት ነው፡፡ መላምቱ የበዓሉን ጅማሮ ወደ ኖህ ዘመን የሚወስደው ሲሆን በዘመኑ የነበረው የጥፋት ውሃ መጉደሉን ለማብሰር የተላከችው እርግብ በአፏ ለምለም ቅጠል(ቄጠማ) ይዛ ከመምጣቷ ጋር ያገናኘዋል፡፡ ምሳሌነቱንም ለጨዋታው የሚወጡ ልጃገረዶች ነጭ መልበሰቸውን ከእርግቧ ነጭ መልክ፣ እንግጫ የሚባለውን የሳር ዘር ነቅለው በእጃቸው መያዛቸውን ከእርግቧ ለጥፋት ውሃ መጉደል ምልክት ይሆን ዘንድ አረንጓዴ ቄጤማ በአፏ ይዛ ከመምጣቷ ጋር፣ የክረምቱን ማለፍ እና የአዲስ ዘመን መምጣትን ማብሰራቸው ከኖህ የጥፋት ውሃ በኋላ ከነበረውን የምስራች እና ተስፋ ጋር ያዛምዱታል፡፡

በዚህ ምክንያት እንግጫ ነቀላ የአዲስ ዘመን መምጣትን አብሳሪ በዓል ሆኖ እስከ ዛሬ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ ልጃገረዶች ልክ እንደ እርግቧ ነጭ ለብሰው የውኃውን መጉደል፣ የክረምቱ ጨለማ ማለፍን እና የጋራ ሸንተረሩ መለምለምና ማበብን ለማየት ወደ መስክ በመውጣት እንግጫ ነቅለው እና በአደይ አበባ አስጊጠው ወደ ዘመድ አዝማድ እና አብያተ ክርስቲያናት እየሄዱ “አዲስ ዓመት ገብቷል፤ ክረምቱ አልፏል፤ እንኳን አደረሳችሁ” እያሉ የምስራች ስጦታ ያበረክታሉ፡፡

እንግጫችን ደነፋ፣
ጋሻዉን ደፋ . . . .

እንግጫችን የወሩ፣
የቦረቦሩ . . . .

የቅዱስ ዮሐንስ፣ የዓመቱ የዓመቱ
ስደድልኝ ድሪ፣ ከነቀለበቱ . . .

እንግጫ ጎንጉኜ፣ በአደይ በሶሪት
እንቁጣጣሽ ብዬ፣ ቤቱ ላክሁለት . . .


8 ቀናት ይቀሩታል
Visit Amhara

 #የእንግጫ ነቀላ ክዋኔ  #ለጎጃም ልጃገረዶች የነፃነት ቀን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስር የሚገኘው የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል  በአዘጋጀው የአማረኛ መዝገበ ቃላት   #እን...
21/08/2025

#የእንግጫ ነቀላ ክዋኔ #ለጎጃም ልጃገረዶች የነፃነት ቀን

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስር የሚገኘው የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል በአዘጋጀው የአማረኛ መዝገበ ቃላት #እንግጫ ' የዘመን መለወጫ ጊዜ ልጃገረዶች ከአበባ ጋር እየጎነጎኑ የመልካም ምኞት ስጦታ የሚያደረረጉበት የሳር አይነት በማለት ይገልፀዋል። #በአበረአረፋይኔ በተዘጋጀው ጥንታዊው የጎጃም ታሪክ መፅሐፍ እንግጫ ማለት ሲበቅል ቢጫ አይነት ቀለም ሲኖረው እያደገ ሲሄድ ወደ አረንጓዴነት የሚቀየር የሳር አይነት ሆኖ ልጃገረዶች በጷግሜ መጨረሻ በህብረት በመንቀል ለመልካም ምኞት የሚጎነጉኑት በማለት ይተረጉመዋል ።
የጎጃም ልጃገረዶች ከፆመ/ፍስለታ ማርያም ጀምሮ እንግጫ የበቀለበትን ቦታ በመለየት እስከሚዘረዝር ሲንከባከቡት ይከርሙና ፍሬ መያዝ ሲጀምር በጷግሜ የመጨረሻ ቀን በህብረትና በጭዋታ ሙሉ ቀን ሲነቅሉ ይውላሉ።በዚህ ቀን ልጃገረዶቹ የቻሉትን በህብረትና በዜማ የነቀሉትን እንግጫ ከሶሪት አበባና አደይ አበባ ጋር ይጎነጉኑታል። በዚሁ ቀን ያላገቡ ወንዶችም የከንፈር ወዳጅ ለማጨት ቃልኪዳን ለማሰር ልጃገረዶች በዜማ እንግጫ ወደሚነቅሉበት ቦታ በህብረት ይሄዳሉ። ልጃገረዶችም የከጀሉትን ወንድ በስርቆት እየተመለከቱ በስንኝ ቋጠሮ በዜማ ይጫወታሉ።
የእንግጬ ነቀላ ቀን ልጃገረዶች ከወገባቸው ላይ ጥልፍ የሌለው በልካቸው የተሰራ #ሸማቀሚስ ለብሰው ወገባቸውን #በምሪ ሸብ አርገው፣ ክብ ጋሜአቸውን ተከርክመው ጠዋት የወጡ ማታ የሚመለሱበትና #በነፃነትናበህብረት የሚዘምሩበት የእኩልነት ቀናቸው ነው።

የጳጉሜ መጨረሻ ቀን በዚህ መልኩ ሲጠናቀቅ በማግስቱ መስከረም 1 ቀን በሶሪትና አደይ አበባ የተዋበውን የእንግጫ ጉንጉን በአንገታቸው አጥልቀው ከደሮ ጩኸት ቀድመው በመነሳት በየቤቱ እየዞረ እንኳን ከዘመን ዘመን አሸጋገራችሁ እያሉ በጋራ ዜማና እልልታ የሰፈሩን ድባብ ይቀይራሉ። በመቀጠልም በእልልታ እየዘመሩ ወደ ቤተክርስቲያን በህብረት ሄደው የተጎነጎነውን እንግጫ አስረው ወደ ሰፈር በመመለስ በእያንዳንዱ አባወራ ቤት በእልልታ በመግባት የእንግጫ ጉንጉን ያስራሉ። በዚህ ጊዜ እናቶች በሆታ ይቀበሏቸዋል፣ ጋሜያቸውንና ሹርባቸውን ቅቤ ይቀቧቸዋል፣ አባቶች ይመርቋቸዋል።

Bahirdar Times

ባሕርዳር ከተማ የተመሰረተችው በ13ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ ሲሆን፣ አሁን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በሚገኝበት ቦታ ላይ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ከታነጸ በኋላ እንደሆነ ይገመታል።...
16/08/2025

ባሕርዳር ከተማ

የተመሰረተችው በ13ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ ሲሆን፣ አሁን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በሚገኝበት ቦታ ላይ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ከታነጸ በኋላ እንደሆነ ይገመታል።
በ13ኛው ክፍለ ዘመን ንጉሡ ይኩኖ አምላክ ሲገዙ ከተማዋ በጣና ሐይቅ አቅራቢያ በመሆኗ ባሕር ዳር (በባሕር አጠገብ ያለች) የሚለውን ስም እንዳገኘችም ይነገራል።

09/08/2025

አሁንኑ 25k መድረስ አለበት

Melkamu Teshome Alemayehu Bahirdar Times Gashaye Getahun Gojjam press-ጎጃም ፕረስ Visit Amhara Ghion press

28/11/2024

ጮቄ፣ ጎጃም ምድረ ገነት
facebook.com/share/p/6EQVikgaeLhUMrmE/

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Visit Gojjam posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Visit Gojjam:

Share

https://g.co/kgs/4EQVoL

The Latest News on Ethiopian Teff around the World

he Latest News on Ethiopian Teff around the World

Hollywood's new favorite food revealed:Victoria Beckham and Gwyneth Pal row are fans of Teff, an iron-rich Ethiopian grain

From kale chips to wheat grass shots, the list of celebrity food crazes is a long one. Now there's a new source of sustenance to add to the list - an Ethiopian cereal named teff. Love dby Gwyneth Pal trow and Victoria Beckham, the grain, which is a staple food inits home country Ethiopia, is packed with protein, calcium and iron. It does, however, come with a Hollywood style price tag - retailing at an eye-watering £7 for a 400g bag of flour.