Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን Amhara Media Corporation Strives for the Betterment of the Life of the People.
(1334)

የአሚኮን ሞባይል መተግበሪያ ፕሌይ ስቶር ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
���
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.AMECO.AMECOapp

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት https://www.ameco.et
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J

አሚኮ ዲጂታል ሚዲያ
+251582265018

ገበያ ልማትና ደንበኞች አገልግሎት
0941272206

በኩር ጋዜጣ
0582265018

አማራ ራዲዮ
0583209919

አማራ ባሕር ዳር ኤፍ ኤም 96.9
0583208314

16/10/2025

ከመካከለኛነት ወደ ተዓምራዊ ታላቅነት የመሸጋገሪያ ሳይንስና ጥበብ

16/10/2025

ከማኅበረሰብ የሚሰወር ወንጀል የለም

16/10/2025

በርካታ ስራዎችን በራስ አቅም የገነቡ የዳንሻ ክንዶች የልማት ተጋድሎ በአሚኮ ዘጋቢ ‎‎ #አሚኮ #ዜና #...

"በአዲስ አበባ የሚታየው ሁለንተናዊ ለውጥ ያለታማኝ ግብር ከፋዮች ሊሳካ አይችልም" አቶ አገኘሁ ተሻገር።አዲስ አበባ: ጥቅምት 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ለታ...
16/10/2025

"በአዲስ አበባ የሚታየው ሁለንተናዊ ለውጥ ያለታማኝ ግብር ከፋዮች ሊሳካ አይችልም" አቶ አገኘሁ ተሻገር።

አዲስ አበባ: ጥቅምት 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ለታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና መርሐ ግብር አካሂዷል።

በእውቅና መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር መንግሥት ኢትዮጵያን መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን እየተገበረ መኾኑን ገልጸዋል።

ለዚህም የገቢ ሠብሣቢ ተቋማት ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ሃብት በቂ ገቢ ለመሠብሠብ እና ሀገራዊ የልማት ዕቅዶችን ለማሳካት እየሠሩ መኾኑን አስረድተዋል።

የፌዴራል መንግሥትም ኾነ የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ገቢ የመሠብሠብ አቅማቸው እያደገ ስለመኾኑም ጠቁመዋል።

ገቢ በሚገባ በመሠብሠባቸውም የማኅበረሰቡን ፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነት እያረጋገጡ ይገኛሉ ብለዋል።

የአዲስ አበባን አዳጊ ፍላጎት በበቂ ደረጃ ለማሟላት የገቢ ሠብሣቢ ተቋማት እና ግብር ከፋዮች ይበልጥ ተቀናጅተው መሥራት እና ገቢ የመሠብሠብ አቅምን ማሳደግ አስፈላጊ መኾኑንም ጠቅሰዋል።

በገቢ ዘርፍ ሪፎርሙ የታክስ አሠባሠብ እና አሥተዳደር ሥርዓትን በማሻሻል የሚሠበሠበው ገቢ እያደገ መምጣቱን ገልጸው ታማኝ ግብር ከፋዮች ለሀገር እና ለከተማዋ ልማት ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመሥግነዋል።

በአዲስ አበባ የሚታየው ሁለንተናዊ ለውጥ ያለታማኝ ግብር ከፋዮች ይሳካል ተብሎ እንደማይታሰብም ነው የጠቆሙት። ግብር ከፋዮች አዲስ አበባ ከተማ እንደገና እንድትሠራ ማድረጋቸውንም ጠቅሰዋል።

የመዲናዋ ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በገቢ ላይ አበክሮ መሥራት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የግብር ከፋዩን መሠረታዊ አገልግሎት እና የመልካም አሥተዳደር ጥያቄዎች በየጊዜው እየፈተሹ መፍትሄ መስጠትን የትኩረት ማዕከል ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ዘጋቢ፦ ኢብራሒም ሙሐመድ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

“አንድን ተቋም በራሱ ልዩ የሚያደርገው የሚሰጠው ተልዕኮ ነው” አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ.ር)ባሕር ዳር: ጥቅምት 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በምክትል ርእሰ መሥተዳደር ማዕረግ የከተሞች ዘርፍ አ...
16/10/2025

“አንድን ተቋም በራሱ ልዩ የሚያደርገው የሚሰጠው ተልዕኮ ነው” አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ.ር)

ባሕር ዳር: ጥቅምት 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በምክትል ርእሰ መሥተዳደር ማዕረግ የከተሞች ዘርፍ አስተባባሪ እና የከተማ ልማት ቢሮ ኀላፊ አሕመዲን ሙሐመድ ዛሬ በጎንደር ከተማ አዘዞ ጠዳ ክፍለ ከተማ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም በክፍለ ከተማው የሚገኘው የአባሳሙኤል ቀበሌ የአገልግሎት አሰጣጥ ዘርፎች ውጤታማነትን ተመልክተዋል።

የመደመር መንግሥት ተልዕኮን የሚያሳካ ቁመና መገንባት ውጤት ተኮር ከመኾን ጋር የተቆራኘ እንደኾንም ዶክተር አሕመዲን ገልጸዋል።

የጎበኟቸው ኢንዱስትሪዎች በሙሉ አቅማቸው ማምረት እንዲችሉ ተደርገው የተሠሩ ስለመኾናቸው መመልከታቸውን ተናግረዋል።

በምልከታቸውም ቀበሌ ለሕዝብ የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት ከከተማው ከሚመለከታቸው ቁልፍ ባለድርሻ አካላት ጋር የተጀመሩ ሥራዎች መኖራቸውን ስለማረጋገጣቸው ነው ያብራሩት።

የኢንዱስትሪዎች ምርታማነት እንዲያድግ አገልግሎትን በየደረጃው ዲጂታላይዝ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።

የተገልጋይ እርካታ እንዲጨምርም ፈጣን የኾኑ እና ፈጠራ የታከለባቸው መፍትሄዎችን መፈለግ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

በተለያዩ መስኮች የተገኙ ስኬቶች እንዲሁም አዳዲስ የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ ሥራዎች ውጤታማ እንዲኾኑ እና ለሁለንተናዊ እምርታ የራሳቸው አበርክቶ እንዲኖራቸው አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

16/10/2025

በአንድነት ተዓምር እንሠራለን!

16/10/2025

አንድነት ለብሔራዊ ጥቅማችን

"የአጠቃቀም ክፍተት ትራንስፎርሜሽኑን ለማፋጠን ተግዳሮት ኾኖ ቆይቷል" ፍሬሕይዎት ታምሩአዲስ አበባ: ጥቅምት 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮ ቴሌኮም ሁሉንም የማኅበረሰብ ክፍል ተጠቃሚ ማድ...
16/10/2025

"የአጠቃቀም ክፍተት ትራንስፎርሜሽኑን ለማፋጠን ተግዳሮት ኾኖ ቆይቷል" ፍሬሕይዎት ታምሩ

አዲስ አበባ: ጥቅምት 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮ ቴሌኮም ሁሉንም የማኅበረሰብ ክፍል ተጠቃሚ ማድረግ የሚችል "ዘ ኔክሰስ" የተሰኘ ዲቫይስን አስተዋውቋል።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ፍሬሕይዎት ታምሩ ኢትዮ ቴሌኮም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እና አካታች ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት እየሠራ መኾኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የ4ጂ እና 5ጂ ኔትወርኮች በስፋት ቢዘረጉም አብዛኛው ዜጋ የዲጂታል ሥነ ምኅዳሩ የፈጠረውን መልካም ዕድሎች በአግባቡ መጠቀም ሳይችል አሁንም መሠረታዊ የ2ጂ እና 3ጂ ስልክ አገልግሎቶችን በመጠቀም ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ተጠቃሚዎች የኔትወርክ ሽፋን ያለበት አካባቢ ቢኖሩም የስማርት ስልኮችን መግዛት ባለመቻላቸው እና "የአጠቃቀም ክፍተት በመኖሩ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽኑን ለማፋጠን ተግዳሮት ኾኖ ቆይቷል" ብለዋል።

አካታች እና ተደራሽ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚያስችሉ እንደ የዲጂታል ክፍያ፣ ኢ-ትምህርት፣ የጤና መተግበሪያዎች፣ የግብርና ፕላትፎርሞች እና ኢ-ገቨርንመንት የመሳሰሉ ቁልፍ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ኢትዮ ቴሌኮም ያስተዋወቀው "ዘ ኔክሰስ" ዲቫይስ ዕድል ይፈጥራል ነው ያሉት።

ዋና ሥራ አሥፈጻሚዋ ዘ ኔክሰስ ክላውድ ወርክስፔስ ሶሊዩሽን የዳታ ደኅንነትን አስተማማኝ በማድረግ ወጭ ቆጣቢ፣ በተጠቀምንበት መጠን ለመክፈል የሚያስችል፣ በራሱ ጊዜ ማዘመን እና መረጃዎችን ማስቀመጥ የሚያስችሉ ጥቅሞች ያሉት እንደኾነ ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱም 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዲቫይሶችን ለማኅበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ገልጸዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም ዛሬ ያስተዋወቀው ዘ ኔክሰስ ዲቫይስ ሁሉንም የማኅበረሰብ ክፍል ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችሉ የሞባይል ቀፎ፣ ታብሌት፣ ላፕቶፕ እና ወርክስቴሽኖችን ያካተተ ነው ተብሏል።

ዘጋቢ:- ቤተልሔም ሰለሞን

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

16/10/2025

ወላጅ እና ትምህርት

ቅዳሜ ምሽት 1:30 ላይ በአሚኮ አስኳላ ይጠብቁን።

ዛሬ ምሽት በትዕይንተ ዜና ይጠብቁንአሚኮ አዲስ አበባ ስቱዲዮ
16/10/2025

ዛሬ ምሽት በትዕይንተ ዜና ይጠብቁን
አሚኮ አዲስ አበባ ስቱዲዮ

16/10/2025

ጥቅምት 06/2018 ዓ.ም #ዜና #አሚኮ

16/10/2025

Address

Bahir Dar, Ethiopia P. O. BOX 955
Bahir Dar
6000

Website

https://www.ameco.et/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን:

Share