Mohammed Getahun Abate

Mohammed Getahun Abate Amhara Region, Bahir Dar, Ethiopia 🇪🇹🇪🇹 YouTube:
https://youtube.com/channel/UCL56NtLhE550GdP7tNe51AQ

21/04/2025

በአማራ ክልል ከ25 ሺህ ቶን በላይ የማር ምርት ተገኝቷል።

ባሕር ዳር:ሚያዝያ 13/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በምሥራቅ ጎጃም ዞን የአዋበል ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ገድፍ ይታይህ በያዝነው በጀት ዓመት ከ10 የሽግግር ዘመናዊ ቀፎ ከ110 ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

የንብ ማነብ ሥራቸውን ከግብርና ሥራቸው ጎን ለጎን በመሥራታቸው ተጨማሪ ገቢ ማግኘት እንደቻሉ እና ኑሯቸውንም መለወጥ እንደቻሉ አርሶ አደሩ ለአሚኮ ገልጸዋል።

በዞኑ ከ2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት ለገበያ መቅረቡንም የዞኑ የእንሰሳት እና ዓሳ ሃብት ልማት ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

የጽሕፈት ቤቱ የንብ ሃብት ባለሙያ ስማቸው ደምሴ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እየለማ ያለው ደን ንብ በማነብ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።

በዚህም በያዝነው በጀት ዓመት ከ2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ማር ለማምረት ታቅዶ እስካሁን ከ2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ማምረት ተችሏል።

የአማራ ክልል የእንስሳት እና አሳ ሃብት ልማት ጽሕፈት ቤት በ2017 በጀት ዓመት 31 ሺህ 531 ቶን ማር ለማምረት አቅዶ ወደ ሥራ ገብቷል።

ክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥም 25 ሺህ 857 ቶን ማር ማምረት መቻሉ ነው የተገለጸው። ይህም ከዓመታዊ ዕቅዱ 82 በመቶ የሚኾነውን ይሸፍናል።

የጽሕፈት ቤቱ የንብ እና ሀር ልማት ባለሙያ ሙሐመድ ጌታሁን እንደገለጹት የተገኘው የማር ምርት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከግማሽ ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ብልጫ አሳይቷል።

ባለፈው ዓመት በዚሁ ወቅት የተገኘው የማር ምርት 22 ሺህ ቶን እንደነበርም ባለሙያው አስታውሰዋል።

የማር ምርት በዓመት ሁለት ጊዜ እንደሚመረት የገለጹት ባለሙያው ሁለተኛው የምርት ሥብሠባ ሲጠናቀቅ በዓመት ከታቀደው በላይ ምርት ይሠበሠባል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል።

ይህ የተሻለ ውጤት የተገኘው 35 ሺህ 179 ባሕላዊ ቀፎዎችን ወደ ዘመናዊ ቀፎዎች በመቀየሩ፣ በሽግግር ቀፎ 29 ሺህ 171 ኅብረ ንቦችን የማዛወር ሥራ በመሠራቱ እና በፊት ከነበረው የኅብረ ንብ ብዛት 155 ሺህ የሚኾን በከፈላ የተገኘ አዲስ ኅብረ ንብ ቁጥር በመጨመሩ እንደኾነ ተገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪ የወቅቱ የዝናብ ስርጭት ምቹ መኾን፣ የደኖች መስፋፋት እና በመስኖ ልማቱ ንቦች የሚቀስሟቸው የአበባ ዛፎች በስፋት መኖር ለምርቱ ማደግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳበረከተም ባለሙያው ተናግረዋል።

ጽሕፈት ቤቱ ለንብ አናቢዎች ሙያዊ ምክረ ሃሳብ በመስጠት፣ አንጻራዊ ሰላም ባለባቸው አካባቢዎች በመገኘት ድጋፍ በማድረግ፣ በተለያዩ መድረኮች እና ፕሮጀክቶች ሥልጠናዎችን በመስጠት እና ጥራቱን የጠበቀ ዘመናዊ ቀፎ ገዝተው እንዲጠቀሙ የማመቻቸት ሥራ በመሥራት የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረጉንም አብራርተዋል።

በቀጣይ ሦስት ወራት ውስጥም ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ለአምራች አርሶ አደሮች ሙያዊ እገዛ እየተደረገ መኾኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Celebrating my 11th  year on Facebook. Thank you all my friends for your continues friendship.🙏🤗🎉
15/04/2025

Celebrating my 11th year on Facebook. Thank you all my friends for your continues friendship.🙏🤗🎉

03/02/2025
 በ1989 ዓ.ም የ1 ሊትር ናፍታ ዋጋ 2 ብር ሲሆን በወቅቱ 1 የአሜሪካ ዶላር በ2 ብር ከ41 ሳንቲም የኢትዮጵያ ብር ይመነዘር ነበር። ከ28 ዓመት በኋላ በ2017 ዓ.ም የ1 ሊትር ናፍታ ...
13/01/2025


በ1989 ዓ.ም የ1 ሊትር ናፍታ ዋጋ 2 ብር ሲሆን በወቅቱ 1 የአሜሪካ ዶላር በ2 ብር ከ41 ሳንቲም የኢትዮጵያ ብር ይመነዘር ነበር። ከ28 ዓመት በኋላ በ2017 ዓ.ም የ1 ሊትር ናፍታ እና የ1 ዶላር ዋጋ ከ100 ብር በላይ ተሻግሯል።

16/11/2024
12/10/2024

For FUN 😂

የአባይ ድልድይ፣ ባህር ዳርAbay Bridge  Dar
30/09/2024

የአባይ ድልድይ፣ ባህር ዳር
Abay Bridge Dar

21/09/2024

ሐሰን ሼህ ማህሙድ እንዴት ከዩክሬኑ መሪ ዘለንስኪ መማር አቃታቸው?

Mohammed Getahun

Marathon Sports
19/09/2024

Marathon Sports

🎉 Facebook recognized me as a top rising creator this week!   Thanks my beloved friends!
16/09/2024

🎉 Facebook recognized me as a top rising creator this week! Thanks my beloved friends!

Address

Bahir Dar
6000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mohammed Getahun Abate posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Mohammed Getahun Abate:

Share