ANRS Justice Bureau የአብክመ ፍትሕ ቢሮ

ANRS Justice Bureau የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ለህግ፣ ፍትሕና ርትዕ እንሰራለን!!! ANRS Justice Bureau Strives for upholding rule of law, justice and equity!

ANRS Justice Bereau an organization that works towards enhancing justice, good governance and democratic system of the amhara region.

24/08/2025

በክልሉ ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን ለመከላከል በቅንጅት በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተመዝግቧል

ባህር ዳር፤ነሐሴ 18/2017(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በ2017 በጀት ዓመት ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን ለመከላከል በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገቡ ተገለጸ።

በአማራ ክልል የተቋቋመው የፀረ ኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድ ቁጥጥር ጥምር ግብረ ኃይል የወንጀል ጉዳዮች ክትትል ቴክኒክ ኮሚቴ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ ተካሂዷል።

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክ ኮሚቴው ሰብሳቢ አያሌው አባተ (ዶ/ር) በመደረኩ እንደገለጹት በክልሉ ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ግብረ ኃይል ተቋቁሞ እየተሰራ ነው።

ግብረ ሀይሉ ከፌደራልና ከክልሉ የተውጣጡ አካላት እንዳሉበት ገልጸው፣ በ2017 በጀት ዓመት ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን በመከላከልና በመቆጣጠር በኩል ትርጉም ያለው ሥራ ተሰርቷል ብለዋል።

ይህም በኢኮኖሚ ወንጀል ዘርፍ ሊፈፀሙ የታቀዱ ወንጀሎችን ቀድሞ ለመከላከልና ምርመራን በተገቢው መንገድ በመምራት ለቀረቡ የወንጀል ክሶች ውሳኔ ለመስጠት ማስቻሉንም ጠቁመዋል።

ጥምር ግብረ ኃይሉ ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ባከናወናቸው ተግባራት ውጤት መመዝገቡንም አያሌው (ዶ/ር) አስታውቀዋል።

በቢሮው የኢኮኖሚ ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አሻግሬ ባቀረቡት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በበጀት ዓመቱ ለጤና ጎጂ የሆኑና ከ121 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ምግብና ምግብ ነክ ዕቃዎች እንዲወገዱ መደረጉን ገልጸዋል።

ለክልሉ ዐቃቤ ህግ፣ ለፌዴራል ፍትህና ገቢዎች ሚኒስቴር ዐቃቤ ህግ ተልከው ክስ ከተመሰረተባቸው 998 መዝገቦች ለ311ዱ የፍርድ ውሳኔ መሰጠቱንም ተናግረዋል።

በተጨማሪም በተጭበረበረ መንገድ መንግስት እንዲከፍል የተጠየቀ ከ121 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ጥምር ግብረ ኃይሉ በቅንጅት ባከናወነው ስራ ለማዳን ተችሏል ብለዋል።

የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ፈንታው ፈጠነ በበኩላቸው እንዳሉት ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን ለመከላከል በተደረገ የተቀናጀ ጥረት 104 ሺህ 167 ሊትር ነዳጅ ተይዟል።

እንዲሁም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የቁም እንስሳት እና የኤክስፖርት ምርቶች በህገወጥ መንገድ ወደጎረቤት ሃገር ሊሻገሩ ሲል በጥምር ግብር ኃይሉ ክትትል መያዛቸውን ጠቁመዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም ህገወጥነትን ለመከላከል ቅንጅታዊ አሰራር ይበልጥ የሚጠናከርበት ነው ሲሉም አመልክተዋል።

ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን ለመከላከል ከሌሎች የፌዴራል የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ምክትል ኮሚሽነር ታደሰ አያሌው ናቸው።

በመድረኩ የክልሉ ፍትህ ቢሮ፣ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ንግድና ገበያ ልማት፣ ጤና ቢሮ፣ ጉምሩክ ኮሚሽንና ገቢዎችን ጨምሮ የ13 የግብረ ኃይሉ አባል ተቋማት አመራሮች ተሳትፈዋል።

#ኢዜአ

24/08/2025
በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስን በተመለከተ የውይይት መድረክ ተካሄደየኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ጀነራል እና የተባ...
24/08/2025

በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስን በተመለከተ የውይይት መድረክ ተካሄደ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ጀነራል እና የተባበሩት መንግስታት የጸረ ህገወጥ መድሃኒት ዝውውርና የወንጀል መቆጣጠሪያ ቢሮ ጋር በመተባበር በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስን በተመለከተ የውይይት መድረክ አካሂዷል፡፡

በውይይት በመድረኩ የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የተለያዩ የስራ ክፍሎች አመራሮች የተሳተፉበት ሲሆን፣ የንብረት ማስመለስ አዋጅ ቁጥር 1364/2017 ፣ የአፈጻጸም መመሪያውንና የአሰራር ማንዋሉን ጨምሮ በወንጀል የተገኘ ንብረትን ህጋዊ አስመለስሎ ማቅረብንና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀል ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005 (የማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1387/2017ን ጨምሮ) ላይ ውይይት ተደርጉዋል፡፡

በሁሉም የህግ ማዕቀፎች ላይ የህግ አርቃቂ ቡድን አባላት የውይይት መነሻ የሚሆን ገለጻ በማድረግ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በመጨረሻም በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ጀነራል እና የሙስና ወንጀል ዳይሬክቶሬት ጀነራል በጋራ ከሠሩት ሥራዎች መካከል ጥሩ ተሞክሮ የሆኑ ሥራዎች ላይ ገለጻ በማድረግ በቀጣይ በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ጀነራል ከሁሉም የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የስራ ክፍሎች ጋር ስለሚሰራበት ሁኔታ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የውይይት መድረኩ ተጠናቋል፡፡

‎ኢኮኖሚያዊ ወንጀል የፈጸሙ አካላት ጉዳያቸው ወደ ፍትሕ ቀርቦ ውሳኔ እየተሰጠ ነው፡፡‎ባሕር ዳር: ነሐሴ 18/2017 ዓ.ም የአማራ ክልል ምርትና ግብይት፣ የገበያ አረጋጊ፣ የሕገ ወጥ ንግድ...
24/08/2025

‎ኢኮኖሚያዊ ወንጀል የፈጸሙ አካላት ጉዳያቸው ወደ ፍትሕ ቀርቦ ውሳኔ እየተሰጠ ነው፡፡

ባሕር ዳር: ነሐሴ 18/2017 ዓ.ም የአማራ ክልል ምርትና ግብይት፣ የገበያ አረጋጊ፣ የሕገ ወጥ ንግድ እና ፀረ ኮንትሮባንድ ጥምር ግብረ ኀይል የወንጀል ጉዳዮች ቴክኒክ ኮሚቴ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ አካሂዷል።

የቴክኒክ ኮሚቴው የፍትሕ ቢሮ፣ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ የፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን እና ሌሎች የፌደራል እና የክልሉን ተቋማትን ያቀፈ ኮሚቴ ሲኾን በፍትሕ ቢሮ ሰብሳቢነት የሚመራው ነው፡፡

‎‌መድረኩ የቴክኒክ ኮሚቴው በ2017 በጀት ዓመት በየተቋማቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ያካተተ ሪፖርት ቀርቧል። ከነዚህም መካከል ለፈጻሚ አካላት ሥልጠና መሰጠቱ እና ወደ ተግባር መገባቱ ተነስቷል፡፡ ለማኅበረሰቡ በሕገወጥ ንግድ እና ጉዳቶቹ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራዎች መከናወኑም በሪፖርቱ ተመላክቷል።

‎በምግብና መድኃኒቶች ላይ የተደረገ ቁጥጥር፣ ሕገ ወጥ ንግድን ለመቆጣጠር በንግድ ድርጅቶች የበር ከበር ጉብኝት፣ የሕገ ወጥ ደረሰኝ ክትትልና ቁጥጥር፣ የኮንትሮባንድ ንግድ ቁጥጥር እና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች መሠራቱ ተጠቅሷል።

በ‎‌ዚህም ለጤና ጠንቅ የኾኑ የተበላሹ የምግብ ሸቀጦች፣ የታሸጉ ምግቦች እና መጠጦች ተገኝተው መወገዳቸው ተነስቷል። በክትትል እና በቁጥጥር ወቅት የተገኙ ሕገወጦች ላይ አሥተዳደራዊ እና ሕጋዊ እርምጃ መወሰዱ ተነግሯል።
‎አማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የኢኮኖሚ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክተር ሙሉጌታ አሻግሬ የቴክኒክ ኮሚቴው የ2017 በጀት ዓመት በንግዱ ማኅበረሰብ ላይ በሚደረጉ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች በሚገኙ ሕገወጥ ድርጊቶች ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል፡፡

ተበላሽተው የተገኙ 121 ሚሊዮን ብር በላይ የሚወጡ ምግብና ምግብ ነክ እቃዎች መወገዳቸውን ገልጸዋል፡፡ ከአሥተዳደራዊ እርምጃ በተጨማሪ ክስ የተመሰረተባቸው መኖራቸውንም ተናግረዋል፡፡

‎በበጀት ዓመቱ 311 ኢኮኖሚነክ መዝገቦች ውሳኔ ያገኙ ሲኾን 285 የጥፋተኝነት ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋል ብለዋል፡፡ በዚህም ከገንዘብ መቀጫ እስከ እስራት ተቀጥተዋል፡፡ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ቅጣት ተወስኗል ነው ያሉት፡፡ ከ76 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የንግድ ዕቃዎች በመንግሥት ተወርሰዋል፡፡ በጥቅሉ በቅጣትና በውርስ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመንግሥት ገቢ ተደርጓል ብለዋል፡፡

መድረኩ የተገኙት የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ምክትል ኀላፊ አያሌው አባተ (ዶ.ር) ባስተላለፉት መልዕክት ኮሚቴው ኢኮኖሚነክ ወንጀሎችን ለመከላከል ውጤታማ በኾነ መንገድ ለመምራት እና ተጠያቂነትን ለማረገጋገጥ የተቋቋመ ነው ብለዋል፡፡

‎ዓላማውም ሕጋዊ በኾነው የንግዱ ማኅበረሰብ እና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚፈጸሙ ሕገ ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ነው ብለዋል፡፡ በኢኮኖሚ ላይ የሚፈጸም ወንጀል አስቸጋሪ ባሕሪ ያለውና ተግዳሮቱ ሰፊ ነው ያሉት ምክትል ኀላፊው ምክንያቱ ደግሞ የወንጀሉ ፈጻሚ አካላት ወንጀሉን የሚፈጽሙት ሥልጣን ካላቸው እና ሕግ ከሚያስከብሩ አካላት ጋር በመኾኑ ነው ብለዋል።

‎ሌላው ምክንያት ሕገ ወጦች ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም እና ቁጥር ያላቸው በመኾኑ ካለው የባለሙያ ስብጥር አኳያ ተጠያቂነትን በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻሉ ከባድ ያደርገዋል ነው ያሉት፡፡

‎በሰው ሠራሽ ችግሮች ምክንያት ያለንን ምርት ከቦታ ቦታ ማንቀሳቀስ አለመቻል እና ኾን ተብሎ የምርት እጥረት እንዲከሰት የሚያደርጉ አካላት በመኖራቸው ገበያው እንዲራቆት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶች በተለያዩ ምክንያቶች ለተጠቃሚዎች አለመድረሱ ገበያው ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩንም አንስተዋል፡፡

‎ሕገ ወጥነትን ለመቆጣጠር በተከናወኑ ተግባራት በኢኮኖሚ ወንጀል ላይ በተሰማሩ አካላት ጉዳያቸው ወደ ፍትሕ ቀርቦ ውሳኔ እየተሰጠ መኾኑን አንስተዋል፡፡ የበለጠ አመርቂ ሥራ ለመሥራት ከማኅበረሰቡ ጋር በትብብር መሥራት ያስፈልጋልም ብለዋል፡፡

‎አማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ኀላፊ ፈንታው ፈጠነ በበኩላቸው ለሕገ ወጥ ንግድ ቁጥጥር ጥምር ግብረ ኀይል የቴክኒክ ኮሚቴው የኑሮ ውድነቱን ለማቃለል በየደረጃው ካሉ የሸማቾች ማኅበራት ጋር በመተባበር በመሰረታዊ እና ፍጆታ ምርቶች አቅርቦት ላይ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን አንስተዋል፡፡

‎‌‌በቀጣይም ከደመወዝ ጭማሪ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጦች ምርቶችን በማከማቸት በኑሮ ውድነቱ ጫና እንዳይፈጥሩ በትኩረት እና በትብብር መሥራት እንደሚገባ በመድረኩ ማጠቃለያ መልዕክት ተላልፏል።


አሚኮ


23/08/2025
20/08/2025
በሴቶች እና ሕጻናት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን እና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመከላከል እየተሠራ ነው።ደሴ: ነሐሴ 11/2017 ዓ.ም  የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር በሕጻናት...
17/08/2025

በሴቶች እና ሕጻናት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን እና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመከላከል እየተሠራ ነው።

ደሴ: ነሐሴ 11/2017 ዓ.ም የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር በሕጻናት እና ሴቶች ላይ የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን ለመከላከል የሚያስችል ውይይት ከፍትሕ፣ ከፖሊስ መሪዎች እና ባለሙያዎች ጋር በኮምቦልቻ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡

የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ምክትል ኀላፊ አያሌው አባተ (ዶ.ር) እንደተናገሩት ቢሮው ለጥቃት ተጋላጭ የኾኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች ሰብዓዊ መብታቸው እንዲከበር እና የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ነው፡፡ በሴቶች ላይ የሚደርሱ ያለ እድሜ ጋብቻ፣ አስገድዶ መደፈር እና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች እንዳይፈፀሙ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን እየሰጠ መኾኑንም ገልጸዋል። አጥፊዎችን ለሕግ በማቅረብ አስፈላጊ ቅጣት እንዲወሰንባቸው እያደረገ መኾኑንም ተናግረዋል።

በቀጣይም ከፖሊስ ጋር በቅንጅት በመሥራት የሴቶችን እና የሕጻናትን ደኅንነት ለመጠበቅ በትኩረት ይሠራል ነው ያሉት፡፡ ወንጀልን በመከላከል እና በማጋለጥ የኅብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ መኾኑን የገለጹት ምክትል ኀላፊው ኅብረተሰቡ በቀጣይም አስፈላጊውን ትብብር ሊያደርግ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

በአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የሙስና ወንጀሎች ምርመራ ዋና መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር ዳምጤ ባዬ ፖሊስ በሴቶች እና ሕጻናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከል ኅብረተሰቡን በማሳተፍ እየሠራ ነው ብለዋል፡፡ ጥቃት የሚያደርሱ አጥፊዎችን ተከታትሎ ለሕግ በማቅረብ ሰፊ ሥራዎች ተሠርተዋል ነው ያሉት፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎችም በሕጻናት እና ሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከል ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።

አሚኮ

16/08/2025

#አሚኮ #ዜና

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የፍትሕና የሕግ ኢንስቲትዩት የፍትህና የህግ ልህቀት ማዕከል ለመሆን የሚያስችሉትን ተግባራት በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተጠቆመየኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ደሴ ...
16/08/2025

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የፍትሕና የሕግ ኢንስቲትዩት የፍትህና የህግ ልህቀት ማዕከል ለመሆን የሚያስችሉትን ተግባራት በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተጠቆመ

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ደሴ ጥላሁን (ዶ/ር) የ17ኛ ዙር ሰልጣኞችን ከተግባር ልምምድ ሲመለሱ ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸው እንደገለጹት ኢንስቲትዩቱ በአዋጅ ቁጥር 299/2ዐ17 በክልሉ ም/ቤት እንደገና ከተቋቋመ በኋላ የፍትህ ትራንስፎርሜሸኑ አካል በመሆን ከፍ ባለ ደረጃ የዳኝነትና የፍትህ ሥርአቱን ተቋማዊ ግንባታ በሚያግዝ አግባብ ስራዎችን እየሰራ ነው ብለዋል፡፡

በተያያዘም፤ ኢንስቲትዩቱ በለውጥ ስራዎች ማዕቀፉ የቅድመ ሥራ ሥልጠና አካሄድ ሥርዓት ላይ ማሻሻያዎችን በማድረግ በአዲስ ዕሳቤ ስልጠናው እየተሰጠ ሲሆን የቅድመ ሥራ ሥልጠና ካሪኩለምን እንደገና በማየት፣ የተግባር ልምምድ ሥራ መጀመሩና ከልምምዱ በፊት ሠልጣኞች በፍላጎታቸውና በተለዩ መስፈርቶች አማካኝነት የሙያ ምደባ ማግኘታቸው፣ የሰልጣኞች የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸው የለውጡ ጅምር ስራዎች መሆናቸውን ጠቁመው፤ የተቋማዊ መሰረተ-ልማት ማሻሻያ ስራዎች የተጀመሩ ሲሆን ተቋሙ በአዲስ መልክ እንደገና እንዲደራጅና የቆዩ ሰፋፊ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ላደረጉት የክልሉ መንግስትና ለቦርድ ሰብሳቢያችን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ አለምአንተ አግደው ከፍተኛ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

በመጨረሻም የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ደሴ ጥላሁን (ዶ/ር) ሰልጣኞች በተግባር ልምምድ ያገኙትን እውቀትና ክህሎት እርስ በእርስ በመማማር ሙያዊ ብቃታችሁን ልታሳድጉ ይገባል ብለዋል፡፡(የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የፍትሕና የሕግ ኢንስቲትዩት)

የአማራ ክልል ኀብረት ስራ ኮሚሽን ረቂቅ  ደንብ  ላይ ውይይት ተደረገነሐሴ 9፣ 2017 ዓ.ም   የአማራ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 10ኛ መደበኛ ጉባዔ በ...
15/08/2025

የአማራ ክልል ኀብረት ስራ ኮሚሽን ረቂቅ ደንብ ላይ ውይይት ተደረገ

ነሐሴ 9፣ 2017 ዓ.ም የአማራ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 10ኛ መደበኛ ጉባዔ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሻሻለው የአስፈፃሚ አካላትን እንደገና ማቋቋሚያ እና ሥልጣንና ተግባራት መወሰኛ አዋጅ መርምሮ ማጽደቁ ይታወቃል።
በአዲስ በተሻሻለው የአስፈፃሚ አካላትን እንደገና ማቋቋሚያ እና ሥልጣንና ተግባራት መወሰኛ አዋጅ መሠረት ፍትህ ቢሮ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ፕላን ኃላፊና ባለሙያዎች፣ከርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ም/ኃላፊና የህግ አማካሪዎች እንዲሁም የኀብረት ስራ ኮሚሽን አመራሩና የማኔጅመንት አባላት በተገኙበት የኀብረት ስራ ኮሚሽንን ረቂቅ ደንብ ቀርቦ ውይይት አደርገዋል።
በአዲሱ አዋጅ መሰረት ረቂቅ ደንብ የክልሉን የሃያ አምስት ዓመቱን አሻጋሪ እድገትና የዘላቂ ልማት እቅድ እንዲሁም የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ ሊያሳካ የሚችል መሆኑን በሚያረጋግጥ መልኩ በቀረበው ረቂቅ ደንብ በተዘጋጀው ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡

በረቂቅ ሰነዱ ሰፊ ውይይት ተደርጎ ለቀጣይም ግባቶችን በማሰባሰብ ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ የሥራ ክፍፍል ተደርጎ ተጠናቋል።(ኀብረት ስራ ኮሚሽን)

የሕዝብ አመኔታ ያለው የፍትሕ ተቋም ለመገንባት እየሠራ መኾኑን የሰሜን ሸዋ ዞን ፍትሕ መምሪያ አስታወቀ። ደብረ ብርሃን፡ ነሐሴ 09/2017 ዓ.ም  የሰሜን ሸዋ ዞን ፍትሕ መምሪያ  የ2017...
15/08/2025

የሕዝብ አመኔታ ያለው የፍትሕ ተቋም ለመገንባት እየሠራ መኾኑን የሰሜን ሸዋ ዞን ፍትሕ መምሪያ አስታወቀ።

ደብረ ብርሃን፡ ነሐሴ 09/2017 ዓ.ም የሰሜን ሸዋ ዞን ፍትሕ መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ በደብረ ብርሃን ከተማ አካሂዷል።

የሰሜን ሸዋ ዞን ፍትሕ መምሪያ ኀላፊ ደመረ ቸሬ የሕዝብ አመኔታ ያለው የፍትሕ ተቋም ለመገንባት እየተሠራ ነው ብለዋል።

በ2017 በጀት ዓመት ለተገልጋዮች ቀልጣፋና ውጤታማ የፍትሕ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱንም ተናግረዋል። በሂደቱም የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ጥረት መደረጉን አንስተዋል።

የፍትሕ አገልግሎቱን የተቀላጠፈ ለማድረግ በአካል እና በስልክ ድጋፍ በማድረግ መሠራቱን ገልጸዋል።

በፈተና ዉስጥ ሆኖ የሕግ የበላይነት እንዲከበር የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ድርሻ ነበረው ብለዋል። በ2017 በጀት ዓመት የነበሩ መልካም አፈጻጸሞችን በመለየት የፍትሕ ሥርቱ ውጤታማ እንዲኾን እና ቀጣይነት እንዲኖረዉ የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል።

አሚኮ

Address

Bahir Dar
995

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ANRS Justice Bureau የአብክመ ፍትሕ ቢሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ANRS Justice Bureau የአብክመ ፍትሕ ቢሮ:

Share