Boditi Town Government Communication Affairs

Boditi Town Government Communication Affairs Governmental

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የወላይታ ልማት ማህበር ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የእስካሁን ስራ አፈጻጸም እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አካሄደ።ቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤26/2017 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦ...
03/07/2025

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የወላይታ ልማት ማህበር ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የእስካሁን ስራ አፈጻጸም እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አካሄደ።

ቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤26/2017 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የወላይታ ልማት ማህበር ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት የእስካሁን ስራ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አካሂደዋል።

ውይይቱ በዋናነት የማህበሩ አጠቃላይ የገቢ ስራዎችን በሚመለከት እና በከተማ ደረጃ የሚካሄደውን የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤን አስመልክቶ የሚካሄድበትን ጊዜ ለመወሰን በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጓል።

የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እና በከተማው የወ/ል/ማህበር ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጳውሎስ በቀለ መድረኩን መርተዋል።

ክቡር ከንቲባ አቶ ጳውሎስ በቀለ በመድረኩ እንደገለፁት ከወላይታ አልፎ በሀገር ደረጃ ዘርፈብዙ የሆኑ የልማት ስራዎችን በብቃት እያከናወነ የሚገኘው የወላይታ ልማት ማህበር በገቢ አቅሙ እንዲያድግ መደገፍ የሁሉም ህብረተሰብ ሀላፊነት እንደሆነ ገልጿል።

ስለዚህ ልማት ማህበሩ በገቢ አቅሙ አድጎ በቀጣይ ከዚህ በበለጠ ስራዎችን መስራት እንዲችል ኮሚቴው ከገቢ አሰባሰብ ጋር ባሉ ስራዎች ላይ ሀላፊነት ወስዶ በተጠያቂነት መንፈስ እንዲንቀሳቀስ አሳስቧል።

በተለይ የገቢ ስራን በሚመለከት በ2024 እአአ/2016 ዓ.ም ክንውን ወቅት በጉድለት የተገመገሙ ጉዳዮች በውጤት መፈጸም እንዲችል በ2025 እአአ/2017 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ተይዘው በትኩረት መመራት አለባቸው ተብሏል።

ለወላይታ ልማት ማህበር ገቢ አሰባሰብ ስራ እንዲረዳና ጤናማ የገቢ አሰባሰብ ስራ እንዲኖር ታስቦ በተለያዩ ጊዜያት የተሰራጩ ደረሰኞች በአሰራር መሰረት ተመላሽ በሚደረጉበት ሁኔታ ላይ ኮሚቴው ሀላፊነት ወስዶ እንዲሄድ አመራርም ተሰጥቷል።

የወላይታ ልማት ማህበር የሚያከናውናቸው ሁሉም ተግባራት የጠቅላላ ህብረተሰብ ጥቅምን መሰረት ያደረጉ እንደሆኑ የተናገሩት ክቡር ከንቲባው አንዳንድ ተቋማትና አካላት ዘንድ የሚገኙ ውዝፍ እዳዎች በአፋጣኝ ተመልሰው ገቢ እንዲሆኑ ኮሚቴው አቋም ይዞ ቀጣይ ስራዎችን እንዲመራ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማና ለህዝቦች አንድነት በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው መጠቀም አለባቸው።ቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤ 24/2017 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር...
01/07/2025

ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማና ለህዝቦች አንድነት በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው መጠቀም አለባቸው።

ቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤ 24/2017 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ማህበራዊ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ጤናማ የሚዲያ አጠቃቀም በሚመለከት ከወጣቶች ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።

መድረኩን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነትና ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ እንዲሁም የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ቡዛዩሁ ደገፉ እና በከተማው ብልጽግና ፓርቲ የማህበራዊ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አስረስ ጴጥሮስ በጋራ መርተዋል።

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነትና ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ እንዲሁም የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ቡዛዩሁ ደገፉ በመድረኩ እንደገለፁት ማህበራዊ ሚዲያ የአንድን አከባቢ ሙሉ ገፅታ በአወንታዊም ሆነ በአሉታዊ መልኩ ለሌሎች በማስተዋወቅ ተፅዕኖ የሚያደርስ የዘመኑ ቴክኖሎጂ ወጤት እንዲሆነ ገልጿል።

ሚዲያን ጥንቃቄ በተሞላ መልኩ በአግባቡ የማንጠቀም ከሆነ ሀገርን የማፍረስ አቅም እንዳለው የገለፁት አቶ ቡዛየሁ ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማና ለህዝቦች አንድነት በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተላልፏል።

የብልጽግና ፓርቲ ማህበራዊ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አስረስ ጴጥሮስ ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ ብቻ ተጠቅመን ለሀገር ለህዝብ የሚጠቅም ስራ መስራት እንደሚቻል አስረድተዋል።

በተለይ ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አለማ ተጠቅመው እጅግ በርካታ የሆኑ አቅመ ደካማ ወገኖቻችን እየረዱ ያሉ የከተማ ወጣቶች እንዳሉ የጠቀሱት አቶ አስረስ ሌሎች ወጣቶችም በእንደዚህ አይነት መልካም ተግባር ላይ በስፋት እንዲሰማሩም ጥሪ አቅርበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገ/መስቀል ጫላ ወላይታ ዲቻ ለአፍሪካ ኮንፈደሬሽን ዋንጫ ተሳታፊ መሆኑን አስመልክተው የተሰማቸውን ደስታ ገለጹ።አቶ ገ/መስቀል ጫ...
01/07/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገ/መስቀል ጫላ ወላይታ ዲቻ ለአፍሪካ ኮንፈደሬሽን ዋንጫ ተሳታፊ መሆኑን አስመልክተው የተሰማቸውን ደስታ ገለጹ።

አቶ ገ/መስቀል ጫላ ''ሃሹ ሃሹ ሃሹ! እንኳን ደስ አለን! አላችሁ !፣ ዲቻ ለአፍርካ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ተሳታፊ በመሆኑ ደስ ብሎኛል'' በማለት በራሳቸው ኦፊሴላዊ ፌስ ቡክ ገጽ ላይ ደስታቸውን አጋርተዋለ።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት አስተላለፉ  ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ውሳኔ መሠረት ዎላይታ ዲ...
01/07/2025

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት አስተላለፉ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ውሳኔ መሠረት ዎላይታ ዲቻ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ በመሆኑ የተሰማቸውን ደስታ በመግለጽ ለወላይታ ዲቻ ስፖርት የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት አስተላልፈዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት በፌደሬሽኑ ውሳኔ እጅግ መደሰታቸውን ጠቅሰው፥ ዲቻ ለአፍርካ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ተሳታፊ በመሆኑ ደስታቸውን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያቶ ውሳኔዎችን ያሳለፈ ሲሆን፥

በዚሁም የሲዳማ ቡና ስፖርት ከለብ የታገዱ ተጫዋቾችን በማሰለፍ ያሸነፈው የኢትዮጵያ ዋንጫ በፎርፌ ተሸናፊ ሆኖ ዋንጫው ለወላይታ ድቻ ተመላሽ እንዲደረግ እና የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ የኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የ2025/26 የውድድር ዘመን ተሳታፊ እንዲሆን ውሳኔ አሳልፏል።

እንኳን ደስ አላችሁ! ደስ አለን!!

የቦዲቲ ከተማ አስተዳዳር የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሰሃ ሳሙኤል ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ የ2017 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ መ...
01/07/2025

የቦዲቲ ከተማ አስተዳዳር የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሰሃ ሳሙኤል ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ የ2017 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል።
❗️ እንኳን ደስ አለን❗️

የቦዲቲ ከተማ አስተዳዳር ከንቲባ አቶ ጳውሎስ በቀለ ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፍፃሜ ዋንጫ አሸናፊ በመሆኑ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል።  ❗️ እንኳን...
01/07/2025

የቦዲቲ ከተማ አስተዳዳር ከንቲባ አቶ ጳውሎስ በቀለ ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፍፃሜ ዋንጫ አሸናፊ በመሆኑ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል።
❗️ እንኳን ደስ አለን❗️

የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘውዱ ሳሙኤል የደስታ መልዕክታቸውን አስተላለፉ።አቶ ዘውዱ ሳሙኤል ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፍፃሜ ዋንጫ አሸናፊ ...
01/07/2025

የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘውዱ ሳሙኤል የደስታ መልዕክታቸውን አስተላለፉ።

አቶ ዘውዱ ሳሙኤል ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፍፃሜ ዋንጫ አሸናፊ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን በማለት የደስታ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ።ዋና አስተዳዳሪው ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፍፃሜ ዋንጫ አሸናፊ በመሆኑ...
01/07/2025

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ዋና አስተዳዳሪው ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፍፃሜ ዋንጫ አሸናፊ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን ብለዋል።

በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በሲዳማ ቡና ላይ የወሰደው ህጋዊ ውሳኔን ተከትሎ የኢትዮጵያ ዋንጫ ለወላይታ ዲቻ እንደሚመለስ በመታወቁ በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የወላይታ ዲቻ ደጋ...
01/07/2025

በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በሲዳማ ቡና ላይ የወሰደው ህጋዊ ውሳኔን ተከትሎ የኢትዮጵያ ዋንጫ ለወላይታ ዲቻ እንደሚመለስ በመታወቁ በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የወላይታ ዲቻ ደጋፊዎች ደማቅ የሆነ የደስታ አገላለጽ እየተደረጉ ይገኛሉ ።

ወላይታ ድቻ በካፍ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን ይወክላል*************************ወላይታ ድቻ በካፍ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን እንደሚወክል የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ...
01/07/2025

ወላይታ ድቻ በካፍ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን ይወክላል
*************************

ወላይታ ድቻ በካፍ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን እንደሚወክል የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ይፋ አደረገ

በቅርብ በኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜበሲዳማ ቡና 2 ለ 1ተሸንፎ የነበረው ወላይታ ድቻ የሲዳማ ቡና ውጤት በመሰረዙ በአፍሪካ መድረክ ተሳታፊ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡

ሲዳማ ቡና በፍጻሜ ጨዋታው የታገዱ ተጫዋቾችን በመጠቀሙ ውጤቱ እንደተሰረዘበት ይፋ ተደርጓል፡፡

አቶ አደም ፋራህ በተገኙበት የክልሉ ሕዝቦች የሠላም፣ የአንድነት እና የልማት ኮንፈረንስ በዛሬው ዕለት ቀጥሎ ይዉላልሰኔ 24/2017 ዓ.ምበ ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግ...
01/07/2025

አቶ አደም ፋራህ በተገኙበት የክልሉ ሕዝቦች የሠላም፣ የአንድነት እና የልማት ኮንፈረንስ በዛሬው ዕለት ቀጥሎ ይዉላል

ሰኔ 24/2017 ዓ.ም

በ ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ በተገኙበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች የሠላም፣ የአንድነት እና የልማት ኮንፈረንስ በዛሬው ዕለት ቀጥሎ ይዉላል።

"ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በትናንትናው ዕለት የተጀመረው ክልል አቀፍ የማጠቃለያ ኮንፈረንስ በስኬት መጠናቀቁ ይታወሳል።

ኮንፈረንሱ በክልሉ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ታስቦ መዘጋጀቱም ተጠቅሷል።

በኮንፈረንሱ "ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል ርዕስ የዉይይት መነሻ ሰነድ ቀርቦ ምክክር የተደረገ ሲሆን የክልሉን ሕዝቦች አንድነት በማጠናከር ክልሉን የሰላም፣ የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ጉዞ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አፅንኦት ተሰጥቷል።

በክልሉ ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ በመጠቀም ክልሉ ከራስ አልፎ በሀገር ደረጃ በተጀመረው ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ የሚጠበቅበትን እንዲወጣ የክልሉ ተወላጅ ምሁራን፣ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡም ጥሪ ቀርቧል።

ባለፉት ጊዜያት ከራስ ፍላጎት በመነጨ መልኩ የተፈጠሩ መቃቃሮችን በይቅርታና በመደመር በመሻገር ክልሉ ሙሉ ኃይሉን የሕዝቡን ልማት፣ ሰላም እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መመለስ ላይ ትኩረት አድርጎ እንዲሠራ ማድረግ ይገባልም ተብሏል።

በአንድ ፓርቲ የሚመራ አንድ ክልል እንደመሆኑም በአመራሩ መካከል የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በመፍጠር ከጊዜያዊ ችግሮች የተሻገረና በጠንካራ ህጋዊና ተቋማዊ አሠራሮች የጎለበተ ክልል ዕዉን አድርጎ በምስረታው ወዳነገበዉ የሰላም፣ የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት የመሆን ክልላዊ ራዕይ መሸጋገር እንደሚገባም ተመላክቷል።

ኮንፈረንሱ በሁለተኛ ቀን ዉሎዉ የክልሉን አንድነት የሚያጠናክሩ ተቋማዊ አደረጃጀቶችና ፎረሞች ምስረታን ጨምሮ በቀሪ ጉዳዮች ላይ በመምከር ዉሳኔዎች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል።

የቦዲቲ ከተማ ወጣት አደረጃጀቶች የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ስራን በማስመልከት ከተማን የማስዋብ ተግባር እያከናወኑ ነውቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤ 23/2017 ዓ.ም በወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ ወጣ...
30/06/2025

የቦዲቲ ከተማ ወጣት አደረጃጀቶች የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ስራን በማስመልከት ከተማን የማስዋብ ተግባር እያከናወኑ ነው

ቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤ 23/2017 ዓ.ም በወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ ወጣት አደረጃጀቶች የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ስራን በማስመልከት ከተማን የማስዋብ ተግባር እያከናወኑ ይገኛሉ።

ወጣቶቹ ከተማን ለማስዋብ የተጠቀሙበትን የተለያዩ ቀለማትን የከተማ ህብረተሰብን በማስተባበር ማዘጋጀት መቻላቸውን የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት አሸናፊ አፋቶ ገልጿል።

ወጣት አሸናፊ አክለውም ይህ ተግባር እንዲሳካ የበኩላቸውን ለተወጡና ድጋፉን ላበረከቱ አካላት በጽ/ቤታቸው ስም አመስግነዋል።

በቀጣይም በንቅናቄ በሚሰሩ በጎ ተግባራት ላይ የከተማ አጠቃላይ ወጣቶች ተሳታፊ እንዲሆኑም ወጣት አሸናፊ ጥሪ አቅርበዋል።

Address

Wolaita
Boditi

Telephone

+251938042228

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Boditi Town Government Communication Affairs posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share