Boditi Town Government Communication Affairs

Boditi Town Government Communication Affairs Governmental

የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ "ጊፋታ" በዓል ልዩ ዝግጅት ላይ የሚሳተፈው የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ልዑካን ቡድን ወደ ወላይታ ሶዶ ጉዞ ጀምሯል።
21/09/2025

የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ "ጊፋታ" በዓል ልዩ ዝግጅት ላይ የሚሳተፈው የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ልዑካን ቡድን ወደ ወላይታ ሶዶ ጉዞ ጀምሯል።

የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሰሃ ሳሙኤል የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።🌼🌼  🌼🌼መላው የ...
20/09/2025

የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሰሃ ሳሙኤል የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

🌼🌼 🌼🌼
መላው የወላይታ ተወላጅ የሆናችሁ እንኳን ለ2018 ዓ.ም የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል በሠላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!!

የጊፋታ በዓል የወላይታ ብሔር ባህላዊ የዘመን አቆጣጠር ጠቢባን (ግሯ) /Giruwaa/ዎች የጨረቃን መታየት “Xeeruwaa”, ”Goobanaa”, “poo’’uaa”, “Xumaa” ለይተዉ በመረዳት በሰላም ጠብቆ አዲስ ተስፋ ለሰጣቸዉ ፈጣሪ ምስጋና በማቅረብ መልካም ምኞትን አንዱ ለሌላዉ የሚያበስርበት የምሰጋና በዓል ነው።

ጊፋታ በዓል ወላይታ ብሔር የማንነት መገለጫ የሆነ የዘመን መለወጫ በዓል ነው እንጂ ምንም አይነት ግንኙነት ከየትኛውም ሀይማኖት ጋር እንደሌለው ህዝቡ ልረዳ ይገባል።

በወላይታ ህዝብ ዘንድ ታላቅ ስፍራ የሚሠጠውና ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣው "ጊፋታ" በዓል በአለም ቅርስነት/UNESCO / እንድመዘገብ እየተደረገ ባለው እንቅስቃሴ ሁሉም ህብረተሰብ የበዓሉን ልዩ ገጽታዎችን የማሳወቅ ስራን በመስራት የበኩሉን አስተዋጽኦ ልያበረክት ያስፈልጋል።

በዓሉን ስናከብር መልካም የሆኑትን የህብረተሰባችንን ነባር እሴቶች ማለትም መደጋገፍ፣ መተሳሰብ፣ መቻቻልና መረዳዳትን አጠናክረን ማስቀጠል እንደሚገባም ተናግሯል።

🌼🌼 🌼🌼

እንኳን ለ2018 ዓ.ም የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል በሠላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!!

አቶ ፍሰሃ ሳሙኤል
የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ

አቶ ጳውሎስ በቀለ የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ እንኳን የ2018 ዓ.ም የወላይታ ብሔር ...
20/09/2025

አቶ ጳውሎስ በቀለ የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን የ2018 ዓ.ም የወላይታ ብሔር የማንነት መገለጫ እና የዘመን መለወጫ ለሆነው 'ጊፋታ' በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

Hashshu Wolaitta Deriyaa Layta lamiya Gidida Gifaataa Balaw Saro Gakketa!!
እንኳን በሰላም አደረሳችሁ/አደረሰን።

የወላይታ ብሐር የዘመን መለወጫ የሆነው ታላቁ የጊፋታ በዓል የብሔሩ ስነ ፈለግ ጠቢባን አባላት( Giruwa) ፣ የጨረቃና የፀሀይ ዑደትን በማስላት ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት፣ ከክረምት ወደ በጋ፣ ከጭጋጋማ ወቅት ወደ Poo'uwa (ብርሀናማ) ወቅት ሽግግር የሚበሰርበት በዓል ነው ብሏል፡፡

"ጊፋታ" በዓል የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ከፍተኛ ነው ፤ በተለይ የእርስበርስ ትስሰር ያጠናክራል ፤ ይቅርታንና መቻቻልን ፣ መተጋገዝንና መተሳሰብን በማጠናከር በሰዎች መካከል ቀጣይነት ያለው ሰላም እንዲኖር ያግዛል ።

🌼🌼YOO YOO GIFAATAA🌼🌼
!!
/አደረሰን።
ዮዮ ጊፋታ!! ጊፋታ ዮዮ
አቶ ጳውሎስ በቀለ
የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ

የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ የሆነው "ጊፋታ" ከመከበሩ በፊት ባሉ ቀናት በእናቶች እለተ አርብ ቀን በድምቀት የሚከበረው Sul"a Bizza/ሱልኣ አርባ በልዩ ዝግጅት ተከበረ ቦዲቲ ፤ መስከ...
19/09/2025

የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ የሆነው "ጊፋታ" ከመከበሩ በፊት ባሉ ቀናት በእናቶች እለተ አርብ ቀን በድምቀት የሚከበረው Sul"a Bizza/ሱልኣ አርባ በልዩ ዝግጅት ተከበረ

ቦዲቲ ፤ መስከረም ፤ 09/2018 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ የሆነው "ጊፋታ" ከመከበሩ በፊት ባሉ ቀናት በእናቶች እለተ አርብ በድምቀት የሚከበረው Sul"a bizza /ሱልኣ አርባ በልዩ ዝግጅት ተከብሯል።

ቀኑን አስመልክቶ የተዘጋጀው ልዩ ዝግጅት በቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አማካኝነት እንደሆነ ማወቅ ተችሏል።

በዚህ ልዩ ዝግጅት ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቦዲቲ ከተማ ምክትል ከንቲባ እንዲሁም የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ብሩክ ባልቻ እንዳሉት "ጊፋታ" ማለት ታላቅ ወይንም ከቀኖች ሁሉ የመጀመሪያ እንደሆነ በመግለፅ ወላይታ ከጥንት ጀምሮ ጊፋታን የዘመን መለወጫ በዓል አድርጎ እያከበረ መምጣቱን አስረድተዋል።

የጊፋታ በዓልን በአለም ቅርስነት ዩኔስኮ ለማስመዝገብ ጠንካራ ስራዎች ተሰርተው ወደመጨረሻው ምዕራፍ እየተደረሰ እንዳለ የጠቆሙት ክብርት ም/ከንቲባ አሁን የሚቀሩ ስራዎች ስላሉ ሁሉም ህብረተሰብ ባህሉን ለአለም የማስተዋወቅ ተግባርን አጠናክሮ እንዲሰራም አሳስበዋል።

የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ስለ ዛሬው ቀን ልዩ ዝግጅት ሲያብራሩ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ የሆነው ጊፋታ በአለም ቅርስነት እንዲመዘገብ ያለንን ውብ ባህል ለማስተዋወቅ በማሰብ እንደሆነ ገልጸዋል።

ሳቫና የህትመት ድርጀት ከወ.ል.ማ ጋር በመቀናጀት ከ200 ሺ ብር በላይ ወጪ በቦዲቲ ከተማ ጁኔር 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚገኙ ቅደመ መደበኛ ተማሪዎች የሚያገለግል ዘመናዊና ልዩልዩ የመማሪያ ቁ...
19/09/2025

ሳቫና የህትመት ድርጀት ከወ.ል.ማ ጋር በመቀናጀት ከ200 ሺ ብር በላይ ወጪ በቦዲቲ ከተማ ጁኔር 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚገኙ ቅደመ መደበኛ ተማሪዎች የሚያገለግል ዘመናዊና ልዩልዩ የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አበረከተ

ቦዲቲ ፤ መስከረም ፤ 09/2018 ዓ.ም Savannah Printing Press ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ደርጅት ከ ወላይታ ልማት ማህበር ጋር በመቀናጀት ከ200 ሺ ብር በላይ ወጪ ለቦዲቲ ጁኔር 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚገኙ ቅደመ መደበኛ ተማሪዎች የሚሆን ዘመናዊ የመማሪያ ቁሳቁስ አበርክተዋል።

ከSavannah Printing Press ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ደርጅት ድጋፉን በስፍራው ተገኝተው የተቀበሉት የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጳውሎስ በቀለ ድርጅቱ እጅግ ቡዙ ገንዘብ በማውጣት ህብረተሰቡን ለማርዳት ባደረገው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸው ለተግባራቸውም በከተማ መንግስት ስም ምስጋና አቅርበዋል።

ድርጂቱ ለቅድመ መደበኛ ተማሪ ልጆች በዛሬው ዕለት ያበረከቱት የመማሪያ ቁሳቁስ ልጆች ዘመናዊና ፈጠራን መሰረት ያደረገ የትምህርት ስርዓትን ተከትለው እውቀት እንዲጨብጡ ዘንድ በእጅጉ እንደሚያግዝ ገልፀዋል።

እንደ ከተማ መንግስትም ይህንን መሰል ዘመናዊ የመማሪያ ቁሳቁስ በከተማው ባሉ በሌሎች ትምህርት ቤቶችም የማሟላት ተግባርን እንደተሞክሮ ወስደው ለማስፋፋት እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።

የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አቅመ ደካማ ለሆኑ ቤተሰብ ተማሪ ልጆች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉቦዲቲ ፤ መስከረም ፤ 9/2018 ዓ.ምየ2018 የትምህርት ዘመን መጀመ...
19/09/2025

የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አቅመ ደካማ ለሆኑ ቤተሰብ ተማሪ ልጆች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ

ቦዲቲ ፤ መስከረም ፤ 9/2018 ዓ.ምየ2018 የትምህርት ዘመን መጀመርን በማስመልከት በወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አቅመ ደካማ ለሆኑ ቤተሰብ ተማሪ ልጆች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ አድርገዋል።

የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ድጋፉን የከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አካላት በተገኙበት ነው ማበርከት የቻሉት ።

የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጳውሎስ በቀለ በስፍራው ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ላደረገው በጎ ተግባር በከተማ መንግስት ስም አመስግነዋል።

ይህንን መሰል ሰው ተኮር ተግባርን በከተማው በሁሉም አከባቢዎች የሴቶች ክንፍ አደረጃጀቶች አጠናክረው ማስቀጠል አለባቸው ሲሉ ክቡር ከንቲባው አሳስበዋል።

በዛሬው ዕለት የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ የተበረከተላቸው ተማሪዎችም ለወደፊት ከራሳቸው አልፈው ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎች ለመሆን ዛሬ ላይ በርትተው መማር እንዳለባቸው ስሉ ምክር ሰጥተዋል።

የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሰሃ ሳሙኤል በበኩላቸው ፓርቲያችን በሀገሪቱ በሁሉም አከባቢዎች የሰው ተኮር ስራዎችን ለማስፋፋት የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት በተለይ የሴቶች ክንፍ ሚና የላቀ እንደሆነ ገልጸዋል።

የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አሁን ላይ የጀመሩትን መልካም ተግባር አጠናክረው ማስቀጠል ልዩ ሀላፊነት እንደሆነ አምነው መንቀሳቀስ አለባቸው ብለዋል።

የቦዲቲ ከተማ ምክትል ከንቲባ እንዲሁም የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ብሩክ ባልቻ በንግግራቸው የሴቶች ክንፍ አቅመ ደካማ ተማሪዎችን ለመርዳት ህብረተሰቡን በማስተባበር ያደረጉት ጥረት የሚደነቅ እና የሚበረታታ እንደሆነ ተናግረዋል።

በተለይ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ በአመቱ አቅደው ከሚፈጽሙት ወሳኝ ተግባራት ውስጥ አቅመ ደካማ ወገኖችን መርዳት ዋነኛው እንደሆነ የገለፁት ኃላፊዋ ተግባሩ በአንድ ወቅት ላይ ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን ቀጣይነት ባለው መልኩ ተግባራዊ እንዲሆን በትኩረት መመራት አለበት ብለዋል።

 #ሁለት (2) ቀናት ብቻ ቀሩየዘንድሮ የወላይታ ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓልን በድምቀት ለማክበር  #ሁለት (2) ቀናት ብቻ ቀሩ።የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል በውቢቷ ወላይታ በሶ...
19/09/2025

#ሁለት (2) ቀናት ብቻ ቀሩ

የዘንድሮ የወላይታ ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓልን በድምቀት ለማክበር #ሁለት (2) ቀናት ብቻ ቀሩ።

የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል በውቢቷ ወላይታ በሶዶ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ይከበራል።

በዞን ደረጃ #ቅዳሜ ዕለት መስከረም 10/2018 ዓ.ም የቋንቋና የባህል ስምፖዚየም በወላይታ ጉተራ አደራሽ የሚካሄድ ሲሆን፤

#እሁድ መስከረም 11/2018 የወላይታ ህዝብ የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል በልዩ ድምቀት ከሌሎች ወንድም ህዝቦች ጋር በወላይታ ሶዶ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም ይከበራል።

ጊፋታ ማለት የስሙ ትርጓሜ የመጀመሪያ(በኩር) ማለት ሲሆን በሌላ አገላለጽ ጊፋታ ማለት መሻገርን ያመለክታል፡፡ ይህም ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት ማለፍን ወይም መሻገርን የሚገልጽ የህዝቡ የደስታና የምስጋና ማቅረቢያ በዓል ሆኖ ዘመናትን የዘለቀ ነው፡፡

ጊፋታ የወላይታ ብሔር ከጥንት ጀምሮ ሲያከብሩ የነበረ የአሮጌው ዓመት ማብቂያና የአድሱ ዓመት መጀመሪያ የዘመን መለወጫ በዓል ነው፡፡

ጊፋታ በዓሉ የአዲስ ዓመት ብርሃን ማብሰሪያ፣ በተለያየ ምክንያት ከአካባቢው ርቀው የሚኖሩ ወገኖች ከወላጆቻቸው ጋር የሚገናኙበት፣ የተጣላ የሚታረቅበት ታላቅ ክብረ በዓል ነው።

ኑ አብረን እናከብር!
እንኳን አደረሰን!

የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጳውሎስ በቀለ የ2018 የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።መላዉ ኢትዮጵያን እንዲሁም የከተማችን ነዋሪዎች...
11/09/2025

የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጳውሎስ በቀለ የ2018 የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

መላዉ ኢትዮጵያን እንዲሁም የከተማችን ነዋሪዎች እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሠላም ፤ በጤና አደረሰን! አደረሳችሁ !

አዲሱ ዓመት የሠላም የፍቅር የመቻቻልና የብልፅግና እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ።

የዘመን መለወጫ በዓል ሁሉም ኢትዮጵያውያን በእምነት ሳይለያዩ በጋራ የሚያከብሩት ታላቅ በዓል መሆኑን አስረድተዋል።

በዓሉ በሁሉም አከባቢ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ በድምቀት መከበር እንዲችል ሁላችንም ድርሻችንን መወጣት አለብን ብለዋል

አዲሱ ዓመት የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የበረከት፣ የአብሮነትና የአንድነት እንዲሁም ወንድማማችነትና እህትማማችነት የምናጠናክርበት እንዲሆን ተመኝተዋል።

በመጨረሻም አቶ ጳውሎስ በዓሉን ስናከብር አቅመ ደካሞችን በማገዝ ፣ የታረዙትን በማልበስ ፣ የተራቡትን በማብላት የኢትዮጵያዊነት መልካም እሴቶችን ማጉላት እንደሚጠበቅብን አሳስቧል።

❗️
ፈጣሪ ኢትዮጵያ እና ህዝቦቿን ይባርክ።

አቶ ጳውሎስ በቀለ
የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ

የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና አቶ ፍሰሃ ሳሙኤል ለ2018 አዲሱ አመት እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ አቶ ፍሰሃ በመልዕክታቸው  ለቦዲቲ ከተማ ህዝ...
11/09/2025

የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና አቶ ፍሰሃ ሳሙኤል ለ2018 አዲሱ አመት እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አቶ ፍሰሃ በመልዕክታቸው ለቦዲቲ ከተማ ህዝብና ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ2018 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል በሠላም አደረሳችሁ ብለዋል።

በዓሉ የሰላም ፣ የደስታና የአንድነት እንዲሆን የተመኙት አቶ ፍሰሃ በዓሉን ስናከብር የተቸገሩትን በመርዳት ፣ አረጋዊያንና አቅመ ደካሞችን የአቅማችንን ያህል በማገዝ እንዲሆንም ጠይቀዋል።

በመጪው አዲሱ ዘመን አብሮነትን፣ መተሳሰብን፣ ፍቅርን፣ አንድነትንና ወንድማማችነትን የምናጎለብትበት እንዲሁም ጠንክረን ሠርተን የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብልጽግና የምናረጋግጥበት እንዲሆን ተመኝተዋል።

በመጨረሻም መጪው አዲስ አመት ጥላቻ በፍቅር ተቀይሮ፣ ስንፍና በትጋት ተለውጦ መከባበራችንና መደማመጣችን የሚጠነክርበት ፣ ድህነት በብልፅግና የሚቀየርበት ፣ ያሰብነውን ያለምነውንና ያቀድነውን የምናሳካበት እንዲሆን ዘንድ በድጋሚ የመንግስት ተጠሪው ተመኝተዋል።

❗️
አቶ ፍሰሃ ሳሙኤል
የቦዲቲ ከተማ የመንግስት ዋና ተጠሪ እና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜን-4 "የማንሰራራት ቀን" በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነውቦዲቲ፤ጳጉሜ ፤04-12-2017ዓ.ም በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ''ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ...
09/09/2025

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜን-4 "የማንሰራራት ቀን" በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው

ቦዲቲ፤ጳጉሜ ፤04-12-2017ዓ.ም በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ''ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሰራራት ''በሚል መሪ ቃል ጳጉሜን-4 የማንሰራራት ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።

የዛሬው ጳጉሜን-4 "የማንሰራራት ቀን" በቦዲቲ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት መሪነት እየተከበረ ሲሆን ዕለቱን አስመልክቶ ከተማን ውብና ፀዱ ለማድረግ ያለመ የፅዳት ዘመቻ እንዲሁም በአመቱ በማዘጋጃ ተቋም አማካኝነት የተሰሩ የተለያዩ የልማት ስራዎች በስዕል አውደርዕይ ቀርበዋል።

የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጳውሎስ በቀለ ቀኑን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት የዘንድሮው ጳጉሜ 4 እንደ ሀገር በኢኮኖሚው ፤ በማህበራዊውና በፖለቲካው ዘርፍ በማንሰራራት ወደ ተሻለ ደረጃ በደረስንበት ወቅት በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

በተለይ የማንሰራራታችንና የኢትዮጵያዊነታችን ልዩና የኩራት ምልክት የሆነው ታላቁ ህዳሴ ግድባችን በሚመረቅበት ቀን የማንሰራራት ቀንን ማክበራችን ከሌሎች ቀናት ለየት ያደርገዋል ስሉ ክቡር ከንቲባው አክለው ገልጸዋል።

በከተማው በልማቱ ዘርፍ የሚታዩ ለውጦችን አጠናክሮ በማስቀጠል የማንሰራራት ጉዞ እንዲሰምር አመራሩ በተሰማራበት ስራ መስክ ከመቸውም ጊዜ በላይ ትኩረት ልያደርግ እንደሚገባም አቶ ጳውሎስ አስረድተዋል።

የቦዲቲ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ስራአስኪያጅ አቶ መዝገቡ ሞሬቦ በበኩላቸው ዘንድሮ እንደ ከተማ አስተዳደር ተቋሙ በርካታ የልማት ስራዎችን በብቃት መፈጸም በመቻሉ ማንሰራራትን ዕውን ያደረገበት አመት ነው ብሏል።

ዛሬ የቀረበው የስዕል አውደርእይ እና የጽዳት ዘመቻ ስራ በቀጣይ ማንሰራራቱ እንዲጸና ዘንድ አመራሩ በበለጠ እንድንቀሳቀስ መነቃቃትን ለመፍጠር ያለመ ነው ሰሉ አብራርተዋል።

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የ2018ዓ.ም ዘመን መለወጫ በዓልን ጨምሮ የጊፋታና የመስቀል በዓላትን ህብረተሰቡ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ ማክበር እንዲችሉ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለፀ ቦዲቲ...
08/09/2025

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የ2018ዓ.ም ዘመን መለወጫ በዓልን ጨምሮ የጊፋታና የመስቀል በዓላትን ህብረተሰቡ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ ማክበር እንዲችሉ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለፀ

ቦዲቲ ፤ ጳጉሜ ፤ 03-13-2017 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር በመጪው መስከረም ወር በድምቀት የሚከበሩ ልዩልዩ በዓላትን መላው የከተማው ማህበረሰብ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲያከብሩ ለማድረግ ያለመ የውይይት መድረክ ከፀጥታ አካላት ጋር ተካሂዷል።

በመድረኩ የከተማ ፖሊስ አመራሮችን ጨምሮ አጠቃላይ የፀጥታ አካላት ተሳትፈዋል።

የቦዲቲ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኢ/ር ታረቀኝ ታዬቦ እንዳሉት የ2018ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን ጨምሮ የጊፋታና የመስቀል በዓላትን ህብረተሰቡ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ ማክበር እንዲችሉ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጀት መጠናቀቁን ለሚዲያችን አሳውቀዋል።

ወቅቱ የበዓል ወቅት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በከተማው በርካታ የሰዎችና የትራፊክ እንቅስቃሴዎች እንደሚኖሩ የጠቆሙት ኢ/ር ታረቀኝ የማጭበርበር ድርጊቶች እንዲሁም የትራፊክ መጨናነቅ ተፈጥሮ በሰዎችና በንብረት ላይ አደጋ እንዳይከሰት አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል ብለዋል።

የከተማ ማህበረሰብም ከበዓሉ ጋር ተያይዞ ምንም አይነት ወንጀሎች ሆነ የትራፊክ አደጋዎች እንዳይከሰቱ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በተጨማሪም በግብይት ወቅት የሀሰተኛ ብር ኖት ስርጭት ሊኖር ስለሚችል እንዲሁም ከባዕድ ጋር ቀላቅሎ እህልን የሚሸጡ አጭበርባሪዎች ስለሚኖሩ ህዝቡ ጥንቃቄ እንዲያደርጉም መልዕክታቸውን አጋርተዋል።

በከተማው ምንም አይነት የወንጀል ድርጊት ተከስቶ ቢገኝ በአስቸኳይ ከታች በተቀመጡ ስልክ ቁጥሮች ጥቆማ እንዲትሰጡ እናሳስባለን። ☎️0913928460 እና 0916290184

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜ- 3 የእምርታ ቀን "እምርታ ለዘላቂ ከፍታ !" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው።ቦዲቲ ፤ ነሐሴ ፤ 03/13/2017 ዓ.ም በወላይታ ዞን በ...
08/09/2025

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜ- 3 የእምርታ ቀን "እምርታ ለዘላቂ ከፍታ !" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው።

ቦዲቲ ፤ ነሐሴ ፤ 03/13/2017 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜ- 3 የእምርታ ቀን "እምርታ ለዘላቂ ከፍታ !" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል

የዛሬው ጳጉሜን 3- የእምርታ ቀን በቦዲቲ ከተማ ግብርና ልማት ጽ/ቤት መሪነት እየተካሄደ እንዳለ ማወቅ ተችሏል።

በዚህ መነሻ የከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አካላትን ጨምሮ ጠቅላላ አመራር በቦዲቲ ሶዶ በር ቀበሌ ፋቴ ቀጠና በመኸር እርሻ እየለማ ያለውን የስንዴ ማሳን መስክ ምልከታ አድርገዋል።

የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጳውሎስ በቀለ በዚህ መስክ መልከታ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ፓርቲያችን ብልጽግና የረጂምና የአጭር ጊዜ ዕቅድ ነድፎ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ብሎም በአለም የብልጽግና ተምሳሌት ሀገር ለማድረግ እየሰራ ያለውን ተግባር ለማሳካት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ አለብን ብለዋል።

ስለዚህ አመራሩ በተመደበበት ቀጠና የመፍጠርና የመፍጠን እሳቤን በመከተል ምርትና ምርታማነት እንዲያድግ የሚጠበቅበትን ሀላፊነት እንዲወጣ አሳስበዋል።

በተለይ በአርሶ አደሩ ዘንድ ያለውን እምቅ አቅምና ሀብት ከዘመናዊ ተክኖሎጂ ጋር በማገናኘት ምርታማ ሆነው የትልቅ ኢኮኖሚ ባለቤት እንዲሆኑ ከዘርፉ ባለሙያዎች ጀምሮ ያለው ድጋፍና ክትትል መጠናከር አለበት ብለዋል።

የቦዲቲ ከተማ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ጽ/ማሪያም ዘካርያስ በበኩላቸው በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚቻለው ጠንካራና ችግር ፈቺ የሆነ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ስኖር እንደሆነ ገልጸዋል።

የዛሬው መስክ ምልከታ ዋና አላማን ኃላፊዋ ስያብራሩ አመራር በተመደበበት የስራ ቦታ ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ አንጻር ልዩ ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግ ዘንድ መነሳሳትን ለመፍጠርና ተሞክሮን ለማስፋፋት ነው ብለዋል።

Address

Wolaita
Boditi

Telephone

+251938042228

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Boditi Town Government Communication Affairs posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share