South West Ethiopia people RegionaState Gov.t Transport & Road Dev.t Bureau

  • Home
  • South West Ethiopia people RegionaState Gov.t Transport & Road Dev.t Bureau

South West Ethiopia people RegionaState Gov.t Transport & Road Dev.t Bureau SWEPRS Transport & Road Dev.t Bureau

በRCFS ፕሮጀክት  የሚሰሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን የዘመናት የመሰረተ ልማት ጥያቄ የሚፈታ ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ  መሆኑ ተገለጸ።የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማ...
16/05/2025

በRCFS ፕሮጀክት የሚሰሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን የዘመናት የመሰረተ ልማት ጥያቄ የሚፈታ ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የማኔጅመንትና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በፕሮጀክቱ የሚሰሩ የመንገድ ዲዛይኖች በአማካሪ መሀንዲሶች ቀርበው ግምገማ ተደርጎበታል።

ፕሮጀክቱ ለሚያሰራቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች በአማካሪ መሀንዲሶች የቀረቡ የዲዛይን ስራዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ቤሌማ አማካሪ ፣ ኤች ቲ ስኩዌር እና ጦና አማካሪ በተባሉ ድርጅቶች የዲዛይን ስራው እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።

በዳውሮ ዞን የባሌ - ሹታ 11.96 ኪሎ ሜትር ፣ በኮንታ ዞን የደልባ - አልፋ የ12.1 ኪሎ ሜትር ፣ በካፋ ዞን የካካ - ሜጫ 26 ኪሎ ሜትር ፣ በቤንች ሸኮ ዞን የኩካ - ማሀ 9.7 ኪሎ ሜትር ፣ በምዕራብ ኦሞ ዞን የባቹማ - ኮላይ 10 ኪሎ ሜትር የመንገድ ስራዎች፣ ሸካ ዞን የኪ ወረዳ ኩብቶ - ባሆመንደራሻ 8.6 ኪ.ሜ መንገድ እና ስትራክቼር
የዲዛይንና የስትራክቸር ስራዎች ቀርበው ተገምግመዋል።

አማካሪ መሀንዲሶቹ በመጀመሪያው የግምገማ መድረክ አስተያየቶችን እንደ ግብዓት በመጠቀም የዲዛይና የስትራክቸር ስራዎችን አዘጋጅቸው መቅረባቸውን ገልጸዋል።

የቢሮው መሀንዲሶችና ባለድርሻ አካላት በሰጡት የግምገማ አስተያየት በመጀመሪያው ዙር የተሰጡ አስተያየቶች በአብዛኛው ተካተውና ተሻሽለው መቅረባቸውን ገልጸዋል። የካካ - ሜጫ መንገድ የቆረጣ ስራዎች ፣ የመረጃ ለቀማ ጥራት ፣ የድንጋይና ጠጠር ማምረቻ ቦታ መረጣዎች እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ አዋጭነት ከግምት ውስጥ ሊገባ ይገባል ብለዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ በመድረኩ ማጠቃለያ እንደተናገሩት የመንገድ ስራዎቹ የህብረተሰቡን የመንገድ ተደራሽነት የሚያሰፋ ፣ ጊዜ ፣ ወጪና ድካምን የሚቀንሱ ይሆናሉ ብለዋል።

የመንገድ ስራዎች ከተደራሽነታቸው ባሻገር ኢኮኖሚካል አዋጭነታቸው ሊረጋገጥ ይገባል ያሉት አቶ ፋጂዮ የዲዛይን ስራዎችም እነዚህ ጉዳዮች ያካተቸ ሊሆን ይገባል ብለዋል። አማካሪ መሀንዲሶቹ በአጭር ጊዜ ውስጥ ስራዎችን አጠናቀው ለማቅረብ የወሰዱት ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው ብለዋል።

በመድረኩ የተነሱ ጥቃቅን አስተያየቶችን በማረም ወደ ጨረታ ሂደት እንደሚገባም ኃላፊው ገልጸዋል።

በክልሉ በRCFS ኘሮጄክት ለሚገነቡት አዳድስ የመንገድ ግንባታ እና ልዩ እስቲራክቸር ዲዛን ቅርቦ ተገመገመ።ግንቦት 1/2017 ዓ.ም ሚዛን አማንየክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በRC...
09/05/2025

በክልሉ በRCFS ኘሮጄክት ለሚገነቡት አዳድስ የመንገድ ግንባታ እና ልዩ እስቲራክቸር ዲዛን ቅርቦ ተገመገመ።

ግንቦት 1/2017 ዓ.ም ሚዛን አማን
የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በRCFS ፕሮግራም ለሚገነቡትን አዳድስ የመንገድ ግንባታ እና ልዩ ስትራክቸር ሥራዎች ከዲዛንና አማካሪ ማህበራት ጋር የውል ስምምነት መግባቱን የሚታወቅ ነው።

አማካሪ ማህበራት በገቡት ውል መሠረት ዲዛን ሠረቶ አቅርቦዋል።

በቀረበው የመንገዶቹ ዲዛን ውይይት ላይ የተናገሩት በምክትል ርዕስ መስተዳደር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ እንደተናገሩት የክልሉ ትልቁ ጥያቄ የመንገድና የድልድይ ችግር እንደሆነ ገልፀው በጋ ከክረምት የሚያገለግል መንገዶችን ለመገንባት የመንገዶቹ እና የልዩ እስቲራክቸር ዲዛይን ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

የቢሮ ኃላፊ አክለው የኘሮጄክቱ ዋና ዓላማ የገጠር መንገድ በመገንባት ከዋና መንገድ በማገናኘት አርሶና አርብቶአደሩ ምርትና ምርታማነትን መጨመር እንደሆነ ገልጸዋል።

አማካሪዎች የሠሩት የመንገድ እና የልዩ እስቲራክቸር ዲዛን አቅርቦ በቢሮ አመራሮችና በባለሙያዎች አስተችተዋል።

በውይይት የተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች በአማካሪዎች ማብራርያዎች ምላሺ የተሠጠ ሲሆን ማስተካከያዎች የሚፈልጉ በግባዓትነት እንደሚውሰዱ ታውቋል ።

6 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር የተመደበለት የዲሪ ማሻ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጀመረሚዛን አማን፣ ሚያዝያ 21፣2017ዓም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 6 ነጥብ 2 ቢሊየን ብ...
29/04/2025

6 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር የተመደበለት የዲሪ ማሻ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጀመረ

ሚዛን አማን፣ ሚያዝያ 21፣2017ዓም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 6 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር የተመደበለት የዲሪ ማሻ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ተጀምሯል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) በፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ ላይ፤ ፕሮጀክቱ በ2010 በጀት ዓመት የግንባታ ሥራው ቢጀመርም በተለያዩ ምክንያቶች በመቋረጡ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ መቆየቱን አንስተዋል።

መንግስት የአካባቢውን የመሠረተ ልማት ስርጭት ለማመጣጠን በወሰደው ቆራጥ ውሳኔ ዛሬ ግንባታው በይፋ መጀመሩን ጠቅሰው፤ የአስፋልት መንገዱ የካፋና ሸካ አካባቢዎችን በማስተሳሰር ክልላዊና ሀገራዊ ኢኮኖሚን ለማነቃቃት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።

ፕሮጀክቶችን ጀምሮ መጨረስ ከተለያዩ ሀገራዊ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ልምድ የተወሰደ መሆኑን አንስተው፤ ይህም ፕሮጀክትም በዚሁ መንገድ የሚቃኝ እንደሆነ አመልክተዋል።

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው፤ የብልጽግናን ጉዞ እውን በማድረግ የህብረተሰቡን ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የመንገድ መሠረተ ልማት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

የዲሪ ማሻ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ተጀምሮ ባለመጠናቀቁ የህብረተሰቡ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ መቆየቱን ገልጸው፤ አስፈላጊውን በጀት በመመደብ ሥራው መጀመሩን ጠቅሰዋል።

ፕሮጀክቱ እስኪጠናቀቅ የፌዴራል መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠው፤ የክልሉ መንግስት፣ የአካባቢው ህብረተሰብና ሌሎች አካላት የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንዲወጡ ጠይቀዋል።

የመንገድ ፕሮጀክቱ 61 ነጥብ 9 ኪሎሜትር የሚሸፍነው ፕሮጀክቱ በ3 ዓመት ከ5 ወራት እንደሚጠናቀቅ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ገልጿል።

ኮርፖሬሽኑ አሠራሩን በማዘመን ለበለጠ ውጤታማነት መትጋት አለበት፡-ኢንጂነር በየነ በላቸውየክልሉ ኮንስተራክሽን ኮርፖሬሽን የሥራ አመራር ቦርድ የኮርፖሬሽኑን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራ...
15/04/2025

ኮርፖሬሽኑ አሠራሩን በማዘመን ለበለጠ ውጤታማነት መትጋት አለበት፡-ኢንጂነር በየነ በላቸው

የክልሉ ኮንስተራክሽን ኮርፖሬሽን የሥራ አመራር ቦርድ የኮርፖሬሽኑን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻፀም በሚዛን አማን ከተማ ገምግሟል፡፡

በግምገማ መድረኩ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ፍቅሬ ኃይሌ የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ከባለፈው በጀት አመት የዞሩ ሶስት ነባር ፕሮጀክቶችን ጨምሮ 10 አዳዲስ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ በዝርዝር አስረድተዋል፡፡

የቦርዱ አባላትም በቀረበው ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ፕሮጀክቶችን በሚቀበልበት ወቅት የመፈፀም አቅሙን ፣ የገበያ ተለዋዋጭነትንና የተለያዩ ወቅታዊና ከባባዊ ሁኔታዎችን ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት መረከብ እንዳለበት ያሳሰቡት የቦርዱ አባላት በዚህም ውጤታማ ሥራ ሰርቶ ተቋማዊ አመኔታን ማትረፍ እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡

የቦርዱ አባላት አክለውም የኮርፖሬሽኑ ማኔጅመንት ጥራት ያለውና ቀልጣፋ የፕሮጀክት አፈፃፀም መርህን በመከተል የክልሉን ልማት በማቀላጠፍ ረገድ መሪ ተዋናይ ተቋም መሆኑን አለበት ብለዋል፡፡

የኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢና የክልሉ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው የሥራ አመራር ቦርዱ አባላት የፕሮጀክቶችን አፈጻፀም ከሪፖርት ባሻገር በአካል በማየት እየደገፉ በመምጣታቸው መልካም አፈጻፀም እየታየ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የቁጠባ አሠራርን በመዘርጋት ተቋሙን ማስቀጠል፣ የፕሮጀክት አፈፃፀምን ማዘመን፣ ሎጅስቲክ ላይ የሚስተዋለውን ክፍተት ህግና ስርዓትን ተከትሎ ማሻሻል እና የአሠሪ ተቋማትን አቅም ቀደም ብለው በመገምገም ኮርፖሬሽኑ ወደ ሥራ መግባት እንዳለበት ያስገነዘቡት ኢንጂነር በየነ ፈጠራን፣ ፍጥነትንና ጥራትን በማቀናጀት በሁሉም ተመራጭና የታመነ የኮንስትራክሽን ተቋም መሆን አንዳለበት አሳስበዋል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ተስፋ ሰጭ አፈፃፀም ላይ መሆኑን የተናገሩት ኢንጂነር በየነ ዘመናዊና ውጤታማ የፕሮጀክት አስተዳደር ዘዴን በመከተል፣ ህጋዊ የሎጅስቲክና ግዥ አሠራር መመሪያን በመጠቀምና ጠንካራ የፋይናንስና ኦዲት ስርዓትን በመከተል የኮርፖሬሽኑን ትርፋማነት ማረጋገጥ እንዳለበት ጠቁመዋል።

RCFS ኘሮጄክት ትኩረቱ የመንገድ ግንባታ በመሥራት  ለግብርና ምርትና ምርታማነት መጨመር የሚያግዝ ነው:_ አቶ ፋጂዮ ሳፒ የገጠር ትስስር  ተደራሽ ለምግብ ዋስትና ( RCFS) ኘሮጄክት የእ...
15/04/2025

RCFS ኘሮጄክት ትኩረቱ የመንገድ ግንባታ በመሥራት ለግብርና ምርትና ምርታማነት መጨመር የሚያግዝ ነው:_ አቶ ፋጂዮ ሳፒ

የገጠር ትስስር ተደራሽ ለምግብ ዋስትና ( RCFS) ኘሮጄክት የእስትሪንግ ኮሚቴ ውይይት ተጠናቋል
ኘሮጀክቱ በክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሥር ለ5 ዓመታት የሚተገበር ሲሆን የኘሮጄክቱ ዋና አላማ የገጠር ቀበሌዎችን ከዋና መንገድ በማገናኘት አርሶና አርብቶአደሩን የሚያመርተውን ምርት ወደ ገበያ በማቅረብ የተሻለ ህይወት እንዲኖረው እንደሆነ ገልጸዋል።

በእስትርንግ ኮሚቴ ውይይት የተናገሩት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ RCFS ኘሮጄክት የመንገድ ግንባታ በመስራት ለግብርና ምርትና ምርታማነት መጨመር የሚያግዝ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ቅንጂታዊ በጋራ መስራት እንደሚጠይቅ ተናግረዋል።

ክልሉ በርካታ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ያሉት ክልል በመሆኑ አዳድስ ኘሮግራሞችና ኘሮጄክቶች ማግኘት እድለኝነት መሆኑን ተናግረዋል።.

ቢሮ ም/ኃላፊና የሁሉ አቀፍ የገጠር ተደራሽ መንገድ ዘርፍ ኃላፊ ኢንጂነር ጌዲዮን እስጥፋኖስ ስነድ ስያቀርቡ እንተናገሩት ኘሮጄክት በክልሉ በሚገኙት በ6 ወረዳዎ የመንገድ ግንባታ ፤ የመንገድ ጥገና፤ እስትራክቸሮች እንደሚገነባ በኘሮግራሞቹ የታወቀ ሲሆን እስከአሁን ባለው የጀመራቸው የዚህ ዓመት የመንገድ ጥገና በውጤታማ መንገድ እያከናወነ መሆኑ ተገልጿል።

የእስትሪንግ ኮሚቴዎች አባላት ያነሱዋቸው ጥያቄዎችና ማብራሪያ ተስጥተው ውይይቱ ተጠናቋል።

በመሠረተ ልማት ዘርፍ የሚከናወኑ ሥራዎች በትጋትና በላቀ ቁርጠኝነት በመሥራት ህዝባችን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል:- አቶ ፋጂዮ ሳፒየደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመሠረተ ልማት ክላስተ...
14/04/2025

በመሠረተ ልማት ዘርፍ የሚከናወኑ ሥራዎች በትጋትና በላቀ ቁርጠኝነት በመሥራት ህዝባችን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል:- አቶ ፋጂዮ ሳፒ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመሠረተ ልማት ክላስተር የ2017 በጀት አመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም በሚዛን አማን ከተማ እየተገመገመ ነው።

በውይይት መድረክ መልእከት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ በመሠረተ ልማት ዘርፍ የሚከናወኑ ሥራዎች በትጋትና በላቀ ቁርጠኝነት በመሥራት ህዝባችን የልማቱ ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል

አቶ ፋጂዮ አክለውም የመሠረተ ልማት ዘርፍ ስራዎች ብዙ ሀብት የሚፈልግ በመሆኑ ህብረተሰቡን በማስተባበርና በማቀናጀት መስራት ይጠበቃል ብለዋል

በመድረኩ የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ፣ የውሃና ማዕድን ፣ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን እንዲሁም የአርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮ የ2017 በጀት አመት የ9 ወራት አፈፃፁም እያቀረቡ ነው።

በምዕራብ ኦሞ እና በቤንች ሸኮ ዞኖች በትራንስፖርት የስምሪት አሰጣጥ ሥራዎች ዙሪያ በጀሙ ከተማ ዉይይት ተደርጓል። ሁለቱ ዞኖችበስምረት አስጣጥ በቅንጂታዊ  ሥራዎች ላይ ያተኮረ ውይይትበጀሙ ...
12/04/2025

በምዕራብ ኦሞ እና በቤንች ሸኮ ዞኖች በትራንስፖርት የስምሪት አሰጣጥ ሥራዎች ዙሪያ በጀሙ ከተማ ዉይይት ተደርጓል።

ሁለቱ ዞኖችበስምረት አስጣጥ በቅንጂታዊ ሥራዎች ላይ ያተኮረ ውይይትበጀሙ ከተማ አድርጓል።

ከቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ከሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ጽ/ቤት እና ሚዛን አማን ካሉ 3ቱ የህዝብ ማመላለሻ ማህበራት ከተወጣጡ ሉዕካን ቡድን ከምዕራብ ኦሞ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ጋር በጋራ የስምሪት መስመሮች ዙሪያ መክሯል።

በመድረኩ የምዕራብ ኦሞ ዞን ምክትል አስተዳደር እና የመንገድ ትራንስፖርት መምሪያ ሃላፊ አቶ ባርኮሮ እንደተናገሩት በዋነኝነት የሚዛን-ቱም መስመር ለውጥ ያሳየ ቢሆንም ቀጣይ ተጨማሪ ስራ እንሚጠይቅ እና መጪው ግዜ በዓል ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሁለቱ ዞኖች ቅንጅት መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል።

በመድረኩ የጋራ የስምሪት መስመሮችን ሂደት በየሶስት ወሩ እየተገናኙ እንደሚገመግሙ በመስማማት ውይይቱ ተጠናቋል።

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ በሚገነቡ የመንገድ ፕሮጀክቶች ዙሪያ ከኢትዮጵያ  መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በጽ/ቤታቸው ተወያዩየደቡብ ምዕራብ ...
11/04/2025

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ በሚገነቡ የመንገድ ፕሮጀክቶች ዙሪያ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በጽ/ቤታቸው ተወያዩ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ስር በሚገነቡ የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ ዓላማ ያደረገ ውይይት ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በጽ/ቤታቸው አድርገዋል።

ውይይቱ በዋናነት የዲሪ _ማሻ እና የታርጫ- ጪዳ የአስፓልት መንገድ ፕሮጀክቶችን እንደገና ሥራ ማስጀመር በሚያስችል ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነዉ።

ከዚህም በተጨማሪ ሌሎች በክልሉ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሥር የሚገነቡ የመንገድ ፕሮጀክቶችን በሚመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ ውይይት ተደርጓል።

ግንባታቸዉ ተጀምሮ የቆሙ እና የተጓተቱ ፣አስቸኳይ ጥገና የሚያስፈልጋቸው እንዲሁም ከካሳ ክፊያ መዘግየት ተያይዞ ባሉ ጉዳዮች ብሎም የአከባቢው የግንባታ እቃዎች እና ቀጣይ ትኩረት በሚጠይቅባቸዉ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት ተወያይተዋል።

በውይይቱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በክልሉ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ስር የሚገነቡ የመንገድ ፕሮጀክቶች አስፈላጊ ድጋፍ ተደርገው ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትኩረት መስራትን ይጠይቃል።

ግንባታቸዉ ተጀምሮ የቆሙትን ወደ ሥራ ማስገባት ፣ አስቸኳይ ጥገና የሚያስፈልጋቸውን መጠገን፣ ተጀምሮ የተጓተቱ ፕሮጀክቶች እንዲፋጠኑ ማድረግ ያስፈልጋል ይ ነዉ ያሉት።

ርዕሰ መስተዳድሩ አያይዘውም ለሥራዎች ማነቆ ሊሆኑ የሚችሉ ካሳ ክፊያ እና ለሌሎች ጉዳዮች መፍትሔ በማበጀት በየደረጃው ከሚመለከታቸው አካላት በጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ነዉ የጠቆሙት።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሂሩት ዮሐንስ በውይይቱ እንዳሉት በክልሉ በኢትዮጽያ መንገዶች አስተዳደር የሚገነቡ የዲሪ _ማሻ እና የታርጫ- ጪዳ የአስፋልት መንገድ ፕሮጀክቶችን እንደገና ወደ ሥራ ለማስገባት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑን ገልጸዋል።

የቆሙትን እንደገና ሥራ ማስጀመር እንደተጠበቀ ሆነዉ፣ አዲስ ዲዛይን ሥራ ለሚፈልጉት ጥናትና ዲዛይን ማድረግ፣ ግንባታቸው የተጓተቱን ለማፋጠን ይሰራል ያሉት ኢንጂነር ሂሩት በክልሉ መንግሥት በኩል መፈታት የሚገቡ ጉዳዮች ትኩረት እንዲሰጥባቸውም ጠይቀዋል።

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በRCFS  ፕሮግራም ለሚያከናውናቸው የመንገድና የስትራክቸር ሥራዎች የዲዛንና የአማካሪ ማህበራት ጋር የውል ስምምነት ተፈራረሙ ሚያዝያ 2/2017 ዓ....
10/04/2025

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በRCFS ፕሮግራም ለሚያከናውናቸው የመንገድና የስትራክቸር ሥራዎች የዲዛንና የአማካሪ ማህበራት ጋር የውል ስምምነት ተፈራረሙ

ሚያዝያ 2/2017 ዓ.ም

ቢሮ በRCFS (የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና) ፕሮግራም የሚያከናውናቸው የመንገድና የስትራክቸር ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የዲዛይንና የማማከር ሥራዎች እንዲያከናውኑ በ3 ሎት ውል መገባቱን አቶ ፋጂዮ ሳፒ ተናግረዋል ።

ፕሮጀክቶች የያዘውን አላማ ስኬታማ እንዲሆን ብቃት ያለው ዲዛይን ከማዘጋጀት ጀምሮ የማማከር ሥራ ወሳኝ በመሆኑ ውል የገቡ አማካሪዎች ሚናቸው የጎላ መሆኑን ነው የተገለጸው።

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለይቶ በመፋታት በትራንስፖርትና በመንገድ ዘርፍ የአገልግሎት አሠጣጥ  ማሻሻል እንደሚገባ :__አቶ ፋጂዮ ሳፒ ገለፁ።  ቢሮ በመልካም አስተዳደር ሰነድና ዙሪያ ከ...
09/04/2025

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለይቶ በመፋታት በትራንስፖርትና በመንገድ ዘርፍ የአገልግሎት አሠጣጥ ማሻሻል እንደሚገባ :__አቶ ፋጂዮ ሳፒ ገለፁ።

ቢሮ በመልካም አስተዳደር ሰነድና ዙሪያ ከማኔጅመንት አባላት ጋር ውይይት አድርጓል።

የውይይት የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጅዋ ሳፒ እንደገለፁት በትራንስፖርትና በመንገድ ዘርፍ የሚታየው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለይቶ በመፋታት የአገልግሎት አሠጣጥ ማሻሻል እንደሚገባ ተናግረዋል።

የትራንስፖርትና መንገድ ዘርፍ ሥራ በባህሪው የባለድርሻ አካላት እንዲሁም የህብረተሰብ ተሳትፎ እገዛ የሚጠይቅ ገልግሎት ሠጪ ተቋም በመሆኑ ህብረተሰቡን የሚያማርሩ ነጥቦችን ለይቶ በመፍታት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
የቀረበው የመልካም አስተዳደር ሰነድ በማኔጅመንት አባላት የተሰጠውን አስተያየት ተካቶ ከቢሮ ጀምሮ በየደረጃው ላሉት የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ መዋቅሮች ለመገምገሚያነት እንደሚያገለግል ተገልጿል

በስሜን ቤንች ወረዳ የሚታየው የመንገድ መሠረተ ልማት ችግር በአፋጣኝ ምላሽ  ለመስጠት ወረዳው የሚያደረገውን ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የቤንች ሸኮ ዞን ተራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ገ...
01/04/2025

በስሜን ቤንች ወረዳ የሚታየው የመንገድ መሠረተ ልማት ችግር በአፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ወረዳው የሚያደረገውን ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የቤንች ሸኮ ዞን ተራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ገለጸ።
መምሪያው በቦታው ተገኝተው ምልከታ ካደረጉ 250ሽህ ብር በዞኑ ስም ለመደገፍ ቃል ገብተዋል።
ሚዛን አማን ፦መጋቢት 23/2017 ዓ.ም

በሰሜን ቤንች ወረዳ ጠ/ያዥ -ቲሹ -ጋይዝቅን -ጎ/ማግ እና ኡፅቅን- ጎ/ማግ የመንገድ ልማት ሥራን የቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖርት መንገድ ልማት መመሪያ ኃላፊ አቶ አበበ ኑራ፤የሰሜን ቤንች ወረዳ ትራንስፖርት መንገድ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰረት ሻንባል እንድሁም የዞኑና የወረዳ የትራንስፖርት መንገድ ማኔጀመንት አካላት በተገኙበት የመስክ ምልከታ ተድርገዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖርት መንገድ ልማት መመሪያ ኃላፊ አቶ አበበ ኑራ ምልከታውን ባደረጉት ወቅት እንደገለፁት በወረዳው የመንገድ ልማት ሥራ ለማህበረሰቡ ትክክለኛውንና ተገቢውን ውጤታማ አገልግሎት መስጠት እንዲቻል እየተሰራ ያለው የመንገድ ልማት ስራ የሚበረታታ ነው ሲሉ ገልጾ ወቅቱ የክረምት ወራት ስለሆነ ኮረት የማልበሰና የመበተን ስራ በጥራትና በፍጥነት መሠራት እንዳለበት ተናግረዋል።

የሰሜን ቤንች ወረዳ ትራንስፖርት መንገድ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሠረት ሻንባል በጉብኝቱ ዕለት እንደገለፁት በመንገድ ችግር ማህበረሰቡ ረጅም ጊዜያትን ለእንግልት የተዳረገ መሆኑን በመጠቆም ችግሩን ለመቅረፍ ዞን እያደረገ ያለውን ክትትልና ድጋፍ አድንቀው በህዝቡ ስምም አመስግነዋል።

አቶ መሠረት ሻንባል አክለውም ወረዳችን የህዝቡን የመሠረተ ልማት ጥያቄ በተቻለ አቅም ደረጃ በደረጃ እየፈታ የመጣ መሆኑን ጠቅሶ በተያያዘው በጀት አመት በመደበኛና በመንግሥት በጀትና ማህበረሰቡን በማነቃቃት ዘረፈ ብዙ የመንገድ ልማት ስራ ለመሥራት ዕቅድ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑን ገልፆ እሰካሁን ጥርጊያና ከፈታ ስራ 26.5 ኪ/ሜ ታቀደው 40.5 ኪ/ሜ ከዕቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

የዋላ እና ጎላ ቀበሌ መንገድ በተመሳሳይ ጠጠር የመበተን እና ጥገና ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታውሰው ባጠቃላይ ጥርጊያና ቦይ የማውጣት ስራ በተጠናቀቀባቸው መንገዶች ላይ ወቅቱ የዝናብ ከመሆኑም ጋር ተያይዞ ጠጠር የማድፋትና ኮረት የማልበስ ስራ መሠራት ጀምሯል ብለዋል።

በወረዳው እየተሰራ ያለውን የመንገድ ጥገናና ጥርጊያ እንድሁም ከፈታ ሥራ በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የትራንስፖርት መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊና የማኔጅመንት አካላት መስክ ምልከታ ካደረጉ ቦኃላ በዞኑ መንግስት ስም የማበረታቻ 250ሺህ ብር ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብቷል።

በመጨረሻም መንገድ የአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ዕድገት መሠረት ስለሆነ የመንገድ መሠረተ ልማት ማስፋፋት ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በጉብኝቱ ተገልጿል።

ለRCAP ኘሮጄክ ውጤታማነት የቴክኒክ ኮሚቴ ሙያዊ  ድጋፍ በተገቢ ማድረግ እንደሚገባ አቶ ፋጂዮ ሳፒ ተናግረዋል። የRCAP ኘጄክት የቴክኒክ ኮሚቴ የውይይት መድረክ በሚዛን አማን ተካሄዷል።ኘ...
01/04/2025

ለRCAP ኘሮጄክ ውጤታማነት የቴክኒክ ኮሚቴ ሙያዊ ድጋፍ በተገቢ ማድረግ እንደሚገባ አቶ ፋጂዮ ሳፒ ተናግረዋል።
የRCAP ኘጄክት የቴክኒክ ኮሚቴ የውይይት መድረክ በሚዛን አማን ተካሄዷል።

ኘሮጄክቱ ከዝግጂት ምዕራፍ ጀምሮ በርካታ ተግባራት ያከናውነ ሲሆን ሥራውን ቴክኒካል የሚያስኬዱ የቴክኒክ ኮሚቴ ውይይት ዛሬበሚዛን አማን ከተማ አካሄዱዋል።

በውይይቱ መልክት ያስተላለፈው በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ እንደተናገሩት RCAP ኘሮጀክት በመንግሥት የሚታዩት የልማት ክፍተቶችን በመሸፈን አጋዥ የሆነ ኘሮጄክት መሆኑ ተናግረዋል።.

ኘሮጄክቱ ውጤታማ እንዲሆን ከዚህ በፍትህ እስትሪንግ ኮሚቴ የተደራጀ ሲሆን አሁን የቴክኒክ ኮሚቴ ማቋቋም ወሳኝ መሆኑን ተናግረው ቴክኒክ ኮሚቴ ኃላፊነቱና ተግባራት ከፍ ያለ እንደሆነ ገልጸዋል ።

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ም/ቢሮ ኃላፊና የሁሉ አቀፍ የገጠር ተደራሽ መንገድ ልማት ዘርፍ ኃላፊ ኢንጂነር ጌዲዮን እስጥፋኖስ ለቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀውን ሠነድ ያቀረበ ሲሆን በሰነዱም ቴክኒክ ኮሚቴ ኃላፊነትና ተግባራት መካተቱን ተመላክቱዋል።

ኘሮጄክቱ በ2017ዓ/ም የሚከናወኑ ተግባራት መጀመሩን ገልጸው በቀጣይ ቀሪ አመታት የመንገድ ግንባታ ፤ የመንገድ ጥገና፤ተንጠልጣይ ድልድይ እና ልዩ እስትራክቸሮች እንደሚገነባ ኢንጂነር ጌዲዮን እስጥፋኖስ ገልጸዋል።

በውይይቱ ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተስጥተው ውይይቱ ተጠናቋል።

Address


Telephone

+251917154319

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South West Ethiopia people RegionaState Gov.t Transport & Road Dev.t Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share