Dicha Media

Dicha Media This is Official facebook Page of Dicha Media

for more information contact us on telegram Bot

Pretty talented actors Henok Wondimu in Gym 🏋️‍♂️ 💪
19/07/2025

Pretty talented actors Henok Wondimu in Gym 🏋️‍♂️ 💪

♦በድጋሚ ለቅሶ ሆነ የሁሉም ልብ ተነካ የአርባምንጭ እና የኢትዮጵያ ልጅ የኔ በሚላቸው ሰዎች እጅ ህይወቱ አለፈች!"በሚስቱ እና በሚስቱ እህት ባል እንደተገደለ ፍርድ ቤት አረጋገጠ" ! በጣም...
19/07/2025

♦በድጋሚ ለቅሶ ሆነ የሁሉም ልብ ተነካ የአርባምንጭ እና የኢትዮጵያ ልጅ የኔ በሚላቸው ሰዎች እጅ ህይወቱ አለፈች!

"በሚስቱ እና በሚስቱ እህት ባል እንደተገደለ ፍርድ ቤት አረጋገጠ" ! በጣም ያማል 🥺💔🥺

የአርባምንጭ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊያን ደግሞ
"ስርዓተ ፍትሃት እንዲደረግለት እንጠብቃለን" አልን!

ይህ ልጅ በህይወት ዘመኑ ላይ በተገለጡ ስኬት እና ድሉ ላይ ሁሉ ቅድስት ቤተክርስቲያን አብራው እንድትገለጥ አድርጎ አልፏል።

ህገወጥ ጵጵስና ወቅት እንደ ታዋቂ ተጫዋች ሳይሆን እንደ ተራ ምዕመን " ለምን?" ብሎ ተሟግቷል። በእዛ በገነነበት ዘመኑ እንኳን እርሱ ለቤተክርስቲያን ምንም እንደሆነ አምኖ በጥምቀት በዓል ወቅት ለታቦት ምንጣፍ እያነጠፈ በታናሽነት ያገለግል ነበር።

ኳስ ለመመልከት ብቻ አስቦ በመጣ ህዝብ መሃል ከክብረ ቅዱሳን እስከ ክብረ ማርያምን አግዝፎ ስብኳል።

ወጣቶች በውድቀታቸው ሰዓት ሱስ ውስጥ ሳይሆን ቅድስት ቤተክርስቲያን አጸድ ውስጥ ሄደው መውደቅ እንዳለባቸው እርሱ በደከመበት ሰዓት ተመላልሶ አሳይቶ አርዓያ ሆኗል። ትዳር በዳንኪራ ሳይሆን በአርምሞ በቅዱስ ቁርባን እንደሚከብር ሆኖ አሳይቷል።

ነገር ግን ድራማ በበዛበት ትርዒት ነፍሱ በሰዎች እጅ ተነጠቀ። በህይወት እያለ ያከበራት እና የገለጣት ቤተክርስቲያን እንኳን በትርዒቱ ተዘናግታ ስርዓተ ፍትሃት ሳትፈጽምለት እንደ ኢአማኝ ተቀበረ። በህይወት ዘመኑ ካልተለያት ቅድስት ቤተክርስቲያን እንኳን ሞቱን ለዩ።

ወጣቶች በቤተክርስቲያን አውደ ምህረት እርሱን ለመዘከር አስበው ስርዓት ስለማይፈቅድ እየተቃጠሉ እንባቸውን ወደ ውስጥ አፍስሰው አለፈ።

ዛሬ ይህ ሁሉ የተሸፋፈነ ድራማ ተገልጦ የሀገር እና የቤተክርስቲያን ድንቅ ልጅ በተቀነባበረ መልኩ በሚስቱ እና በሚስቱ እህት ባል እንደተገደለ ፍርድ ቤት አረጋገጠ። በጣም ያማል።

ይህቺ ነፍስ ድጋሚ ሐዘን እና ለቅሶ ይገባታል? አይገባትም። ምክንያቱም ይህ ልጅ ሞቶ የሚበሰብስ የሰዶቃውያን ዘር ሳይሆን በየምስራች ቃል በክብር የሚነሳ በሥጋ ወደሙ የታተመ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ነው።

ነፍስ ይማርልን!
አሌ የቤተክርስቲያን ልጅ ነበረ በጣም አዝነናል ነፍስ ይማር
Andualem Degefu

ቤት ማማጥ እና መዉለድ ለምን አይመከርም ❓ዶ/ር ጌታሁን ወዳሎእርግዝናም ሆነ ወሊድ በራሱ በሽታ አይደለም ይልቁንስ ተፈጥሯዊ ዑደት ነዉ እንጂ። ስለዚህም ነዉ ወላድ እናቶች ታማሚ ሳይሆን ደም...
19/07/2025

ቤት ማማጥ እና መዉለድ ለምን አይመከርም ❓ዶ/ር ጌታሁን ወዳሎ

እርግዝናም ሆነ ወሊድ በራሱ በሽታ አይደለም ይልቁንስ ተፈጥሯዊ ዑደት ነዉ እንጂ። ስለዚህም ነዉ ወላድ እናቶች ታማሚ ሳይሆን ደምበኞች(Clients)ተብሎ የሚጠሩት።

ወሊድ አብዛኛዉን ጊዜ ተፈጥሯዊ ህደቱን ተከትሎ በሰላም ልጠናቀቅ ይችላል። ድሮ እናቶችም ቤት ይወልዱ ነበር፤ ይሞቱም ነበር! ለዚያም ይመስለኛል እርግዝና ነፍሰ ጡር(በአማርኛ)፣ አበ እጠታ(በወላይትኛ) ፣....የምሉ የሚሰቀጥጡ ስሞች የሚጠራዉ። ታድያ እነዚህ ቀሪዎቹ ጥቅቶች ምን ያጋጥማቸዋል ካላችሁ ከፍተኛ ደም መፍሰስ(postpartum hemorrhage)፣ የማህጸን በር አካባቢ መሰንጠቅ(እስከ ፍንጥጣም ልደርስ ይችላል)/Perineal tear/፣ እርግዝና ጋር የተያያዘ የደም ግፊትና ተያይዞ የሚመጣ ማንቀጥቀጥና ራስን መሳት(Preeclampsia and eclampsia)....ወዘተ። በጊዜ ህክምና ካልተሰጠ እነዚህ ገዳይ ናቸዉ።

እነዚህ ክስተቶች መች እና በማን እንደሚከሰቱ መገመት ስለሚያዳግት ሁሉም እናቶች በጤና ተቋም ከወለዱ አስፈላጊ መድኃኒቶች እና ሌሎች ህክምናዎችን በመስጠት የእናትን ሞት በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ይቻላል። እናት አንድ አይደለችም፤ ህዝብ ነች እንጂ!
መንግስት አገልግሎቱ እንዲሰጥ በማስቻል ኃላፊነቱን ለመወጣት እየሞከረ ያለ ሲሆን ህዝብ በግልም ሆነ በመንግስት ጤና ተቋም የአገልግሎቱ ተጠቃሚ በመሆን ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል። 👉የሚታየንን እሾህ እያነሳን ጉዟችን እንቀጥል!

ዶ/ር ጌታሁን ወዳሎ(የማህጸንና ጽንስ ህክምና ስፔሻሊስት ሐኪም)

የተደገሰለትን ያላውቀው አለልኝ አርሴማፀበል ሊሄድ ቀጠሮ ይዞ ነበርበቁርባን ያገባት ሚስቱ💔1.አለልኝ ከሚወደው ቤተክርስቲያን አጣልታዋለችፍትህት እንዳይደረግለት ራሱን እንዳጠፋ ተናግራለች።2....
19/07/2025

የተደገሰለትን ያላውቀው አለልኝ አርሴማ
ፀበል ሊሄድ ቀጠሮ ይዞ ነበር

በቁርባን ያገባት ሚስቱ

💔

1.አለልኝ ከሚወደው ቤተክርስቲያን አጣልታዋለች
ፍትህት እንዳይደረግለት ራሱን እንዳጠፋ ተናግራለች።

2. አለልኝ በሞተበት ቀን የአብይ ጾም እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ ጾሞ የነበረ ጾመኛ ነበር።

3. በዚያው ቀን መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አስቀድሶም ነበር።

4. በግራ እግሩ ላይ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን፣ "እግሬን!" እያለ ነበር እና ለረጅም ጊዜ መቆም አይችልም ነበር።

5. በማግስቱ ፀበል ሊጠመቅ አስቦ በማለዳ ተነስቶ አርሴማ ጸበል ለመሄድ አቅዶ ነበር፣

6. የቤተሰቡን ቤት በማሰራት ላይ ነበር።

7. በሞተበት ቀን ምሽት 3 ሰዓት ላይ የእናቱ ቤት መጥቶ "እናቴስ?" ብሎ ከጠየቀ በኋላ ወደ ባለቤቱ ጋር እንደሄደ ተገልጿል። ነገር ግን የዛን እለት ምሽት ለእሱ የተደገሰለትን አያውቅም ነበር።

ይህ አሳዛኝ ክስተት መላው ቤተሰብንና ወዳጅ
ዘመድን በሀዘን አጥቅቷል።

የአለልኝ አዘነ ሚስት

በሕይወት መንገድ ላይ ማንም ሰው የነገን አያውቅም። አለልኝ አዘነ ከባለቤቱ ጋር የ9 ዓመት የፍቅር ግንኙነት የነበራቸውና ከልጅነታቸው ጀምሮ በፍቅር የኖሩ ነበሩ......

ወንድሜ .....

ዛሬ ያመንከው፣
ዛሬ ያፈቀርከው፣
ዛሬ የኖርክለት— ነገ የመጥፊያህ ምክንያት ሊሆን ይችላል።

የአለልኝ የሚስቱ እህት ባል የሆነው ሉንጓ ሉቃስ በአለልኝ ሞት ውስጥ ጥፋተኛ የተባለው ይህ ሲሆን:

የአለልኝ የቀብር እለት የአለልኝን ፎቶ ያለበትን ቲሸርት ለብሶ ሀዘንተኛ መስሎ ሲታይ አይተነዋል።

ማን ይታመንስ ይሆን ?

💔

 #እናመስግናለን 👉ALAAS KITCHENALAAS KITCHEN ቦታ አመቻችቶ ዛሬ እጅጉን በጣም በተለየ በተዋበ ሁኔታ 32ኛ ዙር ውይይታችን ተደርጓል። በልህቀት የንባብ ክበብ የዛሬ ውይይት በ...
18/07/2025

#እናመስግናለን 👉ALAAS KITCHEN

ALAAS KITCHEN ቦታ አመቻችቶ ዛሬ እጅጉን በጣም በተለየ በተዋበ ሁኔታ 32ኛ ዙር ውይይታችን ተደርጓል። በልህቀት የንባብ ክበብ የዛሬ ውይይት በርካታ አዳዲስ አባላት ተገኝተውበታል። ተወዳጁን ምን ሆኛለሁ መፅሐፍ ጀምረናል። ስለ ልጅነት ወቅት ጠባሳ(Trauma) ተወያይተናል።

ሻይ ቡናውን ማኪያቶ ሬንጀሩን ከፋንድሻው ከእጣኑ ጋር ባማረ ሀበሻዊ አቀራረብ በነፃ አቅርቦልናል በሶዶ ከተማ በግሩም ምግቦችና በምርጥ የጀበና እና የስቲም ቡና የሚታወቀው አላስ ኪችን። አላስ ኪችን የንባብ ባህልን ለማሳደግ ከጎናችን ስለነበረ በክበቡ ስም ከልብ እናመሰግናለን!.. 33ኛ ዙር ውይይታችን ሐምሌ 25 ይደረጋል

👉ልህቀት የንባብ ክበብ

ቀጣይ ውይይት እኛ ይደረግ የሚትሉ ካላችሁ Inbox አድርጉ👉 Tilahun Hussen 👉Hiwotu Desalgn
ዛሬ ቆንጆ ጊዜ ነበረን 🙏🙏

18/07/2025

Azinay ixxiyo machchiyo giyay sugees giida!

Wolaita Proverbs

ይህ ፔጅ ለማስታወቂያ ክፍት ነው‼️This Page is open for Advertisement‼️ የተከበራችሁ የገፃችን ቤተሰቦች  #ከ200 መቶ ሺ በላይ ተከታይ እና በአንድ ወር  #ከ20 ሚሊ...
18/07/2025

ይህ ፔጅ ለማስታወቂያ ክፍት ነው‼️
This Page is open for Advertisement‼️

የተከበራችሁ የገፃችን ቤተሰቦች #ከ200 መቶ ሺ በላይ ተከታይ እና በአንድ ወር #ከ20 ሚሊዮን በላይ እይታ ባለው ፔጃችን ምርት፣ አገልግሎታችሁን እና ድርጅትዎን ያስተዋወቁ ።
ለበለጠ መረጃ በውስጥ መስመር ያናግሩ 🙏

ጀግናዋ አትሌታችን ብርሀኔ አደሬ ❤ ዛሬ ይህቺ ጀግና አትሌታችን ማይክል ጃክሰንን መስላ መታየቷ ብዙዎችን እያነጋገረ ይገኛል 🙂 በነገራችን ላይ.. ብርሀኔ አደሬ ከአትሌቲክስ ባሻገር ሀይለኛ ...
18/07/2025

ጀግናዋ አትሌታችን ብርሀኔ አደሬ ❤ ዛሬ ይህቺ ጀግና አትሌታችን ማይክል ጃክሰንን መስላ መታየቷ ብዙዎችን እያነጋገረ ይገኛል 🙂
በነገራችን ላይ.. ብርሀኔ አደሬ ከአትሌቲክስ ባሻገር ሀይለኛ ኢንቬስተርም ናት። ከተማችን ላይ ከሚገኙ ባለሀብቶች መካከል አንዷ ናት። መገናኛ አካባቢ ለሁሉም አትሌቶች የተሰጠ የህንፃ መስሪያ ስፍራ ላይም እጅግ ግዙፍ ህንፃ አላት ፤ Berhane Adere Mall የሚባል።
ግብርናን ጨምሮ በሌሎችም በርካታ የኢንቨስትመንት ስራዎች ላይ ትሳተፋለች። ብርሀኔ አደሬ ከ 1984 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2004 ዓ.ም እጅግ በርካታ የሩጫ ውድድሮችን አድርጋለች። በዚህም በተደጋጋሚ አሸንፋለች።
ለረጅም ጊዜ ከሮጡ ቀደምት አትሌቶቻችንም መካከል አንዷ ናት። She retired in 2004. ብርሀኔ መኳኳልና መቀባባት የማያስፈልጋት እንቋችን ናት። መቼስ ሜካፕ መጠቀም ይሻለኛል ካለችን ግን ምን ይደረጋል 🙏

18/07/2025

የአለልኝ አዘነ ታሪክ💔

ነፍስህ በሰላም ትረፍ😭

ታላቅ የአምልኮ ድግስ በሚሊንየም አዳራሽ!!"ለኢየሱስ" በሚል ርእስ ለሐምሌ 26 በሚሊንየም አዳራሽ ሊደረግ የታቀደውን የመዝሙር ድግስ በሚመለከት ጋዜጣዊ መግለጫ በሳሮማርያ ሆቴል ተደረገ የተ...
18/07/2025

ታላቅ የአምልኮ ድግስ በሚሊንየም አዳራሽ!!

"ለኢየሱስ" በሚል ርእስ ለሐምሌ 26 በሚሊንየም አዳራሽ ሊደረግ የታቀደውን የመዝሙር ድግስ በሚመለከት ጋዜጣዊ መግለጫ በሳሮማርያ ሆቴል ተደረገ የተለያዩ የሚድያ አካላት እና ተጋባዦች በተገኙበት በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል፡፡

በእለቱም የፀሎት መርሃግብር ፣ የህይወት ምስክርነት ፣ የዝማሬ እና የአምልኮ ጊዜ ፣ የወንጌል ትምህርት ፣ የአዳዲስ ነፍሳት ጥሪ የሚኖር ሲሆን ሁሉም ሰው ነጭ ለብሶ እንዲመጣ ተጠይቋል::

መጋቢ ትዝታው ሳሙኤል ከሃገር ውጭ ባለው አጥብያ ቤተ ክርስትያን በዝማሬ እና ስብከት ሲያገለግል የቆየ ሲሆን ይኖርበት ከነበረው ሃገር ከመጣ በሗላ እጅግ በርካታ ህዝበ ምዕመን በተሰበሰበበት ይህን መሳይ መርሃ ግብር ላይ ሲያገለግል ይሄ የመጀመሪያው ነው::

አዘጋጆቹ ስለ ዝግጅቱ ዓላማ ሲያብራሩ " የእግዚአብሔር ልጅ መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዝማሬ ማምለክ ወንጌልን በማወጅ እና ጥሪ በማድረግ አዳዲስ ነፍሳትን ለክርስቶስ መማረክ ለምድራችን እና ለህዝባችን መልዕክት ማድረስ እና መጸለይ ነው" ብለዋል::

ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን
ፓስተር ትዝታዉ ሳሙኤል

በድጋሚ ለቅሶ ሆነ የሁሉም ልብ ተነካ የአርባምንጭ እና የኢትዮጵያ ልጅ የኔ በሚላቸው ሰዎች እጅ ህይወቱ አለፈች!"በሚስቱ እና በሚስቱ እህት ባል እንደተገደለ ፍርድ ቤት አረጋገጠ" ! በጣም ...
18/07/2025

በድጋሚ ለቅሶ ሆነ የሁሉም ልብ ተነካ የአርባምንጭ እና የኢትዮጵያ ልጅ የኔ በሚላቸው ሰዎች እጅ ህይወቱ አለፈች!

"በሚስቱ እና በሚስቱ እህት ባል እንደተገደለ ፍርድ ቤት አረጋገጠ" ! በጣም ያማል 😭💔😭
የአርባምንጭ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊያን ደግሞ
"ስርዓተ ፍትሃት እንዲደረግለት እንጠብቃለን" አልን!

ይህ ልጅ በህይወት ዘመኑ ላይ በተገለጡ ስኬት እና ድሉ ላይ ሁሉ ቅድስት ቤተክርስቲያን አብራው እንድትገለጥ አድርጎ አልፏል።

ህገወጥ ጵጵስና ወቅት እንደ ታዋቂ ተጫዋች ሳይሆን እንደ ተራ ምዕመን " ለምን?" ብሎ ተሟግቷል። በእዛ በገነነበት ዘመኑ እንኳን እርሱ ለቤተክርስቲያን ምንም እንደሆነ አምኖ በጥምቀት በዓል ወቅት ለታቦት ምንጣፍ እያነጠፈ በታናሽነት ያገለግል ነበር።
ኳስ ለመመልከት ብቻ አስቦ በመጣ ህዝብ መሃል ከክብረ ቅዱሳን እስከ ክብረ ማርያምን አግዝፎ ስብኳል።

ወጣቶች በውድቀታቸው ሰዓት ሱስ ውስጥ ሳይሆን ቅድስት ቤተክርስቲያን አጸድ ውስጥ ሄደው መውደቅ እንዳለባቸው እርሱ በደከመበት ሰዓት ተመላልሶ አሳይቶ አርዓያ ሆኗል። ትዳር በዳንኪራ ሳይሆን በአርምሞ በቅዱስ ቁርባን እንደሚከብር ሆኖ አሳይቷል።

ነገር ግን ድራማ በበዛበት ትርዒት ነፍሱ በሰዎች እጅ ተነጠቀ። በህይወት እያለ ያከበራት እና የገለጣት ቤተክርስቲያን እንኳን በትርዒቱ ተዘናግታ ስርዓተ ፍትሃት ሳትፈጽምለት እንደ ኢአማኝ ተቀበረ። በህይወት ዘመኑ ካልተለያት ቅድስት ቤተክርስቲያን እንኳን ሞቱን ለዩ።
ወጣቶች በቤተክርስቲያን አውደ ምህረት እርሱን ለመዘከር አስበው ስርዓት ስለማይፈቅድ እየተቃጠሉ እንባቸውን ወደ ውስጥ አፍስሰው አለፈ።

ዛሬ ይህ ሁሉ የተሸፋፈነ ድራማ ተገልጦ የሀገር እና የቤተክርስቲያን ድንቅ ልጅ በተቀነባበረ መልኩ በሚስቱ እና በሚስቱ እህት ባል እንደተገደለ ፍርድ ቤት አረጋገጠ። በጣም ያማል።

ይህቺ ነፍስ ድጋሚ ሐዘን እና ለቅሶ ይገባታል? አይገባትም። ምክንያቱም ይህ ልጅ ሞቶ የሚበሰብስ የሰዶቃውያን ዘር ሳይሆን በየምስራች ቃል በክብር የሚነሳ በሥጋ ወደሙ የታተመ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ነው።

ነፍስ ይማርልን!
አሌ የቤተክርስቲያን ልጅ ነበረ በጣም አዝነናል ነፍስ ይማር

ፊፋም ካፍም የብሄር ስም ቀይሩ አይሉም።በመጀመርያ እነዚ ሰሞኑን ፌዴሬሽኑ እየነገረን ያሉት ህጎች የካፍ ህግ ናቸው።ብዙዎች ረዥም ፅሁፍ ኣትወዱም እንጂ እኔ ስለካፍ ክለብ  ላይሰንሲንግ ከሁለ...
18/07/2025

ፊፋም ካፍም የብሄር ስም ቀይሩ አይሉም።

በመጀመርያ እነዚ ሰሞኑን ፌዴሬሽኑ እየነገረን ያሉት ህጎች የካፍ ህግ ናቸው።ብዙዎች ረዥም ፅሁፍ ኣትወዱም እንጂ እኔ ስለካፍ ክለብ ላይሰንሲንግ ከሁለትና ሶስት ኣመት በፊት ብዙ ፅፍያለው።ኣሁንም የብሄር ስም ቀይሩ ከሚለው ኣያይዤ ሚከተለውን ኣሰፍራለው።

የካፍ ክለብ ላይሰንሲንግን መተገበር ለሁሉም የኣፍሪካ ሀገራት ፌዴሬሽኖች ግድ ነው።ክለብ ላይሰንሲንግ የ ሬጉሌሽን ወይም የደንብ ሰነድ ነው። ይህ ሰነድ በኣጠቃላይ 72 ኣንቀፆች ኣሉት።ታድያ ኣንድ ፌዴሬሽን ይህን ሰነድ ሲቀበል 72ቱንም ኣንቀፆች እንደወረደ ተግብር ኣይባልም። ከነዚ 72 ኣንቀፆች ውስጥ 23ቱ ኣንቀፆች ናቸው ኣስገዳጅ። የተቀረቱን ኣንድ ፌዴሬሽን እንደሀገሩ ኣርጎ ልያስተካክል ሊቀርፅ ይችላል።እንዳልኩህ 23ቱን ግን በፍፁም ኣይችልም።ከነዚ መቀየርም መንካትም ከማይቻሉ ኣንቀፆች መካከል ለዛሬ ሚሆነን ኣንቀፅ 54 ነውና ስለሱ እናውራ።

ኣንቀፁ ክለቦች ልያሟሉዋቸው ስለሚገቡ ህጋዊነቶች ይዘረዝራል ከዛ ንዑስ ኣንቀፅ ኣንድ ላይ ምን ይላል ? "ሙሉ ህጋዊ የሆነ ስም " ይላል። እናማ ፌዴሬሽኑ እቺን ኣንቀፅ ይዞ ነው ለቀጣይ ኣመት ብሄር ስም ኣልፈልግም።ቀይሩ ያለው።ፊፋና ካፍም የብሄር ስም ኣይፈቅዱም ሲባልም ሰምቻለው።የት ነው ያሉት ?? በፍፁም ብለው ኣያቁም።

ፊፋ ኣንድ ክለብ የብሄር ስም ለክለቡ መጠርያ መጠቀም ኣይችልም ሚል ህግ የለውም በፍፁም። ፊፋም ሆነ ካፍ ሚሉት የኣንድ ክለብ ስም የሌሎችን ኣካላት እምነት ፣ባህል፣ቢዝነስና ሎሎች ነገሮችን ማይነኩ እስከሆነ ድረስ መብታቸው ነው።እንደዚም ሆኖ ራሱ ቢገኝ ፊፋ ቀጥታ ስም ቀይሩ ውስጥ ኣይገባም።ለምሳሌ ሮማንያ ታዋቂው ቡድን ስቱዋ ቡካሬስት ባለፉት ሁለት ኣመታት ስሙን fcsb ኣርጎ ኣይተነዋል።ይህ የሆነው በሀገሪቱ ሚገኝ ስቱዋ ቡካሬስቲ ሚባል የሚሊታሪ ቡድን ስሙ የኔ ነው ስሜን ተሰርቅያለው እንደገና የቢዝነስ ኣካሄዴም ላይ ችግር ፈጥሯል ብሎ ከሶ ነው።እዚ ጋር ፊፋ መጥቶ ኣደለም ስም ቀይር ያለው።ክለቦቹ በፍርድቤት ተዳኙ ፍርድቤት የወሰነውን ነው ፊፋ ያፀደቀው።እናማ እንዳልኳቹ ፊፋ በፍፁም በፍፁም የብሄር ስም ያለው ስም ይቀይር ሚል ህግ የለውም።ካፍም በላከው የላይሰንሲንግ ህግ እንደዚ ሚል ነገር የለውም።በቃ ክለቡ የማንንም ጥቅም ማይነካ ስም እስካለው ድረስ መጠቀም መብቱ ነው። የብሄር ስም ተጠቅሞም የኳስ ክለብ ስምን መስጠት የትም ሀገር ያለ ነው። ምሳሌ ..

👉ሴልታ ቪጎ :- ይህን የላሊጋ ቡድን ሁላችሁም በተመሳሳይ።ስሙን የወሰደው ከሚገኝበት የጋላስያ ግዛት ባሉት የሴልቲክ ብሄር ኣባላት ነው።ሴልታ የብሄር ስም ነው።በባስኬትም ከሄድክ የኣሜሪካው ቦስተን ሴልቲክም በተመሳሳይ።
👉ሴልቲክ :- ይህም ሀያል የስኮትላንድ ቡድን ሙሉ ስሙ የብሄር ነው።ሴልቲኮች በብዙ የኣውሮፓ ሀገራት ሚገኙ ብሄሮች ናቸው
👉ሀይበርናይን :- ይህም ቡድን ሚወክለው የሀይበርንያ ህዝብን ነው ስሙም ቀጥታ ብሄሩን ይወክላል።
👉ኮዛከን ቦይስ :- ይህም የሆላንድ ቡድን ከዩክሬን መጥተው ሆላንድ የሰፈሩ የኮዛከን ብሄር ነው ሚወክለው።
👉ዳል ኩርድ :- ይህ ስዊድን ያለ ቡድን በኩርድ ብሄር ስደተኞች የተመሰረተ ነው። ስሙም እንደምታዩት ኩርድ ሚለውን ኣካቷል። ሌላም ልዘርዝር ካልኩ እዘረዝራለው።

ታድያ ፌዴሬሽኑ ከየት ኣምጥቶት ነው የብሄር ስም ቀይሩ ብሎ ኣስገዳጅ ምያረገው ? በእኔ እምነት ፍላጎት ካሌለው በቀር ኣንድም ክለብ ስሙንም ኣርማውንም እንዳይቀይር። የኣርማም ጉዳይ በተመሳሳይ ሚታይ ስለሆነ።

:- ፊፋ በፍፁም በፍፁም በፍፁም የብሄር ስም መጠቀም ኣይችልም ሚል ህግ የለውም።የሀይማኖትም ስም እንደዛው።ፊፋ ሚከለክለው በዋናነት ተጫዋቾች እንደነዚ ኣይነት ሀይማኖታዊ፣ፖለቲካዊና መሰል ነገሮችን በሜዳ ውስጥ እንዳያሳዩ ብቻ ነው።
#እናማ ...ሲዳማ ቡና፣ ወላይታ ዲቻ፣ ሀድያ ሆሳዕና፣ እና መቐለ ሰባ እንደርታ ሌሎቹም ቀይሩ የተባሉት ያለመቀየር ሙሉ ሙብት ኣላቸው።
በኤርሚያስ በላይነህ

Address

Bonga

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dicha Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share