Bonga FM 97.4

Bonga FM 97.4 SRTA-Bonga Branch FM 97.4 is Government Owned Media.

“የቡና ግብይት ችግሮችን በመለየት ለመፍትሔዎቹ መስራት ይገባል” - አቶ አስራት መኩሪያ  የቡናን የግብይት ሰንሰለት ችግሮች በጥናት በመለየት መፍትሔዎችን ለማምጣት መስራት እንደሚገባ የደቡብ...
11/06/2025

“የቡና ግብይት ችግሮችን በመለየት ለመፍትሔዎቹ መስራት ይገባል” - አቶ አስራት መኩሪያ

የቡናን የግብይት ሰንሰለት ችግሮች በጥናት በመለየት መፍትሔዎችን ለማምጣት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡና፣ ሻይና ቅመማ-ቅመም ባለስልጣን አስገነዘበ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አስራት መኩሪያ
በዘርፉ የተካሄደው የዳሰሳ ጥናት ያመላከታቸውን ችግሮች በመቅረፍ ቡና ለክልሉና ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋፅኦ ማሳደግ ይገባል ብለዋል።

በጥናቱ መሠረት የቡና ግብይት ችግሮችን በመለየት ለመፍትሔዎቹ መስራት ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

በክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማ-ቅመም ባለሥልጣን በኤፍ ኤስአርፒ (FSRP) ፕሮጀክት የበጀት ድጋፍ በቡና እሴት ሰንሰለት ዙሪያ በተደረገ ጥናት ውጤት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተካሂዷል።

የዳሰሳ ጥናቱን የክልሉ ኤፍኤስአርፒ (FSRP) ባለሙያ ዶክተር ሀብታሙ ገብረሥላሴ አቅርበዋል።

በክልሉ በስድስት ከፍተኛ ቡና አምራች ወረዳዎች፣ አርሶ-አደሮች፣ አዘጋጆችና አቅራቢዎች የተካተቱበት ጥናት ምንም እንኳን ከ560 ሺህ ሄክታር በላይ የቡና ልማት ሽፋን ቢኖርም ምርታማነቱ ዝቅተኛ ነው ብለዋል።

በክልሉ የቡና ምርታማነት በአማካይ 6.8 ኩንታል በሄክታር ብቻ ስለመሆኑ አብራርተው ፤ ብዙ ሥራ ይጠይቃል ብለዋል።

ክልሉ በዓመት 54 ሺህ 795 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ የሀገሪቱን ቡና ምርት ገበያ 18 በመቶ እየሸፈነ ሲሆን ፤ ይህም ካለው እምቅ አቅም አንፃር ብዙ የሚቀረው ነው ተብሏል።

በጥናቱ እንደተገለፀው ፤ ከአምራች አርሶ-አደሮች መካከል 54 በመቶዎቹ ብቻ ለህጋዊ አቅራቢ ነጋዴ ምርቱን ይሸጣሉ።

በመሆኑም በህገ-ወጦችና በደላሎች ዋጋ ተወስኖ የሚወጣውን ቡና መግታት የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት መስራትና መፍትሔ መቀየስ እንደሚገባ ጥናቱ አመላክቷል።

እንደ ክልል 445 የቡና ኢንዱስትሪዎችና 245 ቡና አልሚ ባለሀብቶች መኖራቸውም ተብራርቷል።

በምክክሩም የቡና አልሚ ባለሀብቶች፣ አቅራቢዎች፣ ባለሙያዎችና የዘርፉ አመራሮች ተስትፈዋል።

ዘጋቢ፡ ፍቅሩ በላይ
ፎቶ፡ በረከት ገብረኪዳን

የሌማት ትሩፋት ስራን ለማሳካት ጥረት እንደሚደረግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።ቢሮው “አልቆ ማቀድ ፤ አልቆ መስራት ለምርታማነት ዕድገት” በሚል መሪ ቃል የ...
10/06/2025

የሌማት ትሩፋት ስራን ለማሳካት ጥረት እንደሚደረግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው “አልቆ ማቀድ ፤ አልቆ መስራት ለምርታማነት ዕድገት” በሚል መሪ ቃል የንቅናቄ መድረክን በቦንጋ ከተማ አካሂዷል።

በእስካሁኑ ጉዞ በክልሉ በሌማት ትሩፋት ዘርፍ የተገኙ ስኬቶችን በማጉላትና ድክመቶችን በመፈተሽ ለቀጣይ በጋራ ለመረባረብ መድረኩ ወሳኝ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትልና የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታመነ በቀለ ተናግረዋል።

በአምስቱም የሌማት ትሩፋት መስኮች በተሰራው ሰፊ ስራ አመርቂ ውጤቶች መታየታቸውን ገልጸዋል።

ዓላማው ስኬታማ እንዲሆን በልዩ ትኩረት በመስራት እንደክልል በቀጣይ ዓመት በሁሉም የእንስሳት ተዋጽኦ ዘርፎች ስኬታማ ለመሆን ይሰራል ብለዋል።

ስኬቱን ለማረጋገጥ ከሚያስችሉ ማሳያዎች መካከል አንዱ የወተት ምርታማነት ማደግ ነው ያሉት አቶ ታመነ ፤ በዚህም ስራው ሲጀመር 316 ሚሊዮን ሊትር ወተት ከነበረበት በዚህ ዓመት 360 ሚሊዮን ሊትር ማድረስ መቻሉን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ መልኩ በዓመቱ እስካሁን ባለው ከ44 ሺህ በላይ ላሞች ላይ የዝርያ ማሻሻያ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።

በክልሉ የሌማት ትሩፋት ስራ ወደተግባር ከገባበት ጊዜ አንስቶ በሁሉም ዘርፎች ስኬታማ ስራዎች መሠራታቸውን የገለጹት ደግሞ በቢሮው የእንስሳት ዝሪያ ማሻሻያ ዘርፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰለች ታደመ ናቸው።

ዘርፉን ይበልጥ በማዘመን የህዝቡን የኑሮ ሁኔታ የማሻሻል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።

ክልሉ በሁሉም ዘርፎች ከተሠራ ውጤታማ መሆን የሚያስችል አቅም አንዳለው የገለፁት የመድረኩ ተሳታፊዎች ፤ የሌማት ትሩፋት የህዝብን ፍላጎት ማሟላት የቻለ ስራ ነው ብለዋል።

ሆኖም ካለው የእንስሳት ብዛት አንጻር አሁንም ብዙ መስራት ይጠበቃል ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ፤ በቀጣይ ተናቦና ተቀናጅቶ በመስራት ለበለጠ ውጤታማነት አንደሚተጉ አንስተዋል።

በታጋይ ገብረሚካኤል

በከተማው የሚከናወነውን የልማት ስራ እንደሚደግፉ በካፋ ዞን የአውራዳ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።የከተማ አስተዳደሩም የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።ከከተማው ነዋሪዎች መካከል...
10/06/2025

በከተማው የሚከናወነውን የልማት ስራ እንደሚደግፉ በካፋ ዞን የአውራዳ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

የከተማ አስተዳደሩም የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።

ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ አደመ ገብሬና ወይዘሮ ሙሀባ መሀመድ የኮሪደር ልማት ከከተማ እድገት ጋር የተሳሳረ መሆኑን በመግለጽ ፤ በሚያዩት እንቅስቃሴ መደሰታቸውን ተናግረዋል።

ልማቱ ሲጀመር ስጋት እንደነበራቸው የገለጹት ነዋሪዎቹ ፤ አሁን ላይ ወጥ በሆነ መንገድ ቤቶቻቸውን ማስዋባቸው የተለያዩ ተግባራትን በተሻለ መልኩ ለማሳለጥ እንደረዳቸው ተናግረዋል።

የከተማ አስተዳደሩ የሚያደርገው ልማታዊ እንቅስቃሴ ማህበረሰቡን የሚጠቅም በመሆኑ የሚጠበቅባቸውን ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የአውራዳ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ኃላፊ አቶ ተክለዓብ ግርማ ህብረተሰቡን በማስተባበር የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸው ፤ ነዋሪዎች ቤቶቻቸውን እያሳመሩ ይገኛሉ ብለል።

ከኮሪደር ልማት በተጨማሪ ወሰን የማስከበር ስራም እየተከናወነ እንደሚገኝ አቶ ተክለዓብ ገልጸዋል።

ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት እና በማቺንግ ፈንድ እየተሰራ ያለ ዲች ቦይ እየተገባደደ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ታረቀኝ ሀይሌ
የኮሪደር ልማት ከተማን ውብ ጽዱና ለነዋሪዎች ምቹ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል።

ለተግባራዊነቱ ከማህበረሰቡ ጋር የተደረጉ ውይይቶች ለውጥ እንዲመዘገብ ረድተዋል ብለዋል።

የከተማውን ፕላን ከማስጠበቅ በተጨማሪ ያረጁ ቤቶችን በማፍረስ ለልማት ዝግጁ የማድረግ ስራ መሰራቱንም አቶ ታረቀኝ ገልጸዋል።

ከእነኚህ ቤቶች ለተነሱ የህብረተሰብ ክፍሎች ልዋጭ መሬት መሰጠቱን ተናግረዋል።

በትዕግስቱ ጴጥሮስ

ክልል-አቀፍ ፈተና በስኬት እንዲጠናቀቅ በትብብር መስራት እንደሚገባ ተመላከተ።የስምንተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በካፋ ዞን ሁሉም ትምህርት ቤቶች መሰጠት ጀምሯል።የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ህዝ...
10/06/2025

ክልል-አቀፍ ፈተና በስኬት እንዲጠናቀቅ በትብብር መስራት እንደሚገባ ተመላከተ።

የስምንተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በካፋ ዞን ሁሉም ትምህርት ቤቶች መሰጠት ጀምሯል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ማርቆስ ቡልቻና የካፋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ መሸሻ በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ሸታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገኘት ፈተናውን አስጀምረዋል።

በማስጀመሪያው ላይ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ማርቆስ ቡልቻ ፈተናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ፈተናው የተማሪዎችን ብቃት ለመለካት የሚያስችል መሆኑን አመላክተዋል።

የካፋ ዞን ትምህርት መምሪ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ መሸሻ በዞኑ 12 ሺ 907 የስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች በ4 መቶ 26 መፈተኛ ጣቢያዎች እየተፈተኑ ነው ብለዋል።

ፈተናው ከኩረጃ የጸዳ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሚመለከታቸው አካላት ክትትል እንዲያደርጉ አሳስበው ፤ ተማሪዎችም በራስ መተማመን ስሜት መፈተን እንዳለባቸው መክረዋል።

የዞኑ መምህራን ማህበር ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ወንድሙ በበኩላቸው ፤ ማህበሩ ፈተናው በአግባቡ እንዲጠናቀቅ ሚናውን እየተወጣ ነው ብለዋል።

ዘጋቢ፡ ሀብታሙ ኃይሌ
ፎቶ፡ በረከት ገብረኪዳን

ክልል-አቀፍ የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በካፋ ዞን በሁሉም ትምህርት ቤቶች መሰጠት ጀምሯል።በዞኑ 12 ሺ ዘጠኝ መቶ 7 ተማሪዎች በ4 መቶ 26 መፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናውን እየወሰዱ ነው። የ...
10/06/2025

ክልል-አቀፍ የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በካፋ ዞን በሁሉም ትምህርት ቤቶች መሰጠት ጀምሯል።

በዞኑ 12 ሺ ዘጠኝ መቶ 7 ተማሪዎች በ4 መቶ 26 መፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናውን እየወሰዱ ነው።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ማርቆስ ቡልቻ እና የካፋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ መሸሻ በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ሸታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገኘት ፈተናውን አስጀምረዋል።

ዘጋቢ:- ሀብታሙ ኃይሌ
ፎቶ:- በረከት ገ/ኪዳን

ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት እንዲሳካ የትኛውም ማሳ ጾም ማደር እንደሌለበት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን አሳሰቡ።ክልሉ ግ...
09/06/2025

ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት እንዲሳካ የትኛውም ማሳ ጾም ማደር እንደሌለበት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን አሳሰቡ።

ክልሉ ግብርና ቢሮ የክልሉን የመኸር እርሻ ልማት ስራዎች የ2016/17 የምርት ዘመን አፈጻጸምና የ2017/18 የምርት ዘመን ዕቅድ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ አካሄዷል።

አጠቃላይ እንደክልል እየመጣ ያለው የግብርና ዘርፍ መሻሻል አበረታች መሆኑን የገለጹት የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን ሆኖም ክልሉ ካለው የግብርና ዘርፍ አንጻር አሁንም ብዙ መስራት እንዳለብን የሚያሳይ ነው ብለዋል።

በተለይ የመሬት አጠቃቀማችን ኋላ ቀር በመሆኑ በርካታ ማሳዎች አሁንም እየታረሱ እንዳልሆነ ጠቁመዋል።

ይህም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ለያዝነው ዕቅድ ትልቅ ማነቆ በመሆኑ በቀጣይ የትኛውም ማሳ ጾም ማደር እንደሌለበት በማሰብ በየአካባቢው ያለ አመራር በጥብቅ ክትትል ሊሰራ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት በጋራ ቅንጅትና መናበብ ለመስራት የክልሉ መንግስት ዝግጁ መሆኑንም አቶ ፍቅሬ አማን ገልጸዋል።

የክልሉ መንግስት ለግብርናው ዘርፍ ውጤታማነት የሰጠው ትኩረት የሚደነቅ መሆኑን የገለጹት የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በየመዋቅሩ እየታየ ያለውን የአፈፃፀምና የግብዓት አጠቃቀም ልዩነቶችን ለማጥበብ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

ለግብርናው ዘርፍ ውጤታማነት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

በታጋይ ገ/ሚካኤል

ለ1 ሺ 431 ወጣቶች የስራ እድል መፈጠሩን የዴቻ ወረዳ ስራ፣ ክህሎት፣ ንግድ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በተለያዩ መስኮች ተደራጅተው ወደስራ የገቡ ወጣቶች በ...
09/06/2025

ለ1 ሺ 431 ወጣቶች የስራ እድል መፈጠሩን የዴቻ ወረዳ ስራ፣ ክህሎት፣ ንግድ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በተለያዩ መስኮች ተደራጅተው ወደስራ የገቡ ወጣቶች በበኩላቸው ፤ ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።

መንግስት ለወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ በሰጠው ትኩረት በተለይ በገጠር ግብርና ዘርፍ በልዩ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ እንዳለ ከበደ ተናግረዋል።

በተገባደደው በጀት አመት 3 ሺ 292 ወጣቶችን በገጠር የስራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ 1 ሺ 375 ወጣቶች በተለያዩ መስኮች መሰማራታቸውን አንስተዋል።

በከተማ የስራ እድል ፈጠራም በሁለት ማዘጋጃ ቤቶች 56 ወጣቶች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው የገለጹት አቶ እንዳለ ፤ ለተግባሩ ውጤታማነት መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ድጋፍ ውጤት እንዲመዘገብ አድርጓል ብለዋል።

ቀደም ሲል ለወጣቶች ስራ እድል ፈጠራ ከተሰራጨዉ የብድር አገልግሎት ከ2 ሚሊዮን 884 ሺ ብር በላይ ለማስመለስ ታቅዶ ከ3 ሚሊዮን 228 ሺ ብር በላይ ማስመለስ መቻሉን ተናግረዋል።

ወጣት ገባቦ ጋነቾና ጓደኞቹ በወረዳው ቦባ ገጫ ቀበሌ ከ2009 ዓመተ-ምህረት ጀምሮ አምስት በመሆን በፈርኒቸር እና ብረታ-ብረት ስራ ተደራጅተው በወሰዱት የ60 ሺህ ብር ብድር የተለያዩ ተግባራት እየከወኑ ባመጡት ለውጥ ማሽኖችን ማሟላት መቻላቸውን ተናግረዋል።

ወጣቶቹ በዚህ ስራ ዉጤታማ በመሆን እስከ 250 ሺ ብር የብድር አገልግሎት በማግኘት ለሌሎች የስራ እድል ከመፍጠራቸው በተጨማሪ በከተማው በሆቴል ዘርፍ ስራ መጀመራቸውን አንስተዋል

ወጣት ከበቡሽ ከተማ እና አባተ ኃይሌም በቦባ ገጫ ቀበሌ የዎዲቲ ዶሮ እርባታ ማህበር አባላት ሲሆኑ ፤ መንግስት ባሰራላቸው ሼድ የአንድ ቀን ጫጩቶችን ለ48 ቀናት ያህል በማቆየት እየሸጡ መጠቀማቸውን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅትም 1 መቶ እንቁላል ጣይ ዶሮዎችን እየተንከባከቡ እንደሚገኙ የገለጹት ወጣቶቹ 1 ሺህ የአንድ ቀን ጫጩት በቅርቡ ለማስገባት ቅድመ-ሁኔታዎችን ማመቻቸታቸውን አንስተዋል።

በወረዳዉ ኤርሞ ቀበሌ በችግኝ ማፍላት ስራ ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል ወጣት ሂሩት አስራት፣ ታሪኩ ገብረማርያምና አስማማዉ ሃብተማርያም የእንሰትና የአቮካዶ ችግኞችን በማዘጋጀት ለገበያ እያቀረቡ ተጠቃሚ መሆናቸዉን ተናግረዋል።

በተጨማሪም የአሳ ፖንድ በማዘጋጀት ለአካባቢዉ ማህበረሰብ አሳ ለማቅረብ እየሰሩ እንደሚገኙ የገለጹት ወጣቶቹ ፤ በተሰጣቸዉ ማሳ ላይም የተሻሻለ ዝርያ ያለዉን ሙዝ መትከል መቻላቸዉን አንስተዋል።

በትዕግስቱ ጴጥሮስ

የባህል ፍርድ ቤት ተቋቁሞ ወደሥራ መግባቱ ፍትህን ለማግኘት የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ ከማስቀረት አንፃር ፋይዳው የጎላ መሆኑን የጨታ ወረዳ ፍርድ ቤት ገለጸ፡፡ዘመናዊውን የፍትህ ስርዓት በማገዝ...
09/06/2025

የባህል ፍርድ ቤት ተቋቁሞ ወደሥራ መግባቱ ፍትህን ለማግኘት የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ ከማስቀረት አንፃር ፋይዳው የጎላ መሆኑን የጨታ ወረዳ ፍርድ ቤት ገለጸ፡፡

ዘመናዊውን የፍትህ ስርዓት በማገዝም ሆነ በመተካት አስተዋጽኦ ሲያበረክት የኖረ መልካም እሴት ነውም ተብሏል፡፡

የጨታ ወረዳ ፍርድ ቤት ተወካይ ፕረዝደንት አቶ አንዱዓለም ታከለ ፤ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደረጃ የሽማግሌ ዳኞች ማቋቋሚያ አዋጅ ጸድቆ ወደሥራ መገባቱን ተናግረዋል።

በወረዳው ካሉት 23 ቀበሌዎች 1 መቶ 15 የሀገር ሽማግሌዎች ለዚህ ስራ መመረጣቸውንም ገልጸዋል።

ለዚህም ስልጠና በመስጠት ወደስራ መገባቱን አንስተው ፤ የተለያዩ ጉዳዮችን የተመለከቱ መዝገቦች ቀርበው ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋልም ብለዋል፡፡

በተለይ በባለትዳሮች መካከል የሚፈጠሩ ግጭቶች በሽማግሌ ዳኞች የመፈታት እድላቸው ከፍተኛ በመሆኑ ፤ በዚህ ረገድ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ስለመሆናቸው ነው የገለጹት፡፡

የባህል ፍርድ ቤቶች በየአካባቢው መኖራቸው ፍትህን ፍለጋ በሚደረግ እንቅስቃሴ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ ከማስቀረትና ጊዜን ከመቆጠብ አንፃር ፋይዳቸው የጎላ በመሆኑ ህብረተሰቡ ይህንን እሴት ማጠናከር እንደሚገባው ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

በመቅደስ ታደሰ

በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።ቢሮው የክልሉን የመኸር እርሻ...
09/06/2025

በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው የክልሉን የመኸር እርሻ ልማት ስራዎች የ2016/17 የምርት ዘመን አፈጻጸምና የ2017/18 የምርት ዘመን ዕቅድ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

ክልሉ ባለፉት ሶስት ዓመታት በግብርናው ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም በሰራው ስራ ምርትና ምርታማነት ከመጨመሩም ባሻገር የማሳ አጠቃቀም ዘይቤ ከፍ ማለቱን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ገልጸዋል።

በዚህም በዓምናው የመኸር አዝመራ በዋና ዋና ሰብሎች ከ3 መቶ 88 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳን በማልማት የማሳ ሽፋንን ከዕቅዱ አንጻር 99 በመቶ ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

በዚህ መነሻነት የዘንድሮ የበልግ አዝመራ አፈጻጸምም የተሻለ መሆኑን የገለጹት አቶ ማስረሻ በዚህም 3 መቶ 59 ሺህ ሄክታር ማሳን በተለያዩ ሰብሎች ለማልማት ታቅዶ ከዕቅድ በላይ ማልማት እንደተቻለ ተናግረዋል።

ከዚምም 25 ሺህ ሄክታሩ በትራክተር የለማ ሲሆን 95 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያና፣ 193 ሺህ ቶን ኮምፖስት ለግብዓትነት መዋሉንም ጠቅሰዋል።

ከዚህም አብዛኛው መሬት በክላስተር መልማቱን የገለጹት አቶ ማስረሻ በዚህ መነሻነት በ2017/18 የመኸር አዝመራ በተሻለ መልኩ ለመስራት ዕቅድ መያዙን ገልጸዋል።

በመሆኑም በዘንድሮ የመኸር አዝመራው እንደ ክልል በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ከ4 መቶ ሺህ ሄክታር በላይ ማሳን በማልማት ከ17 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ተናግረዋል።

ለዚህም እርሻ 1 መቶ 26 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ ለግብዓትነት እንደሚውልም ጠቅሰዋል።

ከዚህ ባሻገር በክልሉ የተጀመረው የሌማት ትሩፋት ስራ በወተት፣ በእንቁላል ፣ በንብ ማነብና በአሳ ማስገር ውጤታማ መሻሻል እንደታየበትም ጠቁመዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ካለን የግብርና እምቅ አቅም አንጻር የቴክኖሎጂ ስርጸት፣ የተባይና የአረም ቁጥጥር ስራና የግብዓት ገንዘብን በወቅቱ ያለመሰብሰብን የመሳሰሉ ችግሮች አሁንም ለግብርናው ዘርፍ ዕድገት ማነቆ በመሆኑ በትኩረት መሰራት እንዳለበትም አሳስበዋል።

በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብርም ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ባላቸው ችግኞች እንደሚሸፈንም ጠቁመዋል አቶ ማስረሻ።

መድረኩን የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማንን ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የየወረዳ ከፍተኛ አመራሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች እየተሳተፉበት ይገኛል።

በታጋይ ገ/ሚካኤል

09/06/2025

ሰኞ ፤ ሰኔ 02 ቀን 2017 ዓ/ም የጠዋት ስርጭታችን(2)

ለዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እየተዘጋጁ መሆናቸውን በዴቻ ወረዳ ቦባ ገጫ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ገለጹ። በወረዳው ከሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የ12ኛ ክፍ...
09/06/2025

ለዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እየተዘጋጁ መሆናቸውን በዴቻ ወረዳ ቦባ ገጫ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ገለጹ።

በወረዳው ከሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል።

በወረዳው ቦባ ገጫ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተን ካነጋገርናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ፌቨን ጌታቸው፣ አልአዛር ወልዴ እና መልካሙ በላይ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተሻለ ውጤት ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል።

በትምህርት ቤቱ የማደሪያ ክፍል ተዘጋጅቶላቸው ምገባን ጨምሮ ለብሔራዊ ፈተና የሚረዳቸውን አስፈላጊውን ድጋፍ እያገኙ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

መምህራን ከመደበኛ የትምህርት ክፍለ-ጊዜ በተጨማሪ አስፈላጊውን እገዛ እያደረጉ እንደሚገኙ ነው የተናገሩት።

ለዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ሙሉ ጊዜያቸውን በመስጠት እየተዘጋጁ መሆናቸውን የገለጹት ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል።

መምህር ፀጋዬ ዬቦ በትምህርት ቤቱ የኬሚስትሪ መምህር ሲሆኑ ፤ ለአዳሪ ተማሪዎች ይህ ፕሮግራም ከተዘጋጀ ጀምሮ በአራት ፕሮግራሞች ልዩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የማታ ትምህርትና የቤተ-መጽሀፍት ንባብ የተማሪዎች የሁልጊዜ ተግባራት መሆናቸውን አንስተዋል።

ተማሪዎቹ ለብሔራዊ ፈተናው የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የቀደሙ ፈተናዎችን እንዲሰሩ ከማድረግ በተጨማሪ ተግባር-ተኮር የመማር ማስተማር ስራም እየተከናወነ መሆኑን መምህር ፀጋዬ ተናግረዋል።

የትምህርት ቤቱ ርዕሰ-መምህር አቶ ብርሃኑ ወልደሚካኤል ከአራት ትምህርት ቤቶች የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ 32 ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ ሙሉ ጊዜያቸውን ተጠቅመው ለብሔራዊ ፈተና እየተዘጋጁ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።

ለዚህ ተግባር የወረዳው አስተዳደር ያደረገው ድጋፍ የሚበረታታ ነው ብለዋል።

የዴቻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወንዱ አደመ በወረዳው ላለፉት ሶስት ዓመታት አንድም ተማሪ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አለማስመዝገቡን ገልጸዋል።

ይህን ችግር ለመቅረፍ የትምህርት ግብዓቶችን ከማሟላት በተጨማሪ የድጋፍ ትምህርት መስጠትና ሌሎች ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከእነኚህ ተግባራት አንዱ በቦባ ገጫ ሁለተኛ ደረጃ ትምርህት ቤት ላይ ለተማሪዎች የሚደረግ ልዩ ድጋፍ መሆኑን አንስተዋል።

ለዚህ ተግባር የወረዳው አስተዳደር ከፍተኛ ወጪ ማውጣቱን የገለጹት አቶ ወንዱ ፤ ለአበነትም ለተማሪዎች ምገባ በቀን ለአንድ ተማሪ ከ180 ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግ አንስተዋል።

አንደ ሀገር በትምህርት ዘርፍ ያጋጠመውን ውድቀት ለመቀልበስ መሰል ተግባራት ወሳኝ መሆናቸውን በመግለፅ ፤ ለተማሪዎች ውጤታማነት ወላጆችን ጨምሮ የሚመለከታቸውን አካላት ድጋፍና ክትትል ይሻል ብለዋል።

በትዕግስቱ ጴጥሮስ

በካፋ ዞን በሁሉም ወረዳዎች የ8ኛና 6ኛ ክፍል ፈተና ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ-ዝግጅት መጠናቀቁን የዞኑ ትምህርት መምሪያ ገለጸ።በዞኑ ከ17 ሺህ 3 መቶ በላይ  የ6ኛ ክፍል እና ከ12 ሺህ...
08/06/2025

በካፋ ዞን በሁሉም ወረዳዎች የ8ኛና 6ኛ ክፍል ፈተና ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ-ዝግጅት መጠናቀቁን የዞኑ ትምህርት መምሪያ ገለጸ።

በዞኑ ከ17 ሺህ 3 መቶ በላይ የ6ኛ ክፍል እና ከ12 ሺህ ዘጠኝ መቶ በላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ ተገልጿል።

ሀብታሙ ኃይሌ ያዘጋጀዉን
ዳንኤል መኩሪያ እንደሚከተለው ያቀርባል

በካፋ ዞን በሁሉም ወረዳዎች የ8ኛና 6ኛ ክፍል ፈተና ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ-ዝግጅት መጠናቀቁን የዞኑ ትምህርት መምሪያ ገለጸ።በዞኑ ከ17 ሺህ 3 መቶ በላይ የ6ኛ ክፍል እና ከ12 ሺህ ዘጠኝ ...

Address

Bonga
138

Telephone

+251473311641

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bonga FM 97.4 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category