25/04/2026
🥊 ወንድሙ ቄራ ለንቃተ ህሊና (ዮሐንስ ምስክር) የግማሽ ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገለት!
#በኢትዮጵያ የቅይጥ ማርሻል አርት (MMA) ስፖርት ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ እየተጻፈ ነው! የዚህ ታሪክ ግንባር ቀደም ተዋናይና የብዙዎች ተስፋ ለሆነው ጀግናው ተፋላሚ ለንቃተ ህሊና (ዮሐንስ ምስክር) ታዋቂው ባለሀብት አቶ ወንድሙ ወልደሚካኤል የማይረሳ አሻራቸውን አሳርፈዋል።
አቶ ወንድሙ ወልደሚካኤል ለንቃተ ህሊና (ዮሐንስ ምስክር) ያደረጉት ድጋፍ ስፖርተኛው ለሀገሩ ያለውን ክብርና "ንቃተ ህሊናን" መሰረት ያደረገውን ጠንካራ ጉዞ የሚመጥን ነው።
አቶ ወንድሙ ወልደሚካኤል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የሆንኬን ቢራ ተወካይና የህንፃ ሥራ ተቋራጭ ባለቤት ሲሆኑ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸው ንቁ ተሳትፎና ለወጣቶች ያላቸው አክብሮት ይታወቃል። ዛሬም ለጀግናው ለንቃተ ህሊና (ዮሐንስ ምስክር)
የግማሽ ሚሊዮን ብር (500,000 ETB) ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ከጎኑ መቆማቸውን አረጋግጠዋል።
"ንቃተ ህሊናን ማገዝ፣ ትውልድን መገንባት ነው!"
ይህ ድጋፍ ለንቃተ ህሊና ከገንዘብ በላይ የሞራል ስንቅ ነው። አቶ ወንድሙ ስፖርቱ የሚጠይቀውን የአእምሮ ዝግጁነትና የንቃተ ህሊና ብስለት በሚገባ የተረዱ ባለራዕይ በመሆናቸው ለዚህ ጀግና ወጣት የጀርባ አጥንት መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
እንደ አቶ ወንድሙ ያሉ ስፖርት ወዳድና የሀገር ባለውለታዎች ለወጣቶች እውነተኛ ምሳሌ ናቸው።
ለአቶ ወንድሙ ወልደሚካኤል ከልብ የመነጨ ምስጋና እያቀረብን ለንቃተ ህሊና (ዮሐንስ ምስክር) ደግሞ በውድድሩ ስኬታማ እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እንገልጻለን!
የበጎ ሰው ስራው፣ የጀግና ደግሞ ታሪኩ ጎልቶ ይጻፋል!