የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit public and government service
(1)

አንቶኒዮ ጉተሬዝ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ በመመረቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉአዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታ...
25/09/2025

አንቶኒዮ ጉተሬዝ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ በመመረቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱ ወገኖች በቀጣናው ብሎም በዓለም አቀፍ የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

አንቶኒዮ ጉተሬዝ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ በመመረቁ ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

በተጨማሪም በቅርቡ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ጉባዔን በስኬት ማስተናገዷን አስታውሰው፥ ለዚህም የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በተመሳሳይ ፕሬዚዳንት ታዬ ከ80ኛው የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን አፍሪካን በኤሌክትሪክ ለማዳረስ ዓላማ ያደረገው“ተልዕኮ 300" ኢነርጂ ኢኒሼቲቭ ላይ ተሳትፈዋል።

ኢትዮጵያ ተልዕኮውን መቀላቀሏ እያካሄደችው ያለውን የኢነርጂ ማሻሻያ የሚያጠናክር ዕውቅና በመሆኑ ትልቅ ምዕራፍ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ባለፈው ጥር ወር በታንዛኒያ በተዘጋጀው “ተልዕኮ 300” ኢነርጂ ኢኒሼቲቭ ስብሰባ ላይ ቡድኑ ውስጥ እንድትካተት ማመልከቷ ይታወሳል፡፡

አሁን ላይም ለአባልነት የሚያበቃትን ስትራቴጂና የትግበራ የጊዜ ሰሌዳዎችን በማዘጋጀት ቁርጠኝነቷን በድጋሚ ለማረጋገጥ የገባችውን ቃል በተግባር አረጋግጣ ኢኒሼቲቩን ተቀላቅላለች፡፡

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ (ሆሳዕና፣መስከረም 15/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ...
25/09/2025

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ

(ሆሳዕና፣መስከረም 15/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ

በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ ( ዶ/ር) ፣የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣
የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የፕሮጀክቶች አስተባባሪ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ብርሀኑ ተስፋዬ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በዛሬው እለት ተመርቆ ስራ የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 5 የፌደራል እና 2 የክልል ተቋማት 20 አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸውን ስራ ጀምረዋል።

በማዕከሉ ንግድና ገበያ ልማት፣ገቢዎች፣ኢሚግሬሽን፣ንግድ ባንክ፣ፖስታ አገልግሎት ፣ፋይዳ እና ኢትዮ ቴሌኮም በነዚህ ተቋማት 20 አገልግሎት መስጠት ያስችላል ተብሏል።

ተቋሙ ወደፊት ከ60 በላይ አገልግሎት ማስተናገድ የሚችል ስለመሆኑም ተመላክቷል።

በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነ ዲጂታላይዝድ ፣የተገልጋዩን ህብረተሰብ ጊዜ ወጪ ፣ሀብት እና እንግልት የሚቀንስ ሲሆን የአገልግሎት ጥራት በከፍተኛ ሁኔታ የሚያሻሽል ስለመሆኑም ተመላክቷል።

በተስፋዬ መኮንን

25/09/2025
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ልዩ የወጣቶች ስልጠና ተጠናቀቀ።መስከረም 14/2018/(ቡታጅራ)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ቢ...
24/09/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ልዩ የወጣቶች ስልጠና ተጠናቀቀ።

መስከረም 14/2018/(ቡታጅራ)

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ከጤድሮስ ትሬዲንግ ኢንካስትሪንግና ቻይና ከሚገኘው ልዩ ሸገር ትሬዲንግ ጋር በጋራ በመሆን ለሴቶችና ወጣቶች ለሶስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ይህ ዕድል የመጀመሪያ በመሆኑ የመጣውን ዕድል በአግባቡ በመጠቀም የክልላችንን ፣የዞናችንንና የአካባቢያችንን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ልናደርግ ይገባል ብለዋል።

አቶ ሙስጠፋ አያይዘውም ይህ ስራ በዘፈቀደ የሚሰራ ሳይሆን በዕውቀትና በክህሎት ከተሰራ ውጤታማ እንድንሆን ያስችለናል ብለዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወይዘሮ ዙልፋ አለዊ በበኩላቸው ሰልጣኞች የቢዝነስ ሀሳባቸው የበለጠ እንዲዳብር የክህሎት ሚኒስቴር ፣የፌደራል ኢንደስትሪ ሚኒስቴር፣የፌደራል ኢንተርፕራይዝ ልማት እንዲሁም የምስራቅ ጉራጌ ዞን፣የስልጢ ዞን እና የማረቆ ልዩ ወረዳ አመራሮች ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

ከአደረጃጀት ጋር ተያይዞ መደራጀት ያለባቸው ወጣቶችና ሴቶች የአካል ጉዳተኞች በተለያየ ምክንያት ከስደት የተመለሱና ስራ አጥተው ለተቀመጡ ዜጎች በመሆኑ በጥንቃቄና በዕውቀት ልንሰራ ይገባል ብለዋል።

ወይዘሮ ዙልፋ አክለው እንደተናገሩት ይህ ዕድል ስራ ለመስራት መንገዱ ለጠፋባቸው ወጣቶችና ሴቶች አካሄዱን ለማሳየት ታስቦና የሀገራችንን የኑሮ ውድነት የተረጋጋ ሆኖ ዜጎች ባላቸው የኑሮ ደረጃ ተሳታፊ ለማድረግ የተሰራ ስራ መሆኑን አንስተዋል።

በስልጠናው ወቅትም ለተነሱ ጥያቄዎች ከመድረክ ሠፊ ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።

በስልጠናው የተሳተፉ አካላትም በስልጠናው መደሰታቸውንና በርካታ የስራ ክህሎቶችን አግኝተናል ያሉ ሲሆን ያገኘነውን ዕውቀት በመጠቀም ሰርተን ራሳችንን እና ሀገራችንን ለመጥቀም ዝግጁ ነን ብለዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮምኒኬሽን መምሪያ ነው።

ዓመታዊ የመስቀል በዓል ለማክበር ከአዲስአበባ እና ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ ምስራቅ ጉራጌ ዞን እየገቡ ላሉ እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደረገመስከረም 14/2018 ዓ/ም...
24/09/2025

ዓመታዊ የመስቀል በዓል ለማክበር ከአዲስአበባ እና ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ ምስራቅ ጉራጌ ዞን እየገቡ ላሉ እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደረገ

መስከረም 14/2018 ዓ/ም (ቡታጅራ)

በጉራጌ ህዝብ ልዩ ሥፍራ የሚሠጠው የመስቀል በዓል ለማክበር ወደ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ለመጡት እንግዶች ቡታጅራ ከተማ ሲገቡ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደርጎላቸዋል

በእንግዶች አቀባበሉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን፣የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልጽግና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሠለ ጫካ፣ የዞኑ ረዳት የመንግስት ተጠሪና የፖለቲካና የሪዕዮተ አለም ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሠረት ሽፋ፣ እና የሚመለከታቸው የዞኑ የመምሪያ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዶ አህመድ፣ የከተማው ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ማርቅስ የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ጽህፈት ቤት በዞኑ የሚገኙ የፖሊስ ጽህፈት ቤቶች አባላት በእንኳን ደህና መጣችሁ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው አቀባበል አድርገዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስአስተዳደር፣ የዞኑ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ፣ የዞኑ መንግድ ልማትና ትራንፖርት መምሪያ በጋራ ያዘጋጀው ፕሮግራም እንግዶቹ በጉራጌ መሀበረሰብ ዘንድ እጅግ የሚወደደው በዓል አከባበር ያማረና የሠመረ እንዲሆን ከመመኘት ባሻገር በቆይታቸው ደህንነታቸው እንዲጠበቅ በትራንስፖርት እንዳይቸገሩ አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ያለውን ዝግጁነት የሚያመላክት ነወ።
ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

የመስቀል በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲውል በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉ የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ  አስታወቀ።መስከረም 14/2018(እንሴኖ)የመስቀል በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ በማ...
24/09/2025

የመስቀል በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲውል በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉ የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስታወቀ።

መስከረም 14/2018(እንሴኖ)

የመስቀል በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ በማስመልከት የከተማው ሰላምና ፀጥታ፣ የፖሊስ አባላት እንዲሁም ከከተማው ደምብ አስከባሪ አካላት ጋር በዛሬው ዕለት ውይይት አድርጓል፡፡

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰብራላ ጀማል እንዳሉት በጉራጌ ማህበረሰብ ዘንድ ዘመድ አዝማድና ቤተሰብ ተገናኝቶ በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል የመስቀል በዓል አንዱ ነው ያሉት መስቀል በጉራጌ በድምቀት የሚከበር በዓል በመሆኑ በርካታ እንግዶች ከተየለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች ከተማውን አቋርጠው እንደሚሄዱና እና ወደከተማው እንደሚገቡ አንስተዋል ።

ስለሆነም ከተለያየ የሀገሪቱ ከተሞች ወደ ከተማችን አቋርጠው የሚመጡ እንግዶች ያለምንም የጸጥታ ችግርና በትራፊክ ፍሰት ቁጥጥር ሳቢያ በየርቀቱ በመቆም የሚፈጠረው መጉላላት ሳይፈጠር እንዲጓዙ በትኩረት ይሰራልም ብለዋል።

የከተማው ፖሊስ አዛዥ ዋና ሳጅን አዲሱ ግማሮ እንደገለፁት መስቀል በጉራጌ ማህበረሰብ ዘንድ ተጠባቂና በድምቀት ከሚከበሩ በዓላቶች ዋነኛውና ትልቁ ከመሆኑ አንጻር እንግዶች ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከተማችንን አቋርጠው የሚያልፉ ሲሆን በዚህም ከታሪፍ በላይ ተጓዥ መንገደኞች መክፈል እንደሌለባቸው እና መሰል ድርጊቶች እንዳይፈጠሩ አስፈላጊውን ዝግጅት የተደረገ ሲሆን መሰል ድርጊቶች ሲያጋጥም በፍጥነት ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ እርምጃ መወሰድ እንደሚቻል ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም የከተማው ፖሊስ አዛዥ ዋና ሳጅን አዲሱ ግማሮ ባስተላለፉት የጥንቃቄ መልዕክት ማህበረሰቡ ባንክ ቤት አካባቢ ጥንቃቄ እንዲያደርግና መሰል፤ ሀሰተኛ የብርኖቶች ባንክ፣ገባያ የነዳጅ ማደያ ማ/ሰቡ ጥንቃቄ እንዲደርግ እንዲሁም ህዝብ በሚበዛቤት መናኸሪያ በመሳሰሉ ባታ ዘረፋ ስርቆት እንዳይከሰት የቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርግና እንዳይታለል አስተውሎ በጥንቃቄ ግብይቶችን መፈጸም እንዳለበት አሳስበዋል።

በመጨረሻም በዓሉ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የሰላም የፍቅር የደስታ የአብሮነት እንዲሆን ምኞታቸው ገልፀዋል ሲል የዘገበው የከተማው መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት ነው።

መስከረም 14/2018 (እንሴኖ)********************************የመስቀል በዓልን ለማክበር ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እንሴኖ ከተማ አስተዳደር እና ምስራቅ መስቃን ወረዳን...
24/09/2025

መስከረም 14/2018 (እንሴኖ)
********************************
የመስቀል በዓልን ለማክበር ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እንሴኖ ከተማ አስተዳደር እና ምስራቅ መስቃን ወረዳን አቋርጠው ወደ ሀገር ቤት ለሚገቡ እንግዶች የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንገድ ትራንስፖርት መምሪያ ባለሙያዎችና የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፤የዘርፉ ባለሙያዎች፤ እንዲሁም የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንገድ ትራንስፖርት ኃላፊና የዘርፉ ባለሙያዎች አንድ ላይ በመሆን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እያደረጉ ይገኛል።

የማህበረሰባችን ተወላጆች እንግዶቻቸውን በመያዝ በዓሉን ለመታደም ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ አካባቢያቸው በመግባት ላይ ይገኛሉ

እንግዶች ወደ ቀዬአቸው ገብተው በዓልን ከማክበር ባለፈ በልማትና በሰላም መረጋገጥ ላይ የድርሻውን መወጣት እንደሚገባ ተጠቁሟል።

በጉራጌ ማህበረሰብ ዘንድ ዘመድ አዝማድና ቤተሰብ ተገናኝቶ በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል የመስቀል በዓል አንዱ ነው፡፡

የመስቀል በዓልን ለማክበር ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እንሴኖ ከተማ አስተዳደርና ምስራቅ መስቃን ወረዳን አቋርጠው ለሚያልፉ መንገደኞች በሁለቱም መዋቅር የሚገኙ የትራንስፖርት ዘርፍ አካላት አንድ ላይ በቅንጅት በመስራት እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ እንዲሁም የከተማው ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ጨምሮ እንኳን አደረሳችሁ መልዕክትና እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት አቀባበል በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡

እንሴኖ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ለመንገደኞች 15 ደርዘን ውሃ አበርክቶዋል፡፡

እንሴኖ ከተማ ሳምንታዊ የእሮብ ቀን ጽዳት እና የመስቀል በዓል ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የጽዳትመርሃ ግብር በምስል📸📷📸
24/09/2025

እንሴኖ ከተማ ሳምንታዊ የእሮብ ቀን ጽዳት እና የመስቀል በዓል ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የጽዳትመርሃ ግብር በምስል📸📷📸

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ የ2018 የመስቀል የበዓል ገበያ ቅኝት የሰንጋ በሬ እንዲሁም ሌሎች ገበያዎች በፎቶ👇👇👇👇(መስከረም 13/2018 ቡታጅራ )
23/09/2025

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ የ2018 የመስቀል የበዓል ገበያ ቅኝት የሰንጋ በሬ እንዲሁም ሌሎች ገበያዎች በፎቶ👇👇👇👇
(መስከረም 13/2018 ቡታጅራ )

የገቢ አቅምን አሟጦ ከመጠቀም አንፃር የቀጣይ አቅጣጫና አመራሩን ስምሪት ከመስጠት አኳያ  የተፈጠረ የውይይት መድረክ ***********///********መስከረም 13/18 ዓ.ም እንሴኖ ከተማ...
23/09/2025

የገቢ አቅምን አሟጦ ከመጠቀም አንፃር የቀጣይ አቅጣጫና አመራሩን ስምሪት ከመስጠት አኳያ የተፈጠረ የውይይት መድረክ
***********///********
መስከረም 13/18 ዓ.ም እንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን

የገቢ አቅምን አሟጦ መጠቀም እንደሚገባ የተገለፅ ሲሆን በዚህም ከመደበኛና፤ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ገቢ ጋር ተያይዞ ሰፋ ያለ ውይይት እና የገቢ ንቅናቄ መድረክ የተከናወነ ሲሆን በዚህም

የደረጃ "ሀ"እና "ለ"ደረሰኝ ግብይት ከመስጠት ቫትና፤ቲኦቲ፤ደረሰኝ ተጠቃሚ ከሆኑ ንግድ ቤቶች አንጻር፤ከማዘጋጃ ቤት ገቢ በአግባቡ ከመሰብሰብ አንፃር፤ከቄራ አገልግሎት አሰጣጥ ከሚገኝ ገቢ፤ከፈረስ ጋርዎች ሰሌዳ ግብር፤ ከከተማ ቦታና ጣሪያ ግብር፤ ከታፔላና ማስታወቂያ ባነሮች፤ ከአከራይ ተከራይ ጋር ተያይዞ ፤እንዲሁም ከምጣኔ ጋር ተያይዞ፤ መደቦች፤በስፋትና በዝርዝር ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡

ገቢን በአግባቡ ለመሰብሰብ አደረጃጀቶችን ባግባቡ መጠቀም እንዳለበት እና ከደረሰኝ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የከተማችን ወጣቶች ሚና አጋዥ መሆን መቻል እንዳለባቸው የተገለጸ ሲሆን ገቢን በአግባቡ ሲሰበሰብ ለወጣቱ የስራ እድል መፍጠር የሚቻለው ከገቢ ጋር ያለው ተግባር መሳካት ሲቻል ብቻ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን ህዝብ ለሚያነሳው የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመፍታት ገቢን አሟጦ መጠቀምና ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ በተለያዩ ግብይቶች ደረሰኝ መጠይቅና መቀበል መቻል የሁሉም የከተማችን ማህበረሰብ ግዴታ መሆኑን ከውይይት መድረኩ ተገልፆል፡፡

እንዲሁም ከፊታችን የሚገኘው የመስቀል በአል ምክንያት በማድረግ በዕቃዎች ላይ ያላግባብ የዋጋ ጭማሪ የሚደረግ ሲሆን ይህንንም ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ህብረተሰቡ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግበት የሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በቅንጅት ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው የተነሳ ሲሆን፡-

በመጨረሻም ከመድረኩ በተነሱ ሐሳብ አስተያየቶች ላይ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ የእለቱ የውይይት መድረክ በማጠቃለል የጋራ ተግባቦት ላይ ተደርሷል፡፡ ሁሉም የከተማው አመራር ተልዕኮዎችን በቼክሊስትና በስታንዳርድ መሰረት መፈጸም እንዳለበት ተቀምጧል፡፡

የመስቀል በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲውል በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ  መምሪያ አስታወቀ።መስከረም 13/2018(ሶዶ ጢያ)መምሪያው የመስቀል በዓል በሰላም እን...
23/09/2025

የመስቀል በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲውል በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ።

መስከረም 13/2018(ሶዶ ጢያ)

መምሪያው የመስቀል በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ በማስመልከት ከከተማና ከወረዳ የፀጥታ ፅ/ቤት ኃላፊዎች የሚሊሻ ፅ/ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም የዞን ፖሊስ መምሪያ ማኔጅመንት አባላት እንዲሁም የወረዳና የከተማ የፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር በዛሬው ዕለት በሶዶ ወረዳ በጢያ አለም አቀፍ መካነ ቅርስ ማዕከል ተገኝተው ውይይት አድርጓል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ተካልኝ ንጉሴ እንዳሉት መስቀል በጉራጌ በድምቀት የሚከበር በዓል በመሆኑ በርካታ እንግዶች ከተየለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች ወደ ዞኑ ይገባሉ። ስለሆነም ወደ ዞኑ የሚመጡ እንግዶች ያለምንም የጸጥታ ችግርና በትራፊክ ፍሰት ቁጥጥር ሳቢያ በየርቀቱ በመቆም የሚፈጠረው መጉላላት ሳይፈጠር እንዲጓዙ በትኩረት ይሰራልም ብለዋል። በዞኑ አጎራባች አካባቢዎች ያሉበመንገድ ላይ የሚስተዋሉ አንዳንድ ችግሮች ከአጎራባች ዞንና ወረዳዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ ያለ መሆኑ ገልፀዋል ማህበረሰቡ በዓሉ ወደ ዞኑና አቋርጠው ወደ ሌሎች አካባቢ ለሚያልፉት ከአዲስ አበባ ቡታጅራ ያለው የመንገድ በሚመለከታቸው አካላት ጥገና ስራዎች እየተሰራ ያለ መሆኑ ገልፀዋል

መንገድ ላይ ያለምንም ምክንያት የሚያስቆሙ እና ያለአግባብ በተለያዩ ከተሞች ገንዘብ የሚያስከፍሉ አካላት ጥብቅ ክትትል ይደረግባቸዋል ነው ያሉት።

የፀጥታ አካላትም ይህንን ተግባር በመቆጣጠር ማስቆም እንደሚገባቸው አመላክተው በከተሞች በዓሉን ታሳቢ ተደርጎ የሚደረጉ የርችት መተኮስ እንደማይቻል አስታውቀዋል።

የመስቀል በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲውል በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉ የገለፁት ሀላፊው ለዚህም በቂ የሰው ሀይል እና ተሽከርካሪዎች በመመደብ፣ የስጋት ቀጠናዎችን በመለየት እና ፀረ ሰላም ሀይሎች በመከታተል እርምጃ መውሰድ እንደየ መዋቅሩ ሁኔታ መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል።

የመንገድ መዘጋጋት እንዳይገጥም በከተሞች ባጃጆች እንቅስቃሴ መስመር ለይቶ መስጠትና መቆጣጠር እንደሚገባ እንዲሁም በተከለከሉ የጉዞ መሰመሮች ላይ የሚደረግ ስምሪት ትኩረት ተሰጥቶ የቁጥጥር ስራ መስራት አለባቸው ብለው የመንግስትም ሆነ የግል የተቋማት የጥበቃ ሰራተኞች በትጋት በመስራት የስርቆት ወንጀሎችን መከላከል ይጠበቅባቸዋል ሲሉ ኃላፊው ተናግረዋል።

አቶ ተካልኝ ንጉሴ አክለውም ለዚህ ተግባር ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ገልጸው እያንዳንዱ መዋቅር ከአጎራባች ካሉ መዋቅሮች ተናቦ መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ተግባሩ በውጤት ለመፈጸም የጸጥታ አካላት ማበረታታት፣ መደገፍና ማብቃት ይጠበቃል ያሉ ሲሆን የጸጥታ ስጋት የሆኑ አካባቢዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግም ኃላፊው አቶ ተካልኝ ገልጸዋል።

ህብረተሰቡ ያሳተፈ የጸጥታ ስራ በመስራት የሚገጥሙ ችግሮች ካሉ አፋጣኝ የመረጃ ልውውጥ በማድረግ መስቀል በጉራጌ በሁሉም የዞኑ አካባቢዎች በድምቀት ተከብሮ እንዲውል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የሶዶ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ በቴ በውጭ ከሚፈትነን ሀይል አስመልክቶ ከችግሩ ያልተላቀቁ አካባቢዎች በመለየት በትኩረትና በቅንጅት መስራት እንደሚገባና እስካሁን በነበረው የሽብር ቡድኑ ፍላጎት የተጨናገፈበት የፀጥታ አካሉ ብዙ ዋጋ የከፈለበት ማህበረሰቡም ብዙ ተጋድሎ ያደረገበትና ውጤት የመጣበት በመሆኑ ሁሉም ሊመሰገን ይገባል ብለው ቀጣይም ይህን ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባና የውስጥ ችግሮቻችን እኛው ራሳችን የጀመርነው የሰላም ስራ በማፅናት ማህበረሰባችን መካስ ሰላሙንና አንድነቱን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

የመስቀል በዓልን በተመለከተ የፀጥታው አካሉ፣ የፖለቲካው አመራሩ መዚህ መንገድ ከመከረ የአካባቢያችን መልካም ስም የሚያበላሹ አሉባልታዎችን በመከላከል ሰው ያለምንም ስጋት በር የምንከፍትበት ደህንነቱ ተጠብቆ ቤቱ መግባት የሚችል መሆኑ የምናሳይበት ነው ያሉት

ለበዓሉ የሚመጡ እንግዶችን በተለየ እንክብካቤና ደህንነቱ ተጠብቆ ወደቤተሰቡ እንዲሄድ ያላሰለሰ ጥረት ሊደረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ሙሰማ ጀማል የመስቀል በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲውል ተገቢውን የቅድመ ዝግጅት ስራ እንደተሰራና በእያንዳንዱ ቀጠና ስምሪት እንደሚሰጥ ጠቅሰው የትራፊክ ፍሰቱም ሰላማዊ እንዲሆን ተገቢውን ክትትልና ቁጥጥር እንደሚደረግ እንዲሁም የመረጃ ልውውጦችን በማቀላጠፍ ውጤታማ ስራ እንደሚሰራ ገልፀዋል።

በውይይቱ የተገኙ አካላት እንዳሉት የስጋት ቀጠናዎችን በመለየት በዓሉ በሰላም እንዲከበር አበክረን እንሰራለን ብለዋል።

ከዚህ በፊት በበዓላት ወቅት የነበሩ ጠንካራ ስራዎች በማጠናከርና ክፍተቶች በመለየት በዓሉ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲውል ይሰራል ሲሉ ገልፀዋል።

መዋቅር ከመዋቅር እና የሚመለከታቸው አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል ብለው በተለይ ከሚሊሻ ሀይል ጋር በትብብር መስራት ይገባል ነው ያሉት ።

በተጨማሪም በጎ ፈቃደኞችን ጨምሮ በማሳተፍና ተገቢውን ስመሪት በመስጠት ተገቢውን መረጃ በመለዋወጥ

ህገ ወጥ ስራ የሚሰሩ አካላት ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ ህጋዊ ተጠያቂነት ማስፈን ይገባል ያሉ ሲሆን አካባቢን የሚያውኩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማስተማር ይጠበቃል ሲሉም በውይይታቸው አንስተዋል። በመጨረሻም በዓሉ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የሰላም የፍቅር የደስታ የአብሮነት እንዲሆን ምኞታቸው ገልፀዋል።

በመድረኩ የተገኙት የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሚሊሻ ፅቤት ኃላፊ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ፖሊስ አዛዥ ጨምሮ የማኔጅመንት አባላት የሁሉም መዋቅር የፀጥታና የፖሊስ አመራሮች ተገኝተዋል።

ዘገባው የሶዶ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት ያለመ የኢንስፔክሽንና ተግባር  በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ተጀምሯል።***********///******መስከረም 13 /18 ዓ.ም እንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙ...
23/09/2025

ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት ያለመ የኢንስፔክሽንና ተግባር በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ተጀምሯል።
***********///******
መስከረም 13 /18 ዓ.ም እንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙንኬሽን

"ጠንካራ ኢንስፔክሽን፤ ለጠንካራ ፓርቲ" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ይህ ኢንስፔክሽንና ሱፐርቪዥን መድረክ፣ የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የፓርቲውና የኮሚሽን ስራዎች ኢንስፔክት የሚያደርግ ነው።

የኢንስፔክሽንና ሱፐርቪዥን ቡድኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን አባላት በሆኑት የዞኑ የቴክኒክና ሙያ መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመዲን ጀማል እና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ቤተልሄም ታደሰ የሚመራ ሲሆን፣ በጸደቀ ቼክሊስት በመታገዝ ለሁለት እስከ ሶስት ቀናት በመቆየት ኢንስፔክሽኑን እንደሚያካሂድ ተጠቅሷል።

በዚህ ጊዜ ውስጥ የከተማ ፓርቲ ስራ አመራር ኮሚቴ፣ የብልፅግና ህብረትና ቤተሰቦች፣ እንዲሁም የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ጽቤትና የህብረት ኮሚሽን አደረጃጀቶች አፈጻጸም ይመረመራል።
ግምገማው ከተጠናቀቀ በኋላ፣ ለከተማውና ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እንዲሁም ለብልፅግና ህብረቶችና ቤተሰቦች ግብረመልስና ምክረ ሀሳብ እንደሚሰጥ ታውቋል። ይህም ፓርቲው የተሻለና ውጤታማ እንዲሆን ይረዳል ተብሎ ይጠበቃል።

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit:

Share