የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit public and government service
(1)

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ቁጥር አንድ ምርጫ ክልል የፌዴራልና የክልል ምክር ቤት ተወካዮች ከቡታጅራ ከተማ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ።በከተማው እየተሰሩ ባሉ  የኢኒሼቲቭ ስራ...
09/08/2025

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ቁጥር አንድ ምርጫ ክልል የፌዴራልና የክልል ምክር ቤት ተወካዮች ከቡታጅራ ከተማ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ።

በከተማው እየተሰሩ ባሉ የኢኒሼቲቭ ስራዎች፤ የሰላም ባህልና እሴት ግንባታ ፤ የመልካም አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የሪፎርም ስራዎች ላይ ነው ወይይት የተደረገው።

በፌዴራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመስቃን ቁጥር አንድ ምርጫ ክልል የፓርላማ ተወካይ እና የውሃ መስኖ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ወርቅነሽ ጀማል ብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር ስራዎች ቅድሚያ በመስጠት እየሰራ ያለ ፓርቲ መሆኑን ገልፀዋል።

በተደረጉ የህዝብ ውይይቶቾ የተነሱ ጥያቄዎች ለሚመለከተው አካል የቀረበ መሆኑንም ተናግረዋል።

በተለያዩ ጊዜያት የቀረቡ ጥያቄዎችም አዎንታዊ ምላሽ ያገኙና በተግባር ለመመለስም እየተሰራ እንደሆነ በዝርዝር አቅርበዋል። ህዝባችን የሚያነሳቸው የተለያዩ ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ እንዲፈቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የመስቃን ቁጥር አንድ ምርጫ ክልል የፓርላማ ተወካይ እና የውሃ መስኖ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ወርቅነሽ ጀማል

የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ በህዝቡ የተነሱ ጥያቄዎችን በተግባር ለመመለስ በቁርጠኝነት ሰፊ ስራ መሠራቱን ገልፀዋል።

በሁሉም ዘርፍ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ በከተማው ሰፊ ስራ መስራት ተችሏል፤ የኮሪደር ልማት 8.35 ለምርቃት ማዘጋጀት ተችሏል፤ አዲስ የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ ዝርጋታ በተመሳሳይ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ለአብነት ከፈትኸል መስጂድ በደስታ ጨርቃ ጨርቅ ዝዋይ መውጫ እየተሰራ ነው። በተጨማሪም በኢራ በኩል የቡታጅራ ዋናው ነአስፓልት መንገድ ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ እየተገነባ መሆኑን በመጥቀስ በጥራትና በፍጥነት መፈፀም እንዲችል ከተማ አስተዳደሩ ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ በማድረግ አብሮ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ደረጃውን የጠበቀ የመድሃኒት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት ኢኒሼቲቭ ተገንብቶ መድሃኒት ማቅረብ ተችሏል።

የመንገድ ከፈታ፣ የመብራትና የውሃ መስመር ዝርጋታ እና አዲስ የውሃ ጉድጓድም ለማስቆፈር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የትምህርት ቤት ማሻሻል ከይገባኛል ነፃ ማድረግ ተችሏል፣ ተጨማሪ ብሎክ ግንባታ ተሰርቷል። አዳሪ ትምህርት ቤትም በ2018 በጀት ዓመት መጀመር እንዲቻል እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

ለስራ ዕድል ፈጠራው ዘርፍ ችግሩን ለመቅረፍ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው።

አገልግሎት ለማዘመን የመልካል አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍም በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን እና ሌሎች ስራዎችን ለአብነት አንስተዋል።
ቡታጅራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን

የኮሪደር ልማት ኢንሼቲቭ ከተሞችን ሳቢና ውብ ከማድረግ ባሻገር በመንገዶች ላይ ፍትሃዊነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ተገለፀ።በዞኑ ቡታጅራ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ የሚገኘው የ8.5 ኪሎ ሜትር...
09/08/2025

የኮሪደር ልማት ኢንሼቲቭ ከተሞችን ሳቢና ውብ ከማድረግ ባሻገር በመንገዶች ላይ ፍትሃዊነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ተገለፀ።

በዞኑ ቡታጅራ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ የሚገኘው የ8.5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራዎች በማጠናቀቅ ለማስመረቅ የመጨረሻ ምዕራፍ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ ተመላክቷል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ መሀመድ ሁሴን የኮሪደር ልማት ኢንሼቲቭ ከተሞችን ሳቢና ውብ ከማድረግ ባሻገር በመንገዶች ላይ ፍትሃዊነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልፀዋል።

ቀድሞ በነበሩት የከተሞች አሰራር መንገዶች እግረኞችን ያገለለ ምቾት የሌለው ኢፍትሃዊነት መሆኑን አንስተው በኢኒሼቲቭ የእግረኛ መንገድ፣ የሳይክልና ሌሎችም አማራጮች በመያዝ በመንገዶች ላይ ፍትሃዊነት እንዲኖር እድል ፈጥሯል ብለዋል።

እንደሀገር በአዲስ አበባ ከተማ ተጀምሮ በማስፋፋት ላይ የሚገኘው የኮሪደር ልማት እንደዞን በቡታጅራ ከተማ 25 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን አስታውሰዋል።

በአሁኑ ሰዓት የ8.5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራዎች በማጠናቀቅ ለማስመረቅ የመጨረሻ ምዕራፍ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ አመላክተዋል።

ፕሮጀክቱ የእግረኛ መንገድ ፤የሳይክል ፤የአረንጓዴ ልማት፤ የመብራት ፤ፕላዛዎችና ፋውንቴኖች እንዲኖሩት ተደርጎ የተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በማህበረሰቡ የተጀመረውን የልማት ስራ እንዲሳካ ከጅምር ጀምሮ ሃብት እስከ ማሰባሰብ ድረስ በባለቤትነት አጋርነቱን እያሳየ ይገኛል ያሉት ኃላፊው ከ377 ቤቶች ፤ከ227 አጥር በማፍረስና በማንሳት ከ3 መቶ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ከመንግሥት ካዝና የሚወጣ የካሳ ብር ማትረፍ ተችሏል ብለዋል።

የከተማዋ ማህበረሰብ በግንባታ ሂደቱም አሻራውን ለማሳረፍ በተደረገው የገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም ከ1 መቶ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ቃል በመግባት 84 ሚሊዮን ብር ለግንባታው እንዲውል በማድረግ ታሪካዊ አሻራ አኑረዋል ሲሉ ለማህበረሰቡ ምስጋና አቅርበዋል።

ከተሞችቻችን ከእርጅና በማላቀቅ ለነዋሪዎች ምቹና ሳቢ ለማድረግ የሚሰራው ሲራ በዞን ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ኃላፊዉ በቀጣይም ቀሪ 17.5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራዎች በከተማዋ ተጠናከረው የሚቀጥሉ መሆኑ አንስተዋል።

8.7 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ስራዎች በዋናው አስፖልት ተያይዞ የፌደራል መንግስ የሚሰራዉ መሆኑን ጠቅሰው አስፓልት መንገድ ከ4.2 ኪ.ሜ ከጨርቃ ጨርቅ ዝዋይ ጀንኪሽን እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል።

ከተማዋ ውብ ማራኪና ለመዝናኛ ተመራጭ እንድትሆን በትኩረት እየተሰራ ነው ለዚህ የፀበል ተፋሰስ ጎርጅ ከእርንዛፍ ድልድይ ጨርቃጨርቅ ወደበሬሳ የሚያካልል ፕሮጀክት ዲዛይን መጠናቀቁን አብራርተዋል።

በኮሪደር ልማት ስራው ያረጁ የመብራት እንጨቶች ከማንሳት አንፃር ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅና በጊዜ ከማንሳት አንፃር መብራት ኃይል ውስንነት ያለበት በመሆኑ ፖሉ ያለመነሳቱ ተግዳሮት ሆኗል ብለዋል።

የመብራት ኃይል ተቋም ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ያሉት ኃላፊው ቴሌኮሚኒኬሽን በአንፃሩ የተሻሉ ስራዎች በመስራት እገዛ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

የኮሪደር ልማት ስራ በዞኑ የሚገኙ ከተሞች በማስፋት መስራት የሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምሪያው በቅርበት እንደሚሰራ ገልፀዋል።

ከእንሴኖና ቡኢ ከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት የውይይት መድረኮች በመፍጠር ሂደት ላይ እንደሚገኙ አንስተዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

በዞኑ የአንድ ከተማ/ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ  የህዝብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች መሰራታቸውን የዞኑ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ገ...
09/08/2025

በዞኑ የአንድ ከተማ/ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ የህዝብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች መሰራታቸውን የዞኑ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ገለፀ።

(ነሀሴ 03/2017 ቡታጅራ) የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ መሀመድ ሁሴን በዞኑ የአንድ ከተማ/ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ የህዝብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።

የአንድ ከተማ/ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ፕሮግራም በጠቅላይ ሚነስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት ወደስራ መገባቱን አንስተዋል።

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቀነስ የህዝብ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት በማድረግ ስራዎች ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።

በዚህም በዞኑ በየመዋቅሮቹ አንድ አንድ በድምሩ ሰባት ፕሮጀክቶች ለማሳካት ግብ ተጥሎ ወደስራ መገባቱ አንስተዋል።

በዋናነት የመድኃኒት ዕጥረት በስፋት የሚስተዋል ችግር መሆኑ በመረዳት በሶስት መዋቅሮች ቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ፣እንሴኖ ከተማ አስተዳደርና ደቡብ ሶዶ ወረዳ ኬላ ከተማ ዘመናዊ የማህበረሰብ መድሀኒት ቤት ግንባታ በመገንባት ስራ መጀመር መቻላቸውን ገልፀዋል።

በምስራቅ መስቃን ወረዳ የወጃ ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላና በሶዶ ወረዳ አዴሌ ቦሮቦር ጤና ጣቢያ ግንባታ በመገንባት ማህበረሰቡ የጤና አገልግሎት መስጠት ችለዋል ብለዋል።

በመስቃን ወረዳ ግዴና አቦራት ቀበሌ ለረጅም ዓመታት የአካባቢው ማህበረሰብ መሻገሪያ ድልድይ ዕጦት የሚፈታ ድልድይ እንዲሁም በቡኢ ከተማ አስተዳደር የመዘጋጃቤታዊ አገልግሎት የማዘመን ስራ መስራት መቻሉ አብራርተዋል።

ፕሮጀክቶቹ የማህበረሰብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን አቶ መሀመድ ተናግረዋል።

ቀድሞ ከነበረው የፕሮጀክቶች መጓተትና አላስፈላጊ ወጪን የቀነሰ በአጭር ጊዜ አጠናቆ ማስረከብ ልምድ መወሰድ የተቻለባቸው መሆኑን አመላክተዋል።

በአጠቃላይ ከ52 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎባቸው የተገነቡት የአንድ ከተማ/ወረዳ አንድ ፕሮጀክቶች በዞኑ መዋቅሮች በራስ አቅምና በማህበረሰብ ተሳትፎ ተገንብተዋል ብለዋል።

በቀጣይ ጊዜያት ፕሮጀክቶቹን ይፋዋዊ የማስመረቅ ፕሮግራም እንደሚደረግ ጠቅሰው መሰል የማህበረሰብ ችግር ፈች ፕሮጀክቶች በመለየት ስራዎች እንደሚሰሩ ኃላፊዉ ገልፀዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

የእንሴኖ ከተማ ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ከአስፈፃሚ ተቋማት  ጋር የግብ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡በማ/ኢ/ክ/በምስ/ጉ/ዞን የእንሴኖ ከተማ ምክር ቤት አፈ -ጉባኤ_ ወ/ሮ ዮዲት አህ...
09/08/2025

የእንሴኖ ከተማ ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ከአስፈፃሚ ተቋማት ጋር የግብ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

በማ/ኢ/ክ/በምስ/ጉ/ዞን የእንሴኖ ከተማ ምክር ቤት አፈ -ጉባኤ_ ወ/ሮ ዮዲት አህመድ በተገኙበት የ3 ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ኢኮኖሚ፤ማህበራዊ፤እና የህግና ፍትህ፤መልካም አስተዳደር ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋች ከሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር በ2018 በጀት አመት ዕቅድ የግብ ስምምነት ተፈራረርመዋል፡፡

በግብ ስምምነት ሂደቱ ላይ የከተማው ሁሉም አስፈፃሚ ተቋማት ተግኝተዋል፡፡

ነሀሴ 3/17 ዓ.ም እንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን፡፡

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!
በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡

ፌስቡክ፦
💻Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=100083292124870

💻Instagram

https://www.instagram.com/ensenoketema?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

💻https://vm.tiktok.com/ZMBHSeb9Q/

💻Telegram

https://t.me/Insenoketema12

💻ትዊተር
https://x.com/EnsenoKete23379?t=D4DcjTvlZYEfhnoxgr0-hA&s=3

ዩቲዩብ ፦ 💻 https://youtube.com/?si=z4thqC6KPHoPPFcf

08/08/2025
ዜና ችሎትከዚህ በፊት በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር  #እዝቅኤል አሳምነው # የተባለ የሁለት አመት ተኩል ህጻን ልጅ ልዩ ስሙ አየር ጤና መንደር ከሚገኘዉ መኖሪያ ቤት ዉስጥ ተሰርቆ የተወሰደ መ...
07/08/2025

ዜና ችሎት
ከዚህ በፊት በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር #እዝቅኤል አሳምነው # የተባለ የሁለት አመት ተኩል ህጻን ልጅ ልዩ ስሙ አየር ጤና መንደር ከሚገኘዉ መኖሪያ ቤት ዉስጥ ተሰርቆ የተወሰደ መሆኑን በፌስቡክ ገጻችን መዘገባችን ይታወቃል፡፡

ሆኖም ህፃን ህዝቅሄል አሳምነውን ጨምሮ 2ልጅ አግታ የተያዘቺው ተጠርጣሪ # በቀን 28 /11/17 በዋለው ችሎት ከፍተኛ ፍርድ ቤት 9 አመት ከ 7 ወር የተወሠነባት መሆኑን በመግለጽ ወንጀል ተሠርቶ ማምለጥ እንደማይቻል የእንሴኖ ከተማ አሥተዳደር ፓሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል ወንጀልን በጋራ እንከለከል።ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!
በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡

ፌስቡክ፦
💻Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=100083292124870

💻Instagram

https://www.instagram.com/ensenoketema?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

💻https://vm.tiktok.com/ZMBHSeb9Q/

💻Telegram

https://t.me/Insenoketema12

💻ትዊተር
https://x.com/EnsenoKete23379?t=D4DcjTvlZYEfhnoxgr0-hA&s=3

ዩቲዩብ ፦ 💻 https://youtube.com/?si=z4thqC6KPHoPPFcf

ከ12ሺ በላይ የደረጃ" ሐ "ግብር ከፋዮች  በወቅቱ ግብር መክፈላቸውን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቁ። ነሀሴ 1/2017ዓ.ም ቡታጅራ መምሪያው 56.9ሚሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡ...
07/08/2025

ከ12ሺ በላይ የደረጃ" ሐ "ግብር ከፋዮች በወቅቱ ግብር መክፈላቸውን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቁ።

ነሀሴ 1/2017ዓ.ም ቡታጅራ

መምሪያው 56.9ሚሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡንና ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ51% ብልጫ እንዳለው ገልጿል ።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ሀላፊ አቶ ይሽል ጌታ በላይነህ በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ገቢ ግብር አዋጅ መሰረት የደረጃ "ሐ "ግብር ከፋዮች የግብር ዓመት ከተጠናቀቀ ጀምሮ ከሀምሌ 1 እስከ 30 ድረስ ግብራቸው እንዲከፍሉ መደንገጉን ገልፀዋል።

በ2017ዓ.ም በዞኑ 11,788 የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች በወቅቱ ግብር እንዲከፍሉ ለማድረግ ታቅዶ እስከ ሀምሌ30/2017ዓ.ም 12,315 ግብር ከፋዮች ግብር መክፈላቸውን ገልፀዋል ።

የተሰበሰበው ገቢ 56.9ሚሊየን ብር ሲሆን ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ19.12ሚሊየን ብር /የ51% / ብልጫ እንዳለው አመላክተዋል ።

መምሪያው የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ(e-payment) ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን የገለፁት ሀላፊው 3,430 ነጋዴዎ ቴሌ ብር በመጠቀም 16.9 ሚሊየን በር መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል ።

ጅምሩ የሚበረታታ ነው ያለት አቶ ይሽል ጌታ በላይነህ በዞኑ በ11 ታክስ ማዕከላት አሰራር በማዘመን ሰፊ ቅድመ ዝግጅት ስራ ስለመሰራቱን ገልፀዋል ።

ግብር ከፋዩ ቴሌ ብር በመጠቀም ልምድ አዳብሮ የእድሉ ተጠቃሚ በመሆን በቀጣይ ግብር መክፈያ ወቅት ሁሉም ግብር ከፋይ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ እንዲከፍል አሳስበዋል ።

በቀሪ የግብር መክፈያ ጊዜ ግብር አሳውቀው መክፈል ያለባቸው የደረጃ ለ 550 እና ደረጃ ሀ 692 ግብር ከፋዮች እንዳሉ ገልፀዋል ።

በክልሉ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 10/2017 መሰረት ደረጃ ለ ግብር ከፋዮች እስከ ጷግሜ 5 እና ደረጃ ሀ እስከ ጥቅምት 30 እንደሚከፍሉ አስታውቀዋል ።

ግብርን በውቅቱ አሳውቆ አለመክፈል ለወለድ እና አስተዳደራዊ ቅጣት የሚዳርግ መሆኑ ታውቆ ግብር ከፋዩ በጊዜ የሂሳብ መዝገቡ በማቅረብ ግብር መክፈል እንዳለበት አሳስበዋል ።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ሶፍትዌር ቲም አማካኝነት ያለማውን ኦፊሻል ድህረ ገፅ ለዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት አስረከበ።ነሃሴ 01/2017ዓ.ም (ቡታጅራ)መም...
07/08/2025

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ሶፍትዌር ቲም አማካኝነት ያለማውን ኦፊሻል ድህረ ገፅ ለዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት አስረከበ።

ነሃሴ 01/2017ዓ.ም (ቡታጅራ)

መምሪያው በሶፍትዌር ቲም አማካኝነት የለማውን ኦፊሻል ድህረ ገፅ በዛሬው ዕለት የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ተረክቧል።

የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ጫካ ይፋዊ ድህረ ገፅ ሰነድ ርክክብ ፈፅመዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ሶፍትዌር ዲቨሎፐር ባለሙያ የሆኑት አቶ ርጋ ነስሩ ይፋዊ ድህረ ገፅ የተዘጋጀ ሰነድ አቅርበዋል።

ድህረ ገፁ በአካበቢውንና በሌሎች ከተሞች ጭምር ያሉ የአካባቢው ተወላጆች በባለቤትነት የማስተዋወቅና የማጋራት ስራ ለመስራት የሚያስችል መሆኑን ተገልጿል።

በሀገር አቀፍ ደረጃም ብሎም በአለም አቀፍ ደረጃ ዞኑን ከማስተዋወቅ አልፎ ከሌሎች ከተሞች እኩል ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያግዝ እንደሆነም ተመላክቷል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

የምስራቅ/ጉ/ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት  ከእንሴኖ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አጠቃላይ  ማኔጅመንት ጋር  የድጋፍ እና የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡///፡፡፡፡፡፡፡...
07/08/2025

የምስራቅ/ጉ/ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ከእንሴኖ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አጠቃላይ ማኔጅመንት ጋር የድጋፍ እና የምክክር መድረክ አካሄደ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡///፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነሀሴ 1/12/2017 እንሴኖ

በመድረኩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ አካላት ጋር በመሆን አጠቃላይ በማዘጋጃ ቤት አገልግሎት ዙሪያና ወደፊት በከተሞች እድገት ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይትና ምክክር እንዲሁም የወደፊት የአሠራር አቅጣጫ በማስቀመጥ ከተሞች የደረሱበትን እድገት መሰረት ያደረገ እውቀት ተኮር ተግባራት ላይ ውይይትና የምክክር መድረክ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ መሀመድ ሁሴን፤የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሸሂቾ ኢብራሂም፤የከተማው ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ ኑር ሰርሞሎ፤የዞን ማኔጅመንት አካላት እንዲሁም የከተማው ማዘጋጃ ቤት ማኔጅመንትና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡ ሲል የዘገበው የከተማው መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው፡፡

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!
በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡

ፌስቡክ፦
💻Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=100083292124870

💻Instagram

https://www.instagram.com/ensenoketema?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

💻https://vm.tiktok.com/ZMBHSeb9Q/

💻Telegram

https://t.me/Insenoketema12

💻ትዊተር
https://x.com/EnsenoKete23379?t=D4DcjTvlZYEfhnoxgr0-hA&s=3

ዩቲዩብ ፦ 💻 https://youtube.com/?si=z4thqC6KPHoPPFcf

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ሳይንስናኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዩኒት ፡ በስፔስ ሳይንስ፣በመሰረታዊ ኮምፒውተር እና የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና አስጀመረ*******///*******ሐምሌ 30/2017 ዓ....
06/08/2025

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ሳይንስና
ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዩኒት ፡ በስፔስ ሳይንስ፣በመሰረታዊ ኮምፒውተር እና የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና አስጀመረ
*******///*******
ሐምሌ 30/2017 ዓ.ም (እንሴኖ)

መሰረታዊ ኮምፒውተር አጠቃቀምና ክህሎት እንዲዳብር እና የተለያዩ ክንዋኔዎችን በቀላሉ ለመፈፀም ፈጣንና ቀልጣፋ የስራ እንቅስቃሴ እንዲኖር እንደዚህ አይነት መሰል ስልጠናዎች ወሳኝ ሚና እንዳለው የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዩኒት ሀላፊ አቶ ፈጅሩ ሸረፋ ገለፁ፡-

አክለውም አቶ ፈጅሩ እንዳሉት ተማሪዎች በኮምፒውተር የዳበሩ በብቃትና በክህሎት የበቁ እንዲሆኑ የሚያገለግሉባቸውን የተለያዩ ቦታዎች እና ኮምፒውተሮች እንዲተዋወቁ እንዲሁም የወጪ ብክነትን መከላከል የሚቻልበትን ስርዓት እንዲኖር ያደርጋል ብለዋል፡፡

ስልጠናው ከሌሎች የክረምት ትምህርት ጋር አቀናጅቶ የሚሠጥ ሲሆን በአግባቡ ጀምረው ለሚያጠናቅቁ ሠልጣኞች በኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ እስፓሻል ኢንስትቲዩት አማካኝነት ሀገር አቀፍ ሠርተፍኬት የሚሠጥ መሆኑንም
ተገልጾዋል።

በመድረኩም የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ክፍ ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊ የሆኑት አቶ መሀመድ ሸምሱ እንዲሁም የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ክፍ ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ጀሚላ አልዬ ተገኝተዋል፡፡

ይህ በዛሬው ቀን 30/11/2017 በእንሴኖ  ከተማ አስተዳደር የዛሬ ረቡዕ የፅዳት ዘመቻ ሥራ ተካሂዷል በጽዳት መርሃ ግብሩ ላይ ሁሉም የከተማው ማህበረሰብ  ግቢውን ብሎም አካባቢውን ጽዱ በ...
06/08/2025

ይህ በዛሬው ቀን 30/11/2017 በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር የዛሬ ረቡዕ የፅዳት ዘመቻ ሥራ ተካሂዷል በጽዳት መርሃ ግብሩ ላይ ሁሉም የከተማው ማህበረሰብ ግቢውን ብሎም አካባቢውን ጽዱ በማድረግ በተጨማሪ ወቅቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ላይ ያለን ሲሆን አትክልት ፍራፍሬ ተክሎችን በመትከል የከተማችንን የደን ሽፋን ማሳደግ መቻል እንዳለበት ተገልፀዋል፡፡

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit:

Share