
09/08/2025
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ቁጥር አንድ ምርጫ ክልል የፌዴራልና የክልል ምክር ቤት ተወካዮች ከቡታጅራ ከተማ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ።
በከተማው እየተሰሩ ባሉ የኢኒሼቲቭ ስራዎች፤ የሰላም ባህልና እሴት ግንባታ ፤ የመልካም አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የሪፎርም ስራዎች ላይ ነው ወይይት የተደረገው።
በፌዴራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመስቃን ቁጥር አንድ ምርጫ ክልል የፓርላማ ተወካይ እና የውሃ መስኖ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ወርቅነሽ ጀማል ብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር ስራዎች ቅድሚያ በመስጠት እየሰራ ያለ ፓርቲ መሆኑን ገልፀዋል።
በተደረጉ የህዝብ ውይይቶቾ የተነሱ ጥያቄዎች ለሚመለከተው አካል የቀረበ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተለያዩ ጊዜያት የቀረቡ ጥያቄዎችም አዎንታዊ ምላሽ ያገኙና በተግባር ለመመለስም እየተሰራ እንደሆነ በዝርዝር አቅርበዋል። ህዝባችን የሚያነሳቸው የተለያዩ ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ እንዲፈቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የመስቃን ቁጥር አንድ ምርጫ ክልል የፓርላማ ተወካይ እና የውሃ መስኖ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ወርቅነሽ ጀማል
የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ በህዝቡ የተነሱ ጥያቄዎችን በተግባር ለመመለስ በቁርጠኝነት ሰፊ ስራ መሠራቱን ገልፀዋል።
በሁሉም ዘርፍ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ በከተማው ሰፊ ስራ መስራት ተችሏል፤ የኮሪደር ልማት 8.35 ለምርቃት ማዘጋጀት ተችሏል፤ አዲስ የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ ዝርጋታ በተመሳሳይ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ለአብነት ከፈትኸል መስጂድ በደስታ ጨርቃ ጨርቅ ዝዋይ መውጫ እየተሰራ ነው። በተጨማሪም በኢራ በኩል የቡታጅራ ዋናው ነአስፓልት መንገድ ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ እየተገነባ መሆኑን በመጥቀስ በጥራትና በፍጥነት መፈፀም እንዲችል ከተማ አስተዳደሩ ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ በማድረግ አብሮ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ደረጃውን የጠበቀ የመድሃኒት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት ኢኒሼቲቭ ተገንብቶ መድሃኒት ማቅረብ ተችሏል።
የመንገድ ከፈታ፣ የመብራትና የውሃ መስመር ዝርጋታ እና አዲስ የውሃ ጉድጓድም ለማስቆፈር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የትምህርት ቤት ማሻሻል ከይገባኛል ነፃ ማድረግ ተችሏል፣ ተጨማሪ ብሎክ ግንባታ ተሰርቷል። አዳሪ ትምህርት ቤትም በ2018 በጀት ዓመት መጀመር እንዲቻል እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
ለስራ ዕድል ፈጠራው ዘርፍ ችግሩን ለመቅረፍ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው።
አገልግሎት ለማዘመን የመልካል አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍም በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን እና ሌሎች ስራዎችን ለአብነት አንስተዋል።
ቡታጅራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን