የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit public and government service

06/12/2025
20ኛውን የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓልን በማስመልከት በሆሳዕና ከተማ የቀረበው የፖሊስ ማርሽ ባንድ ትርኢት በምስል፡-
06/12/2025

20ኛውን የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓልን በማስመልከት በሆሳዕና ከተማ የቀረበው የፖሊስ ማርሽ ባንድ ትርኢት በምስል፡-

የክልል አፈ ጉባኤዎች በበዓሉ ላይ ለመታደም ሆሳዕና ከተማ ገቡ(ቡታጅራ፣ ህዳር 27/2018)፣ አፈ ጉባኤዎቹ በዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል ላይ ለመታደም ...
06/12/2025

የክልል አፈ ጉባኤዎች በበዓሉ ላይ ለመታደም ሆሳዕና ከተማ ገቡ

(ቡታጅራ፣ ህዳር 27/2018)፣ አፈ ጉባኤዎቹ በዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል ላይ ለመታደም ወደ ሆሳዕና ከተማ ሲገቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎና በሌሎች የክልልና የሀዲያ ዞን አመራሮች እንዲሁም በአካባቢው ማህበረሰብ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸው።

አፈ ጉባኤዎቹ በሆሳዕና መዳረሻ ሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ አምቢቾ ጎዴ ቀበሌ ላይ ነው አቀባበል የተደረገላቸው።

የዘንድሮው በዓል "ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ከህዳር 25/2018 ጀምሮ በተለያዩ ሁነቶች በሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ይገኛል።

ዘገባው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው።

20ብሔሮች ፤ብሔረሰቦች ቀን በዓል ለማክበር የኢፍድሪ ፌደረሽን ም/ቤት ልዑኳን ቡድን ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ሲገቡ አቀባበል ተደረገላቸዉ። ህዳር 7/2018 ዓ/ም (ቡታጅራ) የ.ኢ....
06/12/2025

20ብሔሮች ፤ብሔረሰቦች ቀን በዓል ለማክበር የኢፍድሪ ፌደረሽን ም/ቤት ልዑኳን ቡድን ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ሲገቡ አቀባበል ተደረገላቸዉ።

ህዳር 7/2018 ዓ/ም (ቡታጅራ)
የ.ኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፌደሬሽን ም/ቤት ዋና አፈ ጉባሄ የተከበሩ አቶ አገኘሁ ተሻገር እና የ.ኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፌደሬሽን ም/ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ዘህራ ሁመድ የተመራዉ የሉዑካን ቡድን ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ሲደርሱ የተከበሩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን፣ የተከበሩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ አቶ እንዳልካቸዉ ጌታቸዉ እና የምስራቅ ጉራጌ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ እና የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ጫካ እና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች የፀጥታ አበላቶች ደማቅ አቀባበል በማድረግ ተሸኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር) ለፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር አቀባበል አደረጉ (ቡታጅራ፣ህዳር 27/2018)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እን...
06/12/2025

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር) ለፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር አቀባበል አደረጉ

(ቡታጅራ፣ህዳር 27/2018)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር) ለፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር አቀባበል አድርገዋል

የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ወደ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመጡት 20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ለማክበር ነው።

በአቀባበል ስነ ስርዓቱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር )፣በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና ክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፣የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ፣የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣የሀይማኖት አባቶች፣የሀገር ሽማጎሌዎች እና እና የሌሞ ወረዳ ህዝብ ደማቅ አቀባበል አድርገዋል::

ዘገባው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው።

በዞኑ አብሮነትና አንድነት  በሚያጠናክር መልኩ ከፍ ያለና ደማቅ አቀባበል  ስለተደረገላቸው መደሰታቸውን የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ተሳታፊ ተናገሩ።የ20ኛ የኢትዮጵያ የብሔር ...
05/12/2025

በዞኑ አብሮነትና አንድነት በሚያጠናክር መልኩ ከፍ ያለና ደማቅ አቀባበል ስለተደረገላቸው መደሰታቸውን የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ተሳታፊ ተናገሩ።

የ20ኛ የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ለማክበር ወደ ክልሉ እየገቡ ላሉት ከተለያየ ክልሎች የተውጣጡ የሉዑካን ቡድን አባላት በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

አቀባበል የተደረገላቸው የአፋር ፣የቤንሻንጉል ፤አማራ፤ኦሮሚያና ሀረር ክልል ሉዑካን ቡድኖች ኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት በሚያጠናክር መልኩ ደማቅ አቀባበል መሆኑ በሰጡት አስተያየታቸውን ተናግረዋል።

የጉራጌ ማህበረሰብ ስራ ወዳድ፤ ከሌሎች ወንድምና እህት ብሄር ብሄረሰቦች በፍቅር የሚኖር መሆኑ አንስተው የተደረገላቸው አቀባበል ይህንን በግልፅ ማየታቸውን ገልፀዋል።

ጉራጌ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ጉራጌ መሆኑ በግልፅ ያየንበት የእንግዳ አክባሪ ማህበረሰብ ነው ጉራጌ ማህበረሰብ ብለዋል።

በእንግዳ አቀባበል ስነ ስርዓቱ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞንና የታችኛው መዋቅር አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የሀይማኖች አባቶች ፣ሴቶች፣ ወጣቶች፣ የዞኑ የባህል ቡድን፣ የፀጥታ አካላት ተገኝተዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

በ20ኛው የኢትዮጲያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ለማክበር ለሚጓዙ የባህል አምባሳደሮች በቡታጅራ ከተማ ደማቅ አቀባበል ተደረጓል።ህዳር 26/2018 በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል አዘጋ...
05/12/2025

በ20ኛው የኢትዮጲያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ለማክበር ለሚጓዙ የባህል አምባሳደሮች በቡታጅራ ከተማ ደማቅ አቀባበል ተደረጓል።

ህዳር 26/2018 በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል አዘጋጅነት ለሚከበረው የኢትይጲያ ብሄሮች ብሄረሰብች ህዝቦች ቀን በዓል ለማክበር ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማን አቋርጠው ላለፉ የባህል አምባሳደሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የሰላም የፍቅር የአብሮነትና የልማት መገለጫ በሆነችው ውቢት ቡታጅራ ከተማ በጉራጌ -በኢትዮጲያ ባህል በክብር ሞቅ ያለ የእንግዳ አቀባበል ከየክልሎች ለተውጣጡ የባህል አምባሳደሮች ተደርጓል የከተማዋን ልማት እንዲጎበኙም ተደርጓል።

የቡታጅራ ከተማን የልማት የእድገትና ሁለንተናዊ ብልፅግናን እና የማህበረሰቡን የልማት የኢኮኖሚ የማህበራዊ ተጠቃሚነት የወጣቶች ምቹ የስራ ዕድል ለመፍጠር በፍጥነትነትና በጥራት የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችንም የባህል ቡድኖች ተመልክተዋል።

የሰላም የፍቅር የልማት እንዲሁም የአብሮት መገለጫ የሆነችው ውቢት ቡታጅራ ከተማ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ በሚያረጋግጡ እና የወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቂሚነት ከፍ በሚያደርግ ሁኔታ በልማት በዕድገት ጎዳና ላይ ትገኛለች።

የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል በጋራ መከበር በማህበረሰቡ ዘንድ መቀራረብ በመፍጠር ሀገራዊ አንድነት እንደሚያጠናክር ተገለፀ።ህዳር 26/2018 ዓ/ም (ቡታጅራ) ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች በማ...
05/12/2025

የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል በጋራ መከበር በማህበረሰቡ ዘንድ መቀራረብ በመፍጠር ሀገራዊ አንድነት እንደሚያጠናክር ተገለፀ።

ህዳር 26/2018 ዓ/ም (ቡታጅራ)

ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ለሚከበረው በዓል ተጓዥ እንግዶች ምስራቅ ጉራጌ ዞን ሲገቡ በቡታጅራ ከተማ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ለልኡካን እንግዶቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት እንደተናገሩት ክልላችንም ሆነ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተመሠረተ አጭር ጊዜ ቢሆንም ከነባሮቹ ዞኖች ባለተናነሰ የህብረተሠቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎች በመሥራት የብልፅግና ትሩፋት ማድረግ መቻሉን አሳውቀዋል።

የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በጋራ መዘከር በማህበረሰቡ ዘንድ መቀራረብ በመፍጠር ሀገራዊ አንድነት እንደሚያጠናክር ገልፀዋል።

ዞናችን በግብርናው ዘርፍ ያለው እምቅ አቅም እንዳለው ያስረዱት ዋና አስተዳዳሪው የስንዴ ምርት በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ዘርፍም ሀገራችን ከመረዳት ወደ ኤክስፖርት እንድትሻገር አስተዋፅኦ እያደረገ ያለ አምራች አርሶ አድር የሚገኝበት ዞን ነው ብለዋል።

በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ዘርፍ በኮሪደር ልማት ዞኑ በተለይም ቡታጅራ ውበና ለነዋሪዎቿ ተመራጭ የማድረግ ሥራ ሥለመሰራቱም አስታውቀዋል።

ዞኑ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የስራ ባህል ያለውና ዘላቂ ሰላም ያለበት በመሆኑ ለአልሚዎች ተመራጭ ነው ብለዋል።

በቱሪዝምና በባህል ዘርፍም ዞኑ እምቅ የባህልና የቱሪዝም ሀብቶች እንደሚገኙ የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው በወንዝ ዳርቻ ልማት በቢሊዮን የሚቆጠር ሀብት በመመደብ እለማ ያለው የጢያ ዓለም አቀፍ ቅርስ በማልማት ለዘርፉ እድገት እየተሠራ ነው ብለዋል።

በመጨረሻም የብሔር ብሔረሰብ ልኡካኑ የሚኖራቸው ቆይታ ያመረና የሠመረ እንዲሆን በመመኘት በድጋሚ እንኳን ወደ ምስራቅ ጉራጌ ዞን በደህና መጣችሁ ብለዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ እንዳልካቸው ጌታቸው 20ኛው የብሔር ብሔረሰብ ቀን ለማክበር ለመጡት የእንኳን ደህና መጣችሁ በላለዲ ዬምጣ፤ የተኝቢ፣ የብሳቢ በማለት የአክብሮት መልዕክት አስተላልፈዋል።

አገራችን ኢትዮጵያ የ13 ወር ፀጋ የጥቁር ህዝብ ቀንዲል በጉባ ተራራ ስር የዳግማዊ አደዋ ምሳሌ የሆነው ታላቁ የህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን አንድነት ትውልድ ተሻጋሪ ታሪክ መሥራት የቻለች አኩሪ አገርና ህዝብ ያለባት ነች ብለዋል።

በአንድነት በዚህ መድረክ ያሰባሰበን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰብ የዘመናት የማንነት፣ የእኩልነትና እውነተኛ የዲሞክራሲያዊ ጥያቄ በህገ_መንግስት የተረጋገጠበት ቀን ለመዘከር እንደሆነ አስረድተዋል።

የጉራጌ ብሄረሰብ በሁሉም ኢትዮጵያ በመሠራጨት ከትንሽ ቁጠባ ተነስቶ ትልልቅ ድርጅቶች በመመስረት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የአንበሳውን ድርሻ እየተወጣ ያለ ህዝብ ነው ብለዋል።

ጉራጌ ከሚታወቅበት የንግድ ሥራ ባሻገር እቁብ እድርና ውጆ ፤ የመሳሰሉት ጥንታዊ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሠረቶቹን ተጠቅሞ ለሀገራዊ ሁለንተናዊ ለውጥ ያራሱን አሻራ እያኖረ እንደማገኝ አስገንዝበዋል።

ዞኑ በርካታ ኃይማኖታዊና ባህላዊ የቱሪስት መስህቦች ሥራ ወዳድና ሠለማዊ ህዝብ የሚገኝበት ነው ብለዋል።

በክልላችን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰብ ቀን ኢትዮጵያዊ ወንድማማችነትና እህትማችነት ከፍ እንዲል የምስራቅ ጉራጌ ዞን ህዝብም የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

05/12/2025
05/12/2025
20ኛ የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች  ቀን በዓል ለማክበር ከተለያዩ ክልሎች የመጡ ልዑኳን ቡድን እንግዶች አቀባበል እየተካሄደ ነው። ህዳር 26/2018 ዓ/ም (ቡታጅራ) 20ኛ የኢትዮጵያ የብ...
05/12/2025

20ኛ የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ለማክበር ከተለያዩ ክልሎች የመጡ ልዑኳን ቡድን እንግዶች አቀባበል እየተካሄደ ነው።

ህዳር 26/2018 ዓ/ም (ቡታጅራ)

20ኛ የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ለማክበር ወደ ክልሉ እየገቡ ላሉት ከተለያየ ክልሎች የሉዑካን ቡድን በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል።

ወንድማማችነትና እህትማማችነትን በሚያጠናክር መልኩ የጉራጌ ማህበረሰብ የእንግዳ ተቀባይነት በሚያሳይ መልኩ በተለያዩ ሁነቶች አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።

ወንድምና እህት ሉዑክ ቡድኖቹ ወደዞኑ ሲገባ የተለያዩ ባህላዊ ውዝዋዜዎችና በተለያዩ ሁነቶች ተካሂዷል።

የአፋር ፣የቤንሻንጉል ፤አማራ፤ኦሮሚያ፤ሶማሌና ሀረር ክልል ሉዑካኖች ቡድኖች ደማቅ አቀባበል ተደርጎርላቸዋል።

በእንግዳ አቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞንና የታችኛው መዋቅር አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የሀይማኖች አባቶች ፣ሴቶች፣ ወጣቶች፣ የዞኑ የባህል ቡድን፣ የሚድያ ባለሙያዎችና የፀጥታ አካላት በተገኝተዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit:

Share