Radar News

Radar News True info and news

16/04/2023

የፍቅር ጓደኛዬ ፂሜን አይቶ ነው የወደደኝ

አያንቱ አድማሱ ትባላለች ከወለጋ ዩኒቨርሲቲ በእንስሳት ህክምና ተመርቃለች። ተወልዳ ያደገችው በቄለም ወለጋ በዳምቢ ዶሎ ነው። አያንቱ ወደ ጉርምስና ከገባችበት ጊዜ ጀምሮ ከልጃገረዶች የተለየ ነገር ማየት ጀመረች፣ እንደ ወንድ ፂም ማብቀል ጀመረች።

ሳይንሳዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ሴቶች እንደ ወንድ ጢም ማብቀል የተለመደ ባይሆንም አልፎ አልፎ እንደሚከሰት ይገለፃል።

አያንቱ በልጅነቷ መላ ሰውነቷ በፀጉር ተሸፍኖ እንደነበር እና ካደገች በኋላ እንደጠፋላት ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ገልፃለች። "ቤተሰቦቼ በልጅነቴ በሰውነቴ ላይ ብዙ ፀጉር ነበረኝ ይላሉ፣ በኋላ ላይ ጠፋ እና ወደ ጉርምስና ስገባ ፂም መብቀል ጀመረ" ብላለች።

መጀመሪያ ላይ ፊቷ ላይ ፂም ሲወጣ ስታይ ተናዳ እራሷን ጠልታ እንደነበር ገልፃለች።

የፍቅር ጓደኛዋ ፂሟን ወዶላት ለፍቅር እንደጠየቃት ትናገራለች "ይህ የእግዚአብሔር ስጦታ ስለሆነ እንዳልቆረጥ ያበረታታኛል" ስትል ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ሃሳቧን አካፍላለች።

ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/fastmereja

15/04/2023

ካርቱም ውስጥ ምን እየሆነ ነው ?

በሱዳን በአገሪቱ ጦር ሠራዊት እና በተጽእኖ ፈጣሪ ነው በሚባለው " ፈጥኖ ደራሽ ሚሊሻ " መካከል በካርቱም ውጊያ ተቀስቅሶ ከተማው በቶክስ እየተናወጠ ነው።

ዛሬ በመዲናዋ ከፍተኛ የተኩስ እና ፍንዳታ ተሰምቷል።

ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ የካርቱም ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያን ተቆጣጥሪያለሁ ያለ ሲሆን፤ የብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያን ለመቆጣጠር የተኩስ ልውውጥ እየደረገ መሆኑን ከሰዓታት በፊት አሳውቋል።

ፍጥጫው እንዴት ጀመረ ?

በሁለቱ ኃይሎች መካከል ለተፈጠረው ፍጥጫ ምክንያት በወታደራዊ አስተዳደር ስር የቆየችውን ሱዳን ወደ ሲቪል መንግሥት ለማሻገር በቀረበው ሃሳብ የተነሳ ነው።

ሄምቲ በሚለው ቅጽል ስማቸው በሚታወቁት በጀነራል መሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ የሚመራው ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ወደ አገሪቱ ጦር ስለሚቀላቀልበት ሁኔታ አንዲሁም ኃይሉን ማን ይመረዋል በሚለው አለመግባባት ተፈጥሮ ባለፉት ቀናት ውጥረት ሰፍኖ ነበር።

ሁለቱ አካላት ምን አሉ ?

ዛሬ የተኩስ ድምጽ መሰማት የጀመረው በማዕከላዊ ካርቱም ውስጥ በሚገኘው የአገሪቱ ጦር ሠራዊት ዋና መሥሪያ ቤት አቅራቢያ ነበር።

(አርኤስኤፍ) የሚባለው ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ምን አለ ?

በዋና ከተማዋ በስተደቡብ ከሚገኙት ካምፖቹ መካከል አንዱ ላይ ጥቃት እንደተሰነዘረበት ገልጿል።

የሱዳን ጦር ሠራዊት ምን አለ ?

የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተዋጊዎች የጦር ኃይሉን ዋና መ/ቤት ለመቆጣጠር ጥረት እያደረጉ ነው ብሏል።

የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ተዋጊዎች በካርቱም እና በሌሎች የሱዳን ክፍሎች ውስጥ የሚገኙ በርካታ የጦር ሠራዊት ካምፖች ላይ ጥቃት ፈጽመዋል ብላል።

ግጭቶች እየተካሄዱ መሆኑ የገለፀው ጦሩ ፤ ሠራዊቱ አገሪቱን የመጠበቅ ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው ብሏል።

ሱዳን ...

ከሁለት ዓመት በፊት በሱዳን ውስጥ መፈንቅለ መንግሥት ከተካሄደ በኋላ የጦር ጄኔራሎች ሉዓላዊ ምክር ቤት የሚባል አካል አቋቁመው አገሪቱን እየመሩ ይገኛሉ።

አርኤስኤፍ የተባለው ፈጥኖ ደራሽ ሚሊሻ በኃያሉ ጄኔራል እና የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ የሚመራ ነው።

የሉዓላዊ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት የሆኑት ጄኔራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሐን ደግሞ የአገሪቱን ጦር ኃይል ይመራሉ።

ሱዳንን ወደ ሲቪል መንግሥት ለማሸጋገር የቀረበው ዕቅድ የአርኤስኤፍ ኃይሎችን ከአገሪቱ ጦር ሠራዊት ጋር በማዋሃድ የጊዜ ሰሌዳ ዙሪያ ከስምምነት ሳይደረስበት ቆይቷል።

አርኤስኤፍ ውህደቱ በአስር ዓመታት እንዲዘገይ ፍላጎት ያለው ሲሆን፣ የአገሪቱ ሠራዊት ግን በሁለት ዓመታት ውስጥ ተግባራዊ እንዲሆን ይፈልጋል።

በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው ውጥረት በተካረረበት ጊዜ አርኤስኤፍ ኃይሎቹን ሐሙስ ዕለት ሜሮዌ ውስጥ ባሉ የመንግሥት ኃይሎች አቅራቢያ አሰማርቷል።

ጄኔራል ቡርሃን በሚቋቋመው ሲቪል መንግሥት ውስጥ የሚመሠረተውን የተዋሃደ የአገሪቱን ጦር ማን መምራት አለበት በሚለው ጥያቄ ዙሪያ የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት ከጄኔራል ዳጋሎ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልጸው ነበር።

(ቢቢሲ)

Civil war coming.....
15/04/2023

Civil war coming.....

29/10/2021

የከፍተኛ ባለሥልጣናት ውይይት በባሕር ዳር ከተማ

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የሚመራ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት የሕግ አስፈፃሚዎች የግንኙነት መድረክ ዛሬ ባሕር ዳር ከተማ ውስጥ በወቅታዊ ሁኔታ እየመከረ እንደሚገኝ ለመንግሥት ቅርበት ያላቸው መገናኛ አውታሮች ዘገቡ።

በዛሬው ምክክር ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የሁሉም ክልሎች ርእሳነ-መሥተዳድሮች፣ የከተማ አስተዳደሮች ከንቲባዎች እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራር እንደተገኙበት ተጠቅሷል።

መድረኩ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍም ይጠበቃል ተብሏል። የክልል መንግሥታት የሕግ አስፈፃሚዎች የግንኘነት መድረክ የኢፌዴሪ የመንግሥታት ግንኙነት ሥርዓትን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 1231/2013 መሰረት የተቋቋመ መሆኑም ተገልጧል። ዝርዝር መረጃዎችን እየተከታተልን ለማቅረብ እንሞክራለን።
ምስል፦ (ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት)

10/09/2021
10/09/2021

1 📌በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል 20 ኪሎ ግራም የሚመዝን እጢ ከአንዲት እናት በተሳካ ቀዶ ጥገና መወገዱ ተሰማ፡፡

ታካሚዋ በሰባት ወራቸው ለእርግዝና ክትትል በመጡበት በማህፀናቸው እጢ መኖሩን ማወቃቸው የተገለፀ ሲሆን÷ የህክምና ባለሙያዎች ለፅንሱ ደህንነት ሲባል ከወሊድ በኋላ ህክምና ለመስጠት መወሰናቸው ተነግሯል።

ልጃቸውን በሰላም ከተገላገሉ በኋላም ዶክተሮች የሰጧቸውን ቀነ ቀጠሮ በመጠባበቅ ላይ ሳሉ የተለየ ህመም ስለተሰማቸው በአፋጣኝ ወደ ሆስፒታል መጥተዋል።

ዶክተሮችም በተሳካ ሁኔታ ከሆዳቸው 20 ኪሎግራም የሚመዝን እጢ ያወጡ ሲሆን÷ አሁን ላይ ታካሚዋ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

09/09/2021

ግብፅና ሱዳን ቀድመው በዝግ የመከሩበት የአረብ ሊግ ስብሰባ


ጳግሜ 4/2013 (ዋልታ) ግብፅና ሱዳን ቀድመው በዝግ የመከሩበት 74ኛው የአረብ ሊግ ስብሰባ ነገ ይጀመራል፡፡

በግብፅ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ስብሰባ የሊጉ አባል አገራት ተወካዮች ወደ ካይሮ እየገቡ ነው፡፡

ከስብሰባው መጀመር አስቀድሞ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሬም ሳዲቅ በማኅበራዊ የትስስር ገፃቸው “እኔና የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሹክሪ፤ የግብጽና ሱዳን የጋራ ጉዳዮችን በተመለከተ በዝግ መክረናል“ ስሉ ጽፈዋል፡፡

ከምስረታው ጀምሮ በግብፅ ጸሐፊነት የሚዘወረው የአረብ ሊግ በታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ የማይመለከተውንና ሚዛናዊ ያልሆነን መግለጫ በተደጋጋሚ ሲያወጣ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡

በዚህም ሁለቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በዝግ የመከሩበት ጉዳይ የሊጉ ስብሰባ አቋም ሆኖ እንደሚወጣም ከዚህ ቀደም ከነበረው ልምዳቸው ይጠበቃል፡፡

ግብፅ በኅዳሴ ግድብ ሰበብ ኢትዮጵያ ላይ ዓለም ዐቀፍ ጫናን ለማሳደር ስትታትር ኢትዮጵያ የጋራ ተጠቃሚነትና በተፈጥሮ ሃብት የመልማትን ፅኑ አቋም ይዛ ቀጥላለች፡፡ በዚህም የግድቡ ሙሌት አደጋ ይፈጥርብኛል ስትል የከረመችው ካይሮ ከግድቡ 2ኛ ዙር ሙሌት ማግስት የደረሰብኝ ጉዳት የለም የሚልን መግለጫ ማውጣቷም ይታወሳል፡፡

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የኅዳሴ ግድብ እንደማይጎዳት በመግለፅ ታራምድ የነበረውን አቋም ትታ የግብፅ ደጋፊ የሆነችው ሱዳንም በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለማሳደር የኢትዮጵያን መሬት እስከመውረር መድረሷ የሚታወቅ ነው፡፡

ዳሩ ግን ኢትዮጵያ እውነታውን ለዓለም ዐቀፉ ማኅበረሰብ በመግለፅ ሰላምና ልማት ፈላጊነቷን እያስመሰከረች በመጓዝ ላይ ትገኛለች፡፡

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦
የአማርኛ ፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ ይከተሉ
https://www.facebook.com/waltainfo
ከአረብኛ ፌስቡክ ገፃችን ጋርም ይጓዙ
https://bit.ly/3vmjIZR
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/WALTATVEth
የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
የትዊተር ገፃችንን ይከተሉ
https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ ደስተኞች ነን!

09/09/2021

መተከል ዞን ግድያው ቀጥሏል።

ትላንት በዚሁ መተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ 5 የጸጥታ ኃይሎች እና 1 የቻይና ዜጋ በታጣቂዎች ተገድለዋል።

ይህንንም ግድያ የክልሉ የሰላም ግንባታ እና ጸጥታ ቢሮ ለኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገፅ በሰጡት ቃል አረጋግጠዋል።

ትላንት አመሻሽ ላይ በታጣቂዎች በተፈጸመው ጥቃት ፤ በመንገድ ስራ ላይ የተሰማሩ አንድ ቻይናዊ እና ኢትዮጵያዊ መገደላቸውን ቢሮው ገልጿል።

በትላንቱ ጥቃቱ የተገደሉት የጸጥታ ኃይሎች፤ አንድ የመከላከያ ሰራዊት አባል እና አራት የፌደራል ፖሊሶች ናቸው። ከእነርሱ በተጨማሪ ሁለት የጸጥታ ኃይሎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በጥቃቱ ህይወታቸውን ያጡት ቻይናዊ እና ኢትዮጵያዊ የመንገድ ሰራተኞች ፤ ከግልገል በለስ ወደ ጉባ በሚወስደው የ70 ኪሎ ሜትር መንገድ ስራ ላይ የተሰማሩ እንደነበር የክልሉ ሰላም ግንባትና ፀጥታ ቢሮ አሳውቋል።

የግልገል በለስ – ጉባ መንገድ ከአዲስ አበባ በደብረ ማርቆስ፣ አንጅባራ እና ቻግኒ አድርጎ ወደ ህዳሴው ግድብ የሚወስድ ዋነኛ መንገድ ነው።

Credit : www.ethiopiainsider.com

09/09/2021

Breaking News Free TPLF Forces

09/09/2021
09/09/2021

Radar News* ባህር ዳር

"የሰዓት ገደቡ ተነስቷል" - የባህርዳር ከተማ ፀጥታ ም/ቤት

በአማራ ክልል መዲና ባህርዳር_ከተማ እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ተጥሎ የነበረው የሰዓት ገደብ ከዛሬ ጀምሮ መነሳቱን የባህርዳር ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት አስታውቋል።

በሌላ በኩል በየከተማው መግቢያና መውጫ ከፖሊስ፣ ከአድማ ብተና ውጭ ማንም መኪና አስቆሞ መፈተሽ የተከለከለ መሆኑን ጥብቅ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የባህር ዳር ነዋሪዎች ለፖሊስና ለፀጥታ አካላት መረጃ እና ጥቆማ ለመስጠት በ 0582264666 መደወል ይችላሉ ተብሏል።

Credit : ባህር ዳር ኮሚኒኬሽን

Address

Butajira
RAAAAA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Radar News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share