ከፍትህ እንጂ ከበደል አንተባበር

ከፍትህ እንጂ ከበደል አንተባበር "He Who seeks justice must come with clean hands.""Justice must be upheld,no matter the consequences"

24/09/2025

#የህግ ግምት ምንድነው ? በዚህ ረገድ የተሰጡ የሰበር ውሳኔዎች ምን ይላሉ?
========================================

#ሕግ አውጪው ለግምት መነሻ ከሚሆኑ የተወሰኑ ፍሬ ጉዳዮች በመነሳት አንድ ድርጊት ተፈፅሟል ወይም አልተፈፀመም ብሎ የሚደርስበትን መደምደሚያ በሕግ የሚደነግጋቸው ሁኔታዎች
የሕግ ግምቶች ዳኞች አንድን ፍሬ ጉዳይ የተፈፀመ ወይም ያልተፈፀመ መሆኑን በማስረጃ በማረጋገጥ ረገድ የሚገጥማቸውን ክፍተት በመሙላትና የማስረዳት ሸክም ያለበትን ወገን ጫናውን በማቃለል በኩል የላቀ ጠቀሜታ ያላቸው መሆኑ ይታመናል፡፡

#ጠቅለል ባለ መልኩ ሲታይም የሕግ (የህሊና) ግምት ዓይነተኛ ዓላማ የማስረዳት ሸክም ያለበትን ወገን ጫና የማቃለል፣ ውሳኔ ሠጪ አካልንም ተገቢና ግልፅ ሆኖ የሚታይ የጠራ ማስረጃ ካላገኘ ወደ ውሳኔ በአፋጣኝ እና በቀላሉ እንዲደርስ ከፍተኛ ጠቀሜታ የሚሠጥ መሆኑ ይታመናል፡፡ የሕግ ግምት ለዳኞች የሕሊና ሚዛን እድል የማይሰጥ ዳኞች የነገሩን ሁኔታ በማየት ሲፈልጉ የሚጠቀሙበት፣ ከነገሩ ሁኔታ አንፃር አስፈላጊ ሆኖ ካላገኙት የሚተውት ፈቃጅ የሆነ የሕግ ግምት አይደለም፡፡ በአንጻሩ የህግ ግምት ድንጋጌ የሚሸፍነው ጉዳይ ባጋጠማቸው ጊዜ ዳኞች ያለምርጫ ሊከተሉትና ሊፈፅሙት የሚገባና አስገዳጅነት ያለው ነው፡፡

#ሰ/መ/ቁ. 29181 ቅጽ 10

#በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2024 የሰፈረው የሕግ ግምት ተፈፃሚ የሚሆነው በምን ዓይነት ሁኔታ ነው? እንዲሁም ተከሣሽ ቀርቦ የቀረበበትን ክስ ባልካደበት ሁኔታ ተፈፃሚ ይሆናል ወይስ አይሆንም? የሚለው ነጥብም ከዚሁ ተያይዞ የሚነሳ ነው፡፡ የሕግ ግምት አፈፃፀም የስረነገር (Substantive) ሕግ እና የስነ ሥርዓት (Procedural) ህግ ገጽታዎች ያሉት ሲሆን ከላይ የተነሱትን ነጥቦች በአግባቡ ለመመለስ የኢትዮጵያ ሕግ በሁለቱም ረገድ ያለውን ዝርዝር ድንጋጌ መመልከትና መረዳት ያስፈልጋል፡፡

#በኢትዮጵያ የስረነገር ሕጎች በርካታ የሕግ ግምቶች ያሉ ሲሆን በፍትሐብሔር ሕጉ ቁጥር 2024 የሰፈረው ግምት ስለ ውሎች ማስረጃ በሚመለከተው ክፍል የሚገኝ ሲሆን በውል የሚጠየቅ ገንዘብ እንደተከፈለ ከሚያስቆጥሩ የሕሊና ግምቶች አንዱ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ እዳው እንዲከፈል ከሚገባበት ቀን ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ሳይከፈሉ የቀሩ በአንቀጹ ተዘርዝረው የተቀመጡትን እዳዎች እንደተከፈሉ ይቆጠራል፡፡
በዚህ ግምት ከሚሸፈኑ እዳዎች መካከል ለቤት ኪራይ የሚከፈል እዳ አንዱ ነው፡፡ (ቁ. 2024/መ) የሕግ ግምቶች መሠረታዊ ውጤት የማስረዳት ሸክምን ከአንዱ ወገን ወደሌላው እንዲሻገር ማድረግ ቢሆንም የማስረዳት ሸክሙ የዞረበት ወገን የሕግ ግምቱን ማፍረስ የሚችልበት የሕግ ሁኔታ ይለያያል፡፡ አንዳንድ የህግ ግምቶች የግምቱ ተጠቃሚ ያልሆነው ወገን ማንኛውንም ዓይነት ማስረጃ በማቅረብ የሚያፈርሳቸው ሲሆኑ (Rebutable Presumption) ሌሎች የሕግ ግምቶች ደግሞ ማንኛውም ዓይነት ማስረጃ በማቅረብ ማፍረስን የማይፈቅዱ (Irrefutable Presumption) ናቸው፡፡

#የፍትሐብሔር ሕጉ ከ2020 – 2024 ያሰፈራቸውን የህግ ግምቶች ለማፍረስ ማንኛውንም ዓይነት ማስረጃ ማቅረብ የማይቻል ስለመሆኑ ከሕጉ አንቀጽ 2026(1) ድንጋጌ መገንዘብ ይቻላል፡፡ ይኸው ድንጋጌ ‘’ከዚህ በላይ ባሉት ቁጥሮች ላይ ለተገለጠው የሕሊና ግምት መቃወሚያ የሚሆን ማንኛውም ዓይነት ማስረጃ ለመቀበል አይቻልም‘’ በማለት በሕጉ የሰፈሩትን ግምቶች ለማፍረስ አንደኛው ወገን ማንኛውንም ዓይነት ማስረጃ ማቅረብ እንደማይፈቅዱለት በመርህ ደረጃ በግልጽ አስፍሯል፡፡

#ይህ አጠቃላይ መርህ ቢኖርም አንዱ ወገን ይህን አስገዳጅ የህግ ግምት ማፍረስ የሚችለው ሌላው ወገን መሀላ እንዲፈጽምለት በመጠየቅ ብቻ ነው፡፡ በዚህ መልክ ሌላው ወገን መሃላ እንዲወርድለት በመጠየቅ የማስረዳት ሸክሙን ለመወጣት የሚሻ ወገን የፍትሐብሐር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 83 በሚያዘው መሠረት ይህን ማስረጃውን ክሱን በሚያቀርብበት ወቅት እንዲጠቅስ ይጠበቅበታል፡፡

#በውል ሕግ የሰፈሩት እነዚህ ድንጋጌዎች የስረ ነገር ሕግ ክፍሎች በመሆናቸው ፍርድ ቤቶች ሊከተሉዋቸው የሚገባ አስገዳጅ የሕግ ድንጋጌዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ድንጋጌዎች የማስረጃን አቀራረብ የሚመለከቱ ከመሆናቸው በስተቀር እንደማንኛውም ሌላ የውል ሕግ ድንጋጌዎች በባለጉዳዮች ቢጠቀሱም ባይጠቀሱም ፍርድ ቤቱ አግባብነት ባለበት ሁኔታ ሁሉ ተፈፃሚ ሊያደርጋቸው የሚገቡ ድንጋጌዎች ናቸው፡፡ ወደ ፍርድ ቤት የሚቀርቡ ባለጉዳዮች ለጉዳያቸው አግባብነት ያለውን ፍሬነገርና የሚጠይቁትን ዳኝነት ከመግለጽ አልፈው በእያንዳንዱ ጉዳይ ላይ ተፈፃሚ የሚሆነውን ወይም የማይሆነውን ድንጋጌ እንዲጠቅሱ አይጠበቅባቸውም፡፡ በመሆኑም በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2024 የተጠቀሰውን የሕግ ድንጋጌ ተፈፃሚ ለማድረግ የሚያበቃ ፍሬ ነገር የቀረበለት መሆኑን የተረዳ ፍ/ቤት በዚሁ ድንጋጌ መሠረት የሚሸፈነውን ፍሬ ነገር እንደተረጋገጠ የመቁጠር ግዴታ አለበት፡፡

#የሕግ ግምቶችን አስመልክቶ በፍትሐብሔር ሕጉ የሰፈረው ይህ መሠረተ ሃሣብ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉም በተመሣሣይ መንገድ ተደንግጎ የምናገኘው ነው፡፡ በዚሁ ሕግ መሠረት ማንኛውም ተከሣሽ በመርህ ደረጃ ለፍርድ ቤቱ በሚያቀርበው መልስ ክስ የቀረበበትን ነገር በግልጽና በዝርዝር ማስተባበል ይጠበቅበታል፡፡ በክስ አቤቱታ ላይ የቀረበ ማንኛውም ነገር በግልጽ ካልተካደ እንደታመነ ሊቆጠር እንደሚችልም ይደነግጋል፡፡ ይህ አባባል አጠቃላይ የፍትሐብሔር መደበኛ ሙግት አካሄድን የሚመለከት ቢሆንም ተከሣሹ የሕግ ግምት ተጠቃሚ ሲሆን በግምቱ የሚሸፈነውን ፍሬ ነገር በሚመለከት ይህ ግዴታ እንደሚወርድለት የሕጉ አንቀጽ 89 በግልጽ ያስቀምጣል፡፡ ይህ ድንጋጌ ‘’አስቀድሞ በአንደኛው ወገን አቤቱታ ወይም ሙግት በግልጽ የተካደ ጉዳይ ካልሆነ በቀር አንዱ ወገን ተከራካሪ ህጋዊ በሆነ ግምት የሚደገፍበትን ነገር ወይም ሌላው ወገን ማስረጃ እንዲያቀርብ ተገቢ የሆነበትን ጉዳይ ሌላው ወገን በአቤቱታው ውስጥ መጥቀስ አይገባውም’’ በማለት የሕግ ግምት ተጠቃሚ የሆነ ተሟጋች በሚያቀርበው መልስ በህግ ግምት የተሸፈነውን ፍሬ ነገር በግልጽ የመካድ ግዴታ እንደሌለበት ያመለክታል፡፡
በመሆኑም አንድ ተከሣሽ በሕግ ግምት የተሸፈነውን ፍሬ ነገር በማስመልከት በመልሱ በግልጽና በዝርዝር መካድ አይጠበቅበትም፡፡ በመሆኑም በህግ ግምት የተሸፈነን ጉዳይ በማስመልከት ማንኛውም ፍርድ ቤት ቢሆን ተከሣሹ በግልጽ ስላልካደ እንዳመነ ይቆጠራል በማለት ፍርድ ሊሰጥ አይችልም፡፡
#ይህ መሰረተ ሃሣብ በፍትሐብሔር ሕጉ ካለው መሠረተ ሃሣብ ጋር ተመሳሳይ እና የሚጣጣም ነው፡፡ የሕግ ግምትን አስመልክቶ ያለው የሕግ ማእቀፍ ይህ በመሆኑ ፍርድ ቤቶች የሚሰጡት ውሣኔ ይህንኑ መሠረት ያደረገ መሆን ይጠበቅበታል፡፡ ተከሣሹ የሕግ ግምት ተጠቃሚ በሚሆንበት ወቅት የሚከተሉት ሂደትና የሚሰጡት ውሣኔም በሌሎች በመደበኛ የሙግት ሂደት ከሚተከሉዋቸው የሥነ ሥርዓትና የማስረጃ ደንቦች የተለዩ መሆናቸው የማይቀር ነው፡፡ በመሆኑም የቀረበላቸው ፍሬ ነገር በህግ ግምት እስከተሸፈነ ድረስ ፍርድ ቤቶች ተከሣሽ ካደም አልካደ የሕግ ግምቱን ተፈፃሚ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ተከሣሹ በሌለበት ጉዳዩ እንዲቀጥል መደረጉም አስገዳጅ በሆኑት የሕግ አንቀጾች አፈጻጸም ላይ የሚያመጣው ለውጥ አይኖርም፡፡ ተከሳሹ ፍርድ ቤት ቢቀርብም በግልጽ እንዲክድ የማይገደደውን ፍሬ ነገር ጉዳዩ እርሱ በሌለበት በመቀጠሉ እንዳመነ የሚቆጠርበት በቂ ሕግ ምክንያት የለም፡፡
#ሰ/መ/ቁ. 17068 ቅጽ 1

#የይርጋ ሕግ አንድ ፍርድ ቤት የቀረበለትን ጉዳይ ፍሬ ነገር መመርመር ሳያስፈልገው አንድን ክስ ውድቅ የሚያደርግበት ሥርዓት ሲሆን የሕግ ግምት ግን ጉዳዩ ፍርድ ቤት ቀርቦ በተከራካሪዎች መካከል የቀረበው ማስረጃ ሲመዘን ተፈጻሚ የሚሆን ደንብ ነው፡፡ በመሆኑም አልፎ አልፎ የውጤት መመሳሰል የሚያጋጥም ቢሆንም የሕግ ግምትን ተፈጻሚ ለማድረግ ፍርድ ቤቱ የቀረበለትን ፍሬ ነገርና አግባብነት ያለውን ሕግ እንዲመረምር የግድ የሚል ሲሆን ይርጋ ግን ጊዜውን በመቁጠር ብቻ ክሱ በፍሬ ነገር ደረጃ እንዳይሰማ የሚያደርግ ሥርዓት ነው፡፡ የፍትሐብሔር ሕጉ ከ2020-2024 ባሉት ድንጋጌዎች የተለያዩ የህግ ግምቶች አስቀምጧል፡፡ እነዚህ የሕግ ግምቶችን እንደብዙዎቹ የህግ ግምቶች አንድ ክስ ለችሎት ቀርቦ በሚታይበት ወቅት የማስረዳት ሸክም ያለበት ማነው? በሕግ የሰፈረውን ግምት ማፍረስ የሚቻለው እንዴት ነው? ወ.ዘ.ተ. የሚሉትን ማስረጃን የሚመለከቱ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች እንጂ አንድ ጉዳይ በጊዜ ማለፍ ምክንያት ክስ እንዳይቀርብበት የሚከለክሉ የይርጋ ደንቦች አይደሉም፡፡
#ሰ/መ/ቁ. 15992 ቅጽ 1

20/09/2025

በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 145 መሠረት የሚቀርቡ የሰነድ ማስረጃዎች
---------------------------------------------
መግቢያ
የማስረጃ አቀራረብ በተመለከተ በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 137 ጀምሮ እንዴት መቅረብ እንዳለበት እስከ 146 ድረስ ተደንግጎ የተቀመጠ ቢሆንም በዚህ ህግ በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 223 እንዲሁም 234 ላይ ተደንግጎ የተቀመጠ ሲሆን በዚህ ህግ በሌሎች አንቀጾች ወይም ክፍሎች ተቀምጠዋል። ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነው ግን በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 145 መሠረት የሚቀርቡ ማስረጃዎች በተመለከተ ነው።
1. በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 145 መሠረት የሚቀርቡ ማስረጃዎች በአንዳቸው ተከራካሪ ወገን የሚቀርብ የጹህፍ ማስረጃ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ካመነበት በራሱ ስልጣን ትክክለኛውን ፍርድ ለመስጠት ሲባል በትእዛዝ አስቀርቦ የሚመለከተው ማስረጃ ነው። ተከራካሪው ወገን በራሱ ስልጣን አቅም የጹህፍ ማስረጃውን አስቀርቦ በማስረጃነት በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 223 መሠረት አስቀርቦ ለማያያዝ ያልቻለ እንደሆነ በፍርድ ቤቱ በኩል በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 145 መሠረት በማስረጃነት ተቆጥሮለት እንዲያያዝለት ሊጠይቅ ያስፈልጋል። ፍርድ ቤቱም በፍ/ስ/ስ ህግ ቁጥር 231 መሰረት የክሱን ተቀባይነት ከተመለከተ በኋላ በ145 መሠረት እንዲቀርብለት የጠየቀውን ማስረጃ አስረጅነቱን ካመነበት በኀላ ተከሳሽ መልሱን ከማቅረቡ በፊት ፍርድ ቤቱ በትእዛዝ ማስረጃውን ካስቀረበ በኃላ ለተከሳሽ ከክሱ ጋር ደርሶት መልሱን ሊያቀርብ ያስፈልጋል። ምክንያቱም ተከሳሽ መልሱን ሲያቀርብ ከዚህ ማስረጃም ጭምር በመነሳት ነው።
አለበለዚያ ግን ይህ ማስረጃ የሚቀርበው ክስ ተሰምቶ ካለቀ በኋላ ለምርመራ ተቀጥሮ በሆነ ጊዜ ፍርድቤቱ በመጨረሻ ይህ ማስረጃ እንዲቀርብ የታዘዘ እንደሆነ ይህ ማስጃ በሚለው ላይ መልስ፣አስተያየት፣ ክርክር የመሥጠት እድሉ የሚታጣ ይሆናል። ይህ ሲሆን ተከራካሪዎች የመከራከራ መብት ከማጣታቸው በተጨማሪ የሚሰጠው ፍርድም ፍትሀዊነቱ ላይ ሚዛኑን ያጣል።
2. በተከሳሽ በኩሉም ይህ በማስረጃነት ተቆጥሮ እንደቀርብ ከተቆጠረም ፍርድቤት የክስ መስማት ሂደቱን ከመጀመሩ በፊት ይህንን በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 145 መረረት በማስረጃነት በማስቀረብ ለከሳሽ ደርሶት ለክስ መስማት ሂደቱ እንዲዘጋጁበት ማድረግ ያስፈልጋል።
3. ይህ ሂደት ከማስረጃ አቀራብ አላማ አንጻር ጭብጥ በመያዝ ተገቢውን ክርክር ለመያዝ ስለሚረዳ ነው። የፍ/ስ/ስ/ ህ ቁጥር 137 እንኳን የተመለከትነው እንደሆነ የሰነድ ወይም የጹህፍ ማስረጃ ከመጀመሪያ ቀነ ቀጠሮ ወይም በፊት መቅረብ እንዳለበት ያስቀምጣል። ይህ የሚሆንበት ምክንያት ተከራካሪ በፈለገበት ጊዜ ማስረጃ ቢያቀርብ አዲስ ጭብጥ ወይም ክርክር እየተነሳ የክስ መስማት ሂደቱ እንዳይበላሽ ነው።
4. ፍርድ ቤቱም ቢሆን በራሱ አነሳሽነት እንኳን ይህ ማስረጃ በ145 መሠረት እንዲቀርብ ትእዛዝ ቢሰጥ እንኳን ክርክሩ ከመጀመሩ በፊት ቢሆን የተሻለ ነው። ይህ ቀደም ሲል እንደ ተገለጸው የክስ መስማቱ ሂደት የተንዛዛ እንዳይሆን አዲስ ማስረጃ በተፈጠረ ቁጥር አዲስ ክርክር አዲስ ጭብጥ በመያዝ የክርክሩ ሂደት እንዳይቀየር ነው። ጭብጥ ወይም ክርክር ከክስ መልስ ማስረጃ አንጻር ሊያዝ እንደሚቻል ከ246 _ 255 ድረስ ያሉትን የፍ/ስ/ስ/ህግ ድንጋጌዎችን መመልከት ይቻላል። ከእነዚህ ድንጋጌ አንጻር ጭብጥ የሚያዘው ከላይ እንዳስቀመጥነው ማስረጃ ለጭብጥ አያያዝ መሠረታዊ ምክንያት ያለው ሲሆን ለአቤቱታ መሻሻልም ምክንያት ሊኖረው ይችላል።
5. ማስረጃን በክርክር ውስጥ በተፈለገበት ጊዜ ሁሉ ማቅረብ እንደማይገባ ከላይ የተገለጹት ድንጋጌዎች የሚያስረዱ ሲሆን የፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 256 ንም መመልከት የሚቻል ነው። በዚህም ድንጋጌ ከፍርድ በፊት ቀድሞ በስነስረአቱ አግባብ በጊዜው ለማቅረብ ከአቅም በላይ የሆነውን ማስረጃ እንደደተገኘ ማቅረብ የሚቻል ሲሆን ይህም ከአቤቱታው ጋር ወይም በመጀመሪያው ቀነ ቀጠሮ ወይም በፊት ማቅረብ ያልተቻለው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ማግኘት ያልተቻለ ሲሆን ይህም ማስረጃው በተገኘ ከፍርድ በፊት መሆን አለበት(256)።
ይህ ማስረጃ ተቀባይነት ከተገኘ ፍርድ ቤቱ በነገሩ ላይ ለመስማት ቀጠሮ ይዞ ይሰማል።
6. ይህ አጠቃላይ የማስረጃ አቀራረብ ስነስርአት በክስ መስማት ሂደቱ ላይ ትልቅ ድርሻ ያለው ሲሆን ከጭብጥ አመሰራረት ጋር እንኳን ጉልህ ሚና አለው። የፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 249 ን እንኳን ስንመለከት ጭብጥ ለመመሥረት አስፈላጊ ሲሆን የሠነድ እና የሠው ማስረጃዎችን መመርመር አስፈላጊ የሚሆንበት ሁኔታ እንዳለ ያስቀምጣል።
7. ስለሆነም ክርክር ወደ ኋላ እንዳይመለስ በመለወጥ ወይም በማሻሻል የክስ መስማቱ ሂደት እንዳይጓተት ወይም ስህተት እንዳይፈጠር ማስረጃዎች በሙሉ በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 137 መሠረት ቢዘገይ በመጀመሪያ ቀነ ቀጠሮ ሊቀርቡ ወይም ከዚህ ቀጠሮ በፊት መቅረብ ያለባቸው ሲሆን በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁጥር 145 በፍርድ ቤት በኩል ሊቀርቡ የሚገባቸው ማስረጃዎችም ለክርክሩ ሂደት አመቺነት ቀድሞ ክስ መስማት ከመጀመሩ በፊት አስቀድመው ሊቀርቡ የሚገቡ ናቸው።

‎  #የእርቅ ሥምምነት በፍ/ቤት ሊፀድቅ የሚገባው መቼ ነው❓       ==========================‎‎👉🏿አንድ ስምምነት በፍ/ቤት  #ሊፀድቅ የሚችለው ጉዳዩ ስልጣን ባለው ፍ/ቤ...
15/09/2025

‎ #የእርቅ ሥምምነት በፍ/ቤት ሊፀድቅ የሚገባው መቼ ነው❓
==========================

‎👉🏿አንድ ስምምነት በፍ/ቤት #ሊፀድቅ የሚችለው ጉዳዩ ስልጣን ባለው ፍ/ቤት በመታየት‎ #ሂደት ላይ እያለ ተከራካሪ ወገኖች ጉዳዩን #በስምምነት የጨረሱ መሆኑን ገልፀው ይኼው‎ስምምነት ለህግና ለሞራል ተቃራኒ ያለመሆኑ ሲረጋገጥ ስለመሆኑ፣🎯

‎ #ከፍርድ ቤት ውጪ በሚደረግ እርቅ ወይም ግልግል መሰረት ያለመግባባትን ያስቀሩ‎ወይም ለጉዳያቸው እልባት ያገኙ ሰዎች የእርቁን ወይም የግልግሉን ስምምነት በፍርድ‎ቤት #ማስመዝገብ ወይም #ማስፀደቅ የማያስፈልጋቸው ስለመሆኑ፣🎯

‎👨‍⚖️የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቅፅ 15 በሰበር መዝገብ ቁጥር 85873 ላይ በተመሣሣይ ጉዳይ አስገዳጅነት_ያለውን ውሣኔ ሰጥቷል።

15/09/2025

‎ #ጉዳዩ ከይዞታ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት እና ከሰነዶች ጋር የተያያዘ በመሆኑ ብቻ #በፍርድ ሊወሰን የሚችል አይደለም ሊባል ስላለመቻሉ፤

‎ #እንዲሁም የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ካርታ ወይም ሌሎች ሰነዶች #ተወስደውብኛል ተብሎ ክስ በሚቀርብበት ጊዜ የተወሰዱበት አግባብ #ህጋዊ
‎መሆን አለመሆኑ በፍርድ ቤት ሊጣራ የሚችል ጉዳይ ስለመሆኑ፣

‎የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቅፅ 16 በሰበር መዝገብ ቁጥር 97464 ላይ በተመሣሣይ ጉዳይ አስገዳጅነት_ያለውን ውሣኔ ሰጥቷል።

15/09/2025

ለምጣድዋ ልዩ ጥበቃ እሚያደርገው የአደን ጫወታ ሊያበቃ በጣም ጥቂት የባከኑ ጊዜያት ቀርተዋል!!

14/09/2025

ኑዛዜን ለመቃወም የተቀመጠ ጊዜ ገደብ
የኑዛዜ የይርጋ ጊዜ
-------------__-----👇--------------
ኑዛዜ ፈራሽ ነው የሚል ክስ የሚቀርብበትን የጊዜ ገደብ በተመለከተ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በቁጥር 973 ላይ የተመለከተው ተፈጻሚ ሚሆነው ኑዛዜ ፈራሽ ነው የሚለውን ክስ ኑዛዜው ሲነገር በነበሩ ሰዎች የቀረበ እንደሆነ ነው፡፡ ይህም ማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973/1/ ላይ እንደተገለጸው “ኑዛዜ ሲነበብ የነበሩ ወይም የተወከሉ ሰዎች ኑዛዜው አይጸናም ወይም አንዱ በኑዛዜው የተነገረው ቃል አይጸናም በማለት ክስ ለማቅረብ ያላቸውን ሀሳብ መግለጫ ወይም ስለ ክፍያው በሂሳብ አጣሪው የቀረበውን የድልድል አመዳደብ ሀሳብ ለመቃወም ኑዛዜው ከተነበበት አንስቶ በሚቆጠር የአስራ አምስት ቀን ጊዜ አላቸው”፡፡
በሌላ መልኩ ደግሞ ኑዛዜው ሲነበብ ያልነበሩ ሰዎች መቃወሚያቸውን መቼ ሊቀርቡ ይችላሉ ለሚለው በፍ/ሕ/ቁ 974/1/ እና 2 ላይ የተገለጸ ሲሆን በዚህም መሰረት “ በኑዛዜ ንባብ ሥነ-ሥርዓት ላልነበሩ ወይም በኑዛዜው ንባብ ሥነ-ሥርዓት በወኪልነት ላልሰሙ ሰዎች እንዲሁም ኑዛዜው በሌሉበት የተነበበ እንደሆነ ከዚህ በላይ የተገለጸው የጊዜ ገደብ ለመቁጠር መነሻ የሚሆነው ሥለ ክፍያው ድልድልና አመዳደብ ሀሳቡን ከተነገራቸው ቀን አንስቶ ነው”፡፡
በፍ/በ/ህ/ቁ 973/2/ ላይ በተገለጸው መሰረት ኑዛዜ ከፈሰሰበት ጊዜ ከአምስት ዓመት በኋላ ወይም ኑዛዜ የሌለ እንደሆነ ሟች ከሞተ ከአምስት ዓመት በኋላ ስለ ኑዛዜው መጽናትና ስለክፍያው አመዳደብ አጣሪው ያቀረበውን የድልድል ሀሳብ በማናቸውም አስተያየት ቢሆን መቃወሚያ ሊቀርብበት አይችልም፡፡
ከዚህ በላይ ከተገለጹት የሕግ ድንጋጌዎች ጋር በተያያዘ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 82585 በቅጽ 15 ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ የሰጠ ሲሆን በትርጓሜውም “በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ድንጋጌዎች አቤቱታ አቅርቢው ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ ወይም የተወከለ የመሆን አለመሆን መስፈርት መሰረት በማድረግ ይርጋው መቁጠር የሚጀምርበትን ጊዜ እና ፍጹም የሆነ የይርጋ ጊዜ በቁጥር 974/2/ ከመደንገጋቸው በስተቀር ሁለቱም ድንጋጌዎች ኑዛዜው ፈራሽ ነው የሚል ክስ የሚቀርብበትን ስርዓት የሚደነግጉ በመሆቸው ተያያዥነት አላቸው በማለት ኑዛዜ መኖሩን ማወቅ እና የኑዛዜውን ሙሉ ይዘት ማወቅ የተለያዩ ጉዳዮች ናቸው ሲል በፍ/ብ/ህ/ቁ 973/1/ የተመለከተው የ15 ቀን ጊዜ ገደብ የክስ ማቅረቢያ ጊዜ ሳይሆን የመግለጫ ማቅረቢያ ጊዜ ነው፡፡ በመሆኑም ስለ ኑዛዜ መኖር እንጂ ስለድልድሉ የማያውቅ ወራሽ መግለጫ የማቅረብ ግዴታ ስለማይኖርበት ጊዜው መቁጠር የሚጀምረው በኑዛዜው የተደረገውን ድልድል ካወቁበት ቀን ጀምሮ ነው” በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
በሟች የተደረገ ኑዛዜ ከውርስ የነቀለኝ በመሆኑ ሊፍርስ ይገባል በማለት ኑዛዜው ሲነበብ በነበረ አመልካች የሚቀርብ የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 መሰረት በተገለጠው የጊዜ ገደብ ነው ወይስ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 በተገለጸው ጊዜ ውስጥ ነው? የሚለው አከራካሪ ጉዳይ በመሆኑ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 152134 በቅጽ 23 ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በውሳኔውም መሰረት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 ስለ ኑዛዜ መነበብ እንዲሁም ኑዛዜ ሲነበብ የነበሩ ሰዎች ኑዛዜው እንዲፈርስ አቤቱታ የሚያቀርቡበትን ሥርዓትና ጊዜውን በሚመለከት የሚደነግግ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል /ነቅሎናል/ በማለት ኑዛዜው እንዲፈርስ የሚቀርብን ወይም የቀረበ አቤቱታን የሚመለከት አይይለም፡፡ በመሆኑም ኑዛዜው ከውርስ የመንቀል ውጤት ያለው በመሆኑ እንዲፈርስ በሚል የሚቀርብ የዳኝነት ጥያቄ ሊታይ የሚገባው በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት ነውእንጂ በአንቀጽ 973 መሰረት አይደለም በማለት አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በላይ በተጠቀሰው የሕግ ትርጓሜ መሰረት ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ አመልካች ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል በማለት የሚያቀርበው የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ህ/ቁ 973 መሰረት ሳይሆን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ነው የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡
በአጠቃላይ አንድ ኑዛዜ ፈራሽ ነው በሚል ስለሚቀርብ መግለጫ እና እንዲሁም መግለጫው እና ክሱ ሊቀርብ ስለሚገባው የጊዜ ገደብ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 ተፈጻሚነት የሚኖረው ኑዛዜ ሲነበብ በነበሩ ወይም በተወከሉ ሰዎች ጉዳይ ሲሆን በአንቀጽ 974 ድንጋጌ ደግሞ ተፈጻሚነቱ በኑዛዜ ሥነ-ሥርዓት ባልነበሩ ወይም ባልተወከሉ ሰዎች ጉዳይ ነው፡፡ ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ አመልካች ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል በማለት የሚያቀርበው የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ህ/ቁ 973 መሰረት ሳይሆን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት ነው፡፡

✅✅ቼክ በቼኩ ለይ ከተፃፈበት ቀን አንስቶ በሚከተሉት በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ለክፍያ ወደ ባንክ መቅረብ አለበት ን/ሕ/ቁ 855፤ ቼኩ በቂ ስንቅ የሌለለው ከሆነ በሚከተሉት 6 ወራት ክስ ...
14/09/2025

✅✅ቼክ በቼኩ ለይ ከተፃፈበት ቀን አንስቶ በሚከተሉት በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ለክፍያ ወደ ባንክ መቅረብ አለበት ን/ሕ/ቁ 855፤ ቼኩ በቂ ስንቅ የሌለለው ከሆነ በሚከተሉት 6 ወራት ክስ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል ን/ሕ/ቁ/ 881 ። ቼኩ በስድስት ወር ውስጥ ለባንክ ያላቀረበ እና/ወይም በሚከተሉት 6 ወራት ውስጥ ክስ ያላቀረበ ይርጋ ቼኩ በእሡ እያለ የታገደበት ያለው ሕጋዊ ምፍትሔ ምንድነው?
✅✅በቼክ ላይ የተፃፈለትን ገንዘብ በህጉ በተቀመጠው ጊዜ ክፍያ ያልጠየቀበት ሰው ወይም በይዞታው እያለ የታገደበት እንደሆነ ይህንኑ ቼክ እንደ ተራ ሰነድ በማስረጃነት በማቅረብ ያላግባብ የመበልፀግ ክስ ሊመሰርት የሚችል ስለመሆኑ የንግድ ህግ ቁ. 799 ሰ/መ/ቁ 40173
✅✅አንቀፅ 855 ለመክፈል መቅረብ
ቼክ የወጣበት ቀን ከግምት ውስጥ ሳይገባ በቼኩ ላይ ከተፃፈው ቀን አንስቶ በሚከተሉት ስድስት ወራት ውስጥ እንዲከፈልበት መቅረብ አለበት
✅✅በንግድ ህግ ቁጥር 881/1/ ስር በተመለከተው የአንድ ዓመት የጊዜ ገደብ ክስ የማቅረብ መብታቸው በህግ ፊት ተቀባይነት ሊኖር የሚችለው በን/ሕ/ቁ. 855 ስር ቼኩን በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ለባንክ የማቅረብ ቅድመ ሁኔታ ሲያሟላ ስለመሆኑ፣

14/09/2025
14/09/2025

በመንግስት አሰራርና አደረጃጀት መርህ መሰረት በመንግስትና ህዝብ መብትና ጥቅም ላይ በየደረጃው የተዋቀሩ የአስተዳደር እርከኖች እሚኖራቸው መብትና ጥቅም ተመሳሳይ ነው!ህግን ተከትሎ የበላይ አስተዳደር እርከን ከሰጠው አስተዳደራዊ ትዛዝና ውሳኔ በተለየ/በተቃራኒ የታችኛው የአስተዳደር እርከን መብትና ጥቅም በፍጹም ሊኖረው አይችልም!!! የመንግስት የአስተዳደር እርከኖች ማለት "ተመሳሳይ መብትና ጥቅም" ያላቸው በህግ "የመንግስት የአስተዳደር እርከኖች"የተባለ ስውነት የተሰጣቸው በመንግስትና በህዝብ መብትና ጥቅም ላይ የተለያየ መብት ወይም ጥቅም ሳይሆን ተመሳሳይ መብትና ጥቅም ያላቸው እንደ ሁለት የተለያዩ አካላት ሳይሆን እንደ " አንድ አካል" ናቸው

ስለሆነም በጉዳዩ ላይ በህግ ስልጣን የተሰጠው የበላይ የዞን አስተዳደር እርከን በሰጠው አስተዳደራዊ ውሳኔ ላይ የታችኛው የከተማ አስተዳደር እርከን ከዚ ውሳኔ በተቃራኒ መብትና ጥቅም አለኝ ማለት መሰረታዊና ህገ-መንግስታዊ የመንግስት አሰራርና አደረጃጀት የመርህ ጥሰት ነው!!የመንግስት አደረጃጀቶች መርህ አልባ ግንኙነት እንዲኖራቸው ማድረግ ማለት ነው!!

ይዞታው  #ለእርሻ የሚውል (የተመደበ) ሲሆን በዚህ አይነት ይዞታ ላይ  #አትክልትና  #ቤት አለው በሚል ምክንያት የሚደረግ  #ሺያጭ ሆነ  #የመያዣ ውል መሬቱን ከመሸጥ ወይም ከማስያዝ የተ...
14/09/2025

ይዞታው #ለእርሻ የሚውል (የተመደበ) ሲሆን በዚህ አይነት ይዞታ ላይ #አትክልትና #ቤት አለው በሚል ምክንያት የሚደረግ #ሺያጭ ሆነ #የመያዣ ውል መሬቱን ከመሸጥ ወይም ከማስያዝ የተለየ ውጤት አይኖረውም በማለት የፌደሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ሰጥቷል።

ከንግድ ሕጉ አንቀጽ 896 መገንዘብ እንደሚቻለው አንድ ሰው በባንክ ገንዘብ ሲያስቀምጥ ባንኩም ገንዘቡን ተቀብሎ የባንክ ሂሳብ ለአስቀማጩ የባንክ ሂሳብ ከፍቶ ሲያስቀምጥ በመካከላቸው የአደራ ...
13/09/2025

ከንግድ ሕጉ አንቀጽ 896 መገንዘብ እንደሚቻለው አንድ ሰው በባንክ ገንዘብ ሲያስቀምጥ ባንኩም ገንዘቡን ተቀብሎ የባንክ ሂሳብ ለአስቀማጩ የባንክ ሂሳብ ከፍቶ ሲያስቀምጥ በመካከላቸው የአደራ ውል ግንኙነት ይመሰረታል፡፡

በውሉ የተመለከቱ ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው አደራ አስቀማጩ
ገንዘቡ እንዲመለስለት በጠየቀ ጊዜ ባንኩ ለአስቀመጩ የመመለስ ግዴታ አለበት።

ይህም የሚሆነው ለ15 ተከታታይ አመታት እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ የባንክ ሂሳብ (active bank account) እንደሆነ መገንዘብ ይገባል።

ለ15 ተከታታይ ዓመታት ይገባኛል ጥያቄ ያልቀረበበትን፣ በዋና ገንዘብ ላይ የመጨመር ወይም የመቀነስ እንቅስቃሴ ያልታየበትን፣ የባንክ ደብተር ወይም ሌላ የጽሁፍ መረጃ ያልቀረበበትን ወይም የደብዳቤ ልውውጥ ያልተደረገበትን ተከፋይ ሂሳብ የያዘ ማንኛውም ባንክ በዚሁ ሂሳብ ውስጥ ያለውን ገንዘብ ብሔራዊ ባንክ በሚያወጣው መመሪያ መሰረት ለብሔራዊ ባንክ ማስተላለፍ እንዳለበት እና በዚህ አግባብ
የተላለፈ ከሆነ ማንኛውም ሕጋዊ ባለመብት ገንዘቡ እንዲሰጠው
ጥያቄ ማቅረብ ያለበት ለብሔራዊ ባንክ እንደሆነ ስለባንክ ሥራ
በወጣው አዋጅ ቁጥር 592/2011 አንቀጽ 52 ስር ተደንግጓል፡፡

ሆኖም ገንዘብ አስቀማጩ ወይም በገንዘቡ ላይ መብት አለኝ ባይ ገንዘቡ ወጪ ሆኖ እንዲከፈለው ጠይቆ ገንዘቡን በአደራ ያስቀመጠው ባንክም ሆነ ብሔራዊ ባንክ በማንኛውም ምክንያት ለመክፈል ፈቃደኛ ካልሆኑ ባለመብቱ መብቱን ክስ በማቅረብ ማስከበር ያለበት መቼ ነው ለሚለው ጥያቄ የንግድ ሕጉም ሆነ አዋጅ ቁጥር 592/2000 እንዲሁም ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1159/2011 በግልጽ መልስ አልሰጡም፡፡

በመሆኑም በፍትሐ ብሔር ሕጉ ስለውሎች በጠቅላላው የተደነገገውን መመለከት አስፈላጊ ይሆናል፡፡ በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1845 ስር ሕግ በሌላ አኳኋን ካልደነገገ በስተቀር ውሉ እንዲፈጸም የሚቀርብ ክስ በ10 ዓመት ውስጥ ካልቀረበ ክስ የማቅረብ መብት በይርጋ ቀሪ ይሆናል፡፡

ስለሆነም ባለገንዘቡ በ15 አመት ጊዜ ውስጥ መጠየቅ ሲኖርበት
ወራሾች ደግሞ የወራሽነት መብታቸውን ባረጋገጡ በ10 አመት
ጊዜ ውስጥ ካልጠየቁ መብታቸው በይርጋ ይታገዳል።

የሰ/መ/ቁ. 225144 (ጥቅምት 28 ቀን 2015 ዓ.ም)

የቤት ካርታ ፕላን  #የተሰጠበት/የተሻረበት አግባብን አጣርቶ ፍ/ቤት  ውሣኔ ልሰጥ ይችላል ወይ❓‎===============================‎‎👉🏿ፍርድ ቤቶች  #በአስተዳደር ክፍል የ...
13/09/2025

የቤት ካርታ ፕላን #የተሰጠበት/የተሻረበት አግባብን አጣርቶ ፍ/ቤት ውሣኔ ልሰጥ ይችላል ወይ❓
‎===============================

‎👉🏿ፍርድ ቤቶች #በአስተዳደር ክፍል የተሰጠ #የቤት ካርታ #የተሰጠበት ወይም #የተሻረበት ስርዓት እና አስተዳደራዊ ውሳኔው ህግና መመሪያ ያገናዘበ መሆን አለመሆኑን #በማጣራት ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን ያላቸው ስለመሆኑ፣🎯

‎👨‍⚖️የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቅፅ 18 በሰበር መዝገብ ቁጥር 99071 ላይ በተመሣሣይ ጉዳይ አስገዳጅነት_ያለውን ውሣኔ ሰጥቷል።

Address

Butajira

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ከፍትህ እንጂ ከበደል አንተባበር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ከፍትህ እንጂ ከበደል አንተባበር:

Share

Category