ከፍትህ እንጂ ከበደል አንተባበር

ከፍትህ እንጂ ከበደል አንተባበር Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ከፍትህ እንጂ ከበደል አንተባበር, Media, Butajira.

10/07/2025

አስተዳደራዊ መፍትሄ ለማግኘት ለአስተዳደር መ/ቤት የሚቀርብ አቤቱታ ይርጋን የማያቋርጥ ስለመሆኑሰ/መ/ቁ.221828 (ሕዳር 28 ቀን 2015 ዓ.ም)
05/07/2025

አስተዳደራዊ መፍትሄ ለማግኘት ለአስተዳደር መ/ቤት የሚቀርብ አቤቱታ ይርጋን የማያቋርጥ ስለመሆኑ

ሰ/መ/ቁ.221828 (ሕዳር 28 ቀን 2015 ዓ.ም)

ሰበር መዝገብ ቁጥር 38228ሁከት ይወገድልኝ ክስ አንድ ሰው ባለይዞታ ነው ለማለት በግድ በይዞታው ላይ ባለሃብት መሆን እንደሌለበት መገንዘብ ይቻላል፡፡ በዚህም ምክንያት አንድን ነገር በእጁ...
05/07/2025

ሰበር መዝገብ ቁጥር 38228
ሁከት ይወገድልኝ ክስ

አንድ ሰው ባለይዞታ ነው ለማለት በግድ በይዞታው ላይ ባለሃብት መሆን እንደሌለበት መገንዘብ ይቻላል፡፡ በዚህም ምክንያት አንድን ነገር በእጁ አድርጎ በእውነት ያዝበት የነበረ መሆኑን ካስረዳ ባለይዞታ መሆኑ ይረጋገጣል ወደ ፍ/ሕ/ቁ. 1195 ስንመለስ ግን ይህ ድንጋጌ የሚገናረው ስለባለሃብትነት /ownership/ ነው፡፡ በመሆኑም አንድ ሰው የማይንቀሣቀስ ንብርት ባለሀብት መሆኑ ከሚመለከተው አስተዳደር ክፍል የሚሰጠውን የባለሃብትነት የምስክር ወረቀት በማቅረብ ማስረዳት ይችላል፡፡ በእርግጥ መሬት የማይንቀሳቀስ ንብረት ቢሆንም የመሬት ባለሀብት መሆን ባይችልም የመሬቱ የይዞታ ባለሀብት መሆኑን በማረጋገጥ ግን ተመሣሣይ ማስረጃ ማቅረብ ይገባል፡፡ በመሆኑም በፍ/ሕ/ቁ. 1140 እና 1195 መሃከል የሰፋ ልዩነት አለ፡፡ የመጀመሪያው አንድን ነገር ይዞ መገልገል ባለይዞታ የሚያደርግ መሆኑን የሚልጽ ሲሆን ሁለተኛው ግን አንድን ነገር ይዞ መገልገልን ብቻ ሣይሆን ከዛ ባለፈ የዚሁ ነገር ባለቤት መሆንን ለማረጋገጥ የሚያገለግል ድንጋጌው ነው፡፡ ስለሆነም የሁከትን ክስ ለማቅረብ ከሣሽ ማስረዳት ያለበት ሁከት ተፈጠረ የተባለበትን ነገር በእጁ አድርጎ በውነት ያዝበት የነበረ መሆኑን ብቻ እንጂ የዚሁ ነገር ባለሃብት መሆኑን አይደለም።

በሕጋዊ ይዞታ ላይ የተፈጠረ የሁከት ድርጊት እንዲወገድ በቀረብ ክስ ላይ ጣልቃገቦች ከሁከቱ ውጭ አዲስ የዳኝነት ክርክር ማቅርብ የማይችሉ እና ራሱን ችለው መክሰሰ የሚገባ ሰለመሆኑ ======...
26/06/2025

በሕጋዊ ይዞታ ላይ የተፈጠረ የሁከት ድርጊት እንዲወገድ በቀረብ ክስ ላይ ጣልቃገቦች ከሁከቱ ውጭ አዲስ የዳኝነት ክርክር ማቅርብ የማይችሉ እና ራሱን ችለው መክሰሰ የሚገባ ሰለመሆኑ
====================
በሕጋዊ ይዞታ ላይ የተፈጠረ የሁከት ድርጊት እንዲወገድ ባቀረበው ክስ ላይ መውጫ ተዘግቶብናል በማለት ያቀረቡት የጣልቃገብነት ክርክር አብሮ ተስተናግድ የአመልካችን ክስ ውድቅ መደረጉ ተገቢ አለመሆኑ። በመሠረቱ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1149 መሠረት ሁከት እንዲወገድ እና መውጫ መግቢያ ተከልክለናል በማለት የሚቀርበው ክስ ደግሞ በቀጥታ የሚመለከተው የንብረት አገልግሎት ስለመሆኑ ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1221 ድንጋጌ ይዘት መገንዘብ ይቻላል።

ሰ/መ/ቁ.214413 (ሚያዝያ 26 ቀን 2014 ዓ.ም)

ህገ-ወጥ ውል ከሆነ ተከራካሪዎች በመቃወሚያነት ባያነሱትም ችሎቱ በራሱ ሊያነሳው ይችላል።↪️የሰ/መ/ቁ 257723 ↪️ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም. በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ ፍርድ ቤቶች ህ...
24/06/2025

ህገ-ወጥ ውል ከሆነ ተከራካሪዎች በመቃወሚያነት ባያነሱትም ችሎቱ በራሱ ሊያነሳው ይችላል።
↪️የሰ/መ/ቁ 257723
↪️ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም.

በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ ፍርድ ቤቶች ህገ ወጥ የሆነ ውልን ተንተርሰው የሚመጡ ክርክሮችን በሌላ ተከራካሪ ወገን መቃወሚያ ባይቀርብበት እንኳን በራሳቸው በኩል አንስተው ክሱን ውድቅ ለማድረግ ይችላሉ ፤

ክርክር ያስነሳዉን የመሬት ይዞታ ላይ ስጦታ ውል በሚል ሽፋን የተደረገው የሽያጭ ውል ስምምነት ከመነሻውም ዉሉ ሕገ-ወጥ በመሆኑ ተጠሪዎች ክርክር ያስነሳው ይዞታ ለማስለቀቅ መብት የሚሰጣቸው አይሆንም፡፡

ተጠሪዎች በሕገ-ወጥ ዉል መነሻነት በይዞታው ላይ ቋሚ አትክልቶችን አልምተዉበት ከሆነም በሌላ አግባብ ከሰው ከሚጠይቁ በቀር በይዞታው ላይ መብት አገኘንበት የሚሉት የስጦታ ውል ስምምነት ሰነድ ይዘቱ የመሬት ሽያጭ ውጤት ያለው ስምምነት በመሆኑ ከመነሻውም ውል ህጋዊ ውጤት አይኖረውም ፤

ተጠሪዎች ከመነሻውም ይዞታው ላይ ያቋቋሙት መብት ህጋዊ ውጤት በማያስገኝ ውል አመካኝነት በመሆኑ ይህን ተከትሎ በይዞታው ላይ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1168 መሰረት ለረዥም አመታት ግብር መገበራቸውም በይዞታው ላይ የባለይዞታነት መብት ሊያጎናጽፋቸው አይችልም፡፡

21/06/2025

.....የህዝቡ ብሶት እሬታ
ጊዜ አይሰጠው ይመታ!!

✅የሰበር ውሳኔ ወደኃላ ተመልሶ ይሰራል ወይ? ✅የወራሽነት የምስክር ወረቀት ስለያዝን በማንኛውም ጊዜ(ያለ ይርጋ ገደብ) የውርስ ንብረት ጥያቄ ማንሳት እንችላልን በማለት የውርስ ሀብቱ ሳያጣሩ...
18/06/2025

✅የሰበር ውሳኔ ወደኃላ ተመልሶ ይሰራል ወይ?

✅የወራሽነት የምስክር ወረቀት ስለያዝን በማንኛውም ጊዜ(ያለ ይርጋ ገደብ) የውርስ ንብረት ጥያቄ ማንሳት እንችላልን በማለት የውርስ ሀብቱ ሳያጣሩ የቀደመ ሰበር አቋምና የህግ ትርጉም አምነው የተቀመጡ ሰዎች ያላቸው መፍትሄ ምንድ ነው ? ሰ/መ/ቁ.243973 ጥቅምት 06 ቀን 2017 ዓ.ም ውሳኔ ከተሰጠበት በኃላ ውርስ የተከፈተ ከሆነ አከራካሪ አይደለም።
✅ሰበር ሰሚ ችሎቱ በሰመቁ 255592 በቀን ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጠው ውሳኔ ያለኝ እይታ።
በዚህ መዝገብ በፍሬ ነገር ደረጃ የተረጋጠዉ አውራሾች ጥር 25 ቀን 2003 ዓም እና ጥር 04 ቀን 2004 ዓም ከዚህ አለም በሞት የተለዩ መሆኑን፤ወራሾች በ29/08/2005 ዓም ወራሽነታቸውን አረጋግጠው ውርሱ ሳይጣራ መኖሪያ ቤቱን ሳይከፋፈል ቆይቶ በ2015 ዓ.ም ክፍፍል መጠየቃቸውን ነው።
✅ሰበር ሰሚ ችሎቱ ለውሳኔው መሰረት ያደረገው በሰ/መ/ቁ.243973 ጥቅምት 06 ቀን 2017 ዓ.ም በሰባት ዳኞች “ የወራሽነት የምስክር ወረቀት የያዘ ሰው በማንኛውም ጊዜ(ያለ ይርጋ ገደብ) የውርስ ንብረት ጥያቄ ማንሳት ይችላል በሚል ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁ. 205248 /መ/ቁ. 44237፣38533 ወዘተ) የተሰጡ የህግ ትርጉም በመለወጥ 1) የውርስ ማጣራት ተጠናቆ ንብረቱ የጋራ ባልሆነበት ሁኔታ የወራሽነት ምስክር ወረቀት በመያዝ ብቻ የፍ/ሕ/ቁ. 1062 መሰረት በማድረግ ያለጊዜ ገደብ የክፍፍል ጥያቄ ሊነሳ እንደማይችል 2) የወራሽነት ማስረጃ መያዝ አለመያዝ ልዩነት ሳይኖረው በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ የወራሽነት ጥያቄ ካልቀረበ ክሱ በይርጋ ይታገዳል በማለት ውሳኔ የሰጠበትን መሰረት በማድረግ ነው።
✅ሰበር ሰሚ ችሎቱ በሰመቁ 255592 ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም የሰጠውን ውሳኔ በሰ/መ/ቁ.243973 ጥቅምት 06 ቀን 2017 የተሰጠው ውሳኔ መሰረት በመሆኑ ሰመቁ 243973 የተሰጠው የህግ ትርጉም ወደ ኃላ ተመልሶ ስራ ላይ እንዲውል ያደረገ ነው ።
✅እርግጥ ነው የሰበር ውሳኔ የህግ ትርጉም እንጂ የህግ አይደለም ሕግ የማውጣት ስልጣን አልተሰጠውም የሚለውን ክርክር እንደተጠበቀ ሆኖ በፅንሰ ሀሰብ ትክክል ቢሆንም በተግባርና በውጤት ግን ሕግ ነው̀።
✅የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የሚሰጠው የህግ ትርጉም ውሳኔው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በማናቸውም ደረጃ ባሉት የፌዴራልም ሆነ የክልል ፍርድ ቤቶች ላይ የአስገዳጅነት ኃይል ያለው ስለመሆኑ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234 አንቀፅ 10(2) ደንግጓል። ከዚህ ድንጋጌ ያለው በስተጀርባ ያለው መሰረታዊ የህግ መርህ (principle of non retroactivity of laws) ህግ ወደ ኃላ ተመልሶ አይሰራም የሚለውን ነው። የዚህ መርህ መነሻ ሀሳብ የህግ ትርጉም የሚሰጠው የህብረተሰብ ማህበራዊ ግንኙነት ለማሳለጥ እና ለመቆጣጠር እንደመሆኑ መጠን የህግ ትርጉሙ ተፈፃሚነት የሚኖረው ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ የተፈጠረ እና ለወደፊት የሚፈጠውን ግንኙነት ላይ እንጂ ውሳኔ ከመውጣቱ በፊት የተፈጠረውን ኩነት ብቻ በመሆኑ።
✅ለውርስ ክርክር ተፈጻሚነት ያለው ሟች በሞተበት እና ውርሱ በተከፈተበት ጊዜ በስራ ላይ በነበረው ህግ እንጂ ክርክሩ በቀረበ ጊዜ በሥራ ላይ ባለው ሕግ መሠረት አለመሆኑ፤ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥሮች 86089፣ 99587፣ 121822 እና 183645 ላይ ለውርስ ክርክር ተፈጻሚነት ያለው ሟች በሞተበት እና ውርሱ በተከፈተበት ጊዜ የነበረው ህግ ሳይሆን ክርክሩ በቀረበ ጊዜ በሥራ ላይ ባለው ሕግ መሠረት ሊሆን ይገባል በማለት የሰጠው ትርጉም ተለውጧል በማለት በሰባት ዳኞች በሰመቁ 191393 አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል።

ፍርድ ቤት ማንኛውም በፍርድ ሊወሰን የሚችል ጉዳይ ሲቀርብለት ሕግንና ማስረጃን ብቻ መሰረት በማድረግ በገለልተኝነት አከራክሮ ለመወሰን የተቋቋመ ሦስተኛ የመንግስት አካል ነው። የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ...
16/06/2025

ፍርድ ቤት ማንኛውም በፍርድ ሊወሰን የሚችል ጉዳይ ሲቀርብለት ሕግንና ማስረጃን ብቻ መሰረት በማድረግ በገለልተኝነት አከራክሮ ለመወሰን የተቋቋመ ሦስተኛ የመንግስት አካል ነው። የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገመንግሥት አንቀፅ 79 (1) በግልጽ እንደሚያስቀምጠው በፌዴራልም ሆነ በክልል የዳኝነት ሥልጣን የፍርድ ቤት ብቻ ነው።

ሕግን በገለልተኝነት ለመተርጎም የተቋቋመው ይህ አካል ከማንኛውም የመንግስት አካል፣ ባለሥልጣን ወይም ከማንኛውም ሌላ ተጽዕኖ ነፃ ሆኖ ስራውን ሊሰራ ይገባል። ዳኞች የዳኝነት ተግባራቸውን በሙሉ ነፃነት ያከናውናሉ፥ ከሕግ በስተቀር በሌላ ሁኔታ አይመሩም። (የሕገመንግስቱ አንቀፅ 79 (2) እና (3) ይመለከተዋል)

ፍርድ ቤቶች ጉዳዮቹን የሚዳኙት በሕግ እና በቀረቡት ማስረጃዎች ብቻ ላይ ተመስርተው ነው። የተከራካሪዎች ማህበራዊ አቋም፣ ሀብት፣ ጾታ፣ ቋንቋ፣ ሃይማኖት፣ ብሔር፣ ቀለም፣ የፖለቲካ አቋም ወይም አመለካከት ወዘተ ከግምት ሳይገባ ሰዎች ያለ ልዩነት በሕግ ፊት በእኩል ይዳኛሉ። (የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገመንግስት አንቀፅ 25 ይመለከተዋል)

ይህ ሲሆን ነው የሕግ የበላይነት ሊረጋገጥ የሚችለው። መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተጨባጭ እውን ይሆኑ ዘንድ ነፃ እና ገለልተኛ ፍርድ ቤት ሊኖር ግድ ይላል። ሠላምና ዘለቄታ ያለው ልማት ያለ ነፃና ገለልተኛ ፍ/ቤት ሊረጋገጥ አይችልም።

ለዚህም ነው የፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 52 (1) የፍርድ ቤት ወይም የዳኞችን በነፃነት መስራት የሚጋፋ ወይም በዳኞች ላይ ተጽዕኖ የሚያደርግ ወይም ለማድረግ የሞከረ ማንኛውም ሰው በሌላ ሕግ ከፍ ያለ ቅጣት ከሌለ በቀር ከ3 ወር እስራት ባላነሳ ከ2 ዓመት ባልበለጠ ጽኑ እስራት እንደሚያሰቀጣ የሚደነግገው።

ነፃና ገለልተኛ ፍርድ ቤት ስንል ውሳኔያዊ ነፃነትን ከማረጋገጥ ጀምሮ ፍርድ ቤቶች የሚሰጧቸውን ውሳኔዎች፣ ብይኖች ወይም ትዕዛዛት ማክበርን ያጠቃልላል። የዳኝነት ነፃነት ዳኞች በሕግ እና በማስረጃ ላይ ተመስርተው ከውጫዊ ጫና ወይም ተጽዕኖ ነፃ ሆነው እልባት መስጠት ከመቻል ባለፈ የሚሰጡትን ውሳኔዎች ወይም ትዕዛዞችን ማክበር እና ማስከበርን ያካትታል።

ፍርድ ቤት በሰጠው ውሳኔ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ወይም የፍርድ ሂደቱ ላይ ቅሬታ ወይም ስህተት ካለ በይግባኝ እና ሰበር እስከ ፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት አለፍ ሲልም እስከ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ሄዶ ማሳረምና ማስተካከል ከሚቻል በቀር የፀና ሆኖ ተፈፃሚ ይሆናል።

የትኛውም የመንግስት አካል፣ ተቋም ወይም መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ወይም ማንኛውም ሰው ውሳኔዎቹን ወይም ትዕዛዞቹን የመፈጸም እና የማስፈፀም ግዴታ ያለበት ሲሆን ይህን ግዴታ ያልተወጣ አካል በሕግ ተጠያቂ ይሆናል። (የፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጅ አንቀፅ 52 ይመለከተዋል)

ከዚህ ውጭ ያለ አካሄድ የፍትህ ሥርዓቱን የሚያዳክምና የሕግ የበላይነት የሚሸረሽር ከመሆኑም በላይ ኢ-ፍትሃዊ የሆኑ ውጤቶችን ያስከትላል። የፍትህ ሥርዓቱ ላይ ጣልቃ ገብነትን መጋበዝ ብሎም ለሕግ ውሳኔ ተገዢ አለመሆን እንደ ሀገር ሁላችንንም የሚጎዳ ከመሆኑም በላይ ተጠያቂነትም ያስከትላል።

በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 234(1)(ረ) የሚቀርብ የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ተከሳሽ የሆነ ወገን ከሳሽ ላይ የሚጠይቀውን ማንኛውንም ነገር እንዲወሰን የሚያቀርበውን ክስ የሚመለከት ሲሆን ክሱ ተገቢው...
14/06/2025

በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 234(1)(ረ) የሚቀርብ የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ተከሳሽ የሆነ ወገን ከሳሽ ላይ የሚጠይቀውን ማንኛውንም ነገር እንዲወሰን የሚያቀርበውን ክስ የሚመለከት ሲሆን ክሱ ተገቢው ዳኝነት ተከፍሎበት ፣ ከሳሽ የሆነው ወገን መልስ ሰጥቶበት እንደመደበኛው ክስ ክርክርና ማስረጃ ተሰምቶ ውሳኔ ሊሰጥበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡የማቻቻል ጥያቄ ከተከሳሽ ከሳሽነት ክስ የተለየ እና በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 236 እና 237 አግባብ የመከላከያ መልስ አካል ሆኖ የሚቀርብ ነው፡፡ የማቻቻል ክርክር ተከሳሽ የሆነ ወገን ለቀረበበት ክስ ከሳሽ ከሆነው ወገን የሚፈለግ ክፍያ መኖሩንና ለክሱ ማቻቻያ ሆኖ እንዲያዝ የሚቀርብ ነው፡፡ ክርክሩ የመከላከያ መልስ አካል በመሆኑ እንደተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ዳኝነት ተከፍሎበት የሚቀርብ አይደለም፡፡ ሰበር ሰሚ ችልቱ በመዝገብ ቁጥር 177402 ላይ የማቻቻል ጥያቄ የመከላከያ መልስ አካል ሆኖ ቀርቦ ጉዳዩን መርምሮ መወሰኑን ማየት ይቻላል፡፡
የሰ/መ/ቁ 253530 ጥር 27 ቀን 2017 ዓ/ም

 #ያልታተመ። ➿ የሰ/መ/ቁ 254862➿ የተወሰነበት ቀን ↪️ጥር 27 ቀን 2017ዓ.ምየፌዴራል ጠቅሊይ ፍርድ ቤት ከዚህ ጉዳይ ጋር ተመሳሳይ በሆነ ጉዳይ በሰ/መ/ቁጥር 237381 ላይ በቀን...
12/06/2025

#ያልታተመ።
➿ የሰ/መ/ቁ 254862
➿ የተወሰነበት ቀን ↪️ጥር 27 ቀን 2017ዓ.ም

የፌዴራል ጠቅሊይ ፍርድ ቤት ከዚህ ጉዳይ ጋር ተመሳሳይ በሆነ ጉዳይ በሰ/መ/ቁጥር 237381 ላይ በቀን 30/02/2016 ዓ.ም በዋለዉ ቸሎት በአብላጫ ድምጽ አንደኛው ተጋቢ የአርሶ አደር ልጅ በመሆኑ ምክንያት የአርሶ አደር ልጅ ከሌላ ሰዉ ጋር በጋብቻ ውስጥ እያለ የሚሰጠዉ ቤት እንደ ካሣ እንደሚቆጠርና ቤቱም ካሣ የተሰጠዉ ተጋቢ የግል ንብረት ተደርጎ ይቆጠራል እንጂ የተጋቢዎቹ የጋራ ሀብት ተደርጎ ሊቆጠር እንደማይገባ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡ ለክርክሩ መነሻ የሆነዉ ኮንዶሚኒየም ቤቱ የግራ ቀኙ በጋብቻ ግንኙነት ዉስጥ እያለ የተሰጠ ቢሆንም ለአመልካች በካሣ መልክ የተሰጠ በመሆኑ የአመልካች የግል ንብረት ነዉ፡፡

 #ሊታረም የሚችል ስህተት እስከሆነ ድረስ ስህተቱ ሊፈጠር የቻለው በተከራካሪ ወገኖች ይሁን በፍርድ ቤቱ ልዩነት ሳይደረግ ሊታረም የሚችል ስለመሆኑ እና በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 208 መሠረት የሚ...
09/06/2025

#ሊታረም የሚችል ስህተት እስከሆነ ድረስ ስህተቱ ሊፈጠር የቻለው በተከራካሪ ወገኖች ይሁን በፍርድ ቤቱ ልዩነት ሳይደረግ ሊታረም የሚችል ስለመሆኑ እና በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 208 መሠረት የሚሻሻል ሰለመሆኑ
#ከመነሻው ያቀረቡት ክስ ደሳለኝ ሀብቴ በሚል ክስ አቅርበው ነበር በሚል የስም ይታረምልኝ አቤቱታቸው ውድቅ የሚደረግበት የህግ ምክንያትጰየለም፡፡የሰበር መ/ቁ 245834 ጥቅምት 07 ቀን 2017 ዓ/ም
💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️
አመልካች በውሳኔው ላይ የተፈጠረው የስም ስህተት እንዲታረምላቸው የጠየቁ ሲሆን ስህተቱ ሊፈጠር የቻለው አመልካች እራሳቸው አስቀድመው ባቀረቡት ክስ ላይ ስማቸው ደሱ ሀብቴ መባል ሲገባው ደሳለኝ ሀብቴ በማለት በመጥቀሳቸው ነው፡፡
የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 208 አንድ ፍርድ ቤት በሰጠው ውሳኔ ላይ የተፈፀመ ስህተት ስለሚታረምበት ሁኔታ የሚደነግግ ሲሆን ስህተተቶቹም ባለማስተዋል የተፈጠሩ የጽህፈት ወይም የቁጥር ግድፈቶች ስለመሆናቸው ተመልክቷል፡፡ መሰል በድንጋጌው መሰረት ሊታረም የሚችል ስህተት እስከሆነ ድረስ ስህተቱ ሊፈጠር የቻለው በተከራካሪ ወገኖች ይሁን በፍርድ ቤቱ ልዩነት ሳይደረግ ሊታረም የሚችል ስለመሆኑ ይህ ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ 236245 ከሰጠው ትርጉም መገንዘብ ይቻላል

Address

Butajira

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ከፍትህ እንጂ ከበደል አንተባበር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ከፍትህ እንጂ ከበደል አንተባበር:

Share

Category